አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ምንዱባን


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


....ደረጃውን እያንኳኳ ቶሎ ቶሎ ሲሄድ ማሪየስ ኮቴውን ሰማ። በዚህም ወደ ውጭ መውጣቱን አረጋገጠ፡፡ ወዲያው በአካባቢው የሚገኝ ቤተክርስቲያን የስዓት ደወል ደውሎ ሰባት ሰዓት መሆኑን አበሰረ::

ማሪየስ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄዶ ተረኛ መኰንን እንዳለ ጠየቀ
መኮንኑ አለመግባታቸው ተገለጸለት:: ሆኖም አስቸኳይ ከሆነ ዋናውን አዛዥ ማነጋገር እንደሚችል ተነገረው፡፡

«አስቸኳይ ነው» አለ ማሪየስ፡፡

የቀኑ ዘበኛ ወደ ዋናው አዛዥ ቢሮ አመላከተው፡፡ ዋናው ኃላፊ
ከቁመቱ ዘለግ ያለ ጢማምና ቁጡ ሰው ነው: ሲያዩት ከሞት
ይበልጥ ያስፈራል ወፍራምና ረጅም ካፖርት ለብሷል ፊቱ ክብ ሆኖ ሪዙ ላይ ሽበት ጣል ጣል አድርጎበታል አፍጥጦ ሲያይ ወደ ውስጥ የገባውን ኪስ የሚገለብጥ ይመስላል:: ጠቅላላ ሁኔታው ከዦንድሬ የተለየ አልነበረም ሆኖም የሕግ ስው በመሆኑ ብቻ ከተኩላ ውሻን ማየት እንደሚሻል ዓይነት ትርኢት ነበር ለማሪየስ፡፡
«ጉዳይህ ምንድነው?» ሲል አክብሮት በተለየው አነጋገር ጠየቀው:
«እኔ እንኳን የፈለገሁት የእለቱን ተረኛ መኰንን ነበር፡፡»
«አልመጣም እሱ ፤በእርሱ ምትክ ጉዳይህን እኔ ልፈጽምልህ
እችላለሁ፡፡»
«ጌታዬ ትልቅ ምሥጢር ነው፡፡
«ተናገራ ታዲያ፡፡»
«እና ደግሞ በጣም አስቸኳይ ነው፡፡»
«ይሁና አሳብህን ቶሉ ልስማው፡፡»
ዋናው አዛዥ ይህን ተናግሮ ዝም አለ፡፡ ከጥቂት ጊዜ ጨዋታ በኋላ
ከማሪየስ ሳይሆን ከአሰረው ከረባት ጋር ይነጋገር ይመስል አዛዡ እንዳቀረቀ
«መቼስ መጠንቀቅ ያስፈልጋል» ብሎ ከተናገረ በኋላ መልሶ ዝም አለ:
«ቁጥር 50 52 ፤ ሰፈሩን አውቀዋለሁ፡፡»
‹‹ምን ማድረግ ይቻላል?» ሲል ማሪየስ ጠየቀ፡፡
«ያልካቸው ሰዎች ትልቁን በር የሚከፍቱበት ቁልፍ አላቸው! አንተስ አለህ?»
«እነሱም አላቸው፤ እኔም አለኝ፡:››
‹‹ቁልፉን አሁን ይዘኸዋል?»
«ይዤዋለሁ:፡»
«ስጠኝ» አለ ዋናው አዛዥ::
ማሪየስ ቁልፉን ከኪሱ አውጥቶ ሰጠው፡፡
«የነገርክዎት ነገር ካመኑበት ኃይል ይዘው ቢመጡ መልካም ነው፡፡
ዋናው አዛዥ እንደ መናደድ፧ እንደ መብሸቅ ብሎ ማሪየስን ቀና ብሎ
አየው፡፡ ‹‹ልጅ ለእናትዋ ምጥ አስተማረች» ዓይነት ሆነበት፡፡ ቢሆንም ነገሩ?
ናቅ አድርጎ በመተው ከካፖርቱ ግራና ቀኝ ኪስ ሁለት ሽጉጥ አወጣ:
ሁለቱንም በችኮላ ለማሪየስ ሰጠው።

«ያዛቸውና ወደ ቤትህ ተመለስ፡፡ ክፍልህ ውስጥ ተደበቅ፡፡ ስትገባ
ባያዩህ ጥሩ ነው ወደ ወጭ ወጥቷል ብለው እንዲያስቡ ድምፅህን አታሰማ፡፡ ሽጉጦቹ ጥይት አለባቸው:፡ እንደነከረከኝ ከሆነ የሁለታችሁን ክፍል የሚያገናኘው ግድግዳ ቀዳዳ አለው፡፡ ሰዎቹ መጥተው ከክፍሉ
ውስጥ ከገቡና ነገሩ አንተ ባልከው ዓይነት ሲጀመር አንድ ጊዜ ተኩስ ግን እንዳትፈጥን ወይም እንዳትዘገይ:: ጥሩ ሰዓት ነው በምትልበት ጊዜ ነው
የምትተኩሰው:: ከዚያ በኋላ የእኔ ጉዳይ ይሆናል፡፡»

ማሪየስ ሽጉጦቹን ይዞ ለመውጣት እጁን ከበሩ እጄታ ላይ እንዳሳረፈ ዋናው አዛዥ ያናግረዋል፡፡

«በነገራችን ላይ፣ ከአሁን ጀምሮ እስከ ማታ ብትፈልገኝ እኔ ከዚሁ
ስለምሆን ራስህ ልትመጣ ወይም ሰው ልትልክብኝ ትችላለህ፡፡ ከመጣህ ዣቬር ብለህ ጠይቅ::»

ማሪየስ እጅ ነስቶ ወጣ፡፡

የማይደርስ የለም ፤ ሰዓቱ ደረሰ፡፡ ደመና ስለነበረ ገና በአሥራ ሁለት
ለዓይን ያዝ ማድረግ ጀምሮአል፡፡ ማሪየስ ወደ 50 52 ተመለሰ፡፡ ትልቁ በር ክፍት ነበር፡፡ ቀስ ብሎ ድምፅ ሳያሰማና ማንም ሳያየው ከክፍሉ ገባ፡፡ካልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጠ፡፡ ልቡ በኃይል ይመታ ጀመር፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ምን ሊሆን እንደሚችል ታወሰው፡፡ በአንድ በኩል የወንጀል
ሙከራ ሲደረግ በሌላ በኩል ፍትሕ ሲሰፍን ታየው:: ልቡ አልፈራም፡፡ የሕይወት አጋጣሚን መጋፈጥ ደስ እንደሚለው እንደማንኛውም ሰው እርሱም ደስ አለው:: የተወጠነው ነገር ሕልም እንጂ እውነት አልመሰለውም::

ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ፡፡ ማሪየስ በር ሲከፈት ሰማ፡፡ ሁለት ልጆች
በር ከፍተው ሲገቡና አባታቸው ሲጮህባቸው አዳመጠ፡፡ ቀጥሎ የብዙ ሰዎች ድምፅ በሩቁ ተሰማ፡፡
«ስሙ ልጆች፤ አንዳችሁ በላይኛው አንዳችሁ በታችኛው በር በኩል ሆናችሁ የሚመጣ ሰው ካለ ተጠባበቁ፡፡»

«በዚህ ብርድ በባዶ እግራችን ከውጭ ልንቆም» በማለት ትልቅዋ
ልጅ አጉረመረመች::

«ነገ ምን የመሰለ ጫማ ትገዢያለሽ» ሲል አባትዋ መለሰላት፡፡

ማሪየስ ከለመደበት ሥፍራ ወጥቶ መጠባበቅ እንዳለበት ገመተ፡፡

ቀዳዳው ከነበረበት አካባቢ ወጥቶ ቁጭ አለ፡፡ ወደ እነሚስተር ዦንድሬ ክፍል ተመለከተ፡፡

ከክፍሉ ውስጥ ከሰል ተቀጣጠለ እንጂ ሌላ ብርሃን አልነበረም:: ከበሩ አጠገብ ረጅም ገመድና ሁለት ወፍራም የብረት ዱላዎች ተቀምጠዋል፡፡በኋላ ሻማ አያያዙ፡፡

ሚስተር ዦንድሬ ፒፓውን አያይዞ ከወንበር ላይ ቁጭ አለ፡፡ ባለቤቱ ዝግ ባለ ድምፅ ታናግረዋለች:: በድንገት ዦንድሬ ድምፁን ከፍ አድርጎ ተናገረ::

«በነገራችን ላይ በዚህ ብርድ ሰዎቹ በጋሪ እንጂ በእግራቸው
አይመጡም፡፡ ታዲያ አንቺ ምን ማድረግ ያለብሽ ይመስልሻል? ወዲያው የፈረስ ኮቴ እንደሰማሽ ቶሎ ብለሽ ትወጪና ለሰዎቹ ሰላምታ ሰጥተን በፍጥነት እቤት ይዘሻቸው ትመጫለሽ፡፡ ከዚያም «ቤት ለእንግዳ» በማለት
ካስገባሻቸው በኋላ ቶሎ ብለሽ ወደ ጋሪው በመመለስ ሂሣቡን ከፍለሽ ታሰናብቺዋለሽ:: እሺ?»
«የሚከፈለው ገንዘብ የት አለ?» ስትል ሴትዮዋ ጠየቀችው::
ዠንድሬ ኪሱን ዳበስ ፤ ዳበስ በማድረግ አምስት ፍራንክ ሰጣት::
«ምንድነው እርሱ?» ስትል ጠየቀች፡፡
ዛሬ ጠዋት ጎረቤታችን የሰጠን ገንዘብ ነዋ! አሁን እንግዲህ ቶሎ
ብለሽ ወደ በሩ ሄደሽ ብትጠባበቂ ይሻላል፡፡ የለም፤ አሁኑኑ ቶሎ ሂጂ፡፡»
ትእዛዙን ተቀብላ ቶሎ ወጥታ ሄደች:: ዦንድሬ ብቻውን ቀረ፡፡
የእሳት ማንደጃው፤ ጠረጴዛውና የቤቱ ሁለት ወንበሮች ማሪየስ
ከሚያይበት ቀዳዳ ትይዩ ነበሩ፡፡ አካባቢው በጣም ጭር ስላለ ማንኛውም ድምፅ በቀላሉ ከሩቅ ይሰማል፡፡

ዦንድሬ በአሳብ በመዋጡ ፒፓውን መማግ እንዳለበት ረስቶ እሳቱ ይጠፋል፡፡ እጁን ዘርግቶ የጠረጴዛውን ኪስ ሳበ፡፡ ከኪሱ ውስጥ የነበረውን ጩቤ አነሳ፡፡ ስለት እንዳለው በአውራጣቱ ሞከረው:: በኋላ መልሶ ከጠረጴዛው ኪስ ውስጥ አስቀመጠውና መሳቢያውን መልሶ ዘጋው::

ማሪየስ ደግሞ ከቀኝ ኪሱ ውስጥ የነበረውን ሽጉጥ አውጥቶ ቃታውን ስቦ ያዘው:: ቃታውን ሲስብ ሽጉጡ ድምፅ አሰማ፡፡
ዦንድሬ ደንግጦ ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡

‹‹ማነህ?» ሲል ጮኸ፡፡

ማሪየስ ትንፋሹን ያዝ አደረገ፡፡ ዦንድሬ ጆሮውን አቅንቶ አዳመጠ፡፡ ከዚያም ብቻውን ይስቅ ጀመር፡፡
«ምን ጅል ነኝ! የኮርኒሱ እንጨት ድምፅ መሆኑን ማወቅ እንዴት
ተሳነኝ!» ሲል ዦንድሬ ራሱን ነቀፈ::

ማሪየስ ሽጉጡን እንደያዘ ቀረ

ልክ አሥራ ሁለት ሰዓት ስለሆነ በአካባቢው የሚገኘው ቤተክርስቲያን ደወል ተደወለ፡፡ ሚስተር ዦንድሬ የሚጠብቃቸው ሰዎች ከመጡ ብሎ የቤቱን በርና መስኮቶች ዘጋጋ፡፡ ይበራ የነበረውን ሻማ እየተመለከተ ከቤት ውስጥ ይንቆራጠጥ ጀመር፡፡ መንቆራጠጥ ሰልችቶት ከወንበር ላይ ቁጭ አለ፡፡ ወንበር ላይ እንደተቀመጠ የቤቱ በር ተከፈቱ:: የመጣችው ባለቤቱ
👍161👏1
#ምንዱባን


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


...ገባህህ፧ «ቴናድዬ» ሲል ዦንድሬ በድጋሚ ተናገረ: ሽጉጡ ከማሪየስ እጅ ሊወድቅ ምንም ያህል አልቀረው ዦንዴሬ ማን እንደሆነ ሲናገር ከአባባ ሸበቶ ይበልጥ ማሪየስን ነው የረበሸው:: ማሪየስ ገና ስሙን ሲሰማ
ይህ ሰው ማን እንደሆነ አወቀ፡፡ አባባ ሸበቶ ግን ቶሎ አላስታወሰውም::
የዚህ ሰው ስምና ሆቴል አባቱ ትቶለት ከሞተመ ወረቀት ላይ ተጽፎአል፡፡ የአባቱን አደራ ለመጠበቅ ሲያየውና ሊጠይቀው ብዙ ጊዜ ፈልጎ አልተሳካለትም:: በመጨረሻ ግን በዚህ ዓይነት ሁናቴ ተገናኘው፡፡ ለካስ
የአባቱን ሕይወት ያዳነው ሰውዬ ሽፍታ ነው! ምን የሚገርም ጉድ ነው ምን ዓይነት የሕይወት አጋጣሚ ነው? ሕይሀት ራስዋ ትቀልዳለች ሲል አሰበደ

ይህን ቴናድዬ የተባለውን ሰው ቢያገኘው እግሩ ላይ ወድቆና ጫማውን ስሞ ሊያመሰግነው ለራሱ ቃል ገብቶ ነበር፡፡ እርግጥ ነው አሁን አግኝቶታል፡፡
ነገር ግን ማመስገኑ ቀርቶ ለፍርድ አሳልፎ ሊሰጠው ነው:: ቀልድ
አይመስልም፤ ግን አይደለም::
ማሪየስ ሁኔታውን ሲያሰላስል አሳቡን መቋጨት አቃተው:: ድንገት በገጠመው ሁኔታ እንኳን አባባ ሸበቶን ሊረዳ ራሱን መቆጣጠር ተሳነው:: ነገሩ ራሱን አዞረው:: ሁኔታው እየተፋፋመ መጣ፡፡ እርሱ ግን ራሱን
ሊስት ሆነ፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአሁን በኋላ ቴናድዩ እንጂ ዦንድሬ ብለን
የማንጠራው ሰው ከወዲህ ወዲያ ይንቆራጠጥ ጀመር፡፡ የኩራትና ድል የመምታት ስሜት አድሮበታል፡፡ በድንገት ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ
«ተዘፈነ! ተበላ! ተጠጣ! ተተፋ!» ሲል ጮኸ፡፡

እንደገና መንቆራጠጥ ጀመረ::

«አይገርምም» ሲል ጩኸቱን ቀጠለ፡፡ ‹‹በመጨረሻ አገኘሁህ:: የእኛ ምፅዋተኛ፤ የእኛ አዛኝ ቅቤ አንጓች የእኛ ቱጃር! የእኛ አሻንጉሊት ለጋሽ አታውቀኝም? የለም ፧ ሞንት ፈርሜ ላይ ከሆቴል ቤቴ ውስጥ ገብተህ
ያደርህ አንተ አይደለህም፧ ከስምንት ዓመት በፊት የገና እለት፤ በ1823 ዓ.ም! የፋንቲንን ልጅ ከቤቴ የወሰድከው አንተ አይደለህም! የእኛ ቀጣፊ
ያን ጊዜ ለብሰኸው የነበረው ረጅም ብጫ ካፖርት ምን ደረሰ? አለቀ? እንደዛሬ ጠዋት ጠቅልለህ ይዘኸው የነበረውስ ጨርቅ! አሁን ውጣ ከዚህ፣ ዓይንህን ያውጣውና፡፡ አንተ ሰይጣን፤ የእኛ መጽዋች! አታውቀኝም፤ እ
ይሁና፤ እኔ ግን አውቅሃለሁ:: ከዚህች ቤት ውስጥ ገና ስትገባ ነው | የለየሁህ፤ ሞላጫ! ያን ጊዜ አታለልከኝ አሞኘኸኝ:: ለእድሌ መስበር ምክንያት የሆንከው አንተ ነህ:: አንድ ሺህ አምስት መቶ ፍራንክ ወርውረህልኝ ደህና ትረዳኝ፧ ታገለግለኝ የነበረችዋን ልጅ ወሰድክብኝ:: ልጅትዋ ይህን ጊዜ ብዙ ሀብት አስገኝታልኝ ነበር:: የሀብታም ወገን ስለነበረች በስምዋ ብዙ ሀብት ይመጣልኝ ነበር:: አንተ ግን ያንን ምንጭ አደረቅኸው:: ያቺን ሸቃባ ይዘክብኝ ስትጠፋ ድል ያደረገህ መስሎህ ነበር፡፡ ዛሬ ግን አታመልጠኝም፤አታሸንፈኝም:: አንተ ሽባ፤ በቀል ነው የሚታየኝ አሁን! ጻድቁ፣ ዛሬ አልቆልሃል፡፡ ደግሞ ገንዘብ ይዞልኝ መጣ እኮ! ቂል:: ዛሬ ጠዋት ሳይህ ፍዳህን እንደማስቆጥርክ ነው ለራሴ ቃል የገባሁት።

ቴናድዬ ንግግሩን አቋረጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው:: የሚያጨሰው ሲጃራ ፈላበት ፊቱ ግን እንደ ጠዋት ፀሐይ ፈካ፡፡ ሊዋጋ እንደሚዘል ፍየል ፈነጠዘ፡፡ አባባ ሸበቶን ከቀጥጥሩ ስር በማዋለ በጣም ደስ አለው:: ደስታው
የድንኮች ቀውሌን ጠልፎ የመጣል ፤ የቀበሮ የታመመ በሬን ዘንጥለ የመብላት ያህል ነበር፡፡ የታመመ በሬ እንዳይዋጋ አቅም ያንሰዋል፤ ዝም እንዳይል ነፍሰ አልወጣችምና ይንፈራገጣል::

ቴናድዬ ሲለፈልፍ አባባ ሸበቶ ሊያቋርጠው አልፈለገም:: ንግግሩን እስኪጨርስ ጠበቀው:: አሁን ግን ቆም ሲል እርሱ ተናገረ::

የምትለው ነገር አልገባኝም፤ ተሳስተሃል፡፡ እኔ ድሃ እንጂ ባለብዙ ብር ወይም ቱጃር አይደለሁም፡፡ አንተ ትላለህ እንጂ እኔ አንተን አላውቅህም::
ከሌላ ሰው ጋር ተምታትቼብህ ነው::
«እህ» ሲል ቴናድዬ ጮኸ፤ አሾፈ:: «አሁንም ታሾፋለህ፤ ትቀልዳለህ!
ጌታው ወጥመድ ውስጥ ነው የገባኸው:: አታስታውስማ፣ ማን እንደሆንኩ አልለየኸኝማ!

«ይቅርታህን» አለ አባባ ሸበቶ ተኮሳትሮ፧ «ሽፍታ መሆንህን እየለየሁ ነው»

ቴናድዬ የሰውዬው ድፍረት ከማስደንገጥ አልፎ በጣም አናደደው::ይዞት የነበረውን የወንበር ድጋፍ ንዴቱን የተወጣሰት ይመስል ጨምድዶ ያዘው:: ባለቤቱ «ሽፍታ» የሚለውን ቃል ስትሰማ ከአልጋ ጫፍ ተወረወረች፡፡ቴናድዬ «አትነቃነቂ» ሲል ባለቤቱን አስጠነቀቀ፡፡ ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ ሽፍታ አልክ፤ እናንተ ሀብታሞች እኮ እኛን በዚህ ስም እንደምትጠሩን መቼ አጣነው›› ሲል በመጮህ ተናገረ::
«አዎን ተሸነፍኩልህ ፤ ይኸው ተደብቄና ተሰውሬ የሃፍረት ማቄን
ለብሼ እኖራለሁ፡፡ የምበላውና የምልሰው የለኝም:: ግን ሽፍታ ነኝ:: ይኸው ሶስት ቀኔ ነው እህል ከቀመስኩ:: አንተ ደራርበህ ለብሰሃልና ሞቆሃል::እኔን እዚህ ቆፈን ይዞ ያንቀጠቅጠኛል:: አሽከር ቀጥረህ ፎቅ ቤት ውስጥ
ትኖራለህ:: እኔ እንደ ከብት በረት አድራለሁ:: አንተ ሰሐምሌና በነሐሴ ምግብ ስታማርጥ እኛ የማሽላ ቂጣ አሮብናል:: ይህም አነሰና ሽፍታ ትለናለህ! የግሌ የሆነ ሥራ የነበረኝ ሰው ነኝ:: ከዚህም ደግሞ ይበልጥ ሁለታችንም ፈረንሳዮች በመሆናችን አስተዳዳሪ ለመምረጥ እኩል
እንሰለፋለን፡፡ በል አሁን ከላይህ ላይ ወጥተን ከመጨፈራችን በፊት
የምትናገረው ነገር ካለ ተናገር» ሲል አፈጠጠበት::

አባባ ሸበቶ ዝም አለ፡፡ በዝምታው
መካከል የፈረስ ድምፅ ስለተሰማ
ሁሉም ቀና አሉ።

«የሚፈለጥ እንጨት ካለ እኔ እፈረካክሰዋለሁ:::» መጥረቢያ በእጁ የያዘው ሰው ነበር።

«ለምንድነው ፊትህን የሸፈንክበትን ጨርቅ ያነሳኸው?» ሲል ቴናድዬ በቁጣ ጠየቀው
የያዘው ሰው ነበር-
በቁጣ ጠየቀው::

«ለመሳቅ» ሲል መለሰለት::

አባባ ሸበቶ ቁጣው ገንፍሉበት ይንቆራጠጥ የነበረውን ቴናድ።
በዓይኑ ይጠብቃል፡፡ በሩ ላይ ሦስት ዘበኞች ቆመጥ ስለሚጠብቁት ቴናድዬ በጣም ተዝናንቷል፡፡ ከዚህም በላይ ሴትዬዋ እንኳን ባትቆጠር
ዘጠኝ ለአንድ ናቸው:: ስለዚህ አባባ ሸበቶን ናቅ በማድረግ ቴናድዬ ፊቱ ወደ ባለ መጥረቢያው አዞረ፡፡

አባባ ሽበቶ በዚህች እድል ለመጠቀም ወንበሩን በእግሩ፣ ጠረጴዛው በእጁ አሽቀነጠረና በሚያስደንቅ ፍጥነት ተወርውር ለቴናድዬ ጊዜ ሳይሰጠው
ከመስኮቱ ደረሰ፡፡ መስኮቱን ለመክፈትና ለመፈናጠጥ ጊዜ አልወሰደበትም ሆኖም ገና ግማሽ ሰውነቱን እንዳስወጣ ስድስት ሰዎች ከኋላ ጉትተው ወደ
ክፍሉ መለሱት፡፡ ሦስቱ የከሰል ሠራተኞች ከላዩ ላይ ተረባረቡ፡፡ የቴናድዩ ባለቤት በወንበር ጭንቅላቱን አለችው::

ጫጫታ ሲሰሙ ጊዜ ሌሉች ውጭ ቆመው የነበሩት ሽፍቶች ወደ ውስጥ ገቡ፡፡ አልጋ ላይ ተጋድሞ የነበረው ሽማግሌ እንደሰከረ ሰው እየተንገዳገደ መዶሻ ይዞ መጣ፡፡

የሞትና የሽረት ትግል ቀጠለ:: አባባ ሸበቶ አንድ ጊዜ ደረቱ ላይ
በቡጢ ቢለው ሽማግሌው ከመሬት ላይ ተዘረረ: ሌሉች ሁለቱን ደግሞ አንዱን በእርግጫ ሌላውን በጡጫ ሲላቸው ጊዜ እነርሱም ከመሬት ተደፉ፡፡ ከዚያም ላያቸው ላይ ሲወጣ ጊዜ ልክ ድንጋይ እንደተጫነበት ሰው
👍161
#ምንዱባን


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


ዣቬር ምልክት ሲሰጣቸው ብዙ መሣሪያ የያዙ ፖሊሶች ከክፍሉ
ውስጥ ገቡ፡፡ ሽፍቶቹን ያዝዋቸው: ክፍሉ ውስጥ በርቶ የነበረው ሻማ
አንድ ብቻ ስለነበር ክፍሉ ውስጥ ሰው ሲበዛ ጊዜ ብዙ ጥላ በማጥለሉ እየጨለመ ሄደ።

«ሁሉንም በብረት ሰንሰለት እጆቻቸውን እሰሩ» በማለት ዣቬር አዘዘ

«በሉ ወደዚህ ኑ» የሚል ቀጭን የሴት ድምፅ ተሰማ፡፡ ሚስስ
ቴናድዬ ነበረች፡፡ ባልዋ ከለበሰችው ሰፊ ካባ ስር ተሸሽጓል፡፡

ጠንቀቅ በሉ!» ስትል በመጮህ ተናገረች::

ሽፍቶቹ በሙሉ ያለማንገራገር እጆቻቸውን ሰጥተው ሲጠፈሩ
በማየትዋ «ፈሪ ሁሉ!» ስትል አጉረመረመች፡፡

ዣቬር ፈገግ አለ፡፡ ሚስስ ቴናድዬ ወደነበረችበት አመራ፡፡

«አይጠጉኝ፧ ከዚህ ቶሎ ቢወጡ ይሻላል» ስትል በማንጓጠጥ
ተናገረች::«እምቢ ካሉ ዋጋዎን ነው የምሰጥዎት::»

«ደፋር» አለ ዣቬር፡፡ «እመቤቴ እንደ ወንድ ጢም አብቅለዋል፤ እኔ
ደግሞ እንደ ሴት ጥፍር አሳድጌአለሁ» ሲል አሾፈባት።

ዣቬር እየተጠጋት መጣ፡፡ አጠገብዋ አንዳንዴ ልጆችዋ አንዳንዴም ራስዋ የምትቀመጥበት ድንጋይ ነበር፡፡ ዘልላ ሄዳ ያንን ድንጋይ አነሳችና
ዣቬርን ለመምታት ወረወረችው:: ዣቬር ጎንበስ በማለት ራሱን አዳነ፡፡ድንጋዩ ከግድግዳ ጋር ሄዶ ተላተመ:: የግድግዳው ቀለም ፈራርሶ ወለሉን ሞላው:: ድንጋዩ ሲመለስ እየተንከባለለ ከዣቬር እግር ስር ደረሰ።

ዣቬር ወደ ባልና ሚስቱ ሄደ:: በአንድ እጁ የሴትዮዋን፤ በሌላ እጁ የወንዱን ትከሻ ጨምድዶ ያዘ፡፡

«መሣሪያ አምጡ» ሲል ጮኸ፡፡

ወዲያው የብረት ማሠሪያ መጥቶ ሁለቱ ሰዎች ተቀፈደዱ። የራስዋና
የባልዋ እጆች መቀፍደዳቸውን ባየች ጊዜ «ወይኔ ልጆቼ» በማለት ከጮኸች ኋላ ከመሬት ላይ ተዘረረች፡፡

«በእድላቸው ያድጋሉ» ሲል አፌዘባት::

ሦስቱ ፊታቸውን በከሰል ያጠቆሩና ሦስቱ ፊታቸውን በጨርቅ የሸፈኑ ሽፍቶች እጃቸው ታስሮ ቆመዋል::

«ፊታችሁን እንደሽፈናችሁ ቆዩ» አለ ዣቬር፡-

እያንዳንዳቸውን በስም እየጠራ አንዱን «እንደምን አመሸህ»፣ ሌላውን ጤና ይስጥልኝ»፤ ሌላውን ደግሞ «ብርቱም አልሰነበትክ» በማለት
ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ገና ከክፍሉ ሲገባ አንገቱን ደፍቶ ቆሞ
የነበረው እስረኛ ታወሰው::
«እስረኛውን ፍቱት» ሲል አዘዘ፡፡ «ከዚህ ቤት ደግሞ አንድ ሰው .
እንዳይወጣ?»
ይህን እንደተናገረ ከወንበሩ ላይ ሄዶ ቁጭ አለ፡፡ ከኪሱ ወረቀትና
ብዕር አውጥቶ ከጠረጴዛው ላይ አስቀመጠ፡፡ ቀና ብሉ «እያየ እስረኛውን ወደዚህ አምጡት» አለ፡፡
ፖሊሶቹ በዓይን ፈለጉት::
«ምነው፤ ምን ያንቀረፍፋችኋል? የት አለ ሰውዬው?» ሲል
ጮኸባቸው::
እስረኛው አባባ ሸበቶ ከዚያ አልነበረም፧ ወጥቶ ሄዷል፡፡
በሩ ላይ ፖሊስ ቆሞአል፡፡ የነበሩበት ክፍል ፎቅ ቤት ነው:: ታዲያ የት ሄደ? መስኮቱ አጠገብ ፖሊስ አልነበረም:: ትርምሱ ሲበዛ ቀደም ሲል እነቴናድዬ ለማምለጫ ባዘጋጁት የገመድ መሰላል አድርጎ ሾልኮአል። የፖሊሶቹ ዓይን አርፎ የነበረው ሽፍቶቹ ላይ ነበር፡፡

«ጋኔላም!» አለ ዣቬር በጥርሶቹ መሀል፤ «ጥሩ ምስክር ይሆነን
ነበር፡፡»

በሚቀጥለው ቀን ማታ አንድ ልጅ በኃይል እያፏጨና እየዘመረ
በመንገድ ላይ ሲጓዝ ከአንድ ነገር ጋር ይጋጫል፡፡ የተጋጨው ከሴት ጋር ነበር፡፡ ለመውደቅ እንደ መንገዳገድ ይልና ወደኋላ ዞር ብሎ ይመለከታል::

«ምነው! ትልቅ ውሻ መስሎኝ ነበር፡፡»

አሮጊትዋ ገንፍላ ከተኛችበት ብድግ አለች፡፡

«የተረገምክ» አለች ፤ «ከድካም ብዛት ሰውነቴ ባይከዳኝ ምን
እንደማደርግህ አውቅ ነበር፡፡»
ልጁ ኣሁን ትንሽ ራቅ ብሎ ነበር የቆመው፡፡

«ፕስ... ፕስ...» በማለት ካሽሟጠጣት በኋላ «በካልቾ ማቅመሴ አልተሳሳትኩም ፤ አበጀሁ፤ አበጀሁ» ሲል ተናገራት፡፡
ሴትየዋ ከተቀመጠችበት ብድግ አለች፡፡ ልጁ ሮጦ ሸሽ፡፡ እርሱን ለመያዝ ስትሮጥ መብራት ከነበረበት ደረሰች፡፡ የፊትዋ መሸብሸብና የወገብዋ መጉበጥ በግልጽ ታየ:: ልጁ ራቅ ብሎ ቆሞ አጤናት።

«እኔ የምወደው መልክ የለሽም» ብሎአት እያዜመ መንገዱን ቀጠለ፡፡ የቤት ቁጥር 50-52 ስለደረሰ ቆመ፡፡ በሩ መቆለፉን ሲያይ በእርግጫ መታው
አመታቱ የልጅ ሳይሆን የአዋቂ ነበር፡፡ ለካስ መንገድ ተኝታ
ያያት ሴት ትከተለው ኖሮ ከነበረበት ደረሰች::

ምንድነው ነገሩ እባካችሁ? ያ ከበሩ ላይ የቆመው ማነው? የእግዜር ያለህ በሩን እየሰበሩት ነው፤ ሌቦች ከቤቴ ሊገቡ ነው» ስትል ጮኸች፡፡

ልጁ በር መደብደቡን ቀጠለ፡፡ ሴትዬዋ ትንፋሽ አጥሮአት መተንፈስዋ በግድ ሆነ፡፡

«የአሁነስ ዘረፋ ዓይን በዓይን ሆነ እንዴ?» ብላ ከጠየቀች በኋላ ልጁን አተኩራ ስትመለከተው ማን እንደሆነ አወቀችው፡፡

«እንዴ! ያ ርኩስ፤ ያ ሰይጣን ነው እንዴ!»

«ጉድ ፈላ! አሮጊትዋ ናትና» አለ ልጁ ወደኋላ እየሸሸ፡፡ «ዘመዶቼን
መጠየቅ መጥቼ እኮ ነው::»

«ከዚህ ማንም የለም፤ አንተ ጋኔል» አለች ሴትዬዋ ጥላቻዋን ከፊትዋ ላይ ለማሳየት እየሞከረች::

«አይ ምን ይላሉ እርስዎ ደግሞ፤ ታዲያ አባቴ የት ሄደ?»

«ላ ፎርስ ከተባለ ሥፍራ፡፡»
«እናቴስ?»
«ሳን ላዛር፡፡»
«እሺ፧ እህቶቼስ?»
«ሌ ማደለኔ ሄደዋል፡፡»
ልጁ ጆሮውን አከክ እያደረገ ሴትዮዋን ቀና ብሎ አያት:: ሴትዮዋ እነቴናድዬ ይኖሩበት የነበረው ቤት ጠባቂ ነበረች፡፡

«እንዴት ይሆናል?» ሲል ራሱን ጠየቀ።

ከዚያም ፊቱን አዙሮ ቀደም ሲል ያዜመው የነበረውን ዜማ እያዜመ
መንገዱን ቀጠለ፡

ቅዱስ ዴኒስና ከፕሎሜ
ጎዳና ያስ ቤት

ኢፓኒን

ማሪየስ ባጠመደው ወጥመድ ፍርድ ሲገለባበጥ አየ:: የፖሊሱ
አዛዥ እስረኞቹን ይዞ ወጣ፡፡ ማሪየስም ከነበረበት ክፍል ወዲያው ሄደ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ገደማ ሆኖአል፡፡ ወደ ጓደኛው ቤት አመራ፡፡ ከጓደኛ
ው ከኩርፌይራክ ቤት እንደደረሰም ከእርሱ ጋር ለማደር እንደመጣ ገለጸለት፡፡ ኩርፌይራክም ከመሬት ላይ ፍራሽ አነጠፈለት::

በሚቀጥለው ቀን በጠዋት ከቤቱ ተመልሶ ያለበትን ቤት ኪራይ
ክፍሎ ቤቱን ለቀቀ፡፡ እቃውን በጋሪ አስጭኖ ከኩርፌይራክ ሰፈር ሄደ፡፡

ዣቬር የልጁን ስም ረስቶ ከቤቱ አገኘው እንደሆነ ብሉ ቢመጣ
አጣው:: ማሪየስን ለማግኘት ብዙ ሞከረ ፤ ግን አልተሳካለትም:: ምናልባትም ልጁ የሚደርሰውን አደጋ ላለማየት ብሎ በመፍራት ከአገር የጠፋ መሰለው::

ማሪየስ ግን ባየውና በተሰጠው ፍርድ እጅግ ተረብሾ ነበር፡፡ ሁሉም
ነገር ጨለመበት:: የሚያየው የወደፊት ተስፋ ከፊቱ ራቀ፡፡ ልቡ የተሰቀለላት ልጅና አባትዋ ድንገት እንደ ብርሃን ብልጭታ ብቅ ብለው እንደገና ተሰወሩበት:: የእርሱ የወደፊት ተስፋ እነዚህ የማይታወቁ ፍጡሮች ነበሩ፡፡
ልቡ በልጅትዋ ፍቅር ታውሮአል፡፡ «ሂድና ፈልጋት» ብሎ ስሜቱን
ቢገፋፋውም ዓይኑ ማየት ስላልቻለ እንዲያው ዝም ብሎ መረበሽ፤ መጠበብ፤
መጨነቅ ሆነ፡፡ ቀቢጸ ተስፋ ተጠናወተው:: ተስፋ የተለየው ሕይወት ጨለማ ስለሆነ ፀሐይ ወጥቶ ሳለ ምድር ጨለመችበት:: ዓይኖቹ የፍቅር ረሃብተኞች ቢሆኑም ለማየት የፈለጉትን ባለማግኘታቸው ከማየት ተቆጠቡ::ጀሮዎቹ ለመስማት የፈለጉትን ድምፅ ባለመስማታቸው ሌላ ነገር ከመስማት አፈገፈጉ፡፡ ልቡ የፈለገውን ሳያገኝ ሲቀር የፍላጎቱ መጠንና ግለት እየጎላ
👍20
#ምንዱባን


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


ከፕሎሜ ጎዳና ላይ ያለ ቤት

ፕሎሜ ከተባለ ጎዳና ላይ ንብረትነቱ የመንግሥት ባለሥልጣን የሆነ ባለአንድ ፎቅ ቤት ነበር፡፡ ቤቱ ሁለት ክፍል ቤት ከፎቁ ላይ፣ ሁለት ክፍል
ደግሞ ከምድር ቤት ነበረው፡፡ በተጨማሪ እንደ ወጥ ቤት የሚያገለግል ተጨማሪ ክፍል ፎቁ ላይ ነበረው:: ከዋናው ጎዳና ጋር የተያያዘ ትልቅ የውጭ በር ሲኖረው በአበባ ያጌጠ ሰፊ ግቢ አለው:: ከበስተጓሮው እንደ
እቃና ማድቤቶች ሊጠቅሙ የሚችሉ ሌሎች ሦስት ክፍሎች ነበሩ:: በጓሮ በኩል ደግሞ የምሥጢር በር አለው::
ምስጢሩን ለሚያውቅ እንጂ ይህ
በር፣ በር መሆኑ በቀላሉ አይታይም:: ቤቱ ብዙ ጊዜ ሰው አይከራየውም::

በ1829 ዓ.ም አንድ በእድሜ በሰል ያለ ሰው መጥቶ ይህን ቤት
ይከራየዋል፡፡ ሰውዬው ብቻውን አልነበረም:: አንዲት ወጣት አብራው ነበረች፡፡ ይህ ሰው ዣን ቫልዣ ነው:: ወጣትዋ ልጅ ደግሞ ኮዜት ናት፡፡ ቀደም ሲል ዣን ቫልዣ ይረዳት የነበረችው አሮጊት ደግሞ አብራቸው ናት:: ስምዋ ቱሴይ ይባላል:: ዣን ቫልዣ ቤቱን የተከራየው መሴይ ፎሽለማ በሚል ስም ነው::

ዣን ቫልዣ ለረጅም ጊዜ የኖረበትን ገዳም ለቅቆ ከወጣ በኋላ ምን
ተፈጸመ ቢባል ምንም የሆነ ነገር የለም:: እንደሚታወሰው ዣን ቫልዣ ገዳሙ ውስጥ ደስ ብሎት ነበር የሚኖረው:: በየቀኑ፡ ኮዜትን ያገኛታል።በተገናኙ ቁጥር ፍቅራቸው እየጠናና የአባትነት ስሜቱ እየዳበረ ይሄዳል፡፡
ልጅትዋን ፈጣሪ የሰጠው ፀጋ እንደሆነች ከማነ ባሻገር ይህችን ልጅ ከእርሱ ማንም ሊለያት እንደማይችል ገምቷል:: እስከ ሕይወቱ መጨረሻ ከእርሱ የማትለይ ፍጡር ለመሆንዋ አልተጠራጠረም:: ይህም ደስታውን እጥፍ አደረገለት፡፡ ነገር ግን ልጅትዋን የግሉ ሀብት አድርጎ በመቀበልና የደስታው ምንጭ እንድትሆን በማድረጉ በመጠኑም ቢሆን የሕሊና ወቀሣ
ነበረበት::

ይህቺ ልጅ ገና እምቡጥ ናት:: ምንም ነገር አታውቅም:: ሕይወትዋን እንደፈቀደ የሚመራው ዣን ቫልዣ ነው:: ይህንንም ያደረገው ከክፉ ነገር
ላይ እንዳትወድቅ በማሰብ ነበር፡፡ ሆኖም ይህን ዓይነቱ አስተዳደግ የዓለምን ምንነት ለማወቅ እድል አልሰጣትም:: የራስዋን እድል ራስዋ ልትወስን አልቻለችም:: እንደ እውነቱ ከሆነ ሰውዬው ይህቺን ልጅ እንደ ቦይ ውሃ የመራት ከእርሱ እንዳትሄድ እንጂ ሙሉ በመሉ ለእርስዋ ብሎ አልነበረም፡፡
ይህ ነው የሕሊና ወቀሣ ያስከተለበት::
ከመነኩሴ ትምህርት ቤት ያስገባት እርሱ ነው:: መነኩሲት እንድትሆን የወሰነው እርሱ በመሆኑ ምናልባት ስታድግ በዚህ የተነሣ ልትጠላው ትችላለትች፡ ይህንና ይህን የመሳሰለ አሳቦች ናቸው ገዳሙን ለቅቆ እንዲወጣ
ያደረጉት:: ከዚህ ለመውጣት ከውሳኔ አሳብ ከደረሰ በኋላ አልቆየም::ግቢውን ለቅቆ ለመውጣት ጥሩ አጋጣሚ እየጠበቀ ሳለ ሽማግሌው ፎሽለማ መሞታቸው በዚሁ ሳቢያ ግቢውን ለቅቆ ወጣ፡፡

ከገዳሙ ሲወጣ ለገዳሙ አለቃ የነገራቸው ወንድሙ በመሞታቸውና እንደ እርሳቸውም መሞት የተነሣ መጠነኛ ሀብት ስለወረሰ ሌላ ቦታ ሄዶ መኖር የሚችል መሆኑን ነበር፡፡ ስለዚህ ልጁን ይዞ ያለ ብዙ ድካም ከሌላ
ቦታ ለመኖር የወሰነ መሆኑን ሲነግራቸው አልተቃወሙትም:: ልጅትዋን በማስተማር ገዳሙ ላበረከተው አስተዋጽኦ ለገዳሙ አምስት ሺህ ፍራንክ በስጦታ መልክ ሰጥቶ ነው የወጣው::

ከገዳሙ ሲወጣ የማንንም እርዳታ ሳይጠይቅና ማንንም ሳያስቸግር
ያቺን ትንሽ ሳጥን እርሱ ራሱ በእጁ ይዞ ነው የወጣው:: የሳጥንዋን ቁልፍ ዘወትር ከእርሱ አይለያትም:: ስለሳጥንዋ ኮዜት ሁልጊዜም ትገረማለች፡፡አንድ ዓይነት የተለየ ጠረን አላት:: ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሳጥንዋን ከራሱ አይለያትም:: ሁልጊዜም የሚያስቀምጣት ከራሱ ክፍል ውስጥ ነው:: ከቦታ ወደ ቦታ በተዘዋወሩ ቀጥር እርስዋን ብቻ ነው አንጠልጥሉ የሚሄደው::
ኮዜት «ይህቺን ሣጥን ቀናሁባት» እያለች አንዳንዴ ብቻዋን ትስቃለች::

ከጊዜ በኋላ ዣን ቫልዣ ወደ ከተማ በወጣ ቁጥር እየተጨነቀ እንጂ
መዝናናትን ከተወ ሰንበት ብሉአል:: ፕሎሜ ጎዳና ላይ ካለው ቤት ውስጥ ከገባ ጀምሮ ብዙ ጊዜ ከቤት አይወጣም:: ከዚያ ቤት ውስጥ እያለ ስሙ የሚታወቀው ኧልቲስ ፎሽለማ በሚል ስያሜ ነው::

እዚያው ቤት ውስጥ እያለ ሌሉች ሁለት አነስተኛ ቤቶች ከተለያዩ
ሰፈር ተከራይቶ በስሙ ይይዛል:: አልፎ አልፎ ወደ እነዚህ ቤቶች ተራ በተራ አንድ ጊዜ ከአንደኛው በሌላ ጊዜ ደግሞ ከሁለተኛው እየሄደ ወርም ሁለት ወርም ኮዜትን ይዞ ይቀመጣል:: አሮጊትዋን ግን ይዟት አይሄድም፡፡ይህንንም ያደረገው ከፖሊሶች ለመሰወር ነበር፡፡

ከቤት ውስጥ ሲሆኑ ቤቱን የምትመራው ኮዜት ናት ገዳም ውስጥ እያለች ስለቤት አያያዝ ትምህርት ቀስማለች:: ብዙውን ጊዜ ዣን ቫልዣ በጓሮ በኩል ከነበሩት ቤቶች ውስጥ ሲቀመጥ ኮዜት ከትልቁ ቤት ውስጥ
ፎቅ ላይ ነው የምትቀመጠው:: በየቀኑ ዣን ቫልዣ የኮዜትን እጅ እየያዘ ከዚያ ከተንጣለለውና ስአበባ ከአጌጠው ግቢያቸው ውስጥ ይንሸራሽራሉ፡፡
ወደ ከተማ የሚወጠበት ቀን
ውሰን ነው:: እሑድ እሑድ ግን
ወደ ውጭ ወጣ ብለው ይንሸራሸራሉ በዚህ ጊዜ የኮዜትን ቁንጅና ተመልካች እየበዛ መጣ በርግጥ እርሷም ሁሌ የምታስበው ነው ለሽርሽር በወጡ ቁጥር ወንዶች ሰብሰብ ብለው አንዱን አፍጥጣ ስታይ አንድ ሰው ‹‹በእርግጥም ቆንጆ ነሽ የሚላት መሰላት::ትንሽ ተሽኮረመመች:: ያን እለት ማታ ጥሩ እንቅልፍ አልተኛችም፡፡ ከተኛች በኋላ «እውነትም ቆንጆ ነኝ፤ የወንዶች ልብ አሁን እኔን ይመኛል?»
ስትል ብዙ አሰበች:: ገዳም ውስጥ በነበረችበት ጊዜ የምታውቃቸውን ጓደኞችዋን በማስታወስ መልክዋን ከእነርሱ መልክ ጋር ማነፃፀር ጀመረች::
«እኔ እኮ ከእገሊት አላንስም፡፡ እገሊትም ብትሆን እስከዚህም የምትደነቅ ልጅ አይደለችም፡፡ ውይ እገሊት ግን በጣም ቆንጆ ናት:: እኔን ትበልጠኛለች ብቻ ምንዋ ነው ከእኔ የሚበልጠው?» እያለች ስለውበትዋ ታሰላስል
ጀመር::

አንድ ቀን ከግቢው ውስጥ እየተንሸራሸረች ሳለ አሮጊትዋ ቱሴይ
«ጌታዬ ይህቺ ልጅ እንዴት እየቆነጀች እንደሄደች ልብ ብለዋል?» ብላ ስትናገር ትሰማለች:: አባትዋ ምን መልስ እንደሰጠ ግን አልሰማችም::
የቱሴይ ንግግር ግን ስሜትዋን ነካው:: እየሮጠች ወደ ክፍልዋ ሄደች::
ከመስታወት ፊት ቆማ መልክዋን አየችው:: መስታወት በማየት መልክዋ ካስደነገጣት አንድ ሦስት ወር ያህል አልፎአል፡፡ የመጀመሪያው ቀን ሰው
ሳያያት ትንሽ አልቅሳለች:: የምታየው ራስዋን ሳይሆን የሌላ ሰው መስሎአት ነበር።

በጣም ቆንጆ ለመሆንዋ ለሁለተኛ ጊዜ አረጋገጠች:: መስታወቱና
ቱሴይ ያሉት ነገር ትክክል እንደሆነ አልተጠራጠረችም:: ቅርጽዋ፣ የቆዳዋ ቀለም፣ ፀጉርዋ፣ ዓይንዋ፣ ጥርስዋ፣ አፍንጫዋ ይህ ቀረሽ የምትባል ልጅ አልነበረችም:: ውበትዋ እንደጠዋት ፀሐይ ፊትዋ ላይ በራ፤ ተንጸባረቀ፣ ደመቀ፡፡ ወደ አበባው ቦታ ተመለሰች:፡ ወፎች ስለእርስዋ የሚዘምሩ መሰላት።
ራስዋንም እንደ ንግሥት ለመቁጠር ቃጣች::

ተመልሳ ስትመጣ ዣን ቫልዣ በአያት ጊዜ ልቡ ደነገጠ፡፡ የኮዚት
👍194
#ምንዱባን


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

መጨረሻው እንደ አጀማመሩ አልሆነም

ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ኮዜት ከሀዘንዋ እያገገመች መጣች:: የጊዜው
መርዘም፣ ወጣትነትዋ፣ የአባትዋ ፍቅርና የአካባቢዋ ማማር ቀስ በቀስ ሀዘንዋን እንድትረሳ ረዱዋት:: ቀን አልፎ ቀን ሲተካ፧ ወር አልፎ ወር ሲተካ የፍቅርዋ ሙላት በየቀኑ በጠብታዎች እየጎደለ ሄደ:: ወላፈኑ በርዶ
ወደ መጥፋት ተቃረበ፡፡ ሆኖም ረመጠ ጨርሶ ስላልጠፋ ማቃጠሉ፣ ማስጨነቁና ማሰቃየቱን ትቶአታል እንጂ ጨርሶ አልተወገደም::

አንድ ቀን በድንገት ማሪየስ ታወሳት:: «ምን!» አለች:: «ደግሞ ከየት መጣ? ረስቼው አልነበረም እንዴ!» በማሪየስ በኩል ደግሞ «ምነው ከመሞቴ በፊት አንድ ጊዜ ብቻ ባየኋት!» የሚልበት ወቅት ነበር፡፡

የማን ጥፋት ነው? የማንም::

አንዳንድ ሰው ከገባበት ወጥመድ በቀላሉ መውጣት አይችልም፡፡
ማሪየስ የዚያ ዓይነት ሰው ነው:: ከደረሰበት ሀዘን እንደ ኮዜት በቀላሉ ሊላቀቅ አልቻለም:: ሀዘን ውስጥ ገብቶ እዚያው ነው ተዘፍቆ የቀረው።

አንድ አጋጣሚ ይከተላል፡፡ በትልቁ በር በኩል ከአንድ ግቢ ውስጥ
አንድ እንደ መቀመጫ የሚያገለግል ጥርብ ድንጋይ ነበር፡፡ እንደ ሴት ጎፈሬ
የተከረከመ የዛፍ አጥር በአጠገቡ ስለነበር ማንም ሰው በመንገድ ሲያልፍ ወደ ውስጥ ማየት አይችልም፡፡ ነገር ግን ከውስጥ ያለ ሰው ከፈለገ እጁን
በአጥሩ ቀዳዳ በማበጀት አሾልኮ በውጭ የሚያልፈውን ሰው ማየትና መጨበጥ ይችላል፡፡

አንድ ቀን ማታ ዣን ቫልዣ ወደ ውጭ ወጥቶ ነበር፡፡ አየሩ ጥሩ
ስለነበር መሸት ሲል ኮሴት ከዚያ ድንጋይ ላይ ተክዛ ቁጭ ብላለች፡፡ የጥንት ትዝታዋ ተቀሰቀሰባት፡፡ ጊዜው ጨለምለም ብሏል፡፡ የእናትዋ መንፈስ ከዚያ ያለ መሰላት፡፡ ከተቀመጠችበት ብድግ ብላ ሄደች::

ቀደም ሲል ዝናብ ዘንቦ ስለነበር ሳሩ ያቀዘቅዛል፡፡ «ይህስ ጉንፋን
ያሲዛል ፧ ብቀመጥ ይሻላል» ብላ ወደ ድንጋዩ መቀመጫ ስትመለስ
መቀመጫው ላይ አንድ ነገር አየች:: አንድ እጥፍጥፍ ብላ የተጠቀለለ ነገር ከትንሽ ጠጠር ጋር ተያይዟል:: ከመቀመጫው ተነስታ ስትሄድ ከዚያ
አልነበረም::

ኮዜት ገርሞኣት «ምንድነው እሱ?» ስትል ራስዋን ጠየቀች:: መቼም ሰው ካላስቀመጠው በራሱ ኃይል ሊመጣ እንደማይችል ተረዳች:: ፍርሃት፣ፍርሃት፣ አላት፡፡ ድንጋዩን መንካት አልደፈረችም:: ወደኋላ ሳታይ ቤትዋ ሮጠች፡፡ ቤትዋ ከገባች በኋላ በርና መስኮት ዘጋጋች፡፡ መቀርቀሪያዎቹን
ሁሉ ቀረቀረች:: ከጥቂት ጊዜ እረፍት በኋላ ‹አባባ ተመልሷል እንዴ?»
ስትል ቱሴይን ጠየቀቻት::

«ኧረ አልተመለሰም» አለቻት::

ክፍሎቹ በሙሉ ተዘግተው እንደሆነና ከቤት ውስጥ ሰው እንዳለ እንድታይ ቱሴይን አዘዘቻት:: አጎንብሳ ከአልጋዋ ስር እንዲሁም ቁም ሣጥንዋን ከፍታ ሰው እንዳለና እንደሌለ አጣራች:: ከተኛች በኋላ ያ ያየችው
ጠጠር ተራራ አክሉ በውስጡ ዋሻ እንዳለበት አለመች::

ጠዋት ፀሐይ ስትወጣና ጨለማ ለብርሃን ቦታዋን ስትለቅ ማታ
እንደዚያ ያስፈራሩን ነገሮች እንደሚያስቁን ይታወቃል:: ኮዜት ስትነቃ ማታ እንደዚያ ያስፈራት ነገር ቅዠት መስሎ ታያት:: ስለምን ነበር የምቃዠው?» ስትል ራስዋን ጠየቀች::

ልብስዋን ለብሳ ወደ አትክልቱ ቦታ ሄደች:: ስትፈራኛ ስትቸር ማታ
ተቀምጣበት ወደነበረው የድንጋይ መቀመጫ ሄደች:: የተጠቀለለው ነገር ከዚያው ቁጭ ብሉአል:: በመጀመሪያ ትንሽ ፈርታ ነበር:: በኋላ ግን ፍርሃቱ ተወገደላት:: ደግሞም በጨለማ የሸሸነወ ነገር በብርሃን እንጓጓለታለንና ምን እንደሆነ ለማየት ቸኩለች፡፡

«አይ ምን አስፈራኝ፤ ፈትቼ ልየዋ» አለች ለራስዋ:: የተጠቀለለውን
ነገር አንስታ ከፈታታችው በኋላ አብሮ ታስሮ የነበረውን ድንጋይ ጣለችው::

አድራሻ ያልተጻፈበትና በውስጠ ወረቀት ያለው እንደ ደብዳቤ ያለ ነገር መሆኑን ተገነዘበች:: ወረቀቱን ከውስጡ ሳታወጣ አገላብጣ አየችው:: አሁን መፍራትዋ ቀርቶ «ከውስጡ ምን አለ» በማለት በመጓጓት ለማወቅ ፈለገች::
ፖስታውን ከፍታ ከውስጡ የነበረውን ወረቀት አወጣች:: በጥሩ የእጅ ጽሑፍ እንደ ጥቅስ ያሉ ነገሮች ተጽፎበታል፡፡ የገጹ ብዛት ከአንድ በላይ ነው:: እያንዳንዱ ገጽ ላይ ቁጥር ተጽፎበታል:: ሆኖም እያንዳንዱ ገጽ ሞልቶ የተጻፈበት ሳይሆን መሐሉ ላይ ብቻ ነው የተጻፈው:: የመጻፊያ ቦታ እያለ ወደ ሚቀጥለው ገጽ ይዞራል::

ፊርማ ወይም ስም ካለበት በሚል በችኮላ ፈለገች፤ ግን አላገኘችም::
ለማነው የተጻፈው? ለራስዋ እንደሆነ ጠረጠረች፡፡ ምክንያቱም እርስዋ ተቀምጣበት ከነበረው ሥፍራ ነው የተገኘው፡፡ ታዲያ ማነው ጸሐፊው?
ግራ ገባት:: በመገላመጥ አካባቢዋን ቃኘች፡፡ ከርግቦች በስተቀር ምንም ነገር የለም:: ወረቀቱን ማንበብዋን ቀጠለች::
ቀጥሎ የተመለከተው ነበር በወረቀቶቹ ላይ የተጻፈው::

«ዓለም ተጨብጣ አንዲት ትንሽ ነገር ስትሆን፧ አንዲት ትንሽ ነገር
ደግሞ ተነፍታ እግዚአብሔርን ስታክል ፍቅር ትባላለች፡፡ ፍቅር ነፍስን ትመስላለች፤ አፈጣጠራቸው አንድ ነው፡፡ እንደ ነፍስ የመንፈስ ቅዱስ
ብልጭታ ኣለባት፡፡ እንደ ነፍስ ግን አትገድፍም፣ አትነጣጠልም
አትጠፋም፡፡ የእሳት ረመጥ ስትሆን በውስጣችን አለች፤ ዘላለማዊ ናት..ማለቂያና መደምደሚያ የላትም፡፡ ረመጥዋ በምንም ነገር አይጠፋም::
ከአጥንታችን ውስጥ እንኳን ገብታ ስትፋጅ ይሰማናል:: እንዲሁም ከሰማየ ሰማያት ወርዳ፧ ከአካል ውስጥ ዘልቃ ትገባለች፡፡ ሆኖም ስታንፀባርቅ አካላችን ውስጥ በጉልህ እናያታለን፡፡

«ፍቅር! አድናቆት! የሁለት የሚግባቡ አእምሮዎች ፣ የሁለት
የሚወሳሰቡ ልቦች፣ የሁለት አካልን ሰነጣጥቀው የሚገቡ ዓይኖች ያላት ብርሃን! አንቺ ደስታ ወደ እኔ ትመጪያለሽ ወይስ አትመጪም! ፍቅር
ብቸኝነትን ሲያጠቃ አብሮ የሚጓዝ፤ የሚንሸራሽር! የተባረኩ ቀኖች! የሰዎችን እድል፣ የሰዎችን እጣ ፈንታ ለመካፈል መላእክት ከሰማየ ሰማያት ወርደው
በዚህች ምድር ሲኖሩ በሕልሜ ያየኋቸው ነው የመሰለኝ፡፡ አይ ፍቅር!

«ዘላለማዊ ከማድረግ በስተቀር ማንም ከሁለት ከሚዋደዱ ፍጡሮች ደስታ ላይ የሚጨምረው ነገር የለም፡፡ በእርግጥ የፍቅር ዘላለማዊነት
ከፍቅር ዘመን በኋላ የሚታከል ነው:: ግን የፍቅርን መጠን፣ የፍቅርን ግለት ለማሳደግ ከፍቅረኞቹ ከራሳቸው በስተቀር ማንም ሊያስቀረው አይቻለውም፡፡ ፍቅር የሰዎች ፍጹምነት ይታይበታል፡፡

«ከዋክብትን የምናይበት ምክንያት ሁለት ነው:: ይኸውም
ስለሚያብረቀርቁ ወይም ምንነታቸውን ስለማናውቅ! ከጎናችን ግን ከከዋክብት
ይበልጥ ምሥጢሩ ያልታወቀ የላመ፣ የለሰለሰና የሚያንፀባርቅ ፍጡር አለ... ሴት::

«ድንጋይ ከሆንክ ትልቅ ድንጋይ ሁን፤ የዛፍና የቅጠላቅጠል ዘር
ከሆንክ ስሜት፤ ሰው ከሆንክ ደግሞ ፍቅር ይኑርህ::

«ወደ ሽርሽሩ ቦታ ትመጣለች? የለም ጌታዬ! በየሳምንቱ እሑድ ወደ ቤተክርስቲያን ትመጣ የለ? የለም መምጣቱን ትታለች:: አሁን ከዚሁ ቤት ውስጥ ነው የምትኖረው? የለም ለቅቃለች፡፡ አሁን ከየት ሰፈር ገባች?
አድራሻዋ አይታወቅም፡፡ ስትሄድ አልተናገረችም? አልነገረችንም:: ምን ዓይነት የተዳፈነ ጨለማ ነው እባካችሁ የአንድን ነፍስ አድራሻ አለማወቅ!

በፍቅር ምክንያት የምትጨነቅ፣ የምትሰቃይ ነፍስ! አሁንም ውደድ፤ በይበልጥ አፍቅር፡፡ በፍቅር መሞት ማለት በፍቅር መኖር ማለት ነውና፡፡
👍17😱1
#ምንዱባን


#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


....ልክ ፍቅረኛዋን የምትደባብስ ይመስል በለስላሳ እጆችዋ ድንጋዩን በማሻሸት አመሰገነችው:: «ምነው ተጫጫነኝ፣ ማን አለ ከአጠገቤ»
እንደሚባለው ሁሉ ምንም እንኳን በዓይንዋ ባታየውም ከአጠገብዋ ሰው እንደቆመ ከበዳት:: ይህ እንዴት ሆነ ቢባል በቃላት ለመግለጽ ያስቸግራል፡፡
ፊትዋን አዙራ ከተመለከተች በኋላ ብድግ አለች:: እሱው ነበር:: ቆብ
ወይም ኮፍያ አላጠለቀም:: ሰውነቱ ገርጥቶአል፡፡ ትንሽ ከሳ ያለ ሰውነት ያለው ሲሆን የለበሰው ልብስ ጠቆር ያለ ነው፡፡ ፊቱ ጎልቶ ይታይ እንጂ አፍንጫው ሰልከክ ያለ ለመሆኑ ይታያል::

ኮዜት ብትደነግጥም የጩኸት ድምፅ ለማሰማት አልደፈረችም::
አንድ ነገር ወደፊት የሳባት ስለመሰላት ወደኋላ ሸሸት አለች:: ልጁ ከነበረበት አልተነቃነቀም:: ዐይኑን ለማየት ባትችልም በሀዘን መሞላቱን ገመተች::

ኮዜት ወደኋላ ስትሸሽ ከግንድ ጋር ስለተላተመች ያንኑ ግንድ ተደግፋ
ቀረች:: ዛፉን ተደግፋ ባትቆም ኖሮ እጅ እግርዋ ስለዛለባት ትወድቅ ነበር፡፡ዛፉን ተደግፋ እንደቆመች ድምፁን ሰማች:: ያን ድምፅ ከዚያ በፊት ሰምታው አታውቅም:: በጣም ዝግ ብሎ ነበር የሚናገረው::

«ይቅርታሽን፣ እዚህ ነው ያለሁት፡፡ ልቤ ሊፈነዳ ነው:: መኖር እየተሳነኝ ነው ከዚህ የመጣሁት፡፡ ከመቀመጫው ላይ የወረወርኩትን ፅሑፍ አንብበሽዋል? ለመሆኑ ማን እንደሆንኩ አውቀሽኛል? አትፍሪኝ::ጊዜው በጣም
ቆይቷል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የተያየንበት ቀን ታስታውሺዋለሽ?
ዘወትር ትሄጅበት የነበረው የሽርሽር ቦታ! በአጠገቤ ያለፍሽበት ቀንስ ቀኖቹ ሰኔ 16 እና ሐምሌ 2 ነበሩ፡፡ አሁንማ ዓመት ሊሞላው ምን ቀረው።
ዓይንሽን እንኳን ሳላይ ብዙ ጊዜ አለፈ፡፡ ማታ ማታ ከዚህ እመጣለሁ አትፍሪ፣ ግድ የለሽም፣ ከዚህ ማንም የለም:: ከዚህ የምመጣው የመኝታ ክፍልሽን መስኮት በሩቁ ለማየት ነው:: ከዚህ አካባቢ በምመጣበት ጊዜ
ደግሞ ድንገት በአካባቢው ካለሽ እንዳትደነግጪ እያልኩ ስራመድ
በዝግታ ነበር፡፡ አንድ ቀን ስትዘምሪ ሰምቼሽ በጣም ደስ አለኝ፡፡ ከክፍልኝ ውስጥ ሆነሽ ስትዘምሪ መስማቴ ያስከፋሻል? ጉዳት ያለው አይመስለኝም። አየሽ፣ አንቺ እኮ ለእኔ መልአኬ ነሽ፡፡ አንዳንድ ጊዜ እስቲ ከዚህ እንድቀመጥ
ፍቀጂልኝ፡፡ በቅርቡ እንደምሞት አውቃለሁ፡፡ ይህን ብታውቂ! እኔ እኮ እንደ አምላክ ነው የማመልክሽ! ይቅርታ አድርጊልኝ፤ ንግግር አላውቅም
ከአንቺ ጋር ማውራቴን ረስቼአለሁ፡፡ ምናልባት ሳላውቀው አናድጄሽ ወይ አበሳጭቼሽ ይሆናል፡፡ አዘንሽብኝ?

«ወይ እማዬ!» አለች፡፡ ልክ እንደሚሞት ሰው ተዝለፈለፈች፡፡

ከነበረበት ወደ እርስዋ ሮጠ፡፡ ከወደቀችበት እቅፍ አድርጎ አነሳት!
ምን እንደሚያደርግ ሳይታወቀው በጣም በመጭመቅ አቀፋት:: እየተንገዳገደ ወደ ላይ ብድግ አደረጋት፡፡ አካሉ በጭስ የተሞላ ይመስል ሰውነቱ ውስሳ
እየተነነ የሚሄድ ነገር እንዳለ ተሰማው:: መንፈሳዊ ተግባርም የሚያከናው መሰለው፡፡ ምንም እንኳን ከልቡ አስጠግቶ ቢያቅፋትም የፍቶተ ስሜት ጨርሶ አልተሰማውም፤ እውነተኛ ፍቅር የፍቶተ ሥጋ መርካት አይደለምና፡ ልጁ ከእውነተኛ ፍቅር ወጥመድ ውስጥ ለመግባቱ ምልክት
ነበር፡፡

እጁን ይዛ ወደ ልብዋ አስጠጋችው:: ወረቀት ከጡቶችዋ መኖሩን ተገነዘበ፡፡ ዝግ ባለ ድምፅ ተናገረ::

«እንግዲያውማ ትወጂኛለሽ ማለት ነዋ!»
ጆሮን በኃይል ካላቀኑ በማይሰማ በጣም ዝቅ ባለ ድምፅ መልስ
ሰጠችው::

«እስቲ ዝም በል፤ እሱንማ የምታውቀው ነው::»

በሀፍረት የቀላው ፊትዋን ላለማሳየት ኩራት በተሰማውና በፍቅር በሰከረው ወጣት ብብት ስር ራስዋን ደበቀች::

ከድንጋዩ መቀመጫ ላይ ቁጭ ሲል እርሱዋም ከአጠገቡ
አለች:: ዝምታ ሰፈነ፡፡ ከዋክብት ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል:: እንዴት ነው ከንፈሮቻቸው የተገናኙት? እንዴት ነው አእዋፍ በዚህ ሰዓት ማዜም
የጀመሩት? እንዴትስ አበቦች ሊፈኩ ቻሉ?
አለቀ! በቃ ! ሥሮቻቸው የተነቀሉ እስኪመስላቸው ተሳሳሙ::

የሁለቱም ሰውነት ነፋስ እንዳወዛወዘው ቅጠል ተንቀጠቀጠ፡፡ በጨለማ
የሁለቱም ዓይኖች ቦግ ስላሉ ተፋጠጡ፡፡ ብርዱ አልተሰማቸውም፤ ድንጋዩ
አልቆረቆራቸውም፤ መሬቱና ሳሩ አልቀዘቀዛቸውም:: አሁንም በመፋጠጥ እየተያዩ ነው፡፡ ልባቸው በአሳብ ተሞልቷል፡፡ ሳይታወቃቸው እጅ ለእጅ
ተጨባብጠዋል፡፡

ለማንኛውም እንዴት አድርጎ ከአጥር ግቢው ውስጥ እንደገባ
አልጠየቀችውም፤ ለመጠየቅም አልፈለገችም፡፡ የእርሱ ከዚያ መገኘት እንግዳ ነገር
አልሆነባትም::

አልፎ አልፎ የማሪየስ ጉልበት የኮዜትን ጉልበት ሲነካ ሁለቱም
በደስታ ይፈካሉ፡፡ ቆይታ ኮዜት አንዳንድ ቃል ትወረውራለች፡፡ ስትናገር ነፍስዋ ከከንፈርዋ ጫፍ ላይ እንደሆነች ከከንፈርዋ ጋር አብሮ ተንቀጠቀጠ ለማለት ይቻላል፡፡

ቀስ በቀስ ዝምታው ተወግዶ ማውራት ጀመሩ፡፡ እንደገና የፍቅር
ስበታቸው ሞልቶ ስለፈሰሰ ዝም ተባባሉ፡፡ ምድርም ዝም አለች፡፡ ነፋስ እንኳን «ዝም በል» ብለው ያዘዙት ይመስል ፀጥ አለ፡፡ እንደገና ጨዋታ ጀመሩት፡፡ እነዚህ ሁለት እንደ ጥቅምት ውሃ የጠሩ ፍጡሮች ስለነበሩ ስላለፈው ምኞታቸው፣ ወፈፍ አድርጎአቸው ስለፈጸሙት ተግባር፣ ስለደስታ
ዘመናቸውን ፣ ስለተከፉበት ጊዜ እንዲሁም አንዱ ሌላውን ምን ያህል ይመኝ እንደነበር አንድም ነገር ሳይደባበቁ ተጫወቱ፡፡ አንዱ ስለሌላው ስለነበረው
ምኞትና አድናቆትም ተነጋገሩ፡: ሳይተያዩ ሲቀሩ ሁለቱም ምን ያህል ተስፋ ቆረጠው እንደነበር ተገላለጹ፡፡ ከሁለቱም ልብ ውስጥ የነበረው ሁሉ እንደ ውሃ ፈሰሰ፣ ተንቆረቆረ:: ስለዚህ ከአንድ ሰዓት በኋላ ወጣቱ የወጣትዋ፣
ወጣትዋ የወጣቱ ሕይወት ማለት እርሱ እርስዋን፣ እርስዋ እርሱን ሆኑ፡፡አንዱ ሌላው ልብ ወስጥ ዘልቆ ገባ፡፡ አንዱ የሌላው ጌታ ሆነ፡፡ አንዱ በሌላው ረካ፤ ፈካ፤ ተደሰተ፡፡

ልባቸው ውስጥ የነበረው ነገር ተሟጥጦ ሲያልቅ ጭንቅላትዋን
ከትከሻው ላይ አሳርፋ ጥያቄ ጠየቀችው::

«ስምህ ማነው?»

«ስሜ ማሪየስ ይባላል» አለ::

«የአንቺስ?»

«ኮዜት እባላለሁ፡፡››
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ማምለጥ

ምንም እንኳን ቴናድዬ የታሠረው ከተለየ ክፍል ውስጥ ቢሆንም
እርሱና ሌሎች ሦስት ሽፍቶች የማምለጥ አድማ ይመታሉ፡፡ ሁለቱ ሽፍቶች ከምድር ቤት ውስጥ ሲሆኑ ቴናድዬ ብቻውን ፎቅ ላይ ነበር፡፡ ከአደሙ
መካከል አንደኛው አደገኛነቱ ታውቆ እንዲሁ ለብቻው ነበር የታስረው::

በምን ተአምር ጠርሙስ ቪኖ እንዴት ሊያስገባ እንደቻለ ባይታወቅም መጠጡ ቴናድዬ ክፍል ውስጥ ተገኝቷል ይህ መጠጥ በውስጡ ሱስ
የሚያሲዝ እንደ ሐሺሽ ያለ ቅመም እንደነበረበት ይነገራል

መቼስ በእያንዳንዱ እስር ቤት ውስጥ እስረኞች እንዲያመልጡ
የሚተባበሩና እምነታቸውንና መሐላቸውን ለገንዘብ የሚሰጡ ጉበኞች ወይም ሌቦች ወይም ቀጣፊዎች አይታጡም: እንደነዚህ ያሉ ሰዎች ከደመወዛቸው
በላይ ገቢ አላቸው::

ሁለቱ ሽፍቶች አንድ ቀን ጠዋት ማምለጣቸውና ከመንገድ
የሚጠብቋቸው ለመሆኑ የሚያወቁ ሌሎች ሁለት ሽፍቶች ከውስጥ ይቀራሉ እነርሱም ለማምለጥ ዘዴ ይፈጥራሉ በአጋጣሚ በእለቱ በረዶ የተቀላቀለበት ከባድ ዝናብ ይጥል ስለነበር በዚህ አጋጣሚ በመጠቀምና ጨለማን ተገን
በማድረግ እነዚያ ሁለት ሽፍቶች በፈጠሩት ዘዴ ተጠቅመው ለማምለጥ ችለዋል::
👍21👏21😁1
#ምንዱባን


#ክፍል_አርባ


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


መማረክና መረሳሳት

ብረት በማግኔት እንደሚሳብ ፍቅረኛም ባፈቀረው ጠዋት ማታ
ይሳባል፤ ይጉተታል፡፡ ሮሚዮ በዡልየት ፍቅር ተጎትቶ በአትክልት ቦታ እንደ ተንሸራሸረ ሁሉ ማሪየስም ከኮዜት የአትክልት ሥፍራ ለመንሸራሸር ተመላለሰ፡፡ ሆኖም ማሪየስ የሮሚዮን ያህል አልተቸገረም:: ሮሚዮ ከዡልዬት
ግቢ ለመግባት ረጅም ግምብ መዝለል ነበረበት:: ማሪየስ ግን ይህ አላስፈለገውም:: የሽቦ አጥርን በቀላሉ ፈልቅቆ ነበር የሚገባው:: ቀጭን
ስለነበር ሰፊ ክፍት ቦታ አላስፈለገውም::

አካባቢውም ጭር ያለ ስለነበር ሰው ሳያየው በቀላሉ ሊገባ ቻለ፡፡
የሚመጣው ደግሞ ማታ ማታ ነው:: በዚያች በተባረከች ምሽት ከንፈር ለከንፈር ከተገናኙ ወዲህ በእየለቱ ነው የሚመጣው::

በ1832 ዓ.ም የግንቦት ወርን በሙሉ አንድ ቀን እንኳን ሳይጓደል
ማታ ማታ ተመላልሶ ከፍቅረኛው ጋር ተገናኘ:: እነዚህ ሁለት የዋህ
ፍጡሮች እንዳይገናኙ ጨለማ፣ ብርድ፣ ነፋስ አላገዳቸውም::

በየዕለቱ ሲገናኙ ምን ይሠራሉ? ምንም:: አንዱ ሌላውን በማድነቅ
ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ:: የሚረግጡትን መሬት እንደ ተቀደሰ ቦታ ነው የሚቆጥሩት:: ብዙ ጊዜ የሚያወሩት ስለፍቅር ነው:: ማሪየስ የሙት ልጅ
መሆኑን! ስሙ ማሪየስ ፓንትመርሲ እንደሚባልና የሕግ ባለሙያ እንደሆነ ገልጾላታል፡፡ ኑሮውን የሚያሸንፈው ለአሳታሚ ድርጅቶች አንዳንድ ጽሑፍ
እየጻፈ እንደሆነና አባቱ በአገሩ የታወቀ ጀግና እንደነበር ነገራት፡ እንዲሁም ከዲታው አያቱ ጋር መጣላቱንና የአባቱን ሹመት በመውረስ ባሮን እንደሆነም
ገልጾለታል። ባለማዕረግ ስለሆነ ኮዜት ላይ የተለየ ስሜት አላሳደረባትም::ለእርስዋ ምንም ይሁን ምን ማሪየስ ማሪየስ ነው:: በእርስዋም በኩል ገዳም ውስጥ ማደግዋን፣ እናትና አባትዋ መሞታቸውን፣ የእንጀራ አባትዋ ስም። መሴይ ፎሽለማ መሆኑን፣ ይህም ሰው ድሃን የሚወድ እጅግ ደግና ራሱም ምስኪን እንደሆነና እርስዋን ለማስደሰት ሲል ራሱን ረስቶ ያላደረገው ነገር
እንደሌላ ነገረችው፡፡ የእንጀራ አባትዋ ለእርስዋ ሲል ምቾቱን ሁሉ መሰዋቱንም አስረዳችው::

የሚገርመው ማሪየስ ኮዜትን ስላገኘና በምትነግረው ነገር ሁሉ
ስለረካ ሌላው ቀርቶ አንድ ቀን ሌሊት በቀዳዳ ከነቴናድዬ ቤት ውስጥ ያየውን እንኳን ረስቶ አባትዋ ላይ ደርሶ ስለነበረው ትርኢት አልነገራትም::
ሚስተርና ሚስስ ቴናድዬ በአባትዋ ላይ ስላደረሱት በደልና አባትዋ እንዴት አድርጎ ከዚያ ወጥመድ እንዳመለጠ ለጊዜው አልታወሰውም:: ሌላው ቀርቶ ማታ ያደረገውን ጠዋት፣ ጠዋት የሠራውን ማታ ይረሳል፡፡ አንድ
ሰው ቀን ላይ ተገናኝቶ «ቁርስህን ምንድነው የበላኸው?» ብሎ ቢጠይቀው አያስታውስም፡፡ ጆሮውና ሕሊናው በኮዜት ትዝታ ስለተደፈነ የማስታወስ
ችሎታውን ቀንሶበታል፡፡ ከዚህም በላይ ከኮዜት ተለይቶ የሚያሳልፈው ጊዜ ዝም ብሎ የሚያልፍ እንጂ ኑሮን እየኖረ የሚያልፍ ስላልመሰለው በሌላ
ጊዜ የሚፈጽመው ተግባር ሁሉ እርባነቢስ በመሆነ ይረሳዋል:: ለማሪየስ ኑሮ ወይም ሕይወት ማለት ከኮዜት ጋር የሚያሳልፈው ጊዜ ብቻ ነበር፡፡ ይህም የእውነተኛ ፍቅር ባሕርይ ነው::

ኮዜት በጣም የተዋበች ልጅ ስትሆን ማሪየስ ነፍስዋንም ጭምር ለማየት ነው የሚፈልገው:: የአንድን ነገር ሁለንተና በጉልህ ለማየት
የሚቻለው ዓይን ሲጨፈን ስለሆነ ማሪየስ ዓይኑን ብዙ ጊዜ ይጨፍናል፡፡ ማሪየስና ኮዜት መጨረሻቸው ምን እንደሚሆን አንስተውና ተነጋግረውበት
አያውቁም፡፡ ማንኛውም ነገር እንደአመጣጡ ነው የሚቀበሉት፡-
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዣን ቫልዣ ምንም አልጠረጠረም፡ኮዜት ዘወትር ደስ ብሉአት ስላየ
ከዚያ ወዲያ የሚፈልገው ነገር አልነበረምና ደስ እያለው ይኖራል፡፡ ኮዜትም ማሪየስን በማግኘትዋ መንፈስዋ ስለረካ ዘወትር የደስታ ምልክት ግንባርዋ ላይ ይነበባል:: በሁለት ፍቅረኞች መካከል መግባባት ካለ አብረው መኖር
ይችላሉ:: በመካከላቸው ሰላም እስካለ ድሬስ የተለየ ጠባይ ስለማይታይባቸው ሦስተኛ ሰው አዲስ ነገር ሊያይባቸው አይችልም:: ጥቂት ጥንቃቄ በማድረግ ከፍቅረኛቸው ጋር መኖር ይችላሉ::

አባትዋ የፈለገውን ለማድረግ ሲፈልግ ተቃውሞ አላሳየችውም፡፡ ዞርዞር ብዬ ልምጣ? እሺ አባዬ:: ዛሬ ከቤት ልዋል መሰለኝ? እንደፈለግህ፡፡
አብረን እናምሽ፡፡ ደስታውን አልችለውም::አባትዋ ዘወትር አራት ሰዓት አካባቢ ይተኛል፡፡

ማሪየስ እንደሆነ ከኮዚት ጋር ለመጫወት የሚመጣው ከአራት ሰዓት በኋላ ነው:: ቀን ቀን
ተገናኝተው አያውቁም፡፡ ዣን ቫልዣ እንደሆነ የማሪየስ በሕይወት መኖር እንኳን ረስቷል፡፡ አንድ ቀን ጠዋት ግን «ምነው ኮዜት፤ ከኋላሽ ኖራ ነክቶሻል ፤ ከየት መጣ?» ብሎ ይጠይቃታል፡፡ ያን እለት ማታ ከማሪየስ
ጋር ግድግዳ ተደግፋ ቆማ ኖሮ ልብስዋን ኖራ ነክቶባታል፡፡
አሮጊትዋ ቱሴይ በጊዜ ስለምትተኛ እርስዋም እንደ ዣን ቫልዣ ምንም ነገር አልጠረጠረችም:: ማሪየስ ደፍሮ ከቤትዋ ውስጥ ገብቶ
አያውቅም፡፡ አትክልቱ ውስጥ እንኳን ቢሆን አሳቻ ቦታ ይቀመጣሉ እንጂ ራሳቸውን አያጋልጡም:: ከአንድ ቦታ ከተቀመጡ አይነሱም:: ሁለቱም
አብረው በመሆናቸው ብቻ ረክተው ወሬም ባያወሩ ደንታ የላቸውም::ሌላው ቀርቶ በመንገድ የሚያልፍ እንኳን እንዳያያቸው ይጠነቀቃሉ፡፡
አብረው ተቀምጠው ሳለ ዓይን ለዓይን መተያየት፤ በየደቂቃው እጅ ለእጅ ተያይዞ ሃያ ጊዜ መጨማመቅ ደስታ ይሰጣቸዋል፡፡ በዚያች ሰዓት መብረቅ
ካጠገባቸወ: ቢወርድ እንኳን አይሰሙትም:: ይህን ያህል ነበር
ተመስጦአቸው::
ሆኖም ሁለቱ ፍቅረኞች በዚህ ሁኔታ እንዳሉ አንዳንድ ችግሮች
ደግሞ ፈር ቀድደው እየገቡ ነበር፡፡ አንድ ቀን ማታ እንደ ለመደው ማሪየስ ወደ ቀጠሮው ቦታ ለመሄድ አቀርቅሮ ይጓዛል:: ከአንድ ኩርባ መንገድ ላይ
ደርሶ ሊጠመዘዝ ሲል ድምፅ ይሰማል::

‹‹ሚስተር ማሪየስ እንደምን አመሸህ!››

ቀና ብሎ ሲያይ ኢፓኒን ናት:: ደንገጥ አለ፡፡ የኮዜት ቤት ካሳየችው እለት ወዲህ ትዝ ብላው ወይም ተያይተው አያውቁም:: አሁን ላገኘው ደስታ ምክንያት ብትሆንም ጨርሶ ረስቷታል:: መርሳት ብቻ ሳይሆን እንደገና መገናኘታቸው አናደደው::

የተደላደለ ፍቅር አንድን ሰው ፍጹም ያደርገዋል ብንል ተሳስተናል:: በስሜት መዋጥ ዝንጉ እንደሚያደርግም መርሳት የለብንም:: በስሜት የተዋጠ ሰው ክፋትንና ደግነትን መለየት ይሳነዋል፡፡ ውለታን፣ የሥራ
ኃላፊነትንና፡ መቃወስ ያለባቸውን ጉዳዮች ሁሉ ሊያስረሳው ይችላል::

ምን! አንቺ ነሽ እንዴ ኢፓኒን?» ሲል ለሰጠችው ሰላምታ በጥያቄ
መልክ መለሰላት::

«ምነው፣ በጣም ተኮሳትረህ ነው የምታነጋግረኝ? የአጠፋሁት ነገር
አለ?»

«የለም» ሲል መለሰላት::

በእርግጥም የያዘባት ቂም አልነበረም:: ደግሞም የሚቀየምበትም ምክንያት አልነበረውም፡፡ ኮዜትን በሚያነጋግርበት አንደበት ኢፓኒንን በጥሞና ማነጋገሩ ስለከበደው ብቻ ነው እንደዚያ የሆነው:: እርሱ ዝም ሲላት
እርስዋ ጮክ ብላ ተናገረች::

«ንገረኝ እስቲ አሁን» ብላ የሚናገረው ነገር እንደጠፋው ሰው ዝም አለች:: ፈገግታ ለማሳየት ሞከረች፡፡ ግን አቃታት፤ እንደገና ለመናገር ሞከረች::

«እና….» ብላ ንግግርዋን እንደገና አቋርጣ አቀርቅራ ቀረች::

«ደህና አምሽ ማሪየስ» ብላ መንገድዋን ቀጠለች::
👍21
#ምንዱባን


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


....ምን እንደሚያደርጉ ሳይታወቃቸው ከንፈር ለከንፈር ይገናኛሉ፡፡ ዓይናቸው እምባ አቅርሮ አንዱ ሌላው ላይ ማፍጠጥ ሆነ፡፡ ማሪየስና ኮዜትም የፈጸሙት ተግባር ይኸው ነበር፡፡

የማሪየስ አያት በዚህ ጊዜ ዘጠና አንድ ዓመት ሆኖአቸዋል፡፡ አሁንም
ከዚያ ትልቅ ቤታቸው ውስጥ ከሴት ልጃቸው ጋር ነው የሚኖሩት:: በዚህ እድሜያቸው ወገባቸው ሳይጎብጥና ሀዘን ፊታቸውን ሳይሰባብር ቀጥ ብለው
የሚጓዙና ለምሳሌነት ሊቀርቡ የሚችሉ የእድሜ ባለፀጋ ናቸው::
ሽማግሌው ሠራተኞችን መደብደብና ምርኩዛቸውን ሳይዞ መንቀሳቀስ በተው ጊዜ ልጃቸው «አሁንስ አባቴ በእርግጥ አርጅቷል» እያለች ታስብ
ጀመር፡፡ በሐምሌ ወር የተጀመረው የፈረንሣይ አብዮት መጥፎ ስሜት
አሳድሮባቸዋል፡፡ ቢሆንም ሞራላቸው ብርቱ ስለነበር ለማንኛውም ነገር በቀላሉ አልተበገሩም፡፡ ነገር ግን ውስጥ ውስጡን መጎዳታቸው ሳይሰማቸው አልቀረም:: ከአራት ዓመት በኋላ እንኳን አንድ ቀን ማሪየስ ከቤታቸው ተመልሶ ከጫማዬ ሥር ወድቆ ይቅርታ ይጠይቀኛል የሚል እምነት
ነበራቸው:: ማሪየስ ተመልሶ ከቤት ሳይወጣ እሞታለሁ የሚል ሀሳብ
ከሕሊናቸው ውስጥ ገብቶ አያውቅም:: እንዲያውም በቅርበ ማሪየስ ይመለሳል የሚለው እምነታቸው እየጠነከረ ይሄዳል፡፡ ይህም ለውለታቢሱ የልጅ ልጃቸው የነበራቸው ፍቅር አጠነከረባቸው::

ይህ ልጅ ሰማይና ምድር ቀሚጨልምበት በክረምት ወራት ነበር ጥሎአቸው የሄደው:: ሽማግሌው በእርሳቸው በኩል ምንም ጥፋት እንደሌለና
ጥፋቱ የማሪየስ እንደሆነ በፍጹም ልቦናቸው ቢያምኑም ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ግን አልተቀነሰም፡፡ በመጨረሻ ወደ ሞት መቃረባቸው ሲታወሳቸው
ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ያይላል፡፡ ጥርሳቸው መርገፍ ጀምሯል:: ይህም ሀዘናቸውን ከፍ አደረገው::

አንድ ቀን ጉልበታቸውን አጣጥፈውና ዓይናቸውን በከፊል ጨፍነው ቁጭ ይላሉ፡፡ የተስፋ መቁረጥ ምልክት ከፊታቸው ላይ ይነበባል:: ሴት ልጃቸው ጥያቄ ጠየቀቻቸው:

"አባባ፣ አሁንም ልጁን እንደተቀየሙት ነው?»

ይህን ካለች በኋላ ለመቀጠል ስላልደፈረች ዝም አለች::

"ማንን ነው የምትዪው?» ሲሉ ጠየቅዋት::

«ያንን ምስኪን ማሪየስ፡፡»

የሽማግሌ ጭንቅላታቸውን ቀና አደረጉ:: ያንን የተሸበሸበወን
ክርናቸውን ከጠረጴዛ ላይ በማሳረፍ አገጫቸውን ደግፈው ያዙ፡፡ በጣም በተናደደና በተቆጣ አንደበት ተናገሩ፡፡

«ምስኪን ማሪየስ አልሽ? የማይረባ! እርሱ ብሎ ምስኪን፤ አጉራሹን የሚነክስ! የእኛ እልኸኛ! ልስቢስ፣ እንኳን ልብ ነፍስ የለውም::»

እምባ ያቀረረውን ዓይናቸው ልጃቸው እንዳታይ ከነበሩበት ፊታቸውን በማዞር ተነስተው ሄዱ:: ከሦስት ቀን በኋላ በዝምታ አራት ሰዓት ሙሉ ከአንድ ሥፍራ ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ ሽማግሌ ልጃቸውን በመገሰጽ ይናገራሉ::

«ስለዚያ ልጅ ሁለተኛ እንዳታነሽብኝ ብዬ አልነበረም?»

በዚያው ሰሞን መሴይ ጊልኖርማንድ እሳት እየሞቁ አምሽተው ስለደከማቸው በጊዜ ልጃቸውን ደህና እደሪ ብለው ወደ መኝታ ክፍላቸው ሄዱ:: ልጃቸው ከሚቀጥለው ክፍል ውስጥ በሩን ክፍት አድርጋ ልብስ እየሰፋች ነበር:: ሽማግሌው እሳት ይሞቁ የነበረው ብቻቸውን ሲሆን
መጽሐፍ ለስሙ በእጃቸው ይዘው ነበር እንጂ አያነቡትም::
እሳት እየሞቀ ሳለ የልጅ ልጃቸው ማሪየስን አስታወሱት:: አሁንም
ቢሆን ውስጥ ውስጡን ይናፍቃቸዋል:: ሊታረቁት ፈለጉ፡፡ ግን ልባቸው ውስጥ የገነነው ኩራትና እልህ መንገዱን ዘጋባቸው:: እንዲያውም ከነአካቴው የመታረቅ አሳብ ኅሊናቸው ውስጥ ስለገባ መላ ሰውነታቸውን አንገሸገሸው::

«ምን?» ሲሉ ራሳቸውን ጠየቁ፡፡ ከአንገታቸው ቀና አሉ:: ከቤት
ውስጥ የገባ ስለመሰላቸው ተንገሸገሹ:: «ከዚህ ቤት ውስጥ ተመልሶ አይገባም» ሲሉ ለራሳቸው ቃል ገቡ:: ያ መላጣ ጭንቅላታቸው ነገር ስለከበደው ከደረታቸው ላይ ዘንበል ብሎ የወደቁ መሰላቸው:: ቀና ብለው
ከግድግዳ ላይ ከተሰቀለው ስእል ላይ አፈጠጡ:: በአሳብ ተውጠው ሳለ ባስክ የተባለ የቤት አሽከራቸው ይገባል፡፡

«ጌታዬ ማሪየስን ያነጋግሩታል?» ሲል ጠየቃቸው:: ሽማግሌው ቀና ብለው ተመለከቱ:: ከአሳባቸው ባንነው ሲነቁ በጣም
ካመደንገጣቸው የተነሳ ጀርባቻው ቀዘቀዛቸው::
‹‹ምን አልክ?» ማሪየስን ነው ያልከው?
«እኔ እንጃ» ሲል ባስክ እየፈራ መልስ ሰጠ፡፡ «እኔ እንኳን በዓይኔ
አላየሁትም:: ሠራተኛዋ ናት የነገረችኝ፡፡ ውጭ ግን አንድ ወጣት መቆሙ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ምናልባት ማሪየስ ሊሆን ይችላል፡፡»

«ግባ ግባ ግባ በለው» አሉ እየተንተባተቡ፡፡ ልባቸው እንደከበሮ እየመታ ዓይናቸውን በር ላይ ተክለው ቀሩ፡፡ በሩ ተከፈተ:: አንድ ወጣት በሩን ከፍቶ ገባ፡፡ ማሪየስ ነበር፡፡

«ገባ በል እንጂ» በማለት እንዲጋበዝ የሚጠብቅ ይመስል ማሪየስ ከበሩ አጠገብ ቆም አለ፡፡ ጊዜው ጨልሞ ስለነበር የለበሰው አዳፋ ልብስ መቆሸሹ ብዙም አያስታውቅም፡፡ በሀዘን የተጨማለቀው ፊቱ ምንም እንኳን
ፀጥታ ቢሰፍንበትም መከፋቱን በግልጽ ያሳያል::

መሴይ ጊልኖርማንድ በደስታና በአድናቆት ልቡ እንደተነካ ሰው
ለጥቂት ጊዜ ዝም በማለት ሰማይ ሰማዩን አዩ፡፡ ማሪየስ እንደሆነ ለማረጋገጥ ሠርቀው አዩት::

በመጨረሻ! ከአራት ዓመት በኋላ! ደስታ አንደበታቸውን ዘግቶ ሽባ
አደረጋቸው:: ባለፉት አራት ዓመታት እንዲያው ሲያስቡት ቆንጆ፣ ረጋ ያለና ምራቁን የዋጠ የጨዋ ልጅ እንደሚሆን ገምተዋል:: ቢመለስ ልባቸው |
በደስታ ፈክቶና ስሜታቸው በሕሊና ዕረፍት ረክቶ እጆቻቸውን ዘርግተው እንደሚቀበሉት ልቦናቸው ተመኝቶ እንደነበር ልቦናቸው ቢያውቁም ያ ሰዓት ሊመጣ ሳያወቁት የማይሆን ቃል አንደበታቸው ውስጥ ይገባል።

«ለምንድነው የመጣኸው?»

ማሪየስ ሀፍረት እየተሰማው መለሰ፡፡

«ጌቶች...»

መሴይ ጊልኖርማንድ ከመቀመጫቸው ብድግ ብለው ቢያቅፉት ደስ ባላቸው፤ ግን ማሪየስ አስቀይሞአቸዋል፡፡ በአንድ ወቅት ራሳቸውም ቢሆኑ
በወሰዱት እርምጃ ቅር መሰኘታቸው አልቀረም:: ማሪየስ ቢያስቀይማቸውም መታገስ እንደነበረባቸው ያውቃሉ፡፡ ደግና እልኸኛ ሰው የልቡን ደግነት
በእልህና በኃይለ ቃል እየሸፈነ ወስጥ ውስጡን ይሰቃያል:: ምሬቱ ትዝ ብሉአቸው እንዲናገር እድል ሳይሰጡት ጣልቃ ገቡበት::

‹‹ንገረኝ እኮ፣ ለምንድነው የመጣኸው?»

ጉልበቴን ለመሳም ወይም አቅፈህ ጉንጩን በመሳም ይቅርታ ለመጠየቅ ካልሆነ ለምንድነው የመጣኸው ማለታቸው ነበር፡፡ ማሪየስ አያቱን አተኩር
ሲመለከታቸው ሀሞታቸው መፍሰሱን ተገነዘበ፡፡

ሽማግሌው አሁንም በኃይለ ቃል አቋረጡት::

«ይቅርታ ለመጠየቅ ነው የመጣኸው? ተጸጽተህ ነው?»
ወደ እርሳቸው እንዲመለስ በር መክፈታቸው ነበር፡፡ እጁን የሚሰጥና የሚርበተበት መሰላቸው:: እውነትም ማሪየስ በድንጋጤ ሰውነቱ ተርበተበተ፡፡
ዓይኑን ወደ መሬት ሰበረ፡፡ ቢሆንም በድፍረት መልስ ሰጠ፡፡

«የለም ጌቶች::»

«እና ምንድነው የምትፈልገው?» ሲሉ ሽማግሌው ንዴትና ምሬት
እየተናነቃቸው ተናገሩ፡፡ «አሁን ከእኔ የምትፈልገው ምንድነው?»
ማሪየስ ሁለት እጆቹን በኃይል በመጨበጥ አጋጫቸው አንድ
እርምጃ ወደፊት ተራመደ፡፡

እየፈራና እየተንቀጠቀጠ ንግግሩን ቀጠለ፡፡

«አባባ ይዘኑልኝ::»
👍18🥰1
#ምንዱባን


#ክፍል_አርባ_ሁለት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


ወዴት ነው የሚሄዱት?

ያን እለት ከቀኑ ወደ አሥር ሰዓት ገደማ ዣን ቫልዣ ብቸኝነት
ተሰምቶት ብቻውን ተቀምጧል፡፡ ኮዜትን ካየ ስለእርስዋ ብዙ አይጨነቅም፡፡በአንድ ወቅት ገጥሞት የነበረው መጥፎ አጋጣሚ እየተረሳው ሄዷል፡፡
ነገር ግን ከአንድ ወይም ከሁለት ሣምንት በፊት የገጠመው ነገር በጣም እያሳሰበው ሄዶአል:: አንድ ቀን አንድ አውራ ጉዳና ላይ ሲንሸራሸር ቴናድዬን ያየዋል:: የዚህ ክፉ ሰው ከዚያ በነፃ መለቀቅ እጅግ አደገኛ
መሆኑን ተገነዘበ፡፡ ይህም በጣም አስጨነቀው:: ከዚህም በላይ የፓሪስ ከተማ ሰላም ራቀው:: የፖለቲካ ብጥብጥ እያየለ መጣ፡፡ በዚህም የተነሳ ጸጥታ አስከባሪዎችና ፖሊሶች ክትትላቸውን አጠናከሩ፡፡ ዣን ቫልዣ በክትትል መጠናከር ሰበብ የሚያዝ ስለመሰለው በጣም ፈራ:: ዣን ቫልዣ ከሚፈለጉት
ሰዎች አንዱ እንደሆነ ልቡ ያውቃል:: ስለዚህ በአስቸኳይ ከፓሪስ መውጣት ነበረበት:: ከፓሪስ ከተማ ብቻ ሳይሆን ከፈረንሳይ መውጣት እንደሚሻል
አመነ:: ከፈረንሣይ አገር ከሄደ ወደ እንግሊዝ አገር መሄዱን ይመርጣል፡፡ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከፈረንሣይ እንደሚወጡ ለኮዜት የነገራት በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ የቴናድዬ፣ የፖሊስ ክትትል፣ የጉዞውና ፓስፖርት የማውጣቱ
ጉዳይ በጣም አስጨነቀው::

እነዚህ ነገሮች አስጨንቀውት ሳለ ያን እለት በቀን ግቢው ውስጥ
ሲንሸራሸር ከቤቱ ግድግዳ ላይ «ደ ፣ ላ፣ ቤራሪ ጉዳና የቤት ቁጥር 16» የሚል ጽሑፍ በምስማር ተጽፎ ያያል::

ጽሑፉ በቅርቡ ለመጻፉ ያስታውቃል:: ምናልባትም ጽሑፉ ከተጻፈ ቢበዛ አንድ ቀን ውሎ ይደር እንጂ ከዚያ እንደማይበልጥ ይገምታል:: ጽሑፉ ማን ይላል? የሰው አድራሻ ነው? አንድ ሰው ለማመልከት የተጻፈ ይሆን? ለዣን ቫልዣ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ ነው? ምንም ይሁን ምን አንድ
ሰው ግቢውን ደፍሮአል፡፡

ይህን እያሰላሰለ ሰው በአካባቢው ለመኖሩ በጥላው አወቀ፡፡ ሰውዬው ድንገት ይቆማል። ዞር ብዬ ልይ በማለት ሲያስብ የተጠቀለለ ወረቀት
ከእግሩ ሥር ይወድቃል የወረቀታ አወዳደቅ ከላይ ወደታች እንጂ ከሩቅ በጎን የወረወሩት አይመስል
ወረቀቱን አንስቶ ዘረጋው «አስወግድ»የሚል ቃል በትልልቅ ጽሑፍ በእርሳስ ተጽፎ አነበበ::

ዣን ቫልዣ ዞር ዞር አለ፡፡ በዚያ አካባቢ ሰው አልነበረም፡፡ ግን
ግራጫ መልክ ያለው ሸሚዝና የወይን ጠጅ ቀለም ያለው ሰሪ የታጠቀ ልጅ አይሉት ትልቅ ሰው በአጥሩ ዘልሎ ወደ ዋናው ጎዳና ሲወጣ በሩቁ ተመለከተ።

ዣን ቫልዣ ቶሎ ብሎ ወደ ቤቱ ገባ። ከከባድ ጭንቀት ላይ ወደቀ።

ማሪየስ ከመሴይ ጊልኖርማንድ ቤት ከወጣ ቆይቷል:: በታላቅ ተስፋ የገባው ሰውዬ ከቤቱ ሲወጣ ከመጠን በላይ ተስፋ ቆርጦ ነው:: መከራና ስቃይ ያስጨነቀው ሰው እንደሚያደርገው ሁሉ እርሱም
በአሳብ ተውጦ እያቀረቀረ ነው የሚጓዘው:: ጭንቅላቱ ባዶውን ስለቀረ የሚያስበው ነገር አልነበረውም:: ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ከጓደኛው ከኩርፌይራክ ቤት ደረሰ፡፡ ከነልብሱ ራሱን ከአልጋው ላይ ወረወረ፡፡
እስኪነጋ እንቅልፍ አልወሰደውም:: ፀሐይ እንደወጣ እንቅልፍ ወስዶት ኖሮ ክፉኛ አቃዠው::

ቅዠቱ ከእንቅልፉ ቀሰቀሰው:: ዓይኑን ገልጦ ሲያይ ከቤቱ ውስጥ
የነበሩት አራቱም ጓደኞቹ ለመሄድ ተዘጋጅተዋል፡፡

«ከጄኔራል ላማርክ ቀብር ትገኛለህ?» ሲል ጓደኛው ኩርፌይራክ ጠየቀው::

በቻይና ቋንቋ የሚያናግረው መሰለው:: ማሪየስ ጓደኞቹ ከቤት ከወጡ ጥቂት ቆይቶ ነው የወጣው፡፡ ዣቬር ከሰጠው ሽጉጥ አንዱን ኪሱ ውስጥ
አደረገ፡፡ ሽጉጡ ጥይት እንደጕረሰ ነው፡፡ ምን አስቦ ሽጉጡን እንደያዘ
ለማወቅ ያስቸግራል፡፡ የት እንደሚሄድ ሳያውቅ ቀኑን ሙሉ ከወዲያ ወዲህ ሲንቀዋለል
ዋለ፡፡ አንዳንዴ ዝናብ ቢያካፋም እርሱ አልተሰማውም:: ጦሙን እንዳያድር ለእራቱ የሚሆን ዳቦ ገዝቶ ኪሱ ውስጥ አደረገው፡፡ ግን ኪሱ ውስጥ እንዳለ ረስቶት ሳይበላው አደረ፡፡ ጊዜው ቶሎ አልመሽ ስላለው በጣም ተቁነጠነጠ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ከኮዜት ጋር ቀጠሮ ስለነበረው ያቺን ሰዓት በጉጉት ይጠብቃል፡፡ ከተማው ውስጥ ከወዲያ ወዲህ ሲዞር በአሳብ ጭልጥ ይላል፡፡
ከአሳቡ ሲነቃ የተኩስ ድምፅ ስማ፡፡ «ውጊያ ቀጥለዋል ማለት ነው?» ሲል ራሱን ጠየቀ መሽቶ ሦስት ሰዓት ሲቃረብ ወደ ቀጠሮው ቦታ ሄደ፡፡ ኮዜትን ሳያይ
ሁለት ቀን ስላለፈ በጣም ናፍቆአታል:: ሰዓቱ በመድረሱ በጣም ደስ አለው፡፡ የምንጓጓለት ነገር ልብን ያስጨንቃል እንጂ ቶሎ ስለማይደርስ ደቂቃው እንደ ዓመት ይረዝማል፡፡

ማሪየስ በለመደው ቀዳዳ ከግቢው ውስጥ ገባ፡፡ ኮዜት በሌላ ጊዜ ከምትጠብቀው ሥፍራ የለችም፡፡ ምናልባት ከቤቱ አካባቢ ትጠብቀኝ ይሆናል ብሎ ወደዚያ አመራ:: ከዚያም አልነበረችም:: አንገቱን ቀና አድርጎ ሲያይ
የኮዜት መኝታ ቤት መስኮት ተዘግቷል፡፡ አካባቢው በጣም ጭር ብሏል፡፡ በፍቅር ያበደው፣ የነደደው፣ የተቃጠለውና የሰከረው ወጣት ከፍቅረኛው
መኝታ ቤት መስኮት ላይ አፈጠጠ፡፡ ከአሁን አሁን ተከፍቶ «ኮዜትዬ ብቅ ትላለች» ሲል አወጣ፤ አወረደ፡፡ ግን መስኮቱ እንደተዘጋ ቀረ፡፡ በጨለማ
ለማየት እስከቻለ ድረስ በዓይኑ አካባቢውን ቃኘ:: ማንም የለም:: ድንገት አባትዋ ብቅ ያለ እንደሆነ ‹‹ምን ትፈልጋለህ?» ብሎ ያፈጥብኛል በማለት ሳይፈራ ቤቱን ዞረው:: በመጨረሻ አላስችል ብሎት «ኮዜት» እያለ ደጋግሞ
ተጣራ:: መልስ አላገኘም:: አሁንም ደገመና ተጣራ:: መልስ የለም:: ቤቱ ውስጥ ሰው እንደሌለ አወቀ፡፡

ቤቱን ተስፋ በቆረጠ ዓይን አየው፡፡ ከመቃብር ቤት ይበልጥ ጭር
ብሎአል፡፡ ብዙ የደስታ ምሽቶችን ወዳሳለፈበት የድንጋይ መቀመጫ ሄደ:: ልቡ እየከበደው ከመቀመጫው ላይ ቁጭ አለ፡፡ ለኮዜት ያለውን ፍቅር
እያሰላሰለ ኮዜት ከሄደች ከመሞት በስተቀር ሌላ የተሻለ ምርጫ እንደሌለው አመነ፡፡

ከአጥር ውጭ ድንገት ድምፅ ሰማ
«መሴይ ማሪየስ!»
ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡
‹‹ማነህ?» ሲል ተጣራ
«መሴይ ማሪየስ፣ አንተ ነህ?››
«አዎን፡፡»
«መሴይ ማሪየስ» አለ ድምፁ፣ «ጓደኞችህ ባሪኬድ ከተባለ ሥፍራ ይጠብቁሃል፡፡»

ድምፁ እንግዳ የሆነ ድምፅ አልነበረም፡፡ የኢፓኒንን ድምፅ ይመስላል፡፡ ቶሎ ብሎ ወደ አጥሩ ሄደና በቀዳዳ አየ:: አንድ ወጣት ሮጦ ሲሄድ ተመለከተ፡፡ ጨለማ ስለነበር ሊለየው አልቻለም::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመሴይ ማብዩፍ ኑሮ እያቆለቆለ ሄደ እንጂ አልተሻሻለም:: ባለፈው
ዓመት የሠራተኛቸውን ደመወዝ መክፈል አቅቶአቸው ነበር፡፡ በዚህ ዓመት ደግሞ የቤት ኪራይ መክፈል አቃታቸው፡፡ ቀስ በቀስ የቤቱን እቃ ሽጠው ጨረሱ፡፡ የጻፉትንም መጽሐፍ ገዢ ስላጣ እንደ አሮጌ መጽሐፍ ተቆጥሮ
በቅናሽ ሸጡት፡፡ ቀደም ሲል አልፎ አልፎ ሥጋ ይበሉ ነበር፡፡ ዛሬ ግን
ጠፍቶ የሚበሉት ደረቅ ዳቦና የተቀቀለ ድንች ሆነ፡፡ በመጨረሻ
የሚሽጡት ንብረት ሁሉ አልቆ የቀረው በደህና ዘመን የሰበሰብዋቸውና በጣም የሚወዷቸው መጻሕፍት ብቻ ነበሩ፡፡ መሴይ ማብዩፍ የሚያነዱት እንጨት ስላልነበራቸው ገና ጀምበር ስትጠልቅ ይተኛሉ፡፡ ከጊዜ በኋላማ በጣም እየደኸዩ ስለሄዱ ጎረቤት ሀሉ ይሸሻቸው ጀመር:: ሰዎች እንደሚሸሹዋቸው ስለገባቸው እርሳቸውም ይሸሿቸዋል:: በልጅ ስቃይ
👍18👎1
#ምንዱባን


#ክፍል_አርባ_ሦስት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


....ከየቤቱ መስኮት እየተንጠላጠለ ይሳሳቃሉ፣ ወጣቶች የነገሩን ምንነት ሳያጤኑ ጥልቅ ይላሉ፡፡ «ተነስ ተንቀሳቀስ» እያሉ ጩኸት ያስተጋባሉ፡ ሩብ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ፓሪስ ከተማ ላይ የሆነውን ላውጋችሁ።
በየአውራ ጎዳናው፣ በየገበያ ቦታ፣ በየመንደሩ ትንፋሽ ያጠራቸው ሰዎች፣ሠራተኞችና ተማሪዎች፣ «ተነስ፣ ተንቀሳቀስ፣ ክንድህን አንሳ» እያለ በአንድ ቋንቋ ይጮሃሉ፡፡ የመንገድ መብራት፣ መስተዋት፣ የመጓጓዣ ጋሪዎችንና
ሠረገላዎችን ይበረብራሉ፣ ድንጋይ ይወረውራሉ፣ ቤት ውስጥ እየገቡ የቤት እቃ ያንኮታከታሉ፣ ሰሌዳ ይዘው በየመንገዱ ይዞራሉ፡፡ ማን
አስተባበራቸው? ማን አነሳሳቸው? ማን ያውቃል!

የአድመኞቹ ወላፈን እንደ ጭድ እሳት ተቀጣጠለ፡፡ በሦስት ሰዓት
ጊዜ ውስጥ አንዳንድ ቁልፍ የሆኑትን ስፍራዎች ከቁጥጥራቸው ሥር አደረጉ፡፡ ከሰዓት በኋላ ወደ አሥራ አንድ ሰዓት ገደማ የፓሪስ ከተማን |
ሦስት አራተኛ የሚሆነውን ክፍል ያዘ:: ይህም ከድንጋይ ውርወራ ወደ ጦር መሣሪያ መጨበጥ አሸጋገራቸው:: አድመኞቹ የመሣሪያ መጋዘን ስለማረኩ የጦር መሣሪያ ከዚያ ዘረፉ:: በአሥራ ሁለት ሰዓት ቅልጥ ያለ ዝርፊያ
ተጀመረ።

በአንድ ፊት አድመኞቹ በሌላ አቅጣጫ የመንግሥት ወታደሮች
ሥፍራ ሥፍራቸውን ያዙ፡፡ ተኩሰ ተጧጧፈ፡፡ ለወሬ ሞትኩ ያለ፣
ወደፊት በሚሆነው እጠቀማለሁ ብሎ ያለመ፤ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ
ጭምር ሁኔታውን ለማየት እየተሽሎከሎከ ወደ ጦር ሜዳው አመሩ፡፡እንደ እነቪክተር ህዩጎ ያለ አልጠግብ ባይ ከእሳተ ገሞራ ውስጥ ገብቶ መውጫ በማጣት ተቅበዘበዘ፡፡ ከጦርነቱ፡ መካከል በመግባታቸው ጥግ ይዘው
አውጣን» ከማለት በስተቀር ሌላ ምርጫ አልነበራቸውም፡፡ ቅልጥ ያለ ጥይት እሩምታ ግማሽ ሰዓት ወሰደ:: የጦሩ ክፍል በያለበት መሯሯጥ፣መንቀሳቀስ ሆነ፡፡ ከጦር ሜዳው በብዛት የጦር ኃይል ጎረፈ:: ውጊያው ፓሪስ ከተማ ውስጥ ነበር፡፡

የጦር ኃይሉ እንዳላ መንቀሳቀሱን የተመለከተ ሕዝብ ወደኋላ መሸሽ
ጀመረ፡፡ በየአቅጣጫው ተንሰራፍቶ የነበረው ሰልፈኛ እንደመበተን አለ::ትርምስምሱ ወጣ:: አንዳንዱማ ፈሪ በሩጫ እግሬ አውጪኝ አለ፡፡

ዝናብ በሀይል ይጥላል:: ከዚህ ትርምስ ውስጥ አንድ ልጅ ውራጅ
እቃ ከሚሽጥበት ሱቅ አካባቢ ብቅ አለ፡፡ አንዲት አሮጊት ሽጉጥ ይዘው መቀመጣቸውን ስለተመለከተ ልጁ ወደ ሴትዮዋ ሮጠ
«እማማ፣ አንድ ጊዜ ሽጉጥዎን ያውሱኛል?» ሲል ጠየቃቸው:::

ሽጉጡን ለማግኘት ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ ወዲያው መሣሪያውን ከእጁ አስገብቶ ወደ መጣበት ተመልሶ ሮጠ፡፡

ልጁ ከአሁን ቀደም ያነሳነው ሚስተር ቴናድዩ ከእስር ቤት እንዲያመልጥ የረዳውና ጋቭሮች የሚባለው ነበር፡፡ መንገድ ከጀመረ በኋላ ነበር ሽጉጡ
ጥይት እንደሌለው የተገነዘበው:: ቢሆንም መንገዱን ቀጠለ፡፡

እነ ኩርፌይራክና ኤንጆልሪስ ከቁጥጥራቸው ስር ካደረጉት ሰፈር ደረሰ:: ከሌላ አቅጣጫ ሌሎች በድኖች የሚመሩት የአድመኞች ቡድን መጥቶ ሲደባለቅ ተመለከተ፡፡ ጋቭሮችም አብሮ ከሰልፈኞቹ ጋር ተደባለቀ::

««ወዴት ነው የምንሄደው?» ሲል ጠየቀ::

‹‹ተከተለን» ሲል ኩርፌይራክ መለሰለት::

የረብሻው ቀንደኛ መሪዎች ከአፍ እስከ ገደፍ ታጥቀዋል:: ከኋላ
የተከተላቸው ጀሌ አንዳንዱ የጦር መሣሪያ ሲይዝ አንዳንዱ ዱላ ብቻ ነው የያዘውን ፡፡ ከሠራዊቱ መካከል አንድ በእድሜ የገፉ ሽማግሌዎም ነበሩ::
ሽማግሌው ምንም ዓይነት የጦር መሣሪያ አልያዘም:: ግን በጣም እየተቻኮለ ነበር የሚሄዱት፡፡ ፊታቸውን ሲያዩት ከአሳብ ባህር የሰመጠ ይመስላል፡፡

ጋቭሮች ከሩቁ አያቸው::
«ያ ማነው?» ሲል ኩርፌይራክን ጠየቀው::
«አንድ ሽማግሌ ነዋ!» ሲል መለሰለት::
ከአሁን ቀደም ያየናቸው መሴይ ማብዩፍ ነበሩ::
ሽማግሌው ፊት ለፊት ከሚሄደው መስመር ሊደርሱ ምንም ያህል
አልቀራቸውም::

«ምን ዓይነት ቆራጥ ሽማግሌ ናቸው!» ሲሉ ተማሪዎቹ አጉረመረሙ። ማን እንደሆኑ ለማወቅ ተማሪዎቹ ጊዜ አልወሰደባቸውም ገዳም ውስጥ
ይኖሩ እንደነበር የሚያውቋቸው ሰዎች በሹክሹክታ ስማቸውን አስተጋቡ ሠራዊቱ አንዱን ጎዳና ጨርሶ ወደ ሌላው ተሸጋገረ፡፡ ጋቭሮችም መጓዙን ቀጠለ።

ብዙ በተጓዘ ቁጥር የሠራዊቱ ቁጥር እየጨመረ ሄደ፡፡ አንድ ግዙፍ ሰውነት ያለው ረጅም ሰው መጥቶ ተደባለቀ፡፡ ሽበት ጣል ጣል አድርጎበታል ፡መሪዎቹ ይህ ሰው ማን እንደሆነ አላወቁትም፡፡ ግን ወደ እነርሱ ለመጠጋት
በጣም ይፈልጋል፡፡ ጋቭሮች በሚያዜመው መዝሙር ተመስጦ ስለነበረ ሰውዬውን ልብ አላለውም፡፡ ልጁ መዝሙር ሲሰለቸው ያፏጫል፤ አንዳንዴ
ያንን ጥይት የሌለውን ሽጉጡን ያሻሻል፡፡

ሰልፈኛው መንገዱን ቀጥሎ እንደአጋጣሚ ሆኖ በኩርፌይራክ መኖሪያ ቤት ደጃፍ ያልፋል፡፡

«ጥሩ አጋጣሚ ነው» ይላል ኩርፌይራክ፡፡ «ቆቤ ጠፍቷል፤ ጠዋት ደግሞ ቦርሳዬን ረስቼ ነው የመጣሁት፡፡»

ከሰልፈኛው ተገንጥሎ ደረጃዎቹን በእጥፍ እየዘለለ ወደ ቤቱ ገባ
አንድ አሮጌ ቆብና የኪስ ቦርሳውን አነሳ፡፡ ከቆሻሻ ልብስ ውስጥ
የነበረ ሌላ አነስተኛ የእጅ ቦርሳም ወሰደ:: ደረጃውን በችኮላ ሲወርድ በጨለማ ውስጥ አንድ ሰው «ሊያነጋግርህ የሚፈልግ ሰው አለ» ሲል ነገረው፡፡

በዚህ ጊዜ አንድ የተቦጫጨቀ የሴት ቀሚስ ከላይ ያጠለቀ ወንድ
ከወደ ውስጥ ብቅ ብሎ አነጋገረው:: ድምፁ የሴት እንጂ የወንድ አይመስልም:: በጣም ቀጭን ነው::

«ማሪየስን አይተውታል?»
«የለም፤ ከቤት አልመጣም::»
«ማታ ይመጣ ይሆን?»
«እኔ እንጃ፡፡ እኔ ግን ዛሬ ወደቤት አልመለስም::»
አለባበሱና ድምፁ ሴት ያስመስለው ወጣት ኩርፌይራክን አፍጥጦ አየው
ለምን አይመለሱም?» ሲል በድፍረት ጠየቀው::
«ምክንያቱም...»
«እንግዲያው አንተ ወዴት ነው የምትሄደው?» በማለት ጣልቃ ገባ፡፡
«ምን ያደርግልሃል?»
«ቦርሳህን ልያዝልህ?»
«ወደ ጦርነቱ ቦታ ነው የምሄደው?»
«አብሬህ ብሄድ ትፈቅድልኛለህ?»
«ከፈለግህ፣ እኔ ምን ቸገረኝ» ሲል ኩርፌይራክ መለሰለት:: «መንገዱ
ነጻ፣ ጎዳናው የጋራ!»

ኩርፌይራክ ይህን እንደተናገረ ከጓደኞቹ ለመድረስ በሩጫ ወጣ፡፡
እንደደረሰም የእጅ ቦርሳውን እንዲይዝለት ለአንዱ ጓደኛው ሰጠው:: ከሩብ ሰዓት ጉዞ በኋላ መለስ ቢል ወጣቱ እንደተከተለው ተገነዘበ፡፡
ለአመዕ የተነሳሳ ሰልፈኛ ብዙውን ጊዜ የሚመራው በነፋስ ስለሆነ
አንዳንዴ ወደፈለገበት ሳይሆን ወደ አልፈለገበት አቅጣጫ ነው የሚጓዘው::ይህም በመሆኑ ይህ ሰልፈኛ ሴንትሜሪ ከተባለ ሥፍራ ለመሄድ ፈልጎ ሳይታወቀው ይህን ቦታ አልፎ ከሴንት ዴኒስ ይደርሳል፡፡

ከሰላሳ ዓመታት በፊት አንድ መንገደኛ ሴንት ዴኒስ ከተባለ ሥፍራ ቢያልፍ መንገዱ እየጠበበ ሄዶ በመጨረሻ እንደ አቁማዳ ጫፍ መደፈኑን ይገነዘብ ነበር፡፡ አካባቢውን አጥርቶ የማያውቅ ከሆነማ በግራና በቀኝ በኩል
የጨለማ መንገድ መኖሩን ስለማይረዳ መድረሻ ያጣል:: ውስጥ አዋቂ ግን በእነዚህ ጠባብ የጨለማ መንገዶች ተሹለክልኮ ሊያልፍ ይችላል፡፡ በስተቀኝ
በኩል ያለውን የቀኝ መንገድ ይዞ ሲጓዝ ከአንድ መሸታና ምግብ ቤት
👍14😁21