አትሮኖስ
286K subscribers
117 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ባል_አስይዞ_ቁማር


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ከአስር ጊዜ በላይ ደውሎላት ነበር ቀልቧ ቃል ላይ ተለጥፎ ስለነበረ አላነሳችለትም ..እና አሁን ለዛ ነው እየደወለችለት ያለችው፡፡
አነሳላት‹‹‹ምነው አንቺ ይሄን ሁሉ ስደውል?››
‹‹አላየሁትም ነበር..ስልኬን መኝታ ቤት ጥዬ ሳሎን ነበርኩ….››
‹‹ምን አስዋሸሽ ማሚ ጋር ደውዬ መኝታ ቤትሽ እንደሆንሽ ነግራኛለች፡፡››
‹‹አይ አንተ ሰው..ስለእኔ ዘበኞችንም ቤት ሰራተኞችንም እናቴንም መጠየቅ አይደክምህም?››
‹‹እንደዛ እንዳላደርግ ከፈለግሽ ስፈልግሽ ተገኚያ››
‹‹እሺ……››
‹‹በቃ ለንቦጭሽን አትጣይ..ንፍቅ ብለሺኝ እኮ ነው፡፡››
‹‹እንዴ ጥዋት እኮ አብረን ነበርን››አለችው…ስልክ ስላላነሳችለት ብቻ እንዲህ መንጨርጨሩ አስገርሞታል…ምን ስታደርግና ምን ስታስብ የእሱን ስልክ እንዳላነሳች እውነቱን ቢያውቅማ ጨርቁን እንደሚጥል እርግጠኛ ነች፡፡
‹‹እኔ እኮ እንደአንቺ ደንዳና ልብ የለኝም…ለሰከንድም ባትለይኝ ደስ ይለኛል… በጣም እኮ ነው የማፈቅርሽ››
‹‹እኔም አፈቅርሀለሁ››ለምን እንደሆን ባታውቅም ይሄን ቃል ምን አልባት ከሺ ጊዜ በላይ ለእሱ ተጠቅማለች፡፡ከልቧ ደስ ብሏትና የእውነቷን ነበር ቃሉን ከአንደበቷ የምታወጣው….፡፡ዛሬ ግን ከበዳት ….እየሻከረት ነው የተናገረችው፡፡
‹‹…ፍቅርን እያቆሸሽኩት ይሆን እንዴ?…..ቺት እያደረኩብት ይሆን እንዴ…?ምን ያደረኩት ነገር አለ….? ተጀናጀንኩ.. ተሳሳምኩ..ምን ፈፀምኩ….?›› ብላ እራሷን ለማፅናናት ብትሞክርም ልቧ ግን ለሆነ ሌላ ሰው መቅለጥ መጀመሯን መዋሸት አልቻለችም…፡፡
ከእዚህ ጉድ ለመውጣት ቶሎ ይሄን ሰው ማግባት እንዳለባት ቅፅበታዊ ውሳኔ ወሰነች ‹‹…ልዩ ሳትወራጂ ይሄን ነገር አድርጊው››እራሷን መከረች…እና ወዲያውኑ ወደተግባር ተሸጋገረች፡፡
‹‹ስማ…›
‹‹ወዬ የእኔ ፍቅር…››
‹‹ደግሞ ሸጉጠሀኝ ውለህ ሸጉጠኸኝ ማደር ከፈለክ ጠቅልሎ ማግባት ነዋ…››
‹‹ምን?››
‹‹አዎ ሰምተሀል…››
‹‹መለመን ከጀመሪኩ እኮ አመት ሊያልፈኝ ነው…አንቺ ነሽ ሰበብ እየፈጠርሽ ስታዘገይው የነበረ፡፡››
‹‹ለትምህርቴ ብዬ ነዋ..አሁን ደግሞ ለምርቃት ሶስት ወር ነው የቀረኝ፡፡››
‹‹አንቺ የሆነ ሀሳብ መጣልኝ..፡፡››
‹‹ምንድነው ?ልስማው…››
‹‹ለምን አንድ ቀን አናረገውም…?ማለቴ አንድ ቀን እንኳን ባይሆን ተከታታይ ቀን ይሁን..፡፡ ››
‹‹አይ አንደዛ አይሆንም.. ሁለቱንም ለየብቻ ነው ማጣጣም የምፈልገው… ግን ምርቃቴንና ቀለበቴን በአንድ ቀን ማድረግ እንችላለን፡፡
‹‹አሪፍ ነው…ግን ቀለበት አስሮ ብቻ አንድ ቤት መግባት ይቻላል እንዴ?››
‹‹አዝናለሁ እንደዛ አይቻልም፡፡››
‹‹ወይ ታዲያ ምንድነው ትርፌ?››
‹‹በወሩ ደግሞ ሰርግ ይሆናላ…››
‹‹ምሽቱን ሙሉ ስታበሳጪኝ ያመሸሽው እንዲህ አይነት የሚያስፈነጥዝ ዜና ልታሰሚኝ ነው…..በስመአብ ….በጣም ነው የማፈቅርሽ..››
‹‹እኔም አፈቅርሀለሁ..በል ደህና እደር..፡፡››
‹‹ደህና እደሪ …ደግሞ ነገ አላልኩም እንዳትይ….ንግግራችንን ቀድቼዋለሁ››
‹‹የሰው ድምፅ ያለፍቃድ መቅዳት ወንጀል እኮ ነው፡፡››
‹‹የሰው ድምፅ አልቀዳሁም ፤የሚስቴን ነው…የሚስቴ ድምፅ ማለት ደግሞ የራሴ ነው፡፡››
‹‹በል ይሁንልህ… ቻው፡፡›
‹‹ቻው››
ስልኩን ዘጋችና በድንጋጤ ጭንቅላቷን ያዘች‹‹…ልዩ ምድነው የሰራሽው…? አሁን ከአራት ወር በኋላ ሚስትና የቤት አስተዳዳሪ ለመሆን ዝግጁ ነሽ……?ልጅ ወልደሽስ ማሳደግ ትችያለሽ…?.›› እራሷን አምርራ ብትወቅስም አንዴ ከአንደበቷ ያወጣችውን ቃላት ሰብስባ መልሳ ልትወጣቸው አልችለችም፡፡
‹‹….እስኪ ገና ለገና ፍቅር ከሌላ ሰው እንዳይዘኝ ተብሎ ያልሆነ መክለፍለፍ ውስጥ ይገባል…?››እራሷን አምርራ ወቀሰች፡፡
ከልጁ ፍቅር እንዳይዛት ቀላል ዘዴዎች ነበሩላት..ለምሳሌ እቤቱ አለመሄድ… መኝታ ቤቱ የቀበረችውን መከታተያ እንዳይሰራ ማበላሸት…ስልኩን ከስልኳ ላይ ማጥፋት…በቃ ካልደወለችለት እንደማይደውልላት እርግጠኛ ነች..እቤቱ ካልሄደች እሱ እቤቷ አይመጣም…ጭራሽ አድራሻውንም አያውቀውም…ታዲያ ከእሱ ፍቅር እንዳይዛት ልትወስድ ያሰበችው እርምጃ ምን የሚሉት ነው .. በቅፅበታዊ ውሳኔዋ እራሷን ጠላች …
ግን ፍቅር እንዳይዘኝ እንዳይዘኝ የምትለው እስከአሁን አልያዘትም ማለት ነው…..?ፍቅር ያዘት ተብሎ በእርግጠኝነት የሚወራው የፍቅሩ መጠን ምን ያህል ሲሆን ነው? መለኪያውስ ምንድነው?ይህንን እሷስ ታውቀዋለች?
እና ደግሞ አሁን በዚህ ሰአት ቃል ከተኛበት ተነስቶ ከራሷ ኮሚፒተር እሱ ቤት በደበቀችውን ካሜራ ሀክ አድርጎ እሱን መኝታ ቤቱ የሚያደርገውን እያየች እያሳየች የነበረውን ስሜት መድሀኔ ጋር ደውላ ስለመጋባት የተነጋገረችውን ስልኩን ከዘጋች በኃላ በተናገረችው ተፀፅታ ስትቆጭ ጠቅላላ ቆይታዋን ሰምቶ ተገርሞ መልሶ እንደተኛ ብታውቅ ምን ትል ይሆን?

ይቀጥላል
👍95🥰306😁6😱2🔥1
#ተአምራተ_ኬድሮን


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

የድባአለ አባትንና አዲሱ ሚስቱ ግን ከለሌቱ ስምንት ሰዓት  አልጋቸውን ለቀው ወርደው የቤቱ ወለል ላይ ጎን ለጎን በላብ እንደተዘፈቁ ቁጭ ብለው በመነጋገር በጥዋት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንደሚለያዩና ሰውዬውም ወደሚስቱ መመለስ እንዳለበት ወስነው ነበር እዚህ ድምዳሜ ላይ የደረሱት… ኬድሮን ማታ ባስፈራራቻቸው ላይ ተመስርተው ብቻ ሳይሆን እሷ እንዳለችው ሁለቱም ባዩት ህልም የተነሳ ነው..የሚገርመው ደግሞ ሁለቱም ያዩት ህልም በጣም አስፈሪ እና ሰቅጣጭ  መሆኑ ብቻ ሳይሆን ምንም ልዩነት የሌለው ከመጀመሪያው እሰከመዝጊያው ተመሳሳይና አንድ አይነት በመሆኑ ነው፡፡

ጥዋት ሁለት ሰዓት ሳይሞላ ይዞ የወጣውን ሻንጣ እንዳንጠለጠለ ወደቀድሞ ቤቱ ተመልሶ ሚስቱ እግር ስር ተደፋ፤እሷም ሆነች ልጆቹ በእልልታ ተቀበሉት….ኬድሮምም ወደተለመደ እረኝነቷ  ከመሄዷ  በፊት ከድባለ  እናት  እቃ የገዙት የጎረቤት ሴቶች ጋር በየቤታቸው  በመዞር.. ሰውየው ስለተመለሰ የገዛችሁትን እቃ በስጦታ መልክ መልሳችሁ እንደምታስደስቷት አምናለሁ›› በማለት በአዋጅ መልክ ለሁሉም በመናገር ነበር ወደሰራዋ የተሰማራችው...እንዳላቸውም ማታ ስትመለስ ሁለት ጅግራ እንደተሸከመች እነከድር  ቤት ስትደርስ እቤቱ ትናንት ከነበረው በተቃራኒው በደስታ ደምቆና በሳቅ ፍክቶ ነበር የጠበቃት..
ደጃፉን አልፋ‹‹ ቤቶች›› የሚል ድምፅ እንዳሰማች ነበር.ከድር ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ በመብር የተጠመጠመባት እናትየውም በደስታና በስስት አቅፋ እየወዘወዘቻት ሞጨሞጨቻት ..ከዛ ቤቱ ሰላም መመለሱን አረጋግጣ…ከቤቱ የተሸጡ እቃ አንድም ሳይቀር መመለሱን አይታ ጀግራውን ለደስታቸው ማድመቂያ ይሆን ዘንድ አስረክባ ወደቤቷ ስትመለስ  ድባለ  ከኃላዋ ተከትሎ አስቆማት

‹‹እሺ አሁን ደግሞ ምን ፈለክ?››

‹‹አንድ ነገር ልነግርሽ ነው››

‹‹እኮ ቶሎ ንገረኝና ወደቤቴ ልግባበት››

‹‹ሳድግ  አገባሻለሁ፡፡››

‹‹ማግባት ማለት? አንደዚህ እንደአባትህና እናትህ?››

‹‹አዎ ምነው?››

‹‹ቲሽ ምነው ትላለህ እንዴ…?››

‹‹ልጇች አስታቅፈኸኝ ..ሌላ ሴት ልታገባ››

‹‹አረ እንደዛ አላደርግም አንቺን እኮ በጠም ፈራሻለሁ››

‹‹በል እርሳው .እኔ ባል መቼም አለገባም››

‹‹ቻው በቃ ..እኔም ሚስት አላገባም››ብሎ አንገቱን በመድፋት ፊቱን አዙሮ ወደቤቴ ተመለሰ…

እሷም እያጉረመረመች ወደቤቱ እርምጃዋን ቀጠለች፡፡በዛ ዕድሜዋ እኚንና መስል እንደታአምር ሚነገሩ ድርጊቶችን መከወን የዘወትር ተግባሯ ነው፡፡እርግጥ ያው ተደጋግሞ እንደተነገረው እድሜዋና የሰውነቷ እድገት ተመጣጣኝ አልነበረም..ከእኩዬቾ በጣም የገዘፈችና የጠነከረች…ገና በአስር አመቷ ከሩቅ ታይተው ሚለዩ ጡቶች ያጎጠጎጠች..መቀመጫዋ ወደኃላ መግፋትና መንቀጥቀጥ የጀመረ በትክክል ሰትወለድ በአካባቢወ ኖሮ የሚያውቅ ሰው ካልሆነ በስተቀር ስለ ዕድሜዋ የሰማ ማንኛውም ሰው የማያመምነው አይነት ነው፡፡አሁን አብሯት ሲያወራ የነበረው ጓደኛዋ ዱባለ እንኳን  ድፍን ሁለት አመት ቢበልጣትም በማያጠራጥር  ሁኔታ ታላቁ የምትመስለው እሷ ነች፡
///

11 አመት ሲሞላት ወደ ትምህርት ቤት ተመለሰች፡፡ካርዷን ይዛ ሄደችና 3ተኛ ክፍል ተመዘገበች፤በሳምንት ሁለት ወይም ሶስት ቀን ብቻ ነው ክፍል ውስጥ ተገኝታ መምህራኑ የሚያስተምሩትን ትምህር የምትከታተለው፡፡ግን ደግሞ ያ የሚያመጣው ምንም አይነት ለውጥ የለውም…አንዱን የመማሪያ መፅሀፍ አንዴ ካነበች በኃላ  ፍፅም አትረሳውም… ሳምንቱን ሙሉ ክፍል ውስጥ መቀመጥ ለእሷ ብክነት ነው፡፡

13 ዓመት ላይ ሆና ነው፡፡የምትወዳት እናቷ ትታመምና ለተሻለ ህክምና ወደጎባ ሆስፒታል ሪፈር ተባላችና  እዛ ለአንድ ወር እንድትተኛ ይደረጋል፡በወቅቱ በታመመች ጊዜ ወደእዛ ይዟት የሄደው ታላቅ ወንድሟ ወይም የኬድሮን አጎት ነበር፡፡ከሳምንት ቆይታ በኃላ ግን ኬድሮን እናቴን ሄጄ ካለየሁ ሞቼ እገኛለሁ ትላለች…አረ ተይ እሷ እራሷ ሰሞኑን ስለሚሻላት ትመጣለች ብትባል ካላካችሁኝ ጠፍቼ ሄደለሁ በማለቷ ያው ካላቸው ልምድ ምንም ነገር አምርራ ከተናገረች እንደምታደረገው ስለሚያውቁ መሰፈሪያ ገንዘብ ሰጥተው ወደጎባ ከሚሄድ የጎረቤት ሰው ጋር በአደራ ሆስፒታል ድረስ ወስዶ ከእናቷ እና ከአጎቷ ጋር እንዲያገናኛት ይልኳታል፡፡በሰላም ትደርሳለች፡፡
አደራ የተቀበለውም ሰው እጇን ይዞ ሆስፒታል ድረስ በመውስድ ከእናቷና ከአጎቷ ጋር ያገናኛትና ወደራሱ ጉዳይ ይሄዳል…እዛ ሆስፒታል እናቷን እየተንከባከበችና አጎቷን እየገዘች አራት ቀን ያህል ከቆየች  በኃላ ግን ምንም እንኳን እናትዬው እየተሻላት ቢሆንም የጀመረችውን ህክምና እስክታጠናቅ ለተጨማሪ 10 ቀን መቆት አለባት ስለተባለ ከትምህርቷ ብዙ እንዳትስተጓጎል ይዟት የመጣው ሰውዬ ይዟት እንዲመለስ ይስማሙና በለሊት ከሰውዬው ጋር በአይሱዙ የጭነት መኪና አሰፍረው ይልኳታል፡፡

ደሎ መና ከጎባ ከተማ 110 ኪ.ሜትር ያህል የሚርቅ ቢሆንም መንገዱ ግን እጅግ በጣም አስቸጋሪ መልካአምድር ያለበት በተለየ ከጎባ አንስቶ እስከግማሽ ርቀት . ሪራ እስከተባለችው የገጠር ከተማ ድረስ ያለው መሬት በኢትዬጵያ ሁለተኛው ከፍተኛ ቦታ ባቱ ተራራ ሚገኝበት ከ4420 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ከፍታ ያለውና እጅግ ሚያንዘፈዝፍ ብርድ ያለበት በዛ ላይ እጅግ ጠመዝመዛ ገደልና ቁልቁለት እናም ደግሞ እንደእባብ ተጠማዞ በማያልቅ መንገድ  የተነጠፈበት ነው፡፡በአስፈሪው ወጣ ገባ መንገድ 50 ኪሎ ሜትር ያህል ከተጓዙ በኃላ ቀሪው ደግሞ ዝቅ እያለና በተነፃፃሪ የተሻለ የሚባል መንገድ  ሆኖ ግን ጥቅጥቅ ባለ ጫካና በአስፈሪ አውሬዎች የታጨቀ መንገድ በማቋረጥ ነው ደሎ ከተማ የሚገባው፡
ኬደሮን ከደሎ ወጥታ ሌላ ከተማ ስታይ ይሄ መጀመሪያ ገጠመኝ ነበር፡፡ትራንስፖርቱ አይሱዙ ጭነት መሆኑ በአካባበው የተመደ ትራንስፖርት ስለሆነ ነው፤ከመንገዱ አስቸጋሪነት የተነሳ ዋናው የትንስፖርት አይነቶች አይሱዙ ጭነት፤ኤፍ.ኤስ. አር ጭነት ፤ፒካፕ መኪና ሲሆን አልፎ አልፎ አይሱዙ ቅጥቅጥ ይገኛል...ከዛ ውጭ የተለመደው አይነት የህዝብ ማመላለሻ አውቶቢስና ሎንቺን፤ብሎም ሚኒባስ ያንን መንገድ አያስቡትም፡፡አይደለም እነሱ እራሳቸው የአይሱዙ ሹፌሮቹ ቢሆንም እያንዳንዱን የመንገዷን ወጣ ገባና  ኩርባ፤ ዝቅታና ከፍታ አብጠርጥረው የሚያውቁ ሰለሆነ ነው የሚወጡት.እዛ መንገድ ላይ ለመሾፈር ቅድሚያ በረደትነት አራትና አምስት አመት ቀጥቅጦ ማገልገልገልና የመኪናውን ብቻ ሳይሆን የመንገዱንም ፀባይ አብጠርጥሮ  ማወቅ የሚጠይቅ የጀግና ስራ ነው፡፡

ይቀጥላል
👍14611👏6😁5
#ትንግርት


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ከትንግርት ጋር ከሀያ ቀናት በኃላ ነው በአካል የተገናኙት፡፡በጣም ናፍቃዋለች፡፡ ምግቡን እየበላ በመሀል ቀና እያለ ሸርፎ ይመለከታታል፡፡‹‹ቤት መዋል ስትጀምሪ ባለሞያ ወጥቶሻል፡፡›› አለ ሁሴን የቀረበለትን ምግብ በልቶ ጨርሶ እጁን እየታጠበ፡፡

የተበላበትን ዕቃ አነሳስታ ከጨረሠች በኋላ ለሁለቱም ተጨማሪ ቢራ ጠረጴዛ ላይ በማስቀመጥ ፊት ለፊቱ እየተቀመጠች፡፡‹‹ባክህ... በእጄ የተሠራውን ምግብ ለመቅመስ እድሉ ስላልገጠመህ እንጂ ድሮም ባለሙያ ነኝ፡፡ >> አለችው

‹‹መጠጥ አሁንም አልተውሽም ማለት ነው?››

‹‹መተው አልተውኩም... ግን በጣም ቀንሻለሁ፤ አንዳንዴ ሲያሠኘኝ ብቻ ነው ቀመስ የማደርገው››

‹‹ይህቺ ቀመስ እራስን መሸወጃ እንዳትሆን?››

‹‹አይመስልህ፤አልፎ አልፎ መጠጣቱ ያን ያህል መጥፎ መስሎ ስላልተሰማኝ ነው እንጂ ለማቆም ከብዶኝ አይደለም፡፡ ጫት፣ ሲጋራና አንተን በአንዴ እርግፍ አድርጌ መተው የቻልኩ ሠው እኮ ነኝ፡፡››

ሁሴን በንግግሯ ፈገግ አለና ንግግሩን ቀጠለ << እኔም ሱስሽ ነበርኩ ማለት ነው?ለዛውም ከጫትና ከሲጋራ እኩል ውስጥሽን የምጎዳ መጥፎ ሱስ? ለማንኛውም እፈልግሃለሁ ብለሽ ያስጠራሸኝ ለምን እንደሆነ ለማወቅ ጓጉቻለሁ ?>>

‹‹ያን ያህል?››

‹‹ከምትገምቺው በላይ፡፡ አንቺን መፍራት ከጀመርኩ ሠነበትኩ እኮ፡፡ ነገረ ስራሽ ሁሉ ተዓምራዊ ነው፡፡ የዛሬው ደግሞ ምን እንደሆነ ልስማዋ!››

ከመቀመጫዋ ተነሳችና ወደ መኝታ ክፍሏ እየተውረገረገች ገባች፡፡ አተኩሮ ተመለከታት… ውበቷ ከቀድሞው በጣም የጨመረ መሰለው፡፡ አንዳንዴ የማያቃት አዲስ ሴት ትሆንበታለች፡፡ እርጋታዋ ያስፈራዋል፣ ብስለቷ ያስደነግጠዋል፡፡ በፊት ተሸፍነው የነበሩ ምርጥ ስብዕናዎቿ ዛሬ ጎልተውና አብበው መታየት ሲጀምሩ የማያውቃት ሴት መስላ ብትታየው ምኑ ይገርማል?፡፡

ተመልሳ መጣችና አንድ አበጥ ያለ እሽግ ካኪ ወረቀት አቀበለችውና ወደ መቀመጫዋ ተመልሳ ተቀመጠች፡፡

‹‹ምንድነው?›› ግራ በመጋባት ጠየቃት፡፡ዝም አለችው

‹‹ልክፈተው?›› መልሶ ጠየቃት፡፡

‹‹ምን አስቸኮለህ መጠጥህን ጨርሰህ ወደ ቤትህ ሄደህ ተረጋግተህ ታየዋለህ፡፡ ያን ያህል ጠቃሚ ጉዳይ አይደለም››አሁኑኑ ቤቱን ለቆ
ወጥቶ እሽጉን ለመክፈትና ውስጡ ያለውን ሚስጢር ምንነት ማወቅ ፈለገ፡፡ ደግሞም ስሜቱን እንደምንም ተቆጣጥሮ ሀሳቡን ቀየረ፡፡ ከእሷ አጠገብ መቀመጥ ከእሷ ጋር ማውራት ፈልጓል፡፡ አሁን ውድ ሆናበታለች፡፡ ሻይ ለመገባበዝ እንኳን እሷ በፈለገችና ባሰኛት ጊዜ እንጂ እሱ ሲፈልግ ሊያገኛት አይችልም፡፡ ስለዚህ ታግሶ ወደ ወሬው ተመለሠ፡፡

‹‹ያንን የጠየኩሽን ነገር ምን ወሠንሽ?›› ቢራውን ከነጠርሙሱ አንስቶ ተጎነጨና ጠየቃት፡፡

<<የቱን??>>

‹‹የሕይወት ታሪክሽን በጋዜጣዬ ላይ በተከታታይ አምድ ማሳተም እፈልጋለሁ ብዬሽ ነበር እኮ፡፡››

‹‹አስታውሳለሁ .. ግን አልወሰንኩም፡፡››

‹‹ብዙ ብር እኮ ነው የሚያስገኝልሽ .. የፈለግሽውን ያህል እከፍልሻለሁ››

የንዴት ፈገግታ ፈገግ አለች፡፡ ‹‹በቃ አንተ ከእኔ የምትፈልጋቸውን ነገሮች ሁሉ በብር ብቻ ነው ለመግዛት የምትጥረው፡፡ ፍቅሬን ወይንም ገላዬን በገንዘብ ስሸጥልህ ኖርኩ፤ዛሬም ታሪኬን በገንዘብ ልሽጥልህ?ያን ያህል አታውቀኝም ማለት ነው?››

ሁሴን ባላሠበው መንገድ ስለመጣችበት ተሸበረ፡፡ ትንግርት የሕይወቷን አቅጣጫ ከተቀየረ በኋላ ያስተዋለባት አንድ ለውጥ ይሄ ነው፡፡ በፊት ሲያውቃት ቻይ፣ሆደ ሠፊ፣ማንኛውን ንግግር የማያስከፋት፣ ቢያስከፋትም መከፋቷን ሳታሳውቅ በሳቅ ማሳለፍ የምትችል ብልህ ነበረች፡፡ አሁን ግን የተለየች ሆናለች::

‹‹እንደዛ ማለቴ አይደለም፡፡ ልዩ ታሪክ እንዳለሽ አምናለሁ፡፡ ይሄ ታሪክ ደግሞ ለተቀረው ማህበረሰብ አስተማሪ ስለሆነ ተዳፍኖ መቅረት የለበትም ብዬ ስለማስብ ነው፡፡ እስቲ እንዲታተም ባትፈቅጂ እንኳን ለራስሽ ፅፈሽ አስቀምጪው::››

‹‹ጽፌዋለሁ... በተለይ ባለፉት አምስት አመታት ያሳለፍኳቸውን በህይወቴ የተከሠቱ አንኳር ድርጊቶች በዲያሪዎቼ ላይ አስፍሬያቸዋለሁ፡፡››

‹‹በቃ እኔ የፈለኩት ይሄን ነው፤አየሽ ያልተጻፈ ነገር እየደበዘዘ ሄዶ ከእለታት አንድ ቀን መረሳቱ አይቀርም፡፡››

‹‹አይዞህ የሚረሳ ነገር አይኖርም፤መታተም አለበት ብዬ ስወስን ወደ አንተ ቢሮ እንደምመጣ ቃሌን እሠጥሀለሁ፡፡››

‹‹አመሠግናለሁ፤ቃልሽንም እንደምትጠብቂ አምናለሁ፡፡… ብቻ አሁን አንድ ነገር ላስቸግርሽ ነው...መጀመሪያ እሺ በይኝ፡፡››

‹‹ምን እንደምትጠይቀኝ ሳላውቅ እንዴት እሽ እላለሁ?»

‹‹በቃ እሽ በይኝ…ማድረግ የማትችይውን ነገር አልጠይቅሽም፡፡››

‹‹ለማድረግ እኮ ማድረግ መቻል ብቻ በቂ አይደለም...ፍላጎትም ያስፈልጋል፡፡››

‹‹ባክሽ ክርክሩን አቁመሽ እሺ በይኝ፡፡››

‹‹ውጪልኝ እንዳትለኝ እንጂ ለሌላው ችግር የለም፡፡››

ትክዝ ብሎ ሀሳብ ውስጥ ገባ፡፡ እራቁት ገላዋ... ቅብጠቷ... የወሲብ ብቃቷ በዓይነ ህሊናው ተመላለሰበት፡፡

ከት ብላ ሳቀችና‹‹ ተነቅቶብሃል፡፡ በፍፁም እሺ አልልህም፡፡የእሱ ጉዳይ ተዘግቶ ፋይሉ ወደ መዝገብ ቤት ተመልሷል፡፡›› አለችው፡፡

‹‹ግምትሽ የተሳሳተ ነው፡፡ እርግጥ ፍላጎቱ የለኝም ብዬ ልዋሽሽ አልፈልግም… በጣም ተርቤሻለሁ፡፡ አሁን ቃል ግቢልኝ ያልኩሽ ግን ለእሱ አይደለም፡፡››

‹‹ለእሱ ካልሆነ ቃሌን ሠጥቼሀለሁ... ጠይቀኝ፡፡››

ጉሮሮውን በመጠኑ ካረጠበ በኋላ ‹‹ከዲያሪሽ ላይ የአንዱን ቀን ውሎሽን እንድታነቢልኝ እፈልጋለሁ፡፡››

<<መቼ>>

<<አሁን ነዋ>>

‹‹አይሆንም .. አይሆንም .. ሌላ ጊዜ፡፡››

‹‹ቃል ገብተሽልናል፡፡››

እንደማሰብ አለችና ‹‹እሺ... ምን ቸገረኝ.. ስለምንድነው መስማት የምትፈልገው? የዩኒቨርስቲ የህይወት ገጠመኜን፣ የቡና ቤት ህይወት ገጠመኜን .. የቱን?››

‹‹ደስ ያለሽን ...ግን…. ስለ ቡና ቤት ቢሆን እመርጣለሁ፡፡››

ወደ መኝታ ቤቷ በመሄድ ስለ ቡና ቤት የሕይወት ገጠመኟ ካሰፈረችባቸው ድያሪዎቿ መካከል አንዱን መዛ ወደ ሣሎን በመመለስ መቀመጫዋ ላይ ተመቻችታ ቁጭ አለች፡፡

‹‹እንግዲህ አዚህ ዲያሪ ላይ ከተፃፈው የአንዱን ቀን ውሎዬን ወይም አዳሬን አነብልሀለሁ፡፡ ግን መርጬ አይደለም፡፡ ዝም ብዬ እከፍተዋለሁ፤አነብልሃለሁ፡፡›ተስተካክላ ተቀመጠችና ዲያሪዋን ከፈተች ወደ መሃከል ገደማ ነው፡፡ ርዕሱን አነበበች ‹‹40 ፐርሰንት›› ይላል ....ይሄንንማ አላነብልህም በጣም ይሰቀጥጣል፡፡

‹‹እድሌ ነው አንብቢልኝ፡፡››

‹‹በናትህ ደባሪ እኮ ነው፡፡››

‹‹ምንም ቢሆን ምንም መስማት እፈልጋለሁ፡፡››

‹‹እሺ ምን ቸገረኝ>> በማለት የገለጠችውን ዲያሪ በዝግታ ማንበብ ..…ሁሴን በጉጉትና በፀጥታ ማዳመጥ ቀጠለ

ሚያዚያ 20/2005

«40 ፐርሰንት››

ቀድሞ ገባ... ተከተልኩት፡፡ የቤርጎው ስፋት መታጠቢያ ክፍሉን ሳይጨምር አራት በሦስት ይሆናል፡፡ የከፈለኝ የጠየኩትን ያህል ብር ነው፡፡ ዝምተኛ፣ ጭምትና የከፋው ቢጤ ነው፡፡ እንዲህ አይነት ወንዶች አንድ የተለየ ነገር አይታጣባቸውም ብዬ ስለማስብ አብሬያቸው ማደር ደስ ይለኛል፡፡

የቤርጎውን በር ከቀረቀርኩ በኋላ ወደ ውስጥ ዘለቅኩ፡፡ ቀድሞኝ አልጋው ላይ ጋደም አለ ከነልብሱ፡፡ እኔም በእጄ ይዤ የነበረውን ኮንዶም ኮሞዲኖው ላይ ጣል አድርጌ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጥኩ፡፡ ሠረቅ አድርጌ ተመለከትኩት አይኑን ጣሪያ ላይ ሠክቶ ይቆዝማል፡፡ ነገር የገባው ፈላስፋ ይመስላል፡፡
👍815👏3👎2😁2🔥1🥰1
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቢ


‹‹እሺ ሳባ ህይወት እንዴት ነው?››

‹‹አሪፍ ነው…ምንም አይል?››

‹‹ማለቴ የስራ ህይወትሽ እንዴት ነው..ደስተኛ ነሽ?››

‹‹አዎ በስራው ደስተኛ ነኝ….ግን ክፍያው በቂ አይደለም…ማለቴ  በቂ  ሊሆን ይችላል ለእኔ ግን እየበቃኝ አይደለም፡፡›› ስትል በምሬት መለሰችላት፡፡
‹ይገባኛል…አየሽ አንቺ የተማርሽ ቆንጆና ማራኪ ወጣት ብትሆኚም በዕድሜ ግን ገና ለጋ ወጣት ነሽ…ገና ብዙ ብዙ ዕድል ይጠብቅሻል.. በህይወት የተሰጠሸን እድል ትጠቀሚበታለሽ ወይስ ታባክኚዋለሽ….ዋናው ጥያቄ ይሄ ነው፡፡››

‹‹ማለት አልገባኝም፡፡››አለቻት..እውነትም አለመግባትም ብቻ ሳይሆን  ይባስ ብሎም ግራ ገብቷታል፡፡
ስለጀመረችላት ወሬ ይበልጥ ማብራሪያ ትሰጠኛለች ብላ ስትጠብቅ አሷ ‹‹እስኪ ተነሽ አንድ ቦታ ሄደን እንምጣ›› ብላት ቀድማት ከመቀመጫዋ ተነሳች...ሳባም ያለምንም ማቅማማት ተከትላት ተነሳችና ከኋላዋ ተከተለቻት፡፡
በፊት ለፊት በር ትወጣለች ብላ ስትጠብቅ ወደኋላ በር አመራች ..ረጅም ኮሪደር ሰንጥቀው ካቋረጡ በኋላ ወደውጭ ወጡ፡፡ በፅድና በተለያዩ አበቦችና አትክልቶች የተሞላ ውብ ግቢ ነው፡፡በረንዳውን ወርዳ ወደጓሮ ዘልቃ ገባች… ‹‹ይህቺ ሴትዬ ጓሮዋን ልታስጎበኘኝ ነው እንዴ?››እያለች  በማልጎምጎም  ተከተለቻት፡፡ግን ተሳስታ ነበር…፡፡እስከመጨረሻ ጓሮውን ሰንጥቀው ከጨረሱ በኋላ ሰማይ ጠቀስ በሆነው የብሎኬት አጥር መሀከል የሚያብረቀርቅ ወርቅ  ቅብ  አይነት  ቀለም የተቀባ የላሜራ ግዙፍ በር አለ..በራፉ ጋር አንድ ጥቁር  ሱፍ  የለበሰ  መልኩም ጥቁር የሆነ ወጠምሻ ሰው ቆሟል ፡፡
የኋላ ቤት የኋላ በራፍ በመኖሩ ተገርማ ሳትጨርስ ጭራሽ ጠባቂ ስታይ‹‹ይሄ ምን ጉድ ነው?››ስትል ነበር በውስጧ የጠየቀችው
‹‹….ሴትዬዋ ሀሽሽ አከፋፋይ ትሆን አንዴ?››መልስ ባታገኝም በውስጧ የጠየቀችው ጥያቄ ነበር፡፡ወጠምሻው ጠብ እርግፍ በማለት በትህትና እጅ ነሳና በራፉን ከፈተላቸው፡፡ተያይዘው በራፉን አልፈው ወጡ፡፡የወጡት ግን ወደ አስፓልት አይደለም ወይም ኮረኮንች መንገድ ላይ ወስዶ የሚጥልም አይደለም…ወደ ሌላ ግቢ እንጂ፡፡ ግቢው በግምት አንድ ሺ ካሬ ስፋት ያለው

ሲሆን የሎጅ አይነት አሰራርና አደረጃጀት የተከተለ ነው….ራቅ ራቅ ብለው አንደኛው ከአንደኛው በራፍና መግቢያ ተቃራኒ እንዲሆን ተደርጎ በቁጥር አስር በጎጆ ቅርፅ የተሰሩ ግድግዳቸው ባህላዊ ይዘት ኖሮት በተጠረበ ድንጋይ በጥንቃቄ የተሰሩ ቤቶች ዙሪያቸውን በተክሎች፤በአበባና፤በሀረጎች የተሸፈነና   የተከለለ ተደርጎ የተሰራ ነው፡፡
ትብለጥም‹‹ይሄ አንደኛውና ዋነኛው የስራ ቦታችን ነው…ሌሎች ሁለት ቦታዎችም አሉን…ዋናው ግን ይሄ ነው፡፡››በማለት ወደ አንዱ እየመራች ወሰደቻት፡፡
የተዘጋውን በራፍ እጄታውን ጫን አለችና ገፋ አድርጋ ከፈተችው..ሶስት ክፍል አለው፡፡አንዱ ሻወር ቤት…ሁለተኛው ከሻወር  ቤቱ የተያያዘ  መልበሻ  ክፍል፤ሲሆን ሌላው ዋናውና ሰፋ ያለው ክፍል ነው፡፡ ሰፊውና ዋናው ክፍል ውስጥ አንድ ቁም ሳጥን ሁለት ደረቅ ወንበሮች፤ከአንድ አነስተኛ ጠረጴዛ ጋር አንድ መካከለኛ ቁመት ያለው ሰው በምቾት ማስተኛት የሚችል ረዘም ያለ በነጭ ቆዳ የተለበጠ ሶፋ ሲኖር ወለሉ መካከል ላይ ሰፊና ረጅም የማሳጅ  ጠረጴዛ አለ፡፡ዙሪያውን ቃኝታ ሳትጨርስ ደረቅ ወንበሩ ላይ ቁጭ ብሎ የነበረ አንድ የተወጣጠረ ጡንቻ ያለው ወጣት ከተቀመጠበት በፍጥነት ተነሳና ወደ እነሱ በመቅረብ  ‹‹እንኳን በሰላም መጣችሁ ›› ሲል መጀመሪያ ትብለጥን ከዛ ደግሞ ሳባን ጨበጣቸው…
ሳባ ሲጨብጣት የእጁ ልስላሴና ጥንካሬ ውስጧ ድረስ ተሰማት፡‹‹እንዴት በዚህ መጠን ለስላሳና ጠንካራ ሊሆን ቻለ..?››ስትል ተገረመችበት፡፡‹‹አይ  እንደዛማ ሊሆን አይችልም…እኔ ተሳስቼ ነው፡፡›› አለችና ትኩረቷን ለመሰብሰብ ሞከረች፡፡
‹‹ሶፈኒያስ ይባላል እሷዋ ደግሞ ሳባ ትባላለች…ዘመዴ ነች፡፡ሰሞኑን  ከተጨናነቀ ስራ ላይ ነበረች፤ከዛ አስነስቼ ነው ያስመጣኋት፤ትንሽ ዘና ማለት ይገባታል

…አንተን ደግሞ እተማመንብሀለሁ….ልከ ለእኔ እንደምታዳርገው ለእሷም እንደዛው፡፡›› የሚል ትዕዛዝ አስተላለፈችለት፡፡
‹‹እረ ችግር የለውም…ግቢና ልብስሽን ቀይሪ…››ብሎ ፊቱን አዙሮ ወደ ጠረጴዛው ሄደና ለስራ የሚገለገልባቸውን ቅባቶችና የማሳጅ መገልገያ ዕቃዎች ማዘጋጀት ጀመረ፡፡ሳባ የምትለውና የምታደረግው ግራ ገብቷት በተገተረችበት ፈዛ ትብለጥን በትኩረት ትመለከታት ጀመረ፡፡
ገባትና ልትቀመጥ ወደሶፋው መራመድ የጀመረችውን እርምጃ ገትታ እጇን በመያዝ እየጎተተቻት ወደልብስ መቀየሪያው አነስተኛ ክፍል ይዛት ገባች.. የክፍሉ ሁለት የግድግዳው ክፍል ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በመስታወት የተሸፈነ ነው፡፡በአንደኛው ግድግዳ ተደግፎ የቆመ ለክፍሉ እንዲስማማ ተደርጎ የተሰራ አነስተኛ ቁምሳጥን አለ…አንድ መቀመጫ መግቢያው ላይ አለ‹‹…በይ ልብስሽን አውልቂና ይሄንን ፎጣ አገልድመሽ ነይ…››
‹‹ልብሴን አውልቄ…? ማለት ለምን..?››

‹‹እንዴት ለምን ?ማሳጅ ተሰርተሸ አታውቂም?››

‹‹በፍፁም አላውቅም፡፡››

‹‹እንግዲያው እመኚኝ በጣም ትወጂዋለሽ፡፡›

‹‹እረ ይቅርብኝ..እኔ ወንድ ፊት እርቃኔን ቆሜ አላውቅም..››

‹‹እንዴ ምን ነካሽ የተማርሽና ዘመናዊ ሴት አይደለሽ እንዴ…? እንዳልሽ በወንድ ፊት ልብስሽን አውልቀሽ የማታውቂ ከዛም በላይ የወንድ እጅም ሰውነትሽ ላይ አርፎ የማያውቅ ሊሆን ይችላል…ግን ያ ማለት እስክትሞቺ   አንዲህ  ሆኖ ይቀጥላል ማለት እንዳልሆነ መቼስ በደንብ ታውቂያለሽ…አንድ ቀን በየተራ አድርገሽ የማታውቂያቸው ነገሮችን ቀስ በቀስ ማድረግሽ የማይቀርና የሚጠበቅ
ነው..አሁን በይ ልብስሽን አውልቂና ነይ…ደግሞ እኮ ብቻሽን አይደለሽም እኔ በክፍሉ ውስጥ ከፊት ለፊትሽ ቁጭ እላለሁ፡፡››
ምንም ማምለጫ መንገድ ልታገኝ አልቻለችም፡‹‹እሺ በቃ››

‹‹አዎ እንደዛ ነው የሚባለው..በይ አውልቂና ነይ .››ብላት ክፍሉን ጥላላት ወጥታ ሄደች…ሳባ የለበሰችውን ቀሚስ አወለቀችና ቀኑን ሙሉ ስትለፋበት የዋለችውን አዲስ የተሰራ ጸጉሯን አንድላይ ጠቅላላ በማያያዝ ፎጣውን አገልድማ ልክ ለዘመናት ሲያልመውና ሲመኘው ወደከረመው መድረክ   አድል ቀንቶት ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚወጣ አማተር  አርቲስት በፍራቻና   በሚንቀጠቀጡ እግሮቿ ወደ ውስጥ ገባች…ሁለቱም ቀና ብለው አዯት እና እርስ በርስ ተያዩ
…ፈገግ አለች ትብለጥ

‹‹ምነው?ምን አጠፋሁ?››

‹‹ምንም…ግን በማሳጅ ምንም አይነት ልብስ አይፈቀድም…››

‹‹እንዴ ፓንትም?››

‹‹እሺ ለዛሬ ፓንቱን ይሁን ተይው…ጡት ማስያዣውን ግን አውልቂው…››

‹‹ሴትዬዋ ጉድ ልትሰራኝ ነው እንዴ? ያን  ሁሉ  እንክብካቤና  ጠብ  እርግፍማ ለጤና አይደለም›› እያለች ተመልሳ  ወደክፍሉ  ገባችና  ጡት  ማስያዣዋን አወለቀችና ተመለሰች…ወደ ጠረጴዛው ቀረበች…
‹‹ዘና በይና ጠረጴዛው ላይ በደረትሽ ተኚ ››አላት…

ከፍራቻዋ ጋር እየታገለች እንዳላት አደረገች..ቅባቱን በእጆቹ አፈሰና  ከትከሻዋ አካባቢ እጆቹን አሳረፈ፡፡ ሰውነቷ ሽምቅቅ  አለ…ቀስ  እያለ  መገጣጠሚያዋን እየነካካ እያፍታታት፤ወደታች ወደ ጀርባዋ ወረደ…አንዳንዴ ላላና ለስለስ ብሎ
👍819🔥1
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


‹‹ይሄ መንገድ ግን ወደ መጣንበት አቅጣጫ የሚወስድ አይደል እንዴ?››በጥርጣሬ ጠየቀች፡፡
‹‹አይ አይደለም…..ትንሽ ከተጓዝን በኃላ እንታጠፋለን፡፡››ሲል ድጋሜ ዋሻት፡፡

ከዛ በኃላ ለ10 ደቂቃ ያህል ጫካውን ቁጥቆጦ እየገፉና እሾክና እንቅፋቶችን ከፊታቸው እያስወገድ ወደፊት ከመጓዝ ውጭ በሶስቱም መካከል ምንም ንግግር አልነበረም፡፡
ኑሀሚ የህይወቷ የመጨረሻ ጫፍ ላይ እንደደረሰች ተስምቷታል፡፡ከቡድኑ ነጥለው ወደጫካው እየነዷት ያለው ለሰላም እንዳልሆነ ወዲያው ነው የገባት፡፡ በተለይ የካርሎስ መርበትበትና በፊቱ ላይ እየተመለከተችው ያለው ሀዘን በጥርጣሬዋ እርግጠኛ እንደትሆን አድርጓታል፡፡ በዛ ላይ ከኃላ ሆኗ የሚከተላቸው ፊቱ የማፈታው ታጣቂ በጀርባው ባነገተው ቦርሳ አካፋም መቆፈሪያም ሆኖ የሚያገለግል ወታደሮች ምሽግ ለመስራት የሚጠቀሙበትን መሳሪያ ይዞ በማየቷ ሌላ እርግጠኛ እንድትሆን ያደረጋት ምልክት ነው፡፡
አካባቢን ማጥናት..ማንኛውንም እንቅስቃሴ በንቃት መከታተል..ከዛ የይሆናል ትንበያዎችን አስቀምጦ ከቅርቃሩ ለመውጣት የሚያስችሉ አማራጮችን በፍጥነት ማስላት….በስለላ ህይወቷ የቀሰመችው ትምህርት ነው፡፡
እና ዝም ብላ መሞት እንደሌለባት እራሷን እያሳመነች ነው፡፡በህይወቷ እንዲህ መሰል በህይወትና በሞት ቅርቃር መካከል የመውደቅን አጋጣሚ ብዙ ጊዜ ገጥሞት ያውቃል፡፡ በአምስት ሰዎች ተከባ ልትገደል ብላ ግማሹን ገንድሳ ግማሹን ገድላ ነፃ የወጣችበትና ህይወቷን ያተረፈችበት አጋጣሚ ነበረ፡፡ከእዛ አንጻር ሲታይ ይሄ ቀላል ይመስላል..ምክንያቱም ከሁለት ታጣቂዎች ጋር ነው የምትፋለመው፡፡ ካላት ወታደራዊ እውቀትና ልምድ አንፃር አነሱን ገድላ ወይ ፌንት አስበልታ የማምለጥ እድሏ ከ50 ፐርሰንት በላይ ነው ፡፡..ችግሩ ካመለጠች በኃላ ነው፡፡ፊቷ ያፈጠጠው ምኑንም የማታውቀው በየት ገብታ በየት መውጣት እንዳለባት ምንም እውቀት የሌላት የአማዞን ጫካ ነው፡፡ጫካ ውስጥ ያሉት አስፈሪና በስም እንኳን ለይታ የማታውቃቸው አውሬዎችና አንድ ጠብታ መርዛቸው እንኳን ሰውነት ላይ ሲያርፍ በሰከንድ ውስጥ የሚያደርቅ ተሳቢ እንስሳትና በራሪ ነፍሳት ጋር ነው፡፡ቢሆን በሰው ተቦጫጭቆ ከመበላት በአውሬ ጋር ለመፋለም ቁርጠኛ መሆን ይሻላል
፡፡በዚህ ቅፅበት አንድ ታሪክ ትዝ አላትና ለካርሎስ ልትተርክለት ፈለገች፡፡

‹‹አንድ ጣፍጭ ታርክ ልንገርህ?››

እንደ እሱ ግንዛቤ ሰዓቱ ታሪክ መንገሪያም ሆና ማዳመጪያ እንዳልሆነ ቢያምንም ለእሷ ግን ምን አልባት የመጨረሻ ቃሏ ሊሆንላት ይችላል ብሎ ስላሰበ እንድትነግረው ተስማማ፡፡
‹‹ጨቋኝ ገዢ ወይም የሰው ልጅ  ከገዳይ ነብር የበለጠ አስፈሪ እንደሆነ የሚያስረዳ ታሪክ ነው፡፡
‹‹ገባኝ ንገሪኝ…››

ከአንድ የድሮ መፅሀፍ ላይ ያነበብኩት ታሪክ ነው፡፡በአንድ ወቅት በቻይና ግዛት ውስጥ በምትገኘው በታይ ተራራ ስር በሀዘን ተቆራምዳ እንባዋን እያዘራች የምትኖር ሴት ነበረች፡፡የዚህችን ሴት ታሪክ ኮንፌሽዬስ ሰማና አስጠራት፡፡ከዛም"አንቺ ሴት ምን ሆነሽ ነው እንዲህ ሀዘን የበላሽ?"ሲል ጠየቃት።ሴቲቱም ‹‹በተራራው ላይ የሚኖረው ነብር ባሌን ፣የባሌን አባት እና ብቸኛ ልጄን በየተራ እየቀረጣጠፈ በላብኝ-በዛ ምክንያት ነው ሀዘኔ ጥልቅ የሆነው›› ብላ መለሰችለት።
እሱም መልሶ "ታዲያ መላ ቤተሠቦችሽን የበላው ነብር አሁንም በተራራው ላይ መኖን እያወቅሽ .እንዴት ከአካባቢው ሳትሸሺ?››ሲል በመገረም ጠየቃት።
ሴቲቱም‹‹ቦታውን ለቅቄ ያልተሠደድኩት ጨካኝ ገዢ የሌለበት ብቸኛ  ስፍራ ስለሆነ ነው።"ስትል መለሠችለት
ኮንፌሽዬስም ወደ ደቀመዛሙርቱ ዞሮ" አያችሁ ጨቋኝ ገዢ ከገዳይ ነብር የበለጠ አስፈሪ እንደሆነ ከዚህች ሚስኪን ሴት ታሪክ ተማሩ፡፡›› አላቸው።
እኔም አሁን እዚህ አማዞን ደን ውስጥ ካሉት አውሬዎች በላይ ጨካኝ የሆኑ የሰው ልጆች ናቸው እያሰፈሩኝ ያሉት››ብላ ታሪኩን ደመደመች፡፡
‹‹አልተሳሳትሽም….የሰው ልጅ መጨከን ከጀመረ ወሰኑ አይደረስበትም…››

‹‹እኔ ምልህ ..አሁን ልትገድሉኝ ነው አይደል?››

ጥያቄዋ አስደነገጠው…ምን ብሎ እንደሚመልስላት ግራ ስለገባው…ዝም አለ…‹‹አትጨነቅ..ግን ያልገባኝ እንዲህ ልትገድሉኝ ይሄን ሁሉ ቀን እኔንም ማንከራተት እናንተም ከእኔ ጋር መንከራተት ለምን አስፈለገ?››
‹‹ትዕዛዙ የደረሰን አሁን ነው…››

‹‹ትዕዛዙን የሚሰጠው ማን ነው››

‹‹ሀለቃችን ነው…ካለበት ቦታ በሳተላይት መገናኛ ነው ከደቂቃዎች በፊት ትገደል ያለው፡፡››

‹‹ይገርማል…ቆይ ግን ከእኔ ጋር ያገኛችሁትን ሰውዬ ገድላችሁታል አይደል?››

ፈገግ አለ፡፡

የፊቱን ፈገግታ በቆረጣ እይታ አየችውና ተበሳጨችበት…‹‹ምነው? የሰው መገደል ያስቃል እንዴ?››
‹‹አረ በፍፅም … እንደውም በተቃራኒው ልቤን ነው የሚሰባብረው፡፡››

‹‹አይ ስትስቅ አየሁህ ብዬ ነው፡፡››

‹‹ጥያቄሽ ነው ያሳቀኝ …አንቺ እንድትገደይ ትዕዛዙን ያስተላለፈው ሀለቃችን አሁን አንቺ የምትጨነቂለት ዳግላስ መሆኑን ሳስብ ነው ያሳቀኝ..አየሽ አለም በእንደዚህ ይነት ገራሚ ምፀቶች የተሞላች ነች፡፡››
እርምጃውን ገታችና ባለችበት ቆመች..ከኃላ እየተከተላቸው ታጣቂ አይኑን አጉረጠረጠ…የጓደኛውም ሆነ የተገዳዮ ነገረ ስራ ምንም አላማረውም…ጣልቃ ላለመግባት ነው እንጂ ወሬያቸውም አልተመቸውም.. ምክንያቱም እሱ ስፓኒሽኛ ተናጋሪ ሲሆን እንሱ እያወሩ ያሉት በእንግሊዘኛ ነው..እሱ ደግ እንግሊዘኛ ጆሮውን ቢቆርጡጥ አይሰማም፡፡
‹‹ማለት ከእኔ ጋር ያገታችሁት በሌላ ጀልባ ወደሌላ ስፍራ የወሰዳችሁት ዳግላስ የእናንተ ሀለቃ ነው?››ማመን ስላልቻለች ደግማ ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ እሱ የእኛ ብቻ ሳይሆን በሺ ሚቆጠሩ ሌሎች የታጣቂ ቡድኖች መሪ የጫካው ንጉስ እየተባለ   የሚጠራ   ከፍተኛ   ቢሊዬን   ዶላሮች   የሚያንቀሳቅስ   ከፔሩ፤ ኮሎምበያ፤ ፓናማ፤ ነካረጎ፤ ጉታማላ፤  ሚክሲኮ አልፎ አሜሪካ ድረስ እሱ የሚቆጣጠረው የንግድ መስመር ያለው በሶስት በአራት ሀገራት የደህንነት ሰዎች ሚፈለግ አለማ አቀፉ የኢንተርፖል የተፈላጊዎች ስም ዝርዝር ውስጥ የመጀመሪያው ገፅ ላይ የሰፈረ ተአምረኛ ሰው ነው፡፡››የሚላትና ማመን ነው እያቃታት፡፡‹‹እና እሱ እንደእዛ አይነት ሰው ከሆነ ለምን ከእኔ እኩል አፈናችሁት?፡፡››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹ሰውዬው መድሀኒቱን በጊዜ ካልወሰደ ከፍተኛ የመርሳት ችግር አለበት..ማለት እራሱንና ማንነቱን ሙሉ በሙሉ እስኪዘነጋ ድረስ ይደርሳል፡፡ከንቺ ጋር ሊማ አየር ማረፊያ ተገናኝታችሁ ኢኩቶስ እስክታርፉ ድረስ ከዛም ሆቴል ይዛችሁ ስታድሩ ሁሉ ያገጠማችሁ ያ ነው፡፡በወቅቱ ችግሩ እንደተፈጠረ ስናውቅ በግል ቻርተር አውሮፕላን እናንተ ወዳላችሁበት መጣን፡፡ ቀጥታ ሄደን ብናናግረው..አላውቃችሁም ሊለን ይችላል፡፡ ክርክር ብንገጥም ጭቅጭቅ ቢነሳ ደግሞ ትኩረት እንስባለን…እንዳልኩሽ በአለም አቀፍ ደረጀ የሚፈለግ ሰው ነው…ስለዚህ ሁኔታውን አመቻችተን ማፈን ነበረብን፡፡ለዛ ነው እንደዛ ያደረግነው፡፡››
👍697👏2
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧

እለቱ እሁድ ነው፡፡ከፊራኦል ጋር ለመውጣት ስለተነጋገሩ እየተዘጋጀች ነው፡፡ለሊሴ እየረዳቻት ነው፡፡
ሰው ከለገመ ከሻማ በላይ በቀላሉ ቀልጦ የሚጠፋ ከጠነከረ ደግሞ ከአልማዝም በላይ ማይቆረጥና ማይሸረፋ ተአምራዊ ፍጡር መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡በፀሎትም የማያልፍ የመሰላት አሰቃይ ህመም በጥቂት ቀናት ውስጥ ጥሏት ሄዶ ንፅህና ጤነኛ ልጅ ሆናለች፡፡የእግሯን ስብራት ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ድኗል…የፊቷ ቁስል ግን ምንም እንኳን ቢድንም ጣባሳውና ቁስለቱ አሁንም በግልጽ ፊቷ ላይ ይታያል… በዚህ ምክንያት አሳባ ከፊል ፊቷን ሁሌ በሻርፕ እንደሸፈነችው ነው፡፡ዋና ምክንያቷ ግን ማንነቷ በቀላሉ እንዳይለይ በማሰብ ነው፡፡አሁንም ተመሳሳይ አለባበስ አድርጋ በዛ ላይ ጥቁር መነፅር አይኗ ላይ ሰክታ ዝግጁ ሆነች፡፡

‹‹ግን እህቴ ለምንድነው እኔን የማታስከትሉት?››ለሊሴ ተነጫነጨች፡፡

‹‹አይ …መጀመሪያ ከወንድሜ ጋር የምንሄድበት ቦታ አለ…ባይሆን ከዛ ቶሎ ከጨረስን እንደውልልሽና ትቀላቀይናለሽ››

‹‹ይሁንላች ግን ታበሳጭቼባችኋለሁ››

በታክሲ ከሰፈር ሁለት ፌርማታ ያህል ርቀው ከሄዱ በኃላ ‹‹ደርሰናል እንውረድ›› አላት፡፡ያን ያህል ቅርብ ይሆናል ብላ አላሰበችም ነበር፡፡እንደወረዱ ቀጥታ ፊት ለፊት የሚገኝ በፅድና በባህርዛፍ አፅድ የደመቀ ሰፊ መናፈሻ ውስጥ ነው ይዞት የገባው…ቀጥታ ከሰው ነጠል ያለ ቦታ ይዞት ሄደና ቁጭ እንድትል መቀመጫ አመቻችቶላት ከፊት ለፊቷ ተቀመጠ‹‹እሺ ምን ትጠቀሚያለሽ?››

‹‹ቆይ እስኪ… ምን አስቸኮለህ…መጀመሪያ ትምጣ››

‹‹ማን?››

‹‹ምን ….ማንን ልናገኝ ነው የመጣነው…?ፍቅረኛህ ነቻ…በል ደውልላት፡፡››

‹‹ስልክ የላትም››

‹‹ታዲያ እንዴት ነው የምታገኘን››
‹‹የልቤን ምት አዳምጣ ትመጣለች››

‹‹ጥሩ ትቀልዳለህ….ይሄ የተለመደ መገናኛ ቦታችሁ ነው ማለት ነው…ገባኝ›› አስተናጋጁ መጣችና‹‹ምን ልታዘዝ ?››ብላ ጠየቀች፡፡

በፀሎት ቀደም ብላ‹‹ሰው እየጠበቅን ነው….››ብላ ለአስተናጋጆ መለሰችላት

‹‹አይ አሷን አንጠብቅም..ቆንጆ ፒዛ አሰሪልን…ፒዛው እስኪደርስ እሷም ትደርሳለች››

አስተናጋጆ ትዕዛዙን ተቀብላ ሄደች፡፡

ፊራኦል ወደእሷ አትኩሮ እያያት…..‹‹እስኪ ሻርፑን አንሺው››በማለት ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት

‹‹እንዴ ለምን?››

‹‹ሙሉ ፊትሽን ለማየት ፈልጌ››

‹‹ኖ ዌይ…..›

‹‹ምን ችግር አለው?››

‹‹እኔ  እራሴ  ሙሉ  በሙሉ  ፊቴ  እንደዳነ  እና  እንደማያስጠላ  እርግጠኛ  ስሆን እገልጠዋለው፡፡››

‹አንቺ እንዴት ልታስጠይ ትችያለሽ…ውብ እኮ ነሽ››

‹‹ሙሉ ፊቴን ሳታይ ውብ መሆኔን በምን አወቅክ…?››ኮስተር ብላ በመገረም ጠየቀችው፡፡

‹‹እኔ እንጃ ውብ እንደሆንሽ ግን እርግጠኛ ነኝ፡፡››

መልስ ልትሰጠው አፏን ስትከፍት አስተናጋጇ የታዘዘውን ፒዛ ይዛ ፊታቸው ስታስቀምጥ አፏን ያለምንም ንግግር ከደነች፡፡

‹‹‹ለእኔ እስፕራይት አምጪልኝ…..ላንቺስ ?›

‹‹እንዴ ልጅቷ ሳትመጣ….?››
‹‹ባክሽ የሆነ ነገር እዘዢ እሷ ስትመጣ የራሷን ነገር ታዛለች››

ግራ እየገባት አዘዘች …ፒዛውን ቆርሶ መብላት ሲጀምር ፣ በገረሜታ ተከተለችው… በልተው ጨርሰው እንኳን ልጅቷ አልመጣችም››

‹‹እንደዛ  ቅኔ  ምትቀኝላት  ልጅ  እስከአሁን  ካልመጣች  ከአሁን  ወዲያም  የምትመጣ አይመስለኝም፡፡››

‹‹መጣችእኮ››

‹‹የታለች?››

‹‹ይህቹት ፊት ለፊቴ ቁጭ ብላ እያወራቺኝ ነው፡፡››

‹‹እየቀለድክብኝ ነው እንዴ?››

‹‹እሺ አትበሳጪ..እኔ ምንም አይነት ፍቅረኛ የለኝም….አንቺን ወጣ አድርጌ ማዝናናት ስለፈለኩ ነው እንደዛ ያልኩሽ››

‹‹አንተ ውሸታም……..ቆይ ምንም ፍቅረኛ ሳይኖርህ ነው እንደዛ ፈዘህ በውድቅት ለሊት ቅኔ ስትዘርፍ የነበረው››

‹‹በተጨባጭ ፍቅረኛ የለኝም አልኩሽ እንጂ በምናቤ ስዬ የማስባት ሴት የለችም አላልኩሽም…..እንደዛ አወራ የነበረው በልቤ ውስጥ ተንሰራፍታ የተቀመጠችውን ልክ እንደአንቺ ውብ የሆነችውን ልጅ እያሰብኩ ነበር››

‹‹ምን አይነት አዝግ ልጅ ነህ….?እኔ ደግሞ እንዴት አይነት ቆንጆ ልጅ ትሆን እያልኩ ለሊቱን ሙሉ ሳስብና ስጓጓ ማደሬ››

‹‹ምን ያጓጓሻል…የፈለገ ውብ ብትሆን ካንቺ አትበልጥ…አንቺ እኮ ሁለመናሽ ውብ ነው…ማለት ስብዕናሽ ፖስቸርሽ..እርግጠኛ ነኝ መልክሽም ውብ ነው..ፍቅረኛዬ ልክ አንቺን ካልመሰለች ልቤን ማሸነፍ አትችልም››ፊራኦል ቀጥታ መንገር ፈርቶ ነው እንጂ ከበፀሎት ፍቅር ከያዘው ሰነባብቷል…ስሩ ሆና እራሱ ትናፍቀው ከጀመረች ቆይታለች..ለዛ ነው ሙሉ ፊቷን ማየት በጣም የናፈቀው…ቆንጆና ውብ ፊት ነው በምናቡ የሳለው…
‹‹ጥሩ ..ግን ስለውበትና ቁንጅና እኮ በእህትና በወንድም መካከል የሚወራ ኮንሰፕት አይደለም…..ባምርም ባስጠላም እንደእህትህ ነኝ…ለውጥ አያመጣም፡፡››

‹‹እንደእህት እና እህት ግን ይለያያል››

ለዚህ ንግግሩ ምን ብላ መልስ ልትሰጠው እንደምትችል ሊመጣላት አልቻለም…‹‹.እኔ የእህትህን ልብ በውስጤ የተሸከምኩ ሴት መሆኔን ብታውቅ ይሄን ሁሉ ርቀት ለመጓዝ አይዳዳህም ነበር››ስትል በውስጧ አብሰለሰለች

//////

በማግስቱ-----
እቤት ውስጥ ማንም የለም..ሌንሳ ብቻ ከበፀሎት ጎን ቁጭ ብላ እያወራቻት ነው፡፡
እህቴ ስራ በማግኘቴ በጣም ደስተኛ ሆኜያለው….ይገርምሻል ፀሀፊ ሆናለው ብዬ አንድም ቀን ኣስቤ አላውቅም ነበር…››

‹‹ላንቺ እኔ በጣም ደስ ብሎኛል… ስራውን ግን እንዴት ነው..እየለመድሽው ነው? ››

‹‹አሪፍ ነው ..ተመችቶኛል፡፡››
‹‹የፍቅርና የጋብቻ አማካሪ ነው ያልሽው?››

‹‹አዎ እህቴ …ብታይ ሰውዬው ማለቴ አለቃዬ በጣም ነው የሚያሳዝነው፡፡››

‹‹ለምንድነው የሚያሰዝነው? እሱም ፍቅር ይዞታል እንዴ?፡፡››

‹‹አይ እሱን አላውቅም … ያሳዝናል ያልኩሽ…ምንም ደንበኛ የለውም….ዝም ብለን እኔና እሱ ቢሮ ውስጥ ተፋጠን ነው የምንውለው…››ለምን ያሳዝናል እንዳለች ታስረዳት ጀመር፡፡

‹‹ምነው በስራው ጎበዝ አይደለም እንዴ?››

‹‹አረ በቅርብ ነው ከውጭ የመጣው..በሞያው ኤክስፐርት ነው…እንደነገረኝ ከሆነ አሜሪካ እያለ በሞያው ከሶስት አመት በላይ ሰርቶ በጣም ብዙ ሰዎችን ረዳቷል …እዚህ መጥቶ የራሱን ድርጅት ቢከፍትም እንዳሰበው አልሆነለትም….እንደምታውቂው የእኛ ሰው ድብቅ ነው …ባለትዳሮችም ቢሆኑ እዛው ቤታቸው ውስጥ ሲቋሰሉ ይኖራታል እንጂ ገበናቸውን ወደአደባባይ ማውጣት አያስብትም ..ባስ ቢልባቸው እንኳን እዛው የሰፈር ሽማጊሌ ጠርተው በምስክር ፊት ይጨቃጨቃሉ እንጂ ወደባለሞያ አይሄዱም፡፡ለዚህ ጉዳይ ባለሞያም እንዳለው የሚያውቅ የማህበረሰብ ክፍል አንድ ፐርሰንት የሚሞላ አይመስለኝም፡
‹‹ታዲያ እኮ የሰፈር ሽምግልናው ቀላል ነገር አይምሰለሽ…ሁለቱም ለእኛ ጥሩ ያስባል እና ያስማማናል የሚሉትን ሰው በማሀከላቸው አስቀምጠው ችግራቸውን በግልፅ በመነጋገር
ለመፍታት መሞከር ትልቅ ዋጋ ያለው ማህበራዊ እሴታችን ነው፡፡በዚህም መንገድ በጣም በርካታ ሺ ትዳሮች በየአመቱ ስንጥቃቸው ይደፈናል ስብራታቸው ይጠገናል፡፡››
👍6713🥰8👏3😱1
#የጣት_ቁስል


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ

የማን ይሁን ?

የባሰ! እሾክና መርፌ ተነቅሎ የማይጣል፤ በቅርብ ሳይገፋ ያልተደረሰበት ፤ ከላይኛው የወረደ ዱብዳ ፤ የፈጣሪ የቁጣ ስጦታ፡፡ ለማን ታድርገው? ለማን ትስጠው? ለማንስ አቤት ትበል? ተቆርጦ የማይጣል የጣት ቁስል ሆነባት፡፡

ቀኑ ወደ ጨለማ ተቀየረ፡፡ እንደ ተዳፈነ እሳት ውስጧን አቃጠለው፡፡ እንደ ሰኔ ደመና አረምሞ ገፍቷል፡፡ በአንድ ቀን ስህተት የእግዚአብሔር ስራ እንኳን ባይባልም በመቅሰፍቱ በዲያቢሎስ ቅንብር ሆዷ ውፍረትን መከታ እና ከለላ ተጠቅሞ ሳይታወቃት እየገፋ መጥቷል፡፡

እድላዊት ከወንድሟ ከተመስገን ፀንሳለች፡፡ በአንድ እንዴት ላረግዝ እችላለሁ?፡፡ ስታዝን ስትጨነቅ ዘጠኝ ወር ተቆጥሮ ቦርጩ ወደ ልጅ ተቀየረ፡፡ ወንድ ልጅ ከነ ቃጭሉ ተገላገለች፡፡ ግን ከፊቷ አሁንም የማይገፋ ከዳቢሎስ የተገነባ የጨለማ ተራራ ተጋርዶባታል፡፡

ምንጃር ሸንኮራ አውራጃ ውስጥ ነው፡፡ ጉራንባ ማርያም አካባቢ ያለ ማህበረሰብ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ናቸው፡፡ በእምነታቸው አክራሪና ከእምነት ውጭ ለሚከሰቱ ማንኛውም የክርስትና ጥፋት የፈፀመ ከማህበረሰቡ ይገለላል፡፡ እንደ እድር ፣ ባልትና እና ማህበር የመሳሰሉትን መካፈል አይችልም፡፡ በማህበረሱቡ የተጠላ ፤የማይወደድ ፣ ከሰው እንዳልተፈጠረ ከሰው ውጭ ተደርጎ ይቆጠራል።

እድላዊት እያወቀች ሳይሆን ሳታውቅ ከወንድሟ ከተመስገን መውለዷን ከያሬድ ውጭ ማንም አያውቅም፡፡

የወለደችውን ልጅ ክርስትና የሚነሳው የወላጅ አባት ስም ካልታወቀ መነሳት ፤ መጠመቅ የተወገዘና የተከለከለ ነው፡፡ የእድላዊት ልጅ ባለማወቅ አባት ታዲያ ማን ይሁን ? የማንስ ተብሎ ክርስትና ይጠመቅ ? አክ ተብሎ የተተፋ ምራቅ ተመልሶ አይዋጥ፡፡ የተመስገን ብትለው ለእሷ አንዴ ሞት ቢሆንም ለዘመዶቿና ለቤተሰቦቿ አስሬ ሞት ብቻ
ሳይሆን ከሰው እንዳልተፈጠሩና ወግ አጥባቂ የክርስትና አገልጋይ እንዳልሆኑ ከሰው ውጭ ተደርገው እንደሚገለሉ የሚታወቅ ለመሆኑ ጥርጥር የለውም፡፡

ታዲያ እድላዊት ይህ ሁሉ የታዘለባትን የጭንቀት እሳት ማማከር ያለባት ለወንድሟ ለተመስገን እንጅ ለማንም ማማከር እንደ ማይቻል ግልፅ ነው፡፡ ግን አሁንም ሌሊቱ ጨልሞባታል፡፡

"ምን እናድርግ ? የልጁ የክርስትና ቀን እየደረሰ ነው፡፡ እኔ ጨንቆኛል፡፡ የማደርገው ጠፍቶኛል፡፡ ከእንግዴህ ያለኝ አማራጭ መርዝ ጠጥቸ ወይም ታንቄ መሞት ነው፡፡ የወንድሜ ነው ብየ ክርስትና አላስነሳም፡፡ ምርር ብላ አለቀሰች፡፡

ተመስገን የእህቱ ጭንቀት በሱም ላይ ካደረበት እና ከሰነበተበት ቆይቷል፡፡ ጥሎ እንዳይጠፋ እድላዊትን ተመልሶ ዳግመኛ የማያገኛት መሰለው፡፡

እድላዊት እያለቀሰች መልስ እንኳን ሳይሰጣት ከያሬድ ጋር ደርሸ መጣሁ ብሏት ተነስቶ ወደ ያሬድ ቤት ሄደ፡፡

ተመስገን እንደደረሰ ከያሬድ ጋር የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋወጡ፡፡ ያሬድ ወደ እርሻ ሊሄድ ሞፈርና ቀንበር እያዘጋጀ ነው፡፡

"ወደ እርሻ ልትሄድ ነው እንዴ ሞፈርና ቀንበር የምታሰናዳው?" አለ ፤ ተመስገን፡፡

"አዎ፤ እንዴው ትንሽ የፋልማ መሬት ከሰም ነበረኝ፡፡ ቧጠጥ አድርጌያት ልምጣ ብዬ ነበር አነሳሴ፡፡ ስተረካከም እዚሁ እረፈደ ብሎ ወደ ቤት ግባ እንጅ አለው፡፡

"ኧረ አልገባም፡፡ አንተ ጋር ነበር የመጣሁት"፡፡

"ምነው በደህና ነው"? አለ ፤ ያሬድ፡፡

"ምን ደህንነት አለ ፤ ገና ስፈጠር የአርባ ቀን እድሌ በእሳት ተሞልቶ የእሳት እረመጡ ወደ ጭስነት ተቀይሮ የመውጭያ በር አጥቶ በቁሜ እያቃጠለኝ፡፡

"ምነው እድላዊት ሰላም አይደለችም እንዴ?፡፡

"አይ! ተወኝ ፤ አሁን የእድላዊት ነገር አስጨንቆኛል፡፡ የልጁ ክርስትና እየደረሰ ነው፡፡ የአባቱ ስም ካልታወቀ ክርስትና እንደ ማይጠመቅ አንተም ታውቃለህ፡፡

የማደርገው ሁሉ ግራ ገብቶኛል፡፡ ወንድሜ እባክህ ከዚህ ጨለማ አውጣኝ፡፡ ያላንተ ማንም የማዋየውና የማማክረው የለኝም አለው፡፡በሃዘን ተሞልቶ ፡፡

"በምን ልርዳህ የማደርገው ጠፍቶኝ እኮ ነው፡፡ እስከ አሁንም ዝም ያልኩህ እንጅ እኔ እንኳን ወደ አዲስ አበባ ይዘናት እንድንሄድ አስቤ ነበር፡፡ ግን ክርስትና ሳታስነሳ ከቤት መውጣት አይቻልም ብየ ነው፡፡ አሁን በምን ላግዛችሁ ? ንገረኝና በተቻለኝ አቅም ልሞክር አለ፡፡

በፊቱ ላይ ወርዶ ቡሃቃ ያስመሰለውን እንባ በለበሰው ፎጣ እየጠራረገ እኔማ ለመጥፋትም አስቤ ነበር፡፡ ግን እድላዊት ጥሎ የሚሄድ አንጄት አጣሁ፡፡ አሁን አንተን የማስቸግርህ ልጁ ክርስትና እስከሚነሳ ድረስ የአባቱን ስም በአንተ እናድርግና ክርስትና ከተጠመቀ በኋላ ፤ የተፈጠረውንና የተደረገውን ባለመተዋወቅ እንደ ሆነ ለቤተሰብ እንነግራለን አለ፤ ተመስገን ፡፡ ደፍሮ በመናገሩ አይኑን ላለማየት አቀርቅሮ መሬት መሬት እያየ፡፡

የልጁ አባት ሆኘ ክርስትና ቢጠመቅ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ግን የአካባቢያችንን ባህል እንደምታውቀው በሚስቱ ላይ ዲቃላ ወልዷል ተብየ እኔ ከማህበረሰብ እንደምገለል፡፡ ደግሞም ባለቤቴ ይህንን ስሰማ በእኔ ላይ ዲቃላህን ታንጠባጥባለህ ብላ ባዶቤት ዘግታብኝ ትሄዳለች አለ ፤ ያሬድ፡፡

"ያልከው ሁሉም ይገባኛል፡፡ ግን ከወንድሟ ወለደች ቢባል ምን ያህል እንደሚከብድ መገመት አያቅትህም፡፡ ደግሞ አባታችን በዚህ ቦታ ወግ አጥባቂ እንደ ሆነ ታውቃለህ፡፡

እባክህ! ያሬድ ስለፈጠረህ አምላክ! ተለመነኝ ሳላውቅ እንደ ሆነ እሳት ውስጥ የገባሁት አንተም ታውቃለህ፡፡ ሚስጥሩን ለባለቤትህ እንነግራታለን፡፡ መጀመሪያ አንተ ብቻ እሽ በለኝ፡፡ እያለቀሰ ተማፀነው፡፡

ያሬድ የሚለው ሁሉ ጨነቀው፡፡ የእድላዊትና የተመስገን ስቃና መከራ የሱም ሆነ፡፡ ክርስትናው እስከሚያልፍ የልጁ አባት ለመሆን ብቻውን መወሰን አልቻለም፡፡

"ለማንኛውም አበበችን አብረን ሚስጥሩን እናካፍላትና እሷ እሽ ካለች የእኔ አያስቸግርም፡፡ አይቻልም ካለች ግን ምንም ላደርግ አልችልም" አለው

"እሽ አንተ እንዳልክ" ብሎት ወደ ቤት ገቡ፡፡

"ደህና አደርሽ አበበች" ? አለ ፤ ተመስገን፡፡

"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርክ ተመስገን" ? አለች ፤ አበበች፡፡

ጉንጮቹ አብጠው ገና በጥዋቱ አይኖቹ ቀልተዋል፡፡

ምነው ደህና አይደል ይሆን ? ያለቀሰ ይመስላል፡፡ የሞተ ሰው ይኖር ይሆን ? ያሬድም ደስተኛ አይመስልም፡፡ ዛሬ ምን ተፈጥሮ ይሆን ? አበበች ከውስጧ ሳታወጣና ሳታሰማ የተናገረችው ነበር፡፡

ምን ብሎ እንደሚነግራት ግራ ተጋብቷል፡፡ የቤቱን ጣራ ጣራ እየተመለከተ እንባው በጉንጩ ላይ ይወርዳሉ፡፡ አንገቱን ዞር አድርጎ ለመጥረግ ሞክረ፡፡

አበበች ግን ገና ሲገባ አንስታ እየተመለከተችው ነበር፡፡

"ምነው ደህና አይደለህም እንዴ? የምታለቅሰው" አለች ፤ ለተመስገን፡፡ የተፈጠረውን ለመስማት እየተጨናነቀች፡፡
ተመስገን ከተቀመጠበት ብርጩማ ላይ ተነስቶ ምንም በማታውቀው እና ምንም ባልሰማችው አበበች እግር ላይ ተደፋ፡፡ እባክሽን ከጉድ አውጭኝ ፤ በምትወጅው ልጅሽ ፤ በምትኩ ስም እለምንሻለሁ እያለ ያለቅስ ጀመር፡፡

አበበች ተመስገን ስለምን እንደሆነ የሚያወራው ግራ ተጋብታለች፡፡ ሲለምናትና ሲማፀናት ገና ባልሰማችውና ባላወቀችው ቀላል ነገር መስሏት እሽ፡፡አሁን ተነስ ብላ ካስነሳችው በኋላ፤ ምንድ ነው እሱ የቸገረህ"? አለችው፡፡ ተነስቶ ወደ ነበረበት የብሩጩማ ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡ አሁንም ከየት መጀመር እንዳለበት ግራ ቢገባውም መንፈሱ ብትጨነቅም ሚስጥሩን ለአበበች ካላካፈለ መፍትሄ ስለማያገኝ ደፍሮ መናገርና መተንፈስ አለበት፡፡ ራሱን አፅናንቶ ለመናገር ወሰነ፡፡
👍536
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
==================

ሰሎሜ አላዛር ሱቅ መስራት ከጀመረች ከከስድስት ወር በኃላ
እለቱ ሰኞ ነው፡፡የሳምንቱ መጀመሪያ፡፡አላዛር ድንገት ተከሰተና ሱቁን ዘግተው እንዲወጡ አደረገ፡፡ቀጥታ ወደ መዝናኛ ቦታ ወስዳት፡፡ሲዝናኑ አመሹና አረፍ ብለው እየተጫወቱ ሳለ፡፡
‹‹አንድ ሰዓት ሆነ እኮ ወደቤት አንሄድም እንዴ?፡፡››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ወደቤት ስትይ?››
‹‹እንዴ ምኑ ነው ያልገባህ…?ወደየቤታችን ነዋ!!››
‹‹ቤት እንደገዛው ነግሬሻለሁ አይደል?››አላት
‹‹አዎ..በጣም ደስ ብሎኛል..በአጭር ጊዜ ስኬታማ እየሆንክ ነው..ጠንካራ ሰራተኛ ስለሆንክ ይገባሀል፡፡››
‹‹አይ ጠንካራ ሰራተኛ ስለሆንኩ ብቻ አይደለም የተሳካልኝ..እድለኛም ጭምር ስለሆንኩ ነው፡፡አያቴ ያወረሰቺኝ ገንዘብ …ቀላል አልጠቀመኝም..ይሄንን የኮንስትራክሽን ስራ ከጀመርኩ በኃላ ደግሞ አሪፍ የተባሉ ሶስት ፕሮጀክቶችን አገኘሁ…ረጅም አመት በስራው የቆዩ ኮንትራክተሮች እንኳን ይሄንን ያህል ስራ በቀላሉ አያገኙም፡፡››
‹‹ቢሆንም ያገኙትን እድልም በስርአት መጠቀምና ውጤታማ መሆንም እኮ ትልቅ የጥንካሬ ምልክት ነው፡፡››
‹‹እዛ ላይ እንኳን ትክክል ነሽ…ያገኘሁትን እድል ላለማባከን የተቻለኝን ሁሉ ከማድረግ አልሰንፍም››አላት በእርግጠኝነት፡፡
‹‹አዎ…ታዲያ እቤቱን መች ነው የምታሳየን?››
‹‹አሁን ጥቂት የሚስተካከሉ ነገሮች ስላሉ እያሳደስኩት ነው…እንዳለቀ ወስጄ አሳይሻለሁ››ሲል ቃል ገባላት፡፡
‹‹እና ሲያልቅ ጎረቤታችንን ልናጣ ነዋ፡፡››አለችው
‹‹ማለት?››
‹‹ያው ኮንደሚኒዬሙን ለቀህ ..አዲሱ ቤትህ ስትገባ ጓረቤት መሆናችን ይቀራል ማለቴ ነው››
‹‹አይ ..እንደዛ እንኳን አላደርግም..እሺ ካልሺኝ አብረን እንገባበታለን…ካልሆነም እሱን አከራይቼ እዛው ጎረቤትሽ ሆኜ መኖሬን ቀጥላለሁ፡፡››ብሎ ያልጠበቀችውን ነገር ነገራት፡፡
‹‹አልገባኝም…እኔ ደግሞ ለምንድነው አብሬህ የምገባው?››
‹‹አንድ ወንድና ሴት አንድ የጋራ ቤት ውስጥ ለምንድነው አብረው የሚገቡት?››ሲል መልሶ ጠየቃት፡፡
‹‹ቆይ ቆይ…..እየጀነጀንከኝ ነው እንዴ?››
‹‹ከተሳካልኝ አዎ››
‹‹ይገርማል ከዚህ ሁሉ አመት መጓተት በኃላ ድንገት ምን ተፈጠረ?››
ወደልቡ በሌባ ጣቱ  እየጠቆመ ‹‹ሁሌም ሀሳቡ እዚህ ውስጥ ነበር ..ልዩነቱ አሁን ከአንደበቴ ምውጣቱ ነው››አላት፡፡
‹‹ቀልድ ጨምርሀል…ባይሆን አንዷን ጥበስና ደግሼ ልዳርህ!››
‹‹አይ ይቅርብኝ ..እኔ አንቺን ማግባት ካልቻልኩ እስከወዲያኛው መመልኮስ ነው የምፈልገው፡፡››
በድንጋጤ አፏን በመክፈት አፍጥጣ አየችው›‹‹እየቀለድክብኝ ነው እንዴ?››
‹‹አረ የምሬን ነው››
‹‹እኔን ጓደኛህን ማግባት ትፈልጋለህ?››
‹‹አዎ በደንብ፡፡››
‹‹ለምን? ››
‹‹ስለማፈቅርሽ ነዋ!!››
‹‹ከመቼ ጀምሮ››
‹‹እኔ እንጃ …ነፍስ ካወቅኩበት ጊዜ ጀመሮ አንቺን እንደማፈቅቅር ነው የማውቀው››
‹‹ይሄኔ ነው መሸሽ….እና እስከዛሬ ለምን ሳትነግረኝ?››
‹‹ስለምፈራሽ..ዛሬ እራሱ እንዴት እንደነገርኩሽ አላውቅም…››
ዝም አለችው…ምን እንደምትለው ምንም ሀሳብ አልመጣላትም..አስባበት ስለማታውቅ በእሷ በኩል ለእሱ ተመሳሳይ ስሜት ይኑራት ወይስ አይኑራት ማወቅ አልቻለችም፡፡
‹‹በል… አሁን ተነስ እንሂድ፡፡››
‹‹እሺ›› ብሎ …ከተቀመጠበት ተነሳ ና ተከተላት፡፡
ለሶስት ወር ያህል በጉዳዩ ላይ መልሰው በማንሳት አልተነጋሩበትም ነበር…
ከሶስት ወር በኃላ ሱቅ ስራ ላይ እያለች ስምንት ሰዓት ላይ መጣና ‹‹ሱቁን እንዝጋውና ..የሆነ ቦታ እንሄዳለን››አላት፡፡
‹‹የት?››
‹‹ሰርፕራይዝ ነው፡፡››
ተስማማችና ሱቁን አብረው ዘጋግዘው  በፒካፕ መኪናው ተያይዘው ሄዱ…ወደ ላፍቶ ነው የወሰዳት ፡፡አዲስ የገዛው አፓርታማ ቤት ውስጥ ነው ይዞት የገባው……ሙሉ ዕቃው የተሞላ እጅግ ውብ ቤት ነበር፡፡
‹‹ይሄ የእኔ ቤት ነው እንዳትለኝ?››አለችው በመደነቅ ፈዛ፡፡
‹‹አይ የእኔ አይደለም የእኛ ቤት ነው፡፡››
‹‹በጣም እኮ ነው የሚያምረው፡፡››
‹‹ስለወደድሽው ደስ ብሎኛል፡፡››
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ ..?እንዴት ላልወደው እችላለሁ? ቤተ መንግስት እኮ ነው የሚመስለው፡፡››
‹‹እንግዲህ እንዳልሺው ቤተ መንግስት ከሆነ ንግስት ይፈልጋል ማለት ነው፡፡››
‹‹እሱን ጫወታ ለጊዜው ትተን ሁሉንም ክፍል እየዞርን እንየው፡፡››
‹‹ይቻላል››ብሎ እየመራ ወደፎቁ ይዞት ወጣ፡፡ንግግሩን ጠንከር ብላ ስላልተቃወመችው ደስ ብሎታል፡፡ፈፅሞ ጥያቄው  እስከወዲያኛው ላለመቀበል ወስና ቢሆን ኖሮ ቁርጥ አድርጋ ምንም አንደበቷን ሳያደናቅፋት ‹‹አይሆንም ››ትለው ነበር፡፡አሁን ግን …ለጊዜው  እንተወው ››ነው ያለችው፡፡
//
እቤቱን ወስዶ ካስጎበኛት ከ15 ቀን በኃላ ድንገት‹‹በሚቀጥለው ሳምንት እቴቴ ጋር ሽማግሌ ልልክ ነው››ብሎ አስደነገጣት፡፡
‹‹ምን?››
‹‹አዎ …ሽማግሎዎችን አነጋግሬ አዘጋጅቼዋለሁ..በኃላ አዲስ እንዳይሆንብሽ ብዬ ነው አሁን የነገርሽው፡፡››
‹‹ያምሀል እንዴ…?እኔ መች እሺ አልኩህና ነው ሽማግሌ የምትልከው?፡፡››
‹‹ችግር የለውም…ሽማግሌ እልካለሁ…የማትፈልጊ ከሆነ ከእናትሽ ተማክረሽ ለሽማግሌዎች አይ አልፈልገውም ማለት ትቺያለሽ፡፡››
‹‹እንደዛ ብል እና በሽማጊሌዎች ፊት መዋረድ አይሆንብህም››
‹‹ግድ የለኝም….ዋናው አንቺን ለማግኘት ከልቤ መሞከሬ ነው፡፡››
‹‹ከዛ በኃላ ግን እዚህ  መስራት አልችልም…››
‹‹እ ..እሱን በተመለከት በውሳኔሽ ተፅእኖ እንዳያሳድርብስሽ ስለፈለኩ ቅድመ ዝግጅት አድርጌለሁ፡፡››
‹‹የምን ቅድመ ዝግጅት?››
ፊት ለፊቱ ያለውን አጀንዳ አንሳና…‹‹ይሄንን ዝርዘር ተመልከችው..እዚህ ሱቅ ውስጥ ያለው እቃ  ነው፡፡ይሄ ደግሞ ውል ነው..ይሄንን ሱቅ ከአሁን ወዲያ አልፈልገውም….ሁሉንም ዕቃ ትረከቢኝና ቀስ እያልሽ በሁለት አመት ውስጥ ትከፍይኛለሽ…ይሄ ማለት ይሄንን ውል ከፈረምሽ በኃለ የእኔ ሰራተኛ አይደለሽም ማለት ነው፡፡የራስሽን ንግድ ፍቃድ አውጥተሸ በራስሽ መስራት ትቀጥያለሽ ማለት ነው፡፡እናም ያ ማለት እንደከዚህ ቀደሙ በፈለኩ ጊዜ ወደሱቅሽ ዘው ብሎ መምጣትና ወደውስጥ ዘልቆ መግባት አልችልም ማለት ነው….እና ሽማግሌዎች ሲመጡ አሺ አገባዋለሁ ብትይም አላገባውም ብለሽ ብትነግሪያቸውም፤ከዚህ ሱቅና ከስራሽ ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም፡፡በይ ቸው››ብሏት ጥሎት ወጥቶ ሄደ፡፡
እንዳለው በሳምንቱ ሽማግሌ ላከ ….በሚቀጥለው እሁድ ተመልሰው እንዲመጡና መልሳቸውን የዛን ጊዜ እንደሚያገኙ ተነገራቸው፡፡የሰሎሜ እናት እቴቴ አንድ ብቸኛ ልጇን አስቀምጣ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ልጄ ለመሆኑ ከአላዛር ጋ መቼ ነው የጀመራችሁት?››
‹‹ምንድነው የጀመርነው?››
‹‹ሽማጊሌ ልኮ እያየሽ ምን ትይኛለሽ እንዴ?››
‹‹አይ እቴቴ..እንደሚወደኝ ነገረኝ እንጂ ምንም የጀመርነው ነገር የለም …መልስ እንኳን አልሰጠሁትም፡፡››
‹‹ለምን?››
‹‹እኔ እንጃ እያሰብኩበት ነበር፡፡››
‹‹ምንድነው የምታስቢው…አትወጂውም?››
‹‹እኔ እንጃ… የምወደው ይመስለኛል፡፡››
‹‹አዎ ..እኔም ምትወጂው ይመስለኛል፡፡››
ሰሎሜ በእናቷ ንግግር ተገርማ‹‹እንዴት የምወደው ሊመስልሽ ቻለ?››ስትል ጠየቀቻት፡፡
‹‹ባትወጂውና ባትፈልጊው ኖሮ ወዲያውኑ ነበር አልፈልግም ብለሽ መልስ ምትሰጪው….እንደሚወድሽ ከነገረሽ ቀን አንስቶ እስከዛሬ ጉዳዩን እያብላላሽውና  እያሰብሽበት ከሆነ ሌላ ምንም ትርጉም ልሰጠው አልችልም፡፡››
👍6514😁8
#አላገባህም


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////
ሚካኤል ከወህኒ ቤት እንደመጣ ቀጥታ ወደሰፈር ነው ያመራው፡፡ወደቤት ሲገባ አዲስ አለም ከልጇ ጋር እየተዳረቀች ሳሎን ውስጥ ቢያገኛትም ማንኛቸውንም ምንም ሳያናግር ቀጥታ ወደመኝታ ቤት ነበር የተንደረደረው፡፡

‹‹ሚኪ…ምን ሆነሀል.?.ዛሬ ደግሞ ሰላምታ የለም እንዴ?››

‹‹መጣሁ..››ብሎ ብቻ  ወደመኝታ ቤት ገባ…አባቱ የነገሩትን ፎቶ ከግድግዳ ላይ አነሳ ..ከግድግዳው ጋር ተመሳስሎ የተሰራ ነው…በቀላሉ በእጅ የሚፈረከስ አይነት አይደለም…ከእንደገና ተነደርድሮ ወጣና በጓሮ በኩል ወደ ገራጅ በመሄድ መዶሻ እና መሮ  ይዞ መጣ….‹‹አዲስ አለም ቅዱስን ከወለሉ ላይ አንስታ አቀፈችውና ወደመኝታ ቤቱ ተንቀሳቀሰች…እሷ ከመድረሷ በፊት ሚካኤል ወደውስጥ ገብቶ ከውስጥ ዘጋባት

‹‹እንዴ ሚኪ….ምን እየሆንክ ነው…?ለምንድነው የምትዘጋብን?››

‹‹አዲስ..እባክሽ ጥቂት ደቂቃዎችን ስጪኝ……››ብሎ መሮውንና መዶሻውን በመጠቀም  ግድግዳውን መቆርቆር ጀመረ…ግድግዳ ውስጥ የተቀመጠውን የአባቱን ሚስጥራዊ እቃ ለማግኘት 3 ደቃቃ ያህል ፈጀበት…በላስቲክ በስነሰርአት የተጠቀለለ ነው፡፡አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠና የላስቲኩን እሽግ ፈቶ አልጋው ላይ ዘረገፈው፡፡….አምስት የሚሆኑ ፎቶዎች አንድ ሜሞሪ ካርድ  ..አንድ ደብዳቤ ነው፡፡፡

መጀመሪያ ፎቶዎቹን አነሳና ተራ በተራ መመልከት ጀመረ…የመጀመሪያው ፎቶ ላይ  አናትዬው የሆነ ሰው ክንድ ላይ ተደግፋ በፈገግታ ስትፍለቀለቅ ይታያል..ጭንቅላቱን የሆነ መርፌ ነገር ጠቅ አደረገው….ይሄ ሰው በህይወት ዘመኑ አይቶት አያውቅም…የእናቱን ዘመዶች ሁሉንም ያውቃል…ታዲያ ይሄ ማን ነው?፡፡ሁለተኛውን ፎቶ  ገለጠና ተመለከተ…እናትዬው እነሱን ከመውለዷ በፊት ገና ጨቅላ ወጣት ሆና የተነሳቸው ፎቶ ነው..ግን አሁንም ያው ሰው አንገቷ ላይ ተጠምጥሞ በፍቅር ጉንጯን ሲስማት ይታያል…ፎቶውን ገለበጠው…ልቅም ባለ የእጅ ፅሁፍ በአንድ መስመር የተፃፈ ፅሁፍ አለ ‹‹ንጥፍ ወርቅ ፍቅሬ በጣም አፈቅርሻለው….ያንቺው ለሚ በቀለ፡፡››ይላል፡፡
ሁሉንም ፎቶዎች በየተራ እየገለባበጠ ተመለከተው…ተመሳሳይ የሁለቱ ፎቶ ነው…ሲላፉ ሲሳሳሙ….ሲጎራረሱ የተነሱት ፎቶ ነው፡፡
ቤታቸው የወላጆቻቸውን ትዝታ የሚዘክሩ ሁለት ግዙፍ የፎቶ አልበሞች እዳሉ ያውቃል….እናትና እህቱ በአሰቃቂ ሁኔታ ከሞቱ በኃላ በጣም ሲከፋውና ትዝ ሲሉት ለብቻው ክፍል ዘግቶ ተደብቆ  ይመለከት ነበር፡፡እና እዛ አልበም ውሰጥ ዘጠና ፐርሰንት ፎቶ የእሱና የእህትና ወንድሙ ፎቶዎች ፤የበዓል ዝግጅት ፤ የህፃናቱ የልደት በዓል ማስታወሻ ናቸው የሞሉት..እናትና አባቱ በልጆቹ የደስታ ድባብ ውስጥ እንደድምቀት እዚህም እዛም ጣል ተደርገው የተነሱት ነው እንጂ እንዲህ እናቱ ከሌላው ሰውዬ ጋር እንዳደረገችው አይነት አማላይ ፎቶዎች ተነስተው አላየም፡፡

ፎቶውን አስቀመጠና ወረቀቱን አንስቶ አነበበው…
ይድረስ ለምወድሽ ፍቅሬ ንጥፍ ወርቅ …
ይህንን ደብዳቤ ስፅፍልሽ ከአይኖቼ እንባ ሳይሆን ደም እያፈሰስኩ ነው፡፡  ታውቂያለሽ እኔ ከኤለመንተሪ ጀምሮ በጣም ነው የማፈቅርሽ..አንቺም እንደምታፈቅሪኝ አውቃለው፡፡ብዙ አቅድና ብዙ ፕሮግራም ነበረን፡፡በቅርብም ለመጋባት ተነጋግረንና ተማምለን ነበር፡፡አሁን ግን ያንን ቃሌን ማክበር አልችልም፡፡አባዬ ምን ያህል ኃይለኛ እና ጥብቅ ሰው እንደሆነ ታውቂያለሽ  ..አሁን አሜሪካ ካለው ወንድሙ ጋር ተነጋግሮ አሜሪካ እንድሄድ ወስኖ ሁሉም ፕሮሰሶች ጨርሶ ሊልከኛ ነው…ማለቴ… አሁን ይሄ ደብዳቤ ሲደርስሽ ምን አልባት እኔ በርሬም ሊሆን ይችላል፡፡

ይቅር በይኛ…..ያንቺው  ለሚ በቀለ፡፡ይላል
እዛ ደብዳቤ ላይ ብዙ የተንጠባጠቡ የእንባ ጠብታዎች ይታያሉ፡፡ሚካኤል ያየውም ሆነ ያነበበው ነገር  ምንም እየገባው አይደለም..ከውጭ ደግሞ አዲስአለም የመኝታ ቤቱን በራፍ እየቆረቆረች እየረበሸችው ነው፡፡ከተቀመጠበት ተነሳና ሄዶ በራፉን ከፈተ፡፡ በራፉ ላይ ልጇን አቅፋ ተገተትራ በድንጋጤ በድን የሆነችውን አዲስ አለም ላይ አፈጠጠባት፡፡

‹‹አዲስ ምንድነው?››

‹‹እንዴት መኝታ ቤቱን በላይህ ላይ ዘግተህ ምን እያደረክ ነው?››በስጋትና በፍራቻ ተወጥራ ጠየቀችው፡፡

‹‹ኡፍ …ስራ ይዣለሁ ስልሽ አትሰሚም…..ባክሽ አትረብሺኝ››በማለት አንቧረቀና መልሶ ዘጋባት፡፡ከዛ  ወደአልጋው ተመለሰ፡፡አዲስአለም በመጀመሪያ ከደነገጠችውን  በላይ ደነገጠች…ሚካኤል ምንም ባልገባት ነገር እንዲህ አመናጭቋት አያውቅም፡፡

ወደሳሎን ተመለሰችና ፀአዳ ጋር ደወለችላት፡፡
ስታወራ ድምፃ ይንቀጠቀጣል‹‹ሄሎ ፀዲ..አሁኑኑ ወደቤት ነይ››
‹‹እንዴ ምን ሆንሽ..?

ቅዱስ አመመው እንዴ?››
‹‹አይደለም..አባትዬው ነው፡፡››

ፀአዳ በጣም ደነገጠች‹‹እንዴ  ሚኪ ምን ሆነ?››

‹‹እኔ እንጃለት… ቅድም አንቺ ጋር የመጣሁ ጊዜ አባቱን ለመጠየቅ ወህኒ ቤት ሄዶ ነበር…ከዛ ሲመለስ እንደእብድ አድርጎት መኝታ ቤቱ ገባ..ከዛ ወጣና መዶሻና መሮ ይዞ ገብቶ በራፉን ከውስጥ በመዝጋት ግድግዳውን ሲነድለው ነበር…አንኳኩቼ ምን እንደሆነ ስጠይቀው አጓርቶብኝ መልሶ ዘጋው…እህቴ ቶሎ ድረሺኝ…የቀትር ጂኒ ሳያጠናግረው አይቀርም››

‹‹ስለአባቱ መጥፎ ነገር ሰምቶ ይሆን እንዴ?››

‹‹መሰለኝ….ወይ በፈጣሪ ምን አልባት እዛ ሲደርሰ ገድለዋቸው እንዳይሆን ነው የምፈራው..እንደዛ ቢሆንስ በራፍ አስዘግቶ ግድግዳ ያስንዳል እንዴ…?››

‹‹በቃ መጣሁ ..እስከዛው ተረጋጊ››አለቻትና ስልኩን ከመዝጋቷ በፊት ቦርሳውን አንጠለጠለችና መንገድ ጀመረች፡፡

ሚካኤል ሜሞሪውን አነሳና ስልኩ ውስጥ ከተተው፡፡ሁለት ፎልደሮች  አሉት፡፡አንደኛውን ከፈተ ….በምስሉ በቅድሚያ ምትታየው እናቱ ነች፡፡አዎ ቡቲክ ቤታቸው ውስጥ ሆና ልብሶችን ሰታስተካከል ይታያል…ወዲያው አንድ በእሷ እድሜ ያለ ሰው  መጣ …የሰውዬው ጀርባው ነው ሚታዬው እናትዬው ግን በሰውዬው መምጣት ስትደነግጥ ይታያል፡፡

‹‹ለሚ እንዴት መጣህ?››አገላብጣ እየሰማችው ትጠይቀዋለች፡፡

‹‹እንዴት መጣህ ነው እንኳን ደህና መጣህ ነው የሚባለው?እዚህ ስብሰባ ነበረን …ሳላይሽ ተመልሼ መሄድ አልቻልኩም›››

‹‹እንዴ ከሶስት ቀን በኃላ ቀጠሮ ነበረን እኮ…››

‹‹እሱም እንዳለ ነው…ግን እኔ እኮ በየቀኑ ላገኝሽ ነው የምፈልገው…እንደውም ሙሉ በሙሉ የእኔ እንድትሆኚ ነው የምፈልገው፡፡››

‹‹እሱንማ አስረግዘኘኝ  ጥለኸኝ አሜሪካ ከመሄድህ በፊት   ማሰብ ነበረብህ፡፡››

‹‹ይሄንን እኮ ብዙ ጊዜ  ተነጋግረንበት  ሁኔታውን አስረድቼሽ ይቅር ብለሽኛል..አይደል እንዴ የእኔ ፍቅር?››

‹‹አዎ ግን …ይቅር አልኩህ ማለት ለአመታት የገነባሁት ትዳሬንና ልጆቼን በትኜ ወደአንተ ለመመለስ እፈልጋለው ማለት አይደለም፡፡››

‹‹ልጆችሽን በትኚ አልልኩም እኮ ….ባልሽን ፍቺና ልጆቹን ይዘሽ ነይ ነው፡፡›››

‹‹አይ ያንን ሳደርግ ቅጣው እጁን አጣጥፎ የሚቀመጥ ይመስልሀል….?እሱ ምንም እንከን የማይወጣለት ድንቅ አባትና ምርጥ ባል ነው፡፡ልጆቹን እንዴት እንደሚወድ እና እንዴት እንደሚንከባከብ ብታውቅ እንዲህ ለማለት አትደፍርም..በተለይ ትርሲትን በልዩ ሁኔታ ነው የሚወዳት…ሲጠራት እኮ እናቴ ነው የሚላት…እሷስ ብትል..?››

‹‹ግን እውነተኛ ልጁ አይደለችም…ትርሲት የእኔ  ልጅ ነች፡፡››

ሚካኤል በሚሰማው ነገር ሆዱ ሲገለባበጥ ይታወቀዋል…አረ እንደውም ሊያስታውከው እየተናነቀው ነው፡፡

‹‹አረ ድምጽህን ቀንስ..ድንገት ሰው ቢሰማህስ?››
👍6312
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰተ_በዘሪሁን_ገመቹ
___
//

ዛሬ ጠዋት ሎዛን  ከስራ መባረሯን ለመናገር ፀጋን ይዛ  ወደ ፋውንዴሽን ቢሮ ሄዳ ነበር፡፡
የሎዛ ክህደት አሁንም እያመማት ነው፣እሷን በመገላገሏ ደስ ብትሰኝም ከእስከአሁኑ  በባሰ ሁኔታ፣ የስራ ጫናው ሊጠነክርባት እንደሚችል ተሰምቷታል።እሷ የምትፈልገውን ስራ በእቅዳቸው መሰረት እንዲከወንላት ከፈለገች  ሁለት ተጨማሪ ጥንድ እጆች፣ አይኖች እና ጆሮዎች ያስፈልጋታል።

ራሄል በቁጭት እና በንዴት ቢሮ ቁጭ ብላ ከሮቤል ጋር እያወራች ነው፡፡

‹‹ ሮቤል በሆነው ነገር በጣም አዝኛለው…የማፍያ ፀባይ ካላቸው የበጎ አድራጎት ድርጅተች ጋር ተመሳጥራ በእኔ ድርጅት ስም ልትዘረፍ ስትል ነው የያዝኳት››

‹‹አዎ..ከዚህ በፊት የምታደርጋቸው አንዳንድ ሁኔተዎች ሳላላማሩኝ ጥንቀቄ እንድታደርጊ ጠቆም አድርጌሽ ነበረ….ይመስለኛል እንደቁምነገር ወስደሸሽ አላዳመጥሽኝም››

‹‹አዎ ትክክል ነህ…በጣም እኮ ነበር የማምናት››

‹‹ለማንኛውም ከፍተኛ ኪሳራ ሳታስከትል በጊዜ ስለደረሽባት ጥሩ ነገር ነው….ለወደፊቱ ትምህርት ይሆንሻል››አላት፡፡

‹‹ አዎ ትክክል ነህ…ለማንኛውም አሁን ሌላ ጎበዝ እና ታማኝ ረዳት ማግኘት አለብኝ ፡፡››

‹‹ያንን ስራ በንዑስ ኮንትራት  ማሰራት የሚሻል  ይመስለኛል››የሚል ምክር ሰጣት፡፡

‹‹አይ ይህ በራሴ ማድረግ አለብኝ።ብቻ በፋውንዴሽኑ ላይ ሌላ ጉዳት እንዳላደረሰች ተስፋ አደርጋለሁ።››

የቢሮውን ስራ ለሮቤል በአደራ ሰጥታ ፀጋን ይዛ ከቢሮ ወጣችና  ወደሆስፒታል ነው የሄደችው፡፡ፀጋ ታማ ሳይሆን መደበኛ ክትትል የምታደርግባትን ቀን ስለሆነ  ነበር ወደ ሆስፒታል የወሰደቻት..ከዛ በኋላ ነው ወደቤታቸው የተመለሱት፡፡

ራሄል በምትወደው ሶፋ ላይ ተቀምጣ  ትራስ በመደግፋ ወረቀቶች እያገላበጠች ሳለ ስልኳ ጠራ..አነሳችና አየችው፡፡አባቷ ናቸው፡፡በጭኗ ላይ ያሉትን ወረቀቶች ማገለባበጧን ሳታቆም  አባቷን ማውራት ጀመረች፡፡

‹‹አባዬ እንዴት ነህ..እማዬስ?››

‹‹እናትሽ በጣም ቆራጥ ነች እና ዶክተሮቹ በጤናዋ መሻሻል  በጣም ተደስተዋል.››አላት አባቷ፡፡

‹‹ደስ ብሎኛል አባዬ..እኛጋም ነገሮች ጥሩ ናቸው….ስራዬንም ወደቤት አዘዋውሬ አንተ ቢሮ ስሰራ ነው ምውለው››

‹‹አንዳንድ ስራዎችሽን አሁን ለቀጠርሻቸው ረዳቶችሽ መስጠት አልቻልሽም?››ሲሉ ጠየቋት፡፡
ስለ ሎዛ እስካሁን አልነገረቻቸውም። አሁን በትከሻቸው ላይ ምንም ተጨማሪ ሸክም ልትጭንባቸው አልፈለገችም።

‹‹አባዬ ስራውን ለሌሎች ለማከፋል እየሞከርኩ ነው..ቢሆንም ታውቃለህ አመታዊው የገቢ ማሰባሰቢያ በአላችን እየደረሰ ነው..በዚህ ጊዜ ስራ ይበዛብናል›› አለች.፡፡

‹‹በዛ ላይ እህትሽን መንከባከቡ በጣም ፈታኝ ስራ ነው››
‹‹ኖ…ኖ አባዬ….አሁን ከእህቴ ጋር በጣም እየተግባባን ስለሆነ ነገሮች የምታስበውን ያህል ከባድ አይደሉም…እናንተ ምንም አታስቡ››

‹‹ይሁን ልጄ…በጣም ነው የምኮራብሽ››

‹‹አመሰግናለው አባዬ…ለመሆኑ ዶክተሮቹ እናቴ ከሆስፒታል መች ትወጣለች ብለው ያስባሉ?››

‹‹ግምቱን አሻሽለዋል፤ከአሁን በኋላ ቢያንስ ሁለት ሳምንት ሳያቆዬት አይቀርም፡፡ ከፀጋ ጋር መነጋገር እችል ይሆን?››

‹‹ይቅርታ አባዬ አሁን ተኝታለች ››
.የእለቱ ተግባራቸውን ሁሉ አከናውነው  ወደ ቤት እስኪመጡ ድረስ የፀጋ ባህሪ  ከንጭንጭ የራቀና   በፈገግታ የተሞላ ሆኖ በመታየቱ አመስጋኝ ነበረች። ግን ወደቤት ከተመለሱ በኃላ መነጫነጭ ጀመረች ከዛ ሰውነቷን አጥባ እራቷን ካበላቻት  በኋላ አልጋ ላይ አስቀመጠቻት… ከዛ  ትንሿ ልጅ በሰከንዶች ውስጥ ተኛች። ይህም ራሄል ምስኪኗን ልጅ ከወዲህ ወዲያ እያሽከረከረች ስታንገላታት ስለዋለች  የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማት አድርጎታል።..እና አሁን ልትቀሰቅሳትና የበለጠ ልታበሳጫት አልፈለገችም፡፡
አባቷን ለተጨማሪ ጥቂት ደቂቃዎች አወራቻቸው፣ አባቷን ስትናገር እንኳን ስራዋ እያንገበገበባት ነበር ..ትኩረቷን የሚከፋፍልባት ምንም ነገር ባይኖር ደስተኛ ነች  ።ወዲያው ሌላ ስልክ ተደወለላት.. ቃተተች እና ማን እንደሚደውል ሳታረጋግጥ አነሳችው..ቁጣ በሚመስል የድምፅ ቃና  ‹‹ራሄል ነኝ.››አለች

‹‹ሄይ ራሄል… እንዴት ነሽ?››ዔሊያስ ነበር…ፍስስ የሚለውን   ድምፁን ስትሰማ ብስጭቷን አቃለላት። ራሄል ዛሬ ወደቤት ከተመለሰች  በኋላ ዔሊን ለማየት ፈልጋ  ከአሁን አሁን በራፉን ያንኳኳል እያለች  በናፍቆት ስትጠብቅነበር፡፡

‹‹ስልክሽ ለረጅም ጊዜ ተይዞ ነበር››

‹‹ከአባቴ  ጋር እያወራው ነበር ››አለችው።

‹‹ነገሮች እዛ እንዴት እየሄዱ ነው…?ሄጄ ካየዋቸው እኮ ሳምንት ሊያልፈኝ ነው››

‹‹እናቴ ጥሩ እያገገመች ነው። ግን እስከሚቀጥሉት  ሁለት  ሳምንታት ወደ  ቤት እንደማትመጣ ነው የሰማሁት››

‹‹አይዞሽ…ዋናው የመዳን ሂደታችው እድገት እያሳየ መሄዱ ነው››

‹‹እሱስ እውነትህን ነው….ታዲያ አሁን  ምን እያደረክ ነው? ››ብላ ጠየቀችው

‹‹ምንም…ሶፋዬ ላይ ጋደም ብዬ ስለአንቺና ስለፀጋ እያሰብኩ ነበር››አላት፡፡

ደስ አላት‹‹እየፎገርክ ነው?››

‹‹አረ እውነቴን ነው…መቼስ ማል አትይኝም››

‹‹መምጣት ትፈልጋለህ?›› ቃላቶቹ ድንገት ነው ከአንደበቷ ያመለጧት….የአእምሯዋን ሳይሆን የልቧን  ምኞት ነው አንደበቷ ያሳበቀባት….

‹‹ከስራ ከወጣው በኋላ ከሶስት ጊዜ በላይ ልመጣ ተነስቼ ነበር ከዛ ‹‹አረ ኤልያስ እግርና አብዝተሀል…..ሰዎቹን እያጨናነቅካቸው እንዳይሆን ››ብዬ ራሴን በመገሰፅ ያቆምኩት፡፡

‹‹እባክህ ና:: እዚያ ባገኝህ ደስ ኀይለኛል።›› ድጋሚ አመለጣት…በራሷ ሽምቅቅ አለች፡፡

‹‹እንዲህ ከሆነ››አለ ዔሊ በፈገግታ ‹‹ መምጣት የምችል ይመስለኛል….››

‹‹ቆንጆ እራት ሰርቼ ጠብቅሀለው››

‹‹በጣም ደስ የሚል ነገር ነው..በዛውም የሞያ ብቃትሽ ይፈተሻል››

‹‹አንተ የእማዬ ልጅ እኮ ነኝ..በሞያዬማ ምንም ጥርጣሬ ሊገባህ አይገባም››

‹‹እኮ ላየው አይደል?››

‹‹አይ ዛሬ እንኳን አታየውም…ይሄንን ዙሪያዬን የተቆለለ ወረቀት ባለበት ጥዬ ኪችን አልገባም››

‹‹እና እራቱ  የለም እያልሺኝ ነው?››

‹‹እሱማ አለ ..ግን አለም ነች የምትሰራው››

‹‹ይሁን እሺ…..እስክንገናኝ ቻው››
‹‹ቻው››ስልኩን ዘጋች፡፡እንደገና ዘና ያለ ስሜት ተሰማት ፡፡

አለምን ተጣራችን እንግዳ ስለሚመጣ ቆንጆ እራት እንድታዘጋጅ አዘዘቻት እና ትኩረት ሰበሰበች እና ወደ ስራዋ ተመለሰች፡፡
///
ረዳቷ ሮቤል ወደእነ ራሄል ቤት መጥቶ አባቷ ቢሮ ውስጥ ተቀምጠው ስለፋውንዴሽኑ አመታዊ የገቢ ማሰባሰ
ቢያ ዝግጅት እየተወያዩ ነው፡፡
‹‹የትኛውን ስራ በማን እንደማሰራ እና …የተወሰኑ ስራዎችን ውክልና መስጠት ከየት እንደምጀምር አላውቅም።››ራሄል በንዴት ተነፈሰች።

‹‹ እኔም ስለእሱ እያሰብኩነበር…ሁሉንምነገር በራስሽ ለመስራት በመሞከር በራስሽ ላይ አላስፈላጊ ጫና ማሳደር የለብሽም…እኔ አለሁ››

‹‹እኔ ካንተ የበለጠ ጊዜ አለኝ ብዬ አስባለሁ… ።››

ሮቤል ንግግሯ አልተዋጠለትም፡፡ቢሆንም ብዕሩን በፋይሉ ላይ ሰክቶ እያዳመጣት ነው፡፡በሁሉም ነገር  ትዕግስት እያጣ እንደመጣ በሁኔታው መታዘብ ይቻላል፡፡

‹‹ራሄል እህትሽን በመንከባከብ እንደተጠመድሽ አውቃለሁ…የደከመሽ ትመስላያለሽ ።አሁን የሎዛን ስራ የሚሰራ ሌላ ሰው መፈለግ አለብሽ እና ጊዜ እንደሌለሽ አውቃለሁ። ››በማለት የሚያስበውን በግልፅ ነገራት፡፡
57👍1🔥1😁1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////
አለም መተኛት አቅቷት እየተገለበጠች ባለችበት ጊዜ ነበር ስልኩ የጮኸው፡፡ሰዓቱ እኩለ ለሊት በመጠጋቱ የተነሳ ጥሪው በጣም ነበር ያስደነገጣት ። የራስጌ መብራቱን በማብራት የስልኩን እጄታ አነሳችና ጆረዋ ላይ ለጥፋ ጎላ ባለ ድምፅ "ጤና ይስጥልኝ" አለች፡፡ቀደም ብሎ ስታለቅስ ስለቆየች ድምጿ የሻከረ ነበር
"ሰላም ››መለሰላት፡፡

"አወቅሽኝ ወ.ሪት አለም "

ልቧ በደስታ ዘለለ፣"አንተ እንደገና? በዚህ ውድቅት ለሊት ከእንቅልፍ ያስነሳኸኝ ደህና ነገር ልትነግረኝ እንደሆነ ተስፋ አደርጋለሁ" አለችው።እምቢተኛ ምስክሮች ብዙ ጊዜ የሚናገሩትን ነገር አስፈላጊነት ሲጠቀስላቸው ለመናገር እንደሚበረታቱ ከልምድ ታዝባለች፡፡

"ከኔ ጋር ድብብቆሽ አትጫወቺ …. ማወቅ የምትፈልጊውን በጠቅላላ አውቃለሁ። "

"ለምሳሌ ምን?"

"ለምሳሌ እናትሽን ማን እንደገደላት››

አለም አተነፋፈስዋን በመቆጣጠር ላይ ትኩረት አደረገች።

" ይመስለኛል ዜናው አስደምሞሻል››

"ታዲያ ንገረኝ ማን ነበር?"

"እመቤት ደደብ እመስልሻለሁ እንዴ? ኩማንደሩ ቀደም ሲል ስልክሽን አለማስጠለፉን በምን አውቃለው ?"

"ይመስለኛል….በጣም ብዙ ፊልሞችን አይተሃል?››

‹‹ተረቡን አቁሚና ይልቅ በፅሞና አድምጪኝ ….ነገ ማታ አንድ ሰዓት ሸዋበር የሚገኘው ደንበል ሆቴል እንገናኝ" በማለት ሰዓቱንና ቦታውን ነገራት፡፡

"እንዴት ላውቅህ እችላለሁ?"

"እኔ አውቅሻለሁ"

ሌላ ነገር ከመናገሯ በፊት ስልኩን ዘጋው። አለም በአልጋው ጠርዝ ላይ ለጥቂት ጊዜ ተቀምጣ ጨለማውን እያየች ደርቃ ቀረች። ልትጎዳ እንደምትችል የነገራትን የኩማንደሩ ማስጠንቀቂያ አስታወሰች። የእርሷ ምናባዊ አእምሮ በሴት ላይ ብቻ ሊደርስ የሚችለውን አሰቃቂ ነገር ሁሉ አስተናገደ። በተኛችበት ሆና በላብ ተጠምቀው ነበር።
///
የከተማው የፖሊስ አዛዥ እንፋሎት የሚትገለግበትን ቡናውን አንስቶ ጠጣ። ምላሱን አቃጠለው። ግን ግድ አልነበረውም። በጣም በከፋ መንገድ የካፌይን ማነቃቂያ ያስፈልገዋል
‹‹ስለማን ነው የምናወራው?›› ሲል በግል ቢሮው ደጃፍ ላይ ቆሞ የነበረውን ምክትሉን ጠየቀ ..

" ስለአቃቢ ህግ ፅ/ቤት ነው››

"ስለ ወ.ሪት አለም እያወራህ ነው ?" ምክትሉ መለሰ " አዎ ጌታዬ ስለእሷ ነው።" "እሺ ምን አዲስ ነገር አለ?"

"  የእናቷን  የሬሳ  ምርመራ  መዝገብ  አስወጥታ  ዠለመመርመር  ወደ  ተክለሀይማኖት ቤ/ክርስቲያን ሄዳለች ››

"ምን?"

"አዎ ጌታዬ እንዲከታተሏት የመደብናቸው ፖሊሶች  ናቸው ደውለው የነገሩኝ፡፡››

‹‹በል አሁኑኑ ደውልላቸውና ወደእነሱ እየመጣሁ እንደሆነ ንገራቸው››

ገመዶ ኮቱን ከተሰቀለበት አንስቶ ቢሮውን ለቆ ወጣ…፡፡ ትምህርት ቤቶችን እና አብዛኛዎቹን የንግድ ድርጅቶች እንዲዘጉ ያደረጋቸውን የፀጥታ ችግር ቢኖርም ግድ አል ነበረውም። ሰልፈኛውን እየሰነጠቀ እና ወንበር እያሳበረ ወደሆስፒታል ነዳው፡፡

"የት ነው ያለችው?" እንደደረሰ ኩማንደሩ ጮኸ፣..አንድ አነስተኛ ቢሮ መሰል ክፍል ውስጥ ቁጭ ብላ ከአስተዳዳሪው ጋር ስታወራ ተመለከታ…ወደእዛው ተንደርድሮ ሄደ፡፡
ምንም ፍቃድ ሳይጠይቅ ሰተት ብሎ ገባና " ምን እየሰራሽ ነው ?"አንቧረቀባት፡፡ "እንደምን አደርክ ኩማንደር"አለችው ለስለስ ብላ፡፡

"ጥያቄዬን መልሺልኝ?"

‹‹ምን እያደረኩ እንደሆነማ በደንብ ታውቃለህ?››

"በአንቺ ምክንያት ሴትዮዬ ስራዬን መስራት አልቻልኩም….ከተማዋ በበጥባጭ ጎረምሶች ተረብሻ ያንን ማረጋጋት ሲጠበቅብኝ እኔ አንቺን በየመቃብር ቤቱ እከታተልሻል። ለማንኛውም እንዴት እዚህ ደረስሽ?"

" እየነዳሁ።"

በንዴት በጠረጴዛው ላይ የተበተኑትን ፋይሎች አያመለከተ"ይህ ሁሉ ምንድን ነው?"ሲል ጠየቃት፡፡

" መዛግብት ነዋ…..እናቴ ስትቀበር ለአገልግሎት የተከፈሉ ካርኒዎች እና መሰል መረጃዎች ሊኖሩ ስለሚችሉ ያንን እያዩልኝ ነው፣ ፡፡

"አስገድደሽው ነው?::"

‹‹እኔ እንደዚህ ያለ ነገር አላደረኩም..እንዴት ነው ምታስበኝ…?ደፍሬ አባቶቼን የማስገድድ ይመስልሀል?."

" ታዲያ የፍተሻ ማዘዣ ፍቃደሽን አልጠየቁሽም?"

ካህኑ‹‹ልጆቼ ይቅርታ እስኪ እናንተ አውሩ እኔ መጣሁ››ብለው ከመቀመጫቸው ተነሱና ክፍሉን ለቀውላቸው ወጡ … ገመዶ ወደሷ ቀረበና በንዴት ክንዷን ጨምድዷ ያዘ፡፡

‹‹ምን እያደረክ ነው?››

‹‹ቄሱን የሆነ ነገር ብዬ ከማስቀየሜ በፊት ቀጥ ብለሽ ቦታውን ለቀሽ ውጪ››

‹‹ለምንድነው እንደዛ የምታደርገው?››

‹‹ነገርኩሽ እኮ..አሁን ተከትለሺኝ ትሄጂያለሽ ወይስ…የማደርገውን ቆመሽ ትመለከቻለሽ?››

ትኩር ብላ አየችው … ፊቱ እንደ ተራራ ሰንሰለታማና ወጣ ገባ ነው፣በአጭሩ ቋጥኝ ይመስላል፣ ነገር ግን እስካሁን ካጋጠሟት በጣም ማራኪ ወንዶች ውስጥ አንዱ ነው።አብረው በሚሆኑበት ጊዜ ሁሉ፣ ስለ እሱ፣ ስለ ሰውነቱ ታስባለች፡፡ የእሷ ለእሱ ያላት መስህብ ሥነ ምግባር የጎደለው እና ከዛም አልፎ እንዝላልነት እንደሆነ ታውቃለች። መጀመሪያ የእናቷ ፍቅረኛ ነበረ።ያንን በደንብ ታውቃለች ..ሆኖም ብዙ ጊዜ እሱን ለመንካት ትፈልግ ነበር። ትናንት ማታ በምታለቅስበት ጊዜ እንዲያባብላት ትፈልግ ነበር። ወደመኝታ ቤቷ ተከትሏት እንዲገባም ፈልጋ ነበር…ደግነቱ እሱ በተሻለ ብቃት እራሱን የመቆጣጠር ችሎታ ነበረው እና ምንም ሳያደርግ ትቷት ሄደ።

‹‹የሰሎሜ ሬሳ እንደተቃጠለ ነግሬሻለሁ።››
"አንተ እና ዳኛው  ጭንቅላታችሁን አንድ ላይ አድርጋችሁ እያሻጠራችሁ መሆኑን ማወቄ የተመቸኝ ይመስልሀል?።››

"ነገሮችን መገመት ያስደስትሻል?."

"ጁኒየር እናቴ ሬሳ መቃጠሏን ለምን አልነገረኝም?እንደተቀበረች ነበር የነገረኝ ››

‹‹እኔ እየዋሸሁሽ ይምስልሻል….?ለምን ብዬ?" " አስከሬኑ እንዳይወጣ ስለምትፈልግ ነዋ።"

"ሬሳው እንዳይወጣ ለምንድነው የምፈልገው? በእኔ ላይ ምን ለውጥ ያመጣል?"

ፍርጥም ብላ "የእድሜ ልክ እስራት" በማለት መለሰችለት፡፡ "የፎረንሲክ ሪፖርቱ አንተን ነፍሰ ገዳይ መሆንህን የሚያመለክት ፍንጭ ከሰጠን ወደወህኒ መወርወርህ የማይቀር ነው።››

" “አህ...” አለ..ደም ስሯቹ ሲግተረተር እየታዘበች ነው፡፡ "አንቺ ጠበቃ አይደለሽም, ጠንቋይ አዳኝ ነሽ."

"ወንጀል ባይኖር ኖሮ ያ እውነት ሊሆን ይችላል….ግን አንድ ሰው ወደዚያ በረት ውስጥ ገብቶ እናቴን ወግቶ ገድሏታል..እና እስከአሁን ለጥፋቱ የሚመጥን ቅጣት አላገኘም።››

"በእስክሪፕት ደረጃ ትክክል ነሽ" አለ እየተሳለቀ።

"ጋሽ ፍሰሀ ፣ ጁኒየር ወይስ እኔ የቀዶ ጥገና መሳሪያ ይዘን እናትሽን እንደወጋናት ነው ግምትሽ? ለምን በባዶ እጃችን አንገቷን አንቀን አንገድላትም??"

"ሁላችሁም ጎበዝ ስለሆናችሁ።ከመካከላችሁ ወንጀሉን የፈፀመው ሰው እንደዛ ያደረገው ወንጀሉን የአእምሮ ሚዛናዊ የተዛባ ሰው ያደረገው እንዲመስል ፈልጎ ነው።››

‹‹አመንሽም አላመንሽም …እኔ አላደረግኩም

"በብስጭት መለሰላት፡፡

"ታዲያ ማን እንዳደረገው ማወቅ አትፈልግም? ወይስ ነፍሰ ገዳዩ የምትወደው ሌላ ሰው እንዳይሆን ትፈራለህ ?"ስትል ሞጋች ጥያቄ ጠየቀችው፡፡

‹‹አይ ማወቅ አልፈልግም" ሲል በአጽንኦት መለሰላት፡፡

"እኔ ግን ገዳዩን እስካገኝ ድረስ ምርመራዬን አላቋርጥም..››

ሊመልስላት አፉን ሲከፍት አንድ ግራ እግራቸው ሸንከል የሚል አዛውንት አንድ ያረጀች መዝገብ ይዘው ወደውስጥ ሲገቡ ሲመለከት አፉን መልሶ ከደነ፡፡
43👍1