#እንደምነሽ #ሸገር
በውቀቱ ስዩም ከአሜሩካ
እንደምነሽ ሸገር የቤት አከራዬ የጋሽ ጣሰው አገር የምትተከዪ የምትነቀዬ የዘመቻ ድንኳን
ብጉርና ችግር ከአባቴ ወርሼ ብኖርብሽ እንኳን
የማልቀያምሽ ሁሌ የማልምሽ
ኦ ማይ ጎድ ይመስገን እኔ እንዳለሁ አለው
ግማሽ እሩዝና ግማሽ ጤፍ በልቼ
አዋጅ እና ዜና ከአደባባይ ሳይሆን ከአይፎኔ ሰምቼ
ሀሜት ሲናፍቀኝ በስካይፒ አምቼ
ጥቃት ሲሰማኝ ፊስቡክ ላይ ሸፍቼ
በኮመንት እሩምታ ጠላቴን ደፍቼ
እኔ እንዳለው አለው
እንደምነሽ ሸገር እንደምነሽ ሸገር
የማይበገረው ወር እየጠበቀ የሚያገራግረው
የቤት አከራዬ የጋሽ ጣሰው አገር
የከሰመው ወንዝሽ የሚታየው ነጥፎ
እንደምነው ጣፎ እንዴት ነው ቀበና
እስቲ ድንጋይ ላጥምድ መረብ ልጣልና
ልክ እንደነ ፓሪስ እንደለንደን ሁላ
ፋፋቴም ባይኖርሽ ሽቅብ የሚፈላ
ምንጭሽ ከማን ያንሳል
ከፈነዳ ትቦ የወጣ ሰገራ ሰንጥቆሽ ይፈሳል
እንደምነሽ ሸገር የቅጠላቅጠል የፍራፍሬ አገር
አንድ ዘለላ ሙዝ ልጠሽ ባታበይኝ
በሙዝ ልጣች ጠልፈሽ የምታከባልይኝ
አሳድገሽኛል አሳድገሽኛል በማርና ወተት
የተሞላ ተረት እየተረክሽልኝ
ጥማቴን በጥማት እያረካሽልኝ
እንደምነሽ ሸገር ኦ ማይ ጎድ ይመስገን
እኔ እንዳለው አለው ሰርቼ ቀፍዬ
ሲነጋ ቀፍዬ ሲመሽም ከፍዬ
ስጋ ምታወፍር ነብስ የምታሳሳ
ዘናጭ አልጋ ሰታ እንቅልፍ የምትነሳ
አገር ላይ ተጥዬ
በውቀቱ ስዩም ከአሜሩካ
እንደምነሽ ሸገር የቤት አከራዬ የጋሽ ጣሰው አገር የምትተከዪ የምትነቀዬ የዘመቻ ድንኳን
ብጉርና ችግር ከአባቴ ወርሼ ብኖርብሽ እንኳን
የማልቀያምሽ ሁሌ የማልምሽ
ኦ ማይ ጎድ ይመስገን እኔ እንዳለሁ አለው
ግማሽ እሩዝና ግማሽ ጤፍ በልቼ
አዋጅ እና ዜና ከአደባባይ ሳይሆን ከአይፎኔ ሰምቼ
ሀሜት ሲናፍቀኝ በስካይፒ አምቼ
ጥቃት ሲሰማኝ ፊስቡክ ላይ ሸፍቼ
በኮመንት እሩምታ ጠላቴን ደፍቼ
እኔ እንዳለው አለው
እንደምነሽ ሸገር እንደምነሽ ሸገር
የማይበገረው ወር እየጠበቀ የሚያገራግረው
የቤት አከራዬ የጋሽ ጣሰው አገር
የከሰመው ወንዝሽ የሚታየው ነጥፎ
እንደምነው ጣፎ እንዴት ነው ቀበና
እስቲ ድንጋይ ላጥምድ መረብ ልጣልና
ልክ እንደነ ፓሪስ እንደለንደን ሁላ
ፋፋቴም ባይኖርሽ ሽቅብ የሚፈላ
ምንጭሽ ከማን ያንሳል
ከፈነዳ ትቦ የወጣ ሰገራ ሰንጥቆሽ ይፈሳል
እንደምነሽ ሸገር የቅጠላቅጠል የፍራፍሬ አገር
አንድ ዘለላ ሙዝ ልጠሽ ባታበይኝ
በሙዝ ልጣች ጠልፈሽ የምታከባልይኝ
አሳድገሽኛል አሳድገሽኛል በማርና ወተት
የተሞላ ተረት እየተረክሽልኝ
ጥማቴን በጥማት እያረካሽልኝ
እንደምነሽ ሸገር ኦ ማይ ጎድ ይመስገን
እኔ እንዳለው አለው ሰርቼ ቀፍዬ
ሲነጋ ቀፍዬ ሲመሽም ከፍዬ
ስጋ ምታወፍር ነብስ የምታሳሳ
ዘናጭ አልጋ ሰታ እንቅልፍ የምትነሳ
አገር ላይ ተጥዬ
#Re #post
‹‹ ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ ፀሃይና ጨረቃን ተመልከት፡፡ ሁለቱንም ማወዳደር አትችልም፡፡ ምክንያቱም ሁለቱም በየጊዜያቸው ዓለምን ያበራሉና፡፡ ››
የእኔ፣ የአንተ፣ የእሱ፣ የእሷ እና የሁላችንም የሕይወት ፍሠት፣ የደስታ ስኬት፣ የኑሮ ተዳፋት፣ እጣ ፋንታ እና ዕድል አንድ አይደለም፡፡ እንደየተፈጥሯችን፣ እንደየመልካችን፣ እንደየአስተሳሰባችን፣ እንደየፍላጎታችን፣ እንደየስጦታችን፣ እንደየአካሄዳችን፣ እንደአጠቃቀማችን ሁለነገራችን፣ ዕጣ ፋንታችን፣ ዕድል ገጠመኛችን ፍፁም የተለያየ ነው፡፡ ከአንድ እናት የወጡ መንታ ልጆች እንኳን ስኬታቸውም ሆነ ውድቀታቸው ይለያያል፡፡ ስለዚህ ራስን ከሌሎች ጋር ማወዳደር አይቻልም፡፡
ለአንዳንዱ በቀለም ትምህርት በሕይወቱ ስኬትን ለመጎናፀፍ ይቀለዋል፡፡ ለሌላው ደሞ ዳገት ይሆንበታል፡፡ ለእከሌ ንግድ የሚሳካለት ሲሆን ለእንቶኔ ደሞ ንግድ ኪሳራ በኪሳራ ያደርጋታል፡፡ ይሄ ማለት ግን በጥረትና በልፋት ነገሮችን ማሳካት አይቻልም ማለት አይደለም፡፡ በልፋትና በጥረት የሚሳካላቸው ሠዎች እንዳሉ ሁሉ የማይሳካለቸውም እልፍ ናቸው፡፡ ስንት ዓመት ለፍተው ፍሬውን ሊያዩ ትንሽ ሲቀራቸው ገደ-ቢስ ሆነው ልፋታቸው መና የቀረ ጥቂቶች አይደሉም፡፡
ለዚህ ጥሩ ምሣሌ የሚሆነው የጨረቃና የፀሃይን ተፈጥሮ ማየት ነው፡፡ አንዱን ካንዱ ማበላለጥ አይቻልም፡፡ ጨረቃን ከፀሃይ ብናሳንስ በድቅድቅ ጨለማ የምታበራውን ብርሃን መካድ ይሆናል፡፡ ጨረቃንም ከፀሃይ ብናስበልጥ የፀሃይን ውለታ አይቶ እንዳላየ ማለፍ ነው የሚሆነው፡፡ ሁለቱም በየራሳቸው ጠቃሚዎቻችን ናቸው፡፡ ሠውን ከሠው ማሳነስም ሆነ ማበላለጥ የተገባ አይደለም፡፡ ሁሉም ሠው ለሃገሩም ሆነ ለዓለም የሚታይና የማይታይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ አለውና፡፡ ምንም እንኳን ታዋቂ ሠዎች ቢሞገሱም በነሱ ስር ግን ብዙ ተራ ሠዎች ለእነሱ እውቅና የድርሻቸውን አዋጥተዋል፡፡ ለዚች ዓለም በየትኛውም ደረጃ ያለ ሠው አስፈላጊ ነው፡፡ አምላክ የሠው ልጅን ወዶና ፈቅዶ ነው የፈጠረው፡፡ በመሆኑም ሁሉም የራሱን አሻራ ጥሎ ያልፋል፡፡
ስለዚህ አበበን ከከበደ ማወዳደር አይቻልም፡፡ አበበም የሚበረታበት ነገር እንዳለው ሁሉ ከበደም የራሱ ጠንካራ ጎን አለው፡፡ በርግጥ ከበደ የሚደክምበትን አበበ ሊበረታበት ይችል ይሆናል፡፡ ይሄ ደሞ ከበደ ከአበበ ያነሠ ነው ማለት አይደለም፡፡ ከበደም በራሱ አቅምና ተፈጥሮ ብርታቱን የሚያሳይበትና የሚነሳበት ጊዜ አለውና፡፡
‹‹ለሁሉም ጊዜ አለው›› እንዳለው ጠቢቡ ሠለሞን እከሌ በስኬት ፏ ብሎ እኔ እስካሁን እዛው ነኝ ብለህ አትዘን፡፡ አንተም ጠንክረህ ከሠራህ ኑሮህን ታበራ ዘንድ ስኬት ካንተ ጎን የሚቆምበት ጊዜ ሩቅ አይደለም፡፡ ዋናው ነገር በስራ እየተጉ ጊዜውን በትዕግስት መጠባበቅ ብቻ ነው፡፡
💚መልካም 💛ቀን ለሁላችን❤️
‹‹ ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ ፀሃይና ጨረቃን ተመልከት፡፡ ሁለቱንም ማወዳደር አትችልም፡፡ ምክንያቱም ሁለቱም በየጊዜያቸው ዓለምን ያበራሉና፡፡ ››
የእኔ፣ የአንተ፣ የእሱ፣ የእሷ እና የሁላችንም የሕይወት ፍሠት፣ የደስታ ስኬት፣ የኑሮ ተዳፋት፣ እጣ ፋንታ እና ዕድል አንድ አይደለም፡፡ እንደየተፈጥሯችን፣ እንደየመልካችን፣ እንደየአስተሳሰባችን፣ እንደየፍላጎታችን፣ እንደየስጦታችን፣ እንደየአካሄዳችን፣ እንደአጠቃቀማችን ሁለነገራችን፣ ዕጣ ፋንታችን፣ ዕድል ገጠመኛችን ፍፁም የተለያየ ነው፡፡ ከአንድ እናት የወጡ መንታ ልጆች እንኳን ስኬታቸውም ሆነ ውድቀታቸው ይለያያል፡፡ ስለዚህ ራስን ከሌሎች ጋር ማወዳደር አይቻልም፡፡
ለአንዳንዱ በቀለም ትምህርት በሕይወቱ ስኬትን ለመጎናፀፍ ይቀለዋል፡፡ ለሌላው ደሞ ዳገት ይሆንበታል፡፡ ለእከሌ ንግድ የሚሳካለት ሲሆን ለእንቶኔ ደሞ ንግድ ኪሳራ በኪሳራ ያደርጋታል፡፡ ይሄ ማለት ግን በጥረትና በልፋት ነገሮችን ማሳካት አይቻልም ማለት አይደለም፡፡ በልፋትና በጥረት የሚሳካላቸው ሠዎች እንዳሉ ሁሉ የማይሳካለቸውም እልፍ ናቸው፡፡ ስንት ዓመት ለፍተው ፍሬውን ሊያዩ ትንሽ ሲቀራቸው ገደ-ቢስ ሆነው ልፋታቸው መና የቀረ ጥቂቶች አይደሉም፡፡
ለዚህ ጥሩ ምሣሌ የሚሆነው የጨረቃና የፀሃይን ተፈጥሮ ማየት ነው፡፡ አንዱን ካንዱ ማበላለጥ አይቻልም፡፡ ጨረቃን ከፀሃይ ብናሳንስ በድቅድቅ ጨለማ የምታበራውን ብርሃን መካድ ይሆናል፡፡ ጨረቃንም ከፀሃይ ብናስበልጥ የፀሃይን ውለታ አይቶ እንዳላየ ማለፍ ነው የሚሆነው፡፡ ሁለቱም በየራሳቸው ጠቃሚዎቻችን ናቸው፡፡ ሠውን ከሠው ማሳነስም ሆነ ማበላለጥ የተገባ አይደለም፡፡ ሁሉም ሠው ለሃገሩም ሆነ ለዓለም የሚታይና የማይታይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ አለውና፡፡ ምንም እንኳን ታዋቂ ሠዎች ቢሞገሱም በነሱ ስር ግን ብዙ ተራ ሠዎች ለእነሱ እውቅና የድርሻቸውን አዋጥተዋል፡፡ ለዚች ዓለም በየትኛውም ደረጃ ያለ ሠው አስፈላጊ ነው፡፡ አምላክ የሠው ልጅን ወዶና ፈቅዶ ነው የፈጠረው፡፡ በመሆኑም ሁሉም የራሱን አሻራ ጥሎ ያልፋል፡፡
ስለዚህ አበበን ከከበደ ማወዳደር አይቻልም፡፡ አበበም የሚበረታበት ነገር እንዳለው ሁሉ ከበደም የራሱ ጠንካራ ጎን አለው፡፡ በርግጥ ከበደ የሚደክምበትን አበበ ሊበረታበት ይችል ይሆናል፡፡ ይሄ ደሞ ከበደ ከአበበ ያነሠ ነው ማለት አይደለም፡፡ ከበደም በራሱ አቅምና ተፈጥሮ ብርታቱን የሚያሳይበትና የሚነሳበት ጊዜ አለውና፡፡
‹‹ለሁሉም ጊዜ አለው›› እንዳለው ጠቢቡ ሠለሞን እከሌ በስኬት ፏ ብሎ እኔ እስካሁን እዛው ነኝ ብለህ አትዘን፡፡ አንተም ጠንክረህ ከሠራህ ኑሮህን ታበራ ዘንድ ስኬት ካንተ ጎን የሚቆምበት ጊዜ ሩቅ አይደለም፡፡ ዋናው ነገር በስራ እየተጉ ጊዜውን በትዕግስት መጠባበቅ ብቻ ነው፡፡
💚መልካም 💛ቀን ለሁላችን❤️
👍3
#እኔ #እምፈልገው
እውነት ለመናገር እኔ ምፈልገው
ካንቺ ጋር መጋባት
ይህን ሀምሌ ፊቴን : ደጋግሞ ማራባት
ከወፎች ጋር መንቃት : በጊዜ ቤት መግባት::
"ምንም ደሃ ቢሆን: ባይኖረውም ሀብት
ከደጃፍ ሲቀመጥ: ደስ ይላል አባት"
ለሚል መናኛ ጥቅስ: ኑሮየ ማይመጥን
ሲሻኝ በየባንኩ: ስፈልግ በሳጥን
የተረፈኝ ገንዘብ
ደጃፍ ላይ ቁጭ ብየ: ድሀ የምታዘብ
ተምሳሌትነቴ የሚዳረስ ባለም
ሞዴል አባወራ ተብየ ምሸለም
አገሬን ማስከበር
ህዝቤን ማስተባበር
የልጅ ልጅ አፍርቼ
በመቶ አመት ሙቼ
ስላሴ መቀበር
ምኞቴ ይህ ነበር::
እውነት ለመናገር እኔ እምፈልገው
ወንደላጤ ኑሮ
በሴቶች መታጀብ : ልክ እንዳውራ ዶሮ
ጊዜ ጥሎኝ ቢሄድ : ቀን ቢገሰግስም
መላው ጭንቅላቴ : ገብስማ ቢለብስም
ላቅማዳም ነው እንጂ: ለትዳር አልደርስም::
ደሞ
ዘር መዝራት እርሜ ነው : ደጋግሜ ባርስም
ባለመኖር ላሉት: ስቃይ አላወርስም
ቢፈልግ ሌላው ህዝብ
ይፈልፍል እንደዝንብ
ይባዛ እንደንጉዳይ
አገር ስራው ያውጣው! ሰው የራሱ ጉዳይ!!
የራሴ ፈጣሪ- ነኝ የራሴ ገዳይ!!
እኔ እምፈልገው...
እኔ እምፈልገው..
እኔ እምፈልገው
-----------
ገንዘብ ቢመዘበር: በገንዘብ ይተካል
እድሜ ለጉልበትሽ : በላቡ ለሚያድር
በውርስ በስጦታ : ግፋ ቢል በብድር::
በቆጠብነው ቁጥር
ጊዜ ነው የሚያጥር
እድሜ ነው የሚያልቀው
የምንፈልገውን በቅጡ ሳናውቀው::
👉በውቀቱ ስዩም
እውነት ለመናገር እኔ ምፈልገው
ካንቺ ጋር መጋባት
ይህን ሀምሌ ፊቴን : ደጋግሞ ማራባት
ከወፎች ጋር መንቃት : በጊዜ ቤት መግባት::
"ምንም ደሃ ቢሆን: ባይኖረውም ሀብት
ከደጃፍ ሲቀመጥ: ደስ ይላል አባት"
ለሚል መናኛ ጥቅስ: ኑሮየ ማይመጥን
ሲሻኝ በየባንኩ: ስፈልግ በሳጥን
የተረፈኝ ገንዘብ
ደጃፍ ላይ ቁጭ ብየ: ድሀ የምታዘብ
ተምሳሌትነቴ የሚዳረስ ባለም
ሞዴል አባወራ ተብየ ምሸለም
አገሬን ማስከበር
ህዝቤን ማስተባበር
የልጅ ልጅ አፍርቼ
በመቶ አመት ሙቼ
ስላሴ መቀበር
ምኞቴ ይህ ነበር::
እውነት ለመናገር እኔ እምፈልገው
ወንደላጤ ኑሮ
በሴቶች መታጀብ : ልክ እንዳውራ ዶሮ
ጊዜ ጥሎኝ ቢሄድ : ቀን ቢገሰግስም
መላው ጭንቅላቴ : ገብስማ ቢለብስም
ላቅማዳም ነው እንጂ: ለትዳር አልደርስም::
ደሞ
ዘር መዝራት እርሜ ነው : ደጋግሜ ባርስም
ባለመኖር ላሉት: ስቃይ አላወርስም
ቢፈልግ ሌላው ህዝብ
ይፈልፍል እንደዝንብ
ይባዛ እንደንጉዳይ
አገር ስራው ያውጣው! ሰው የራሱ ጉዳይ!!
የራሴ ፈጣሪ- ነኝ የራሴ ገዳይ!!
እኔ እምፈልገው...
እኔ እምፈልገው..
እኔ እምፈልገው
-----------
ገንዘብ ቢመዘበር: በገንዘብ ይተካል
እድሜ ለጉልበትሽ : በላቡ ለሚያድር
በውርስ በስጦታ : ግፋ ቢል በብድር::
በቆጠብነው ቁጥር
ጊዜ ነው የሚያጥር
እድሜ ነው የሚያልቀው
የምንፈልገውን በቅጡ ሳናውቀው::
👉በውቀቱ ስዩም
👍1
📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚
ውድ የቻናላችን ተከታታዮች በዘነበ ወላ የተፃፈውን ልጅነት የተሰኘውን መፅሐፍ ያላነበበው ካለ ሙሉውን በPdf ቀርቦላችኋል መልካም ንባብ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ውድ የቻናላችን ተከታታዮች በዘነበ ወላ የተፃፈውን ልጅነት የተሰኘውን መፅሐፍ ያላነበበው ካለ ሙሉውን በPdf ቀርቦላችኋል መልካም ንባብ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
💦 ከልጅነት ፍቅር አንዲት ጠብታ💦
በሰላላው መንገድ የትየለሌ እግር እንደ ሊጥ ባቦካው
ጸአዳ ጣትሽን ጉድፍ እንዳይነካው
ማጡን እየዘለልሽ
ዳጥ ዳጡን እያለፍሽ
ጤዛ የወረረው ዛፍ እየተደገፍሽ
ትንሽ ስትመጪ ብዙ ስታዘግሚ
ሁለቴ ተራምደሽ አስሪ ስትቆሚ
የተላከ ህፃን አስቁመሽ ስትስሚ
እኔ ስናፍቅሽ
እኔ ስጠብቅሽ
እንደ ጉድ ተውቤ ላማልልሽ ጥሬ
በጆትራ ዘይቤ ፀጉሬን አበጥሬ
ጅማት እያጠበኩ ጅማት እያላላሁ
የገዛ ከንፈሬን ቀርጥፌ እየበላሁ
ስጠብቅሽ በጣም
ምስልሽ ነው እንጂ አካልሽ አልመጣም
ባይኖቼ ስፈልግ መስኮት እከፍትና
ሌላ ነው የሚያልፈው በሰፊው ጎዳና
ያው ገጣባ አህያ ያቻት ድኩም በቅሎ
በግ እየጎተተ አለፈ ቆለኛ
ቅርጫት ያጎበጣት ሚስቱን አስከትሎ
ያውና ደሀ አደግ መንገድ ዳር የተኛ
የተጎነ ጎነ የሳር አንባ መስሎ
ባይኖቼ ሳማትር መስኮት እከፍትና
ሌላ ነው የሚያልፈው በሰፊው ጎዳና
ሁሉም ተለውጦ ያ ገጣባ አህያ ፀጉር አቆጥቁጦ
ያቺ ድኩም በቅሎ ሰጋር ፈረስ ቀድማ
ቆለኛው ሰውዬ ሙክት በጉን ሽጦ ለሚስቱ ነጭ ሻሽ ለሱ ሸራ ጫማ በትርፉ ሸምቶ
ሀሉም ከሄደበት ቀንቶት ተመልሶ
ሁሉም ከድቀቱ በወግ ተፈውሶ
እኔ ብቻ ቀረሁ
መንገድሽ እረዝሞ ባሳብ እያሳጠርኩ
አንቺን እየናፋኩ
አንቺን አየጠበኩ
ጅማት አያላላሁ ጅማት እያጠበኩ
፨በውቀቱ ስዩም፨
በሰላላው መንገድ የትየለሌ እግር እንደ ሊጥ ባቦካው
ጸአዳ ጣትሽን ጉድፍ እንዳይነካው
ማጡን እየዘለልሽ
ዳጥ ዳጡን እያለፍሽ
ጤዛ የወረረው ዛፍ እየተደገፍሽ
ትንሽ ስትመጪ ብዙ ስታዘግሚ
ሁለቴ ተራምደሽ አስሪ ስትቆሚ
የተላከ ህፃን አስቁመሽ ስትስሚ
እኔ ስናፍቅሽ
እኔ ስጠብቅሽ
እንደ ጉድ ተውቤ ላማልልሽ ጥሬ
በጆትራ ዘይቤ ፀጉሬን አበጥሬ
ጅማት እያጠበኩ ጅማት እያላላሁ
የገዛ ከንፈሬን ቀርጥፌ እየበላሁ
ስጠብቅሽ በጣም
ምስልሽ ነው እንጂ አካልሽ አልመጣም
ባይኖቼ ስፈልግ መስኮት እከፍትና
ሌላ ነው የሚያልፈው በሰፊው ጎዳና
ያው ገጣባ አህያ ያቻት ድኩም በቅሎ
በግ እየጎተተ አለፈ ቆለኛ
ቅርጫት ያጎበጣት ሚስቱን አስከትሎ
ያውና ደሀ አደግ መንገድ ዳር የተኛ
የተጎነ ጎነ የሳር አንባ መስሎ
ባይኖቼ ሳማትር መስኮት እከፍትና
ሌላ ነው የሚያልፈው በሰፊው ጎዳና
ሁሉም ተለውጦ ያ ገጣባ አህያ ፀጉር አቆጥቁጦ
ያቺ ድኩም በቅሎ ሰጋር ፈረስ ቀድማ
ቆለኛው ሰውዬ ሙክት በጉን ሽጦ ለሚስቱ ነጭ ሻሽ ለሱ ሸራ ጫማ በትርፉ ሸምቶ
ሀሉም ከሄደበት ቀንቶት ተመልሶ
ሁሉም ከድቀቱ በወግ ተፈውሶ
እኔ ብቻ ቀረሁ
መንገድሽ እረዝሞ ባሳብ እያሳጠርኩ
አንቺን እየናፋኩ
አንቺን አየጠበኩ
ጅማት አያላላሁ ጅማት እያጠበኩ
፨በውቀቱ ስዩም፨
👍1
#እንትንሽ #እንዴት #ነው😳
እንትንሽ እንዴት ነው?እዩኝ እዩኝ የሚለው
ሲየዩት ግን የሚያመው
መጠን ያላገኘው የሚፎካከረው
እንዴት ነው እንትንሽ ማለቴ አይኖችሽ
አሁንም ያያሉ እንደ ጥንቱ ናቸው
እንደ ጥንቱ ናቸው ቀልብን ይገዛሉ
ከንፈርሽስ ውዴ ሳሙኝ ሳሙኝ የሚለው
ስስመው የሚጣፍት ጣፋጩ የማያልቀው
ዛሪም ለስላሳ ነው ወይስ ፀሀይ አ ደረቀው
አረ በፈጣሪ እንትንሽ እንዴት ነው
እንዴት ነው እንትሽ ማለቴ ጥርሶችሽ
እንደድሮ ያምራል
ስትስቂ ያየሽ ሰው በፍቅር ይወድቃል
ፀጉርሽ እንዴት ነው ሀረግ የሚያስንቀው
አሁን አጥሮብሻል ወይ ስ እረጅም ነው
አረ ተናገሪ እንትንሽ እንዴት ነው
አፍንጫሽስ ውዴ ዛሪም እንደ አክሱም ነው
ጎብኝው በጣም በዛ ወይስ አናሳ ነው
አንገትሽስ እንዴት ነው ቀጥኖ የረዘመው
ምን ይሆን ምክንያቱ እንዲ ያሳመረው
ጡትሽ ግን እንዴት ነው ተወጥሮ የቆመው
ወይስ አስተኛሽው እንቅልፍ አሸለበው
ወገብሽ እንዴት ነው ሞዴል የሚያ ስብልሽ
መጠን ተገኘለት ይሚፎካከረው
ውይ እረስ ቼው እንዴት ነው እንትንሽ
ሀገር ጉድ የሚያ ስብለው ያኛው ትልቅ ዳሌሽ
ሁሉም ደና ናቸው
ከቶ አልተቀየሩም ምንም አልነካቸው
ምንድን ነው ያልጠቀሰው
ምንድን ነው ያልዘረዘረው
አልቃሻው ብእሬ
እስቲ ተናገሪ ስሞትልሽ ፍቅሬ
ብቻ ያልገለ ፅኳት አልች አንድ ነገር
ላወጣት አልቻልኩም አቃተኝ መናገር
እንትን እንትን ብዬ ከዘረዘርኳቸው
ያልጠቀስኩት አለ ሁሉን የሚበልጣቸው
በቃ ልናገረው እስቲ ልተንፍሰው
ምን አጨናነቀኝ ቃሉ ሶስት ፊደል ነው
.
.
.
.
.
.
#ፍቅር ነው ፊደሉ #ፍቅር ነው ቃላቱ
#ፍቅር ነው የሱ ስም ጤነኛ የሚያሳብድ
እብዶችን የሚያክም
#ፍቅር ነው ፊደሉ #ፍቅር ነው የሱ ስም
ሌላ ምንም አይደል #ፍቅር ማለት እንትን
እንትን ማለት #ፍቅር ምንም ነገር የለም እሱን የሚፎካከር እናልሽ አለሜ
እናልሽ አለሜ እንትንሽ ደህና ይሁን
ደህና ሁኚ ፍቅሬ
ደህና ሁኚ
ደህና ሁኚ
በጆጆ አሌክስ
እንትንሽ እንዴት ነው?እዩኝ እዩኝ የሚለው
ሲየዩት ግን የሚያመው
መጠን ያላገኘው የሚፎካከረው
እንዴት ነው እንትንሽ ማለቴ አይኖችሽ
አሁንም ያያሉ እንደ ጥንቱ ናቸው
እንደ ጥንቱ ናቸው ቀልብን ይገዛሉ
ከንፈርሽስ ውዴ ሳሙኝ ሳሙኝ የሚለው
ስስመው የሚጣፍት ጣፋጩ የማያልቀው
ዛሪም ለስላሳ ነው ወይስ ፀሀይ አ ደረቀው
አረ በፈጣሪ እንትንሽ እንዴት ነው
እንዴት ነው እንትሽ ማለቴ ጥርሶችሽ
እንደድሮ ያምራል
ስትስቂ ያየሽ ሰው በፍቅር ይወድቃል
ፀጉርሽ እንዴት ነው ሀረግ የሚያስንቀው
አሁን አጥሮብሻል ወይ ስ እረጅም ነው
አረ ተናገሪ እንትንሽ እንዴት ነው
አፍንጫሽስ ውዴ ዛሪም እንደ አክሱም ነው
ጎብኝው በጣም በዛ ወይስ አናሳ ነው
አንገትሽስ እንዴት ነው ቀጥኖ የረዘመው
ምን ይሆን ምክንያቱ እንዲ ያሳመረው
ጡትሽ ግን እንዴት ነው ተወጥሮ የቆመው
ወይስ አስተኛሽው እንቅልፍ አሸለበው
ወገብሽ እንዴት ነው ሞዴል የሚያ ስብልሽ
መጠን ተገኘለት ይሚፎካከረው
ውይ እረስ ቼው እንዴት ነው እንትንሽ
ሀገር ጉድ የሚያ ስብለው ያኛው ትልቅ ዳሌሽ
ሁሉም ደና ናቸው
ከቶ አልተቀየሩም ምንም አልነካቸው
ምንድን ነው ያልጠቀሰው
ምንድን ነው ያልዘረዘረው
አልቃሻው ብእሬ
እስቲ ተናገሪ ስሞትልሽ ፍቅሬ
ብቻ ያልገለ ፅኳት አልች አንድ ነገር
ላወጣት አልቻልኩም አቃተኝ መናገር
እንትን እንትን ብዬ ከዘረዘርኳቸው
ያልጠቀስኩት አለ ሁሉን የሚበልጣቸው
በቃ ልናገረው እስቲ ልተንፍሰው
ምን አጨናነቀኝ ቃሉ ሶስት ፊደል ነው
.
.
.
.
.
.
#ፍቅር ነው ፊደሉ #ፍቅር ነው ቃላቱ
#ፍቅር ነው የሱ ስም ጤነኛ የሚያሳብድ
እብዶችን የሚያክም
#ፍቅር ነው ፊደሉ #ፍቅር ነው የሱ ስም
ሌላ ምንም አይደል #ፍቅር ማለት እንትን
እንትን ማለት #ፍቅር ምንም ነገር የለም እሱን የሚፎካከር እናልሽ አለሜ
እናልሽ አለሜ እንትንሽ ደህና ይሁን
ደህና ሁኚ ፍቅሬ
ደህና ሁኚ
ደህና ሁኚ
በጆጆ አሌክስ
👍2
#ናፍቆት
እንዲህ እንደዛሬ...
በመሀከላችን
ንፋስ ሳይግባብን ፣ ፍጥረት ሳይፈጠር
በኔና አንቺ መሀል...
የነበረው ክፍተት ፣ አንድ ስንዝር ነበር።
አንቺ ሰማይ ሆነሽ እኔ ደግሞ ምድር!!!
............................................
በዚህ ስንዝር መሀል....
እስትንፋስ ያላቸው ሰዎች ተፈጠሩ
እነዚህ ሰዎችም....
ቅርብ ላለች ሰማይ
የምድርን ሀጥያት ይነግሯት ጀመሩ።
"ምድር ዘማዊ ነው
ምድር ሀጣዊ ነው
ብትሸሺው ይሻላል ይህ ዓለም ጠፊ ነው"
እያሉ ሲነግሯት የሰው ወሬ ሰምታ
ሰማይ ፊኛ ሆና...
ትለጠጥ ጀመረ ከኔ ተለይታ
በሰዎች እስትንፋስ...
ወደ ላይ ተነፍታ
ወደጎንም ሰፍታ።
.......................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
................................................
እንደውም እንደውም...
በዛ ስንዝር መሀል ያኔ የተፈጠሩ
እዛሬ ላይ ሆነው..
"ሰማይ ቅርብ ነበር" እያሉ ሚያወሩ
እድሜ የሰጣቸው
ጥቂት ሰዎች አሉ
የኔና ያንቺ ፍቅር የሚመሰክሩ።
.............................................
እንደውም እንደውም....
ሌላ አይነት ማስረጃ ሌላ አይነት ምስክር
ሰማይ ቅርብ ሳለሽ ምጣድ ሆኜ ምድር
እንዲህ እንደዛሬው...
ነፋስ አቀጣጥሎት
ነፋስ የሚያጠፋው እሳት ሳይፈጠር
የሰው ልጆች ሁሉ
በፀሐይ በርሀን ምግብ ያበስሉ ነበር።
.............................................
ፀሐይ ውበትሽ ነው ጠዋት የምሞቀው
ቀን ተቃጥዬበት ሌት የምናፍቀው።
ለሊት ላይ ያመኛል ህመሜም አንቺው ነሽ
ቀኑ ጨለማ ነው...
ነግቶ እስካይሽ ድረስ ትናፍቂኛለሽ።
...........................................
መቼ ነው ሚነጋው?
ፀሐዩ ውበትሽ ምድርን የሚከድነው
መርዙ መድሀኒትሽ...
በሽታዬን ገድሎ ህመሜን ሚያድነው
ካፈቀሩት ጋራ....
እንኳን ላንድ ለሊት
ላፍታ ያህል እንኳን መለያየት ሞት ነው።
.............................................
መቼ ነው ሚነጋው ልቤን ይበርደኛል
ንጋት ላይ የሚሸሽ..
ወረተኛ ፍቅር ጤዛው በዝቶብኛል
አንቺ የሌለሽበት...
ራሴን ሳስበው ራሴን ያዞረኛል።
ለራስ ምታት ህመም..
መድሀኒት እንዲሆን
በሽታን የሚገድል መርዝ ነው ሚቀመም።
...................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ.
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
..በበላይ በቀለ ወያ..
እንዲህ እንደዛሬ...
በመሀከላችን
ንፋስ ሳይግባብን ፣ ፍጥረት ሳይፈጠር
በኔና አንቺ መሀል...
የነበረው ክፍተት ፣ አንድ ስንዝር ነበር።
አንቺ ሰማይ ሆነሽ እኔ ደግሞ ምድር!!!
............................................
በዚህ ስንዝር መሀል....
እስትንፋስ ያላቸው ሰዎች ተፈጠሩ
እነዚህ ሰዎችም....
ቅርብ ላለች ሰማይ
የምድርን ሀጥያት ይነግሯት ጀመሩ።
"ምድር ዘማዊ ነው
ምድር ሀጣዊ ነው
ብትሸሺው ይሻላል ይህ ዓለም ጠፊ ነው"
እያሉ ሲነግሯት የሰው ወሬ ሰምታ
ሰማይ ፊኛ ሆና...
ትለጠጥ ጀመረ ከኔ ተለይታ
በሰዎች እስትንፋስ...
ወደ ላይ ተነፍታ
ወደጎንም ሰፍታ።
.......................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
................................................
እንደውም እንደውም...
በዛ ስንዝር መሀል ያኔ የተፈጠሩ
እዛሬ ላይ ሆነው..
"ሰማይ ቅርብ ነበር" እያሉ ሚያወሩ
እድሜ የሰጣቸው
ጥቂት ሰዎች አሉ
የኔና ያንቺ ፍቅር የሚመሰክሩ።
.............................................
እንደውም እንደውም....
ሌላ አይነት ማስረጃ ሌላ አይነት ምስክር
ሰማይ ቅርብ ሳለሽ ምጣድ ሆኜ ምድር
እንዲህ እንደዛሬው...
ነፋስ አቀጣጥሎት
ነፋስ የሚያጠፋው እሳት ሳይፈጠር
የሰው ልጆች ሁሉ
በፀሐይ በርሀን ምግብ ያበስሉ ነበር።
.............................................
ፀሐይ ውበትሽ ነው ጠዋት የምሞቀው
ቀን ተቃጥዬበት ሌት የምናፍቀው።
ለሊት ላይ ያመኛል ህመሜም አንቺው ነሽ
ቀኑ ጨለማ ነው...
ነግቶ እስካይሽ ድረስ ትናፍቂኛለሽ።
...........................................
መቼ ነው ሚነጋው?
ፀሐዩ ውበትሽ ምድርን የሚከድነው
መርዙ መድሀኒትሽ...
በሽታዬን ገድሎ ህመሜን ሚያድነው
ካፈቀሩት ጋራ....
እንኳን ላንድ ለሊት
ላፍታ ያህል እንኳን መለያየት ሞት ነው።
.............................................
መቼ ነው ሚነጋው ልቤን ይበርደኛል
ንጋት ላይ የሚሸሽ..
ወረተኛ ፍቅር ጤዛው በዝቶብኛል
አንቺ የሌለሽበት...
ራሴን ሳስበው ራሴን ያዞረኛል።
ለራስ ምታት ህመም..
መድሀኒት እንዲሆን
በሽታን የሚገድል መርዝ ነው ሚቀመም።
...................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ.
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
..በበላይ በቀለ ወያ..
ውድ የቻናላችን ተከታታዮች የጃገማ ኬሎ የህይወት ታሪክ በፍቅረ ማርቆስ ደስታ የተፃፈውን መፅሐፍ ሙሉውን በPdf ቀረቦላችኋል መልካም ንባብ📖👇👇👇
#ፍቅር #ፈራን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
#ፈራን
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
#ናቅን
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
#ናቅን
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
#ጠላን
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
#ራቅን
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
#ፈራን
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
#ናቅን
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
#ናቅን
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
#ጠላን
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
#ራቅን
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
👍2
"በእጅህ ያለን አትልቀቅ ፤ ባለፈ ነገርም አትፀፀት"
ከቀናት በአንዱ ቀን ይህ ሆነ ።
አንድ ሰው ላባዋ በህብረ ቀለማት ያሸበረቀ የምታምር ወፍ አጥምዶ ያዘ ። በመዳፉ ላይም ጨፍልቆ ሊገድላት ሲሞክር ፤
ወፊቱም ፤" እባክህ ጌታዬ ህይወትህን በሙሉ ባለፀጋ ሆነህ እንድትኖርና ስኬታማም እንድትሆን የሚያስችሉ ሦስት ጠቃሚ ምክሮች አሉኝና እባክህን አትግደለኝ " ስትል ተማፀነችው ።
ይህ ሰውም ሦስቱን ጠቃሚ ያለቻቸውን ምክሮች ትናገር ዘንድ ፈቀደላት ።
................
"የመጀመሪያው ምክሬ በእጅህ የገባን ነገር አትልቀቅ ነው ።"
"ሁለተኛው ደግሞ ባለፈ ነገር አትፀፀት ነው ። ሦስተኛውና የመጨረሻው ምክሬ ግን ከአንተ አልፎ ለልጅ ልጆችህም የሚጠቅም ታላቅ ምክር በመሆኑ ካለቀከኝ አልነግርህም ።" አለችው ።
ይህ ሰውም ለምክሩ በጣም ጓግቶ ነበርና ከመዳፉ ለቀቃት ።
ወፊትም በርራ ዛፍ ላይ አረፈች ።
ሰውዬውም ሦስተኛውን ምክር ትነግረው ዘንድ ጠየቃት ።
............
ወፏም ፤ "በአንደኛና በሁለተኛ ምክሬ የነገርኩህ ነገር ምን ነበር አለችው ።"
"በእጅህ የያዝከውን አትልቀቅ ፤ ሁለተኛው ደግሞ ባለፈ ነገር አትፀፀት ነው ።" ሲል ሰውዬው መለሰ ።
"አየህ ምክሬን ሰምተህ ቢሆን ኖሮ ፣ ሆዴ ውስጥ ከአንተ አልፎ ለልጅ ልጆችህ የሚተርፍ ወርቅ ነበር ፤ ምክሬን ባለመቀበልህና ባለመስማትህ ግን ዕድሜህን ሙሉ ድሃ እንደሆንክ ትኖራለህ ። " አለችውና ክንፉን እያርገበገበች ርቃ በረረች ።
ከቀናት በአንዱ ቀን ይህ ሆነ ።
አንድ ሰው ላባዋ በህብረ ቀለማት ያሸበረቀ የምታምር ወፍ አጥምዶ ያዘ ። በመዳፉ ላይም ጨፍልቆ ሊገድላት ሲሞክር ፤
ወፊቱም ፤" እባክህ ጌታዬ ህይወትህን በሙሉ ባለፀጋ ሆነህ እንድትኖርና ስኬታማም እንድትሆን የሚያስችሉ ሦስት ጠቃሚ ምክሮች አሉኝና እባክህን አትግደለኝ " ስትል ተማፀነችው ።
ይህ ሰውም ሦስቱን ጠቃሚ ያለቻቸውን ምክሮች ትናገር ዘንድ ፈቀደላት ።
................
"የመጀመሪያው ምክሬ በእጅህ የገባን ነገር አትልቀቅ ነው ።"
"ሁለተኛው ደግሞ ባለፈ ነገር አትፀፀት ነው ። ሦስተኛውና የመጨረሻው ምክሬ ግን ከአንተ አልፎ ለልጅ ልጆችህም የሚጠቅም ታላቅ ምክር በመሆኑ ካለቀከኝ አልነግርህም ።" አለችው ።
ይህ ሰውም ለምክሩ በጣም ጓግቶ ነበርና ከመዳፉ ለቀቃት ።
ወፊትም በርራ ዛፍ ላይ አረፈች ።
ሰውዬውም ሦስተኛውን ምክር ትነግረው ዘንድ ጠየቃት ።
............
ወፏም ፤ "በአንደኛና በሁለተኛ ምክሬ የነገርኩህ ነገር ምን ነበር አለችው ።"
"በእጅህ የያዝከውን አትልቀቅ ፤ ሁለተኛው ደግሞ ባለፈ ነገር አትፀፀት ነው ።" ሲል ሰውዬው መለሰ ።
"አየህ ምክሬን ሰምተህ ቢሆን ኖሮ ፣ ሆዴ ውስጥ ከአንተ አልፎ ለልጅ ልጆችህ የሚተርፍ ወርቅ ነበር ፤ ምክሬን ባለመቀበልህና ባለመስማትህ ግን ዕድሜህን ሙሉ ድሃ እንደሆንክ ትኖራለህ ። " አለችውና ክንፉን እያርገበገበች ርቃ በረረች ።
👍5
Re-post
#አሮጊቶ
አንድ ጠዋት አሮጊቷ መስታውት ፈትለፊት ቁማ እራሷን ስትመለከት ሦስት ፀጉሮች እንደቀሯት ተመለከተች፡፡ ነፍሷን ያስደሰተች ሴት ናትና እንዲህ አለች “ዛሬ ፀጉሬን ማበጠር፣ ቅባት መቀባት፣ መንከባከብ አለብኝ” ተንከባከበችውም፡፡ እናም ደስስስ…የሚል ቀን አሳለፈች፡፡ ከቀናቶች በኋላ በአንደኛው ጠዋት መስታውት ፊት ቁማ ለቀኑ መዘጋጀት ጀመረች፡፡ ወደ መስታውቱ ተጠግታም ስትመለከት ሁለት ፀጉሮች ብቻ እንደቀሯት ተመለከተች፡፡ ህምምም… ሁለት ፀጉር !!! በማለት ተገርማ ለቀኑ ዝግጅቷን ቀጠለች ሁለቱን ጸጉሮቿን አሰማምራ እንደተለመደው ሸጋ ቀን ዋለች፡፡ እንዲሁ ደግሞ ከሳምንት በኋላ አንዲት ፀጉር ብቻ እንደቀረቻት ተመለከተች አሃ… አንድ ፀጉር ብቻ! አለችና ለአንድ ፀጉር የሚመች ስታይል ተጠቅማ እንዲሁ ቀኗን አሳመረች፡፡ በማግስቱ ጠዋት መስታውት ፊት ላይ ቆመች ጭራሽ መላጣ እንደሆነች ተመለከተች፡፡ በመጨረሻም መላጣ! ኦሁሁሁ.. ስትል ለራሶ አሰምታ ተናገረች፡፡ እራሷ ራሷ እንዴት ያለ ድንቅ ነገር ነው! ከዚህ በኋላ ፀጉሬን ለመንከባከብ የማጠፋው ጊዜ አይኖረኝም ስትል ነገረቸው፡፡ እራሷን እንደራስ መቀበል መቻል ችግር ነው ያልነውን ችግር እንዳልሆነ መረዳት ያስችላል፡፡
መልካም ቀን💚💛❤️
#አሮጊቶ
አንድ ጠዋት አሮጊቷ መስታውት ፈትለፊት ቁማ እራሷን ስትመለከት ሦስት ፀጉሮች እንደቀሯት ተመለከተች፡፡ ነፍሷን ያስደሰተች ሴት ናትና እንዲህ አለች “ዛሬ ፀጉሬን ማበጠር፣ ቅባት መቀባት፣ መንከባከብ አለብኝ” ተንከባከበችውም፡፡ እናም ደስስስ…የሚል ቀን አሳለፈች፡፡ ከቀናቶች በኋላ በአንደኛው ጠዋት መስታውት ፊት ቁማ ለቀኑ መዘጋጀት ጀመረች፡፡ ወደ መስታውቱ ተጠግታም ስትመለከት ሁለት ፀጉሮች ብቻ እንደቀሯት ተመለከተች፡፡ ህምምም… ሁለት ፀጉር !!! በማለት ተገርማ ለቀኑ ዝግጅቷን ቀጠለች ሁለቱን ጸጉሮቿን አሰማምራ እንደተለመደው ሸጋ ቀን ዋለች፡፡ እንዲሁ ደግሞ ከሳምንት በኋላ አንዲት ፀጉር ብቻ እንደቀረቻት ተመለከተች አሃ… አንድ ፀጉር ብቻ! አለችና ለአንድ ፀጉር የሚመች ስታይል ተጠቅማ እንዲሁ ቀኗን አሳመረች፡፡ በማግስቱ ጠዋት መስታውት ፊት ላይ ቆመች ጭራሽ መላጣ እንደሆነች ተመለከተች፡፡ በመጨረሻም መላጣ! ኦሁሁሁ.. ስትል ለራሶ አሰምታ ተናገረች፡፡ እራሷ ራሷ እንዴት ያለ ድንቅ ነገር ነው! ከዚህ በኋላ ፀጉሬን ለመንከባከብ የማጠፋው ጊዜ አይኖረኝም ስትል ነገረቸው፡፡ እራሷን እንደራስ መቀበል መቻል ችግር ነው ያልነውን ችግር እንዳልሆነ መረዳት ያስችላል፡፡
መልካም ቀን💚💛❤️
👍2