አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ናፍቆት

እንዲህ እንደዛሬ...
በመሀከላችን
ንፋስ ሳይግባብን ፣ ፍጥረት ሳይፈጠር
በኔና አንቺ መሀል...
የነበረው ክፍተት ፣ አንድ ስንዝር ነበር።
አንቺ ሰማይ ሆነሽ እኔ ደግሞ ምድር!!!
............................................
በዚህ ስንዝር መሀል....
እስትንፋስ ያላቸው ሰዎች ተፈጠሩ
እነዚህ ሰዎችም....
ቅርብ ላለች ሰማይ
የምድርን ሀጥያት ይነግሯት ጀመሩ።
"ምድር ዘማዊ ነው
ምድር ሀጣዊ ነው
ብትሸሺው ይሻላል ይህ ዓለም ጠፊ ነው"
እያሉ ሲነግሯት የሰው ወሬ ሰምታ
ሰማይ ፊኛ ሆና...
ትለጠጥ ጀመረ ከኔ ተለይታ
በሰዎች እስትንፋስ...
ወደ ላይ ተነፍታ
ወደጎንም ሰፍታ።
.......................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
................................................
እንደውም እንደውም...
በዛ ስንዝር መሀል ያኔ የተፈጠሩ
እዛሬ ላይ ሆነው..
"ሰማይ ቅርብ ነበር" እያሉ ሚያወሩ
እድሜ የሰጣቸው
ጥቂት ሰዎች አሉ
የኔና ያንቺ ፍቅር የሚመሰክሩ።
.............................................
እንደውም እንደውም....
ሌላ አይነት ማስረጃ ሌላ አይነት ምስክር
ሰማይ ቅርብ ሳለሽ ምጣድ ሆኜ ምድር
እንዲህ እንደዛሬው...
ነፋስ አቀጣጥሎት
ነፋስ የሚያጠፋው እሳት ሳይፈጠር
የሰው ልጆች ሁሉ
በፀሐይ በርሀን ምግብ ያበስሉ ነበር።
.............................................
ፀሐይ ውበትሽ ነው ጠዋት የምሞቀው
ቀን ተቃጥዬበት ሌት የምናፍቀው።
ለሊት ላይ ያመኛል ህመሜም አንቺው ነሽ
ቀኑ ጨለማ ነው...
ነግቶ እስካይሽ ድረስ ትናፍቂኛለሽ።
...........................................
መቼ ነው ሚነጋው?
ፀሐዩ ውበትሽ ምድርን የሚከድነው
መርዙ መድሀኒትሽ...
በሽታዬን ገድሎ ህመሜን ሚያድነው
ካፈቀሩት ጋራ....
እንኳን ላንድ ለሊት
ላፍታ ያህል እንኳን መለያየት ሞት ነው።
.............................................
መቼ ነው ሚነጋው ልቤን ይበርደኛል
ንጋት ላይ የሚሸሽ..
ወረተኛ ፍቅር ጤዛው በዝቶብኛል
አንቺ የሌለሽበት...
ራሴን ሳስበው ራሴን ያዞረኛል።
ለራስ ምታት ህመም..
መድሀኒት እንዲሆን
በሽታን የሚገድል መርዝ ነው ሚቀመም።
...................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ.
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
..በበላይ በቀለ ወያ..
#ናፍቆት

"የሃምሌ ዶፍ መጣ
ብርድ ተከናንቦ
ውርጭ አዝሎ ባንቀልባ፣
ሙቀቴ አንች ነበርሽ
ዘንድሮስ ምን ልሁን-የት አባቴ ልግባ?"
ብሎ ሰው ቢቀኝም፣
እንደዚህ ማርገድ ግን
እኔስ አያምረኝም።
እኔማ...
በጠራራ ፀሃይ-ገላ በሚያቃጥል፣
የለበሱትን ጨርቅ-የትሙን በሚያስጥል፣
እጠብቅሻለሁ-ካቦርቴን ደርቤ፣
በሳሳ አካላቴ-ናፍቆት ተኮንቤ።
እጠብቅሻለሁ...
ቁሩ ቢወበራም
መስኮቴን ከፍቼ ሳንቃየን ሳልዘጋ፣
አንቺ የሌለሽበት
መች ይበርዳል ክረምት
መች ይሞቃል በጋ?

🔘በዘነበ ወላ 🔘
👍1
#ናፍቆት



እንዲህ እንደዛሬ...
በመሀከላችን
ንፋስ ሳይግባብን ፣ ፍጥረት ሳይፈጠር
በኔና አንቺ መሀል...
የነበረው ክፍተት ፣ አንድ ስንዝር ነበር።
አንቺ ሰማይ ሆነሽ እኔ ደግሞ ምድር!!!

በዚህ ስንዝር መሀል....
እስትንፋስ ያላቸው ሰዎች ተፈጠሩ
እነዚህ ሰዎችም....
ቅርብ ላለች ሰማይ
የምድርን ሀጥያት ይነግሯት ጀመሩ።
"ምድር ዘማዊ ነው
ምድር ሀጣዊ ነው
ብትሸሺው ይሻላል ይህ ዓለም ጠፊ ነው"
እያሉ ሲነግሯት የሰው ወሬ ሰምታ
ሰማይ ፊኛ ሆና...
ትለጠጥ ጀመረ ከኔ ተለይታ
በሰዎች እስትንፋስ...
ወደ ላይ ተነፍታ
ወደጎንም ሰፍታ።

እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።

እንደውም እንደውም...
በዛ ስንዝር መሀል ያኔ የተፈጠሩ
እዛሬ ላይ ሆነው..
"ሰማይ ቅርብ ነበር" እያሉ ሚያወሩ
እድሜ የሰጣቸው
ጥቂት ሰዎች አሉ
የኔና ያንቺ ፍቅር የሚመሰክሩ።

እንደውም እንደውም....
ሌላ አይነት ማስረጃ ሌላ አይነት ምስክር
ሰማይ ቅርብ ሳለሽ ምጣድ ሆኜ ምድር
እንዲህ እንደዛሬው...
ነፋስ አቀጣጥሎት
ነፋስ የሚያጠፋው እሳት ሳይፈጠር
የሰው ልጆች ሁሉ
በፀሐይ በርሀን ምግብ ያበስሉ ነበር።

ፀሐይ ውበትሽ ነው ጠዋት የምሞቀው
ቀን ተቃጥዬበት ሌት የምናፍቀው።
ለሊት ላይ ያመኛል ህመሜም አንቺው ነሽ
ቀኑ ጨለማ ነው...
ነግቶ እስካይሽ ድረስ ትናፍቂኛለሽ።

መቼ ነው ሚነጋው?
ፀሐዩ ውበትሽ ምድርን የሚከድነው
መርዙ መድሀኒትሽ...
በሽታዬን ገድሎ ህመሜን ሚያድነው
ካፈቀሩት ጋራ....
እንኳን ላንድ ለሊት
ላፍታ ያህል እንኳን መለያየት ሞት ነው።

መቼ ነው ሚነጋው ልቤን ይበርደኛል
ንጋት ላይ የሚሸሽ..
ወረተኛ ፍቅር ጤዛው በዝቶብኛል
አንቺ የሌለሽበት...
ራሴን ሳስበው ራሴን ያዞረኛል።
ለራስ ምታት ህመም..
መድሀኒት እንዲሆን
በሽታን የሚገድል መርዝ ነው ሚቀመም።

እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ.
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።

እየሔዱ መጠበቅ


በላይ በቀለ ወያ
1