ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
1.85K subscribers
842 photos
55 videos
20 files
394 links
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ።
ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን።

We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
Download Telegram
'እኔ ማን ነኝ?' የሚለውን ጥያቄ ለራሳችሁ ጠይቁና በአንድ ቃል ወይም ሐረግ ብቻ መልሱን አቀብሉን። በአዲሱ አደባባይ በኢንተርኔት አማካኝነት በሚካሄደው የዚህ አመት የ ጥበብ በአደባባይ ኦንላይን ፌስቲቫል ላይ መልሳችሁን ግጥማችን ውስጥ ተካትቶ ታገኙታላችሁ።

መልሳችሁን ከስር ባለው
Show Comments በሚለው ቁልፍ በጽሁፍ አድርሱን ወይም እራሳችሁን በቪድዮ በመቅረጽ መልሱን ብቻ በመናገር #ግጥምሲጥም ብላችሁ በማንኛውም የማህበራዊ ሚድያ በኩል አጋሩን።

ማን ነሽ? - ማን ነህ? - ማን ናችሁ?

በአንድ ቃል ወይም ሐረግ ብቻ በመመለስ ቃልና ሃሳብ አቀብሉን - አብረን ግጥም እንጻፍ። ምናልባትም ብዙ ሰው በማሳተፍ ቀዳሚው የሚሆን ግጥም አብረን እንፈጥር ይሆናል።

ተመስገኑልን!

#ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ስነ_ግጥም #ሙዚቃ #gitemsitem #tibebbeadebabay #poetry #music #Yisaacandfriends #digitalartfestival #artinaddis #tba

http://tibebbeadebabay.org/
Forwarded from ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem (S e i f e - T e m a m)
'እኔ ማን ነኝ?' የሚለውን ጥያቄ ለራሳችሁ ጠይቁና በአንድ ቃል ወይም ሐረግ ብቻ መልሱን አቀብሉን። በአዲሱ አደባባይ በኢንተርኔት አማካኝነት በሚካሄደው የዚህ አመት የ ጥበብ በአደባባይ ኦንላይን ፌስቲቫል ላይ መልሳችሁን ግጥማችን ውስጥ ተካትቶ ታገኙታላችሁ።

መልሳችሁን ከስር ባለው
Show Comments በሚለው ቁልፍ በጽሁፍ አድርሱን ወይም እራሳችሁን በቪድዮ በመቅረጽ መልሱን ብቻ በመናገር #ግጥምሲጥም ብላችሁ በማንኛውም የማህበራዊ ሚድያ በኩል አጋሩን።

ማን ነሽ? - ማን ነህ? - ማን ናችሁ?

በአንድ ቃል ወይም ሐረግ ብቻ በመመለስ ቃልና ሃሳብ አቀብሉን - አብረን ግጥም እንጻፍ። ምናልባትም ብዙ ሰው በማሳተፍ ቀዳሚው የሚሆን ግጥም አብረን እንፈጥር ይሆናል።

ተመስገኑልን!

#ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ስነ_ግጥም #ሙዚቃ #gitemsitem #tibebbeadebabay #poetry #music #Yisaacandfriends #digitalartfestival #artinaddis #tba

http://tibebbeadebabay.org/
ግጥም ሲጥምን በጥበብ በአደባባይ
ቅዳሜ፣ ነሐሴ 30 ከቀኑ 8:30 ጀምሮ

'እኔ ማነኝ? የሚለውን ጥያቄ በስነግጥም እንፈትሻለን በሙዚቃ ባለሞያው ይዛቅና በባንዱ የተደረሱ ኦሪጅናል ሙዚቃዎችም አሉን።

ፒያሳ ከሚገኘው ሃይ5 ፒዛና ቡና ዘመኑ በከሰተልን ሌላው አደባባይ በኢንተርኔት አማካኝነት በዙምና በፌስቡክ በቀጥታ ከያላችሁበት እንደርሳለን።

ለመታደም ማስፈንጠሪያውን (ሊንኩን) ተጠቀሙ። ከእኛ ወደእናንተ የሚደርስ ብቻ ሳይሆን እናንተንም የሚያሳትፍ ነውና ተሳትፋችሁም ተሸለሙ።

https://us02web.zoom.us/j/82843118327?pwd=b0tVUVZqZ1JHaU5BUkIwM29URFBzQT09

#ግጥምሲጥም #ይዛቅ #ጥበብበአደባባይ #ሃይ5
#tba #gitemsitem #yizaac #artinaddis #tibebbeadebabay #digitalartfestival #hi5pizzaandcoffee #hi5
'እኔ ማን ነኝ?' የሚለውን ጥያቄ ለራሳችሁ ጠይቁና መልሱን አቀብሉን ባልናችሁ መሰረት የሰበሰብናቸው ቃላት ይህን ይመስላሉ።

መልሳችሁን ምስሉ ውስጥ አገኛችሁት?

#ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#gitemsitem #tibebbeadebabay #tba #tba2020 #artinaddis #digitalartfestival #poeticsaturdays
~የጠበበኝ እኔ
(ሀናን ሁሴን)

በጥልፍልፍ ጉያ የተሰነቀርኩ
በጥብቅ መቀነት የተሰረሰርኩ
በጎታች እትብት ወግ የተሰየምኩ

እኔ የታፈንኩኝ ...እኔ

ከስዬ አላበቃሁ ግና ነው መጫሬ
ከአመዱ ስር ነው ውሎና አዳሬ
በትኜ ለመውጣት ከተዳፈንኩበት
ለትንፋሽ የሚሆን አየር ልስብበት
አመድን ምቾቴ ከማለት በሩቅ ስርቅ
በደራው ሂደቴ ሙቀትን መኖሬን ማሳብቅ

እኔ.... የጠበበኝ እኔ

ብናኝ ሲውጠኝ ተከማችቶ
ዝቆ አስተንፋሽን ገፍቶ
ግለቴ ቢያጎላው መኖሬን
ሊያየኝ የዳዳው ከብናኝ መደበኝ
ቀርቦ ሳይምሰው ከአመድ አስጠጋኝ

እኔ....የጠበበኝ እኔ

በጥልፍልፍ ጉያ የተሰነቀርኩ
በጥብቅ መቀነት የተሰረሰርኩ
በጎታች እትብት ወግ የተሰየምኩ

እኔ....የታፈንኩኝ እኔ

ከባቢው ያፍናል
ላያፈናፍን ይጋፋል
በክብደቱ የውስጥ ጠሊቅን ያናጋል
ከሸክሙ አስማምቶ አየር ያሳጣል።
ሽቅብ ለመቃናት
በነፃነት ለመቃኘት
ከስር ቆሰቆስኩ
ውስጤን አጋልኩ
ክምሩን ብሰጋ
ከአመድ አልረጋ
ጠፍቼ ያልጠፋሁ እኔ ነኝ የተዳፈንኩ....
አመዱን ገርስሼ ብቅ ልል የደፈርኩ...

እኔ...የጠበበኝ እኔ

#hanan_hussen #ሀናን_ሁሴን #ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#tba #tibebbeqdebabay #digitalartfestival #artinaddis
የቱ ጋር?
(ቶማስ አድማሱ)

ከአድዋ በፊት ያው ከድሉም ኋላ
ላንድ የዝና ታሪክ ላንድ የጋራ ጥላ
እንዴት ታጣ መላ?
እንደ ሰው ወደታች ያወረደን ማነው?
ከአድዋ ኋላ የቱ ጋር ነው የቆምነው?
*
እጃችን ማሸነፍ ረስቶ
ልባችን ወኔ ተነስቶ
ነፍሳችን ሃቅ እውነት ስቶ!
በካቻምና ታሪክ ዜማ
ልብ ባይን ሲደማ።
እዚያ ጋር ነው የቆምን እግር በእግር ሲወጋ?
ባንዲራ ላብ ማበስ ትቶ እግር ጠልፎ ሲያዋጋ፡፡
አያምም??
/ያማል/
ጎን ላይ እንደመወጋት
ተሰቅሎ በችንካር ቅጣት
ሆምጣጤ ከከርቤ ቅንጣት
ከሰፍነግ ላይ እንደመጋት፡፡
እሳት ላይ እንደቆመ እግር
እንደ ሰፋ የአራሽ ድግር
ያሸነፉት ሲያሸንፍ የጣሉት መልሶ ሲጥል
ሲያቃጥል!!!
*
“መንገዳችን ያሳዝናል”
የምንሄደው ያሰጋናል
አሁን ደሞ እንዲህ ሆነናል
/እንዲህ/
ይሁዳን እያሞገሱ ከዮሐንስ ጋር መጣለት
እዚህ በርባንን መስደብ በዚያ በኩል መስቀል መጥላት
በጉን ወዶ ተንከባክቦ ምን ይሉታል መጠየፍ ላት??
***
የጣልናቸው እየጣሉን
ያዘልናቸው እየጠሉን
እውነት?
አፈር አፈርን በላ?
ድንጋይ ድንጋይ ላይ ሰላ?
የቱ ጋር ነው የቆምን ከአድዋ ኋላ??

#ቶማስአድማሱ #ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#ThomasAdmasu #tba #tibebbeqdebabay #digitalartfestival #artinaddis #gitemsitem
መንገደኛ
(ሰይፈ ተማም)

ከደመናት ቅድስናን የምቀዳ
በጉንዳን መስመር ‘ምቀና
በልቤም በ’ግሬም ‘ማቀና
ረቂቅ የመንገድ ጀግና

ከየትም ወዴት ያልመጣሁ
ካለመኖር ውስጥ ኖሬ - ከመኖር መዝገብ የታጣሁ
መጣህብኝ ባይ የሌለኝ
መንገድ ነኝ - መንገደኛ ነኝ

ካልነበረውም ወደ ነበረው መጥቼ
ያልነበረውም ሲነብር አይቼ
እርጥበት ላይ ትኩሳትን
እርኩሰት ላይ ምርቃትን
እርግበት ላይ ክርራትን
እየበተንኩ የማቀና
በጉንዳን መስመር ‘ምቀና
ረቂቅ የመንገድ ጀግና
መ ን ገ ደ ኛ

በቅድስናም ሆነ በፍልስፍና ‘ምነጉድ
‘ሚያመጣ ‘ሚወስደኝ መንገድ
የሆንኩት ሁሉ ቢሰፈር
ቢመጣ ቢሄድ ቢቀመር
ቢለካ በሰፈር ባገር
ቢመተር በቀለም በዘር
ስዘረፍ ቅኔ ወርቅ አሰር
ስታሰር ስንኝ ምቋጠር
ስቋጠርም ስንቅ ‘ምካፈል
ስካፈል አሸዋ ‘ምገረፍ
ስገረፍ ቅኝት ‘ምካረር
ንዝረት ነኝ ያውታር በገና
በጉንዳን መስመር ‘ምቀና
በልቤም በ'ግሬም 'ማቀና
ረቂቅ የመንገድ ጀግና
መ ን ገ ደ ኛ

#ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#seifetemam #gitemsitem #poeticsaturdays #tba #tibeb2020 #tibebbeadebabay #digitalartfestival #artinaddis
እኔ ፀሐይ

እሰይ አደይ ፈነዳች፤
የመስከረም ፀሐይ ወጣች፤
አበባየሁ አሉ ልጆች፤
አበባ ያልያዙ እጆች፤
በምርቃት ሊወለዱ 30 እና 60 ጥጆች፤
ቀልዬ ከሶሪት ላባ፤
ካባቴ ገቦ ወጥቼ ከናቴ ማ'ጸን ስገባ፤
ይኸው መስከረም ጠባ።
እልል አበብሽ ብዬ
ለምለም አደይ ነቅዬ፤
እንግጫሽ አበባ፤አበባየሽ ለምለም
የመስከረም ጸሐይ ወጣች
ከእንዲህ ነጎድጓድ መፍራት በሰማይ ማማረር የለም።
በክረምት ጠል ርሶ፤ ሊመጣ ጸደይ ያማረ፤
በምርቃት ወንድ ሊሰጥ በሴት አካል ወንድ አደረ።
አበባ ነኝ እኔ አበባ
ከአድማስ ፀሐይ ሳትገባ
መታፈር በከንፈር ያልኩ ጥርሴ መንታ የሚያነባ
ቢጫነት በሆዴ ያለ ልቤ መዓት የሚያደባ፤
አበባ ነኝ እኔ አበባ።
ለወደድኩት የዓይን ጥም
ከካህን ማስር ምፈታ ከደብተራ ምጠመጥም
የጠላሁት የሚሰጥም
ለተናቀ ረባዳ
ለተከበረ ሰው ሜዳ።
አበባ ነኝ እኔ አበባ።
እሰይ አደይ ፈነዳች፤ ይኸው ጳጉሜ ከነዳች።
ከሰማይ ምንም ሳይጎድል ከመሬት ሳይጨምር አንዳች።
(ቶ)በምን አገባኝ ፍካሬ አክናፌን ስዘረጋጋ
(ማ) ነህ ብሎ ለሚያዛጋ
(ስ)ብዬ አፉን የማሲዝ የማልፈጥን የማልረጋ።
መሬት ቢጫ ስትለብስ። የአምናን መከራ አልፌ
እልል የምል ችቦ ወገብ ተደግፌ
ለከርሞ ትልሜን ለፍፌ
የሚል ግጥም ሳሰናዳ
እሰይ አደይ ፈነዳ::

#ቶማስአድማሱ #ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#ThomasAdmasu #tba #tibebbeqdebabay #digitalartfestival #artinaddis #gitemsitem
ጥበብ በአደባባይ የተለያዩ የጥበብ ስራዎችን በገጸ-ድሩ ላይ እያስጎበኘ ይገኛል።
'እኔ ማነኝ?' የሚለውን ዋነኛ ርዕሰ ጉዳዩ አድርጎና 'የስደት ታሪኮችን መንገር' የሚለውን በሁለተኛ መሪ ቃልነት አስከትሎ ባካሄደው የጥበብ ፌስቲቫል ላይ የግጥም ሲጥም ቤተሰቦች በሙሉ ከተሰጡት ርዕሶች ጋር ዝምድና ያላቸውን ግጥሞችም ሆነ ማንኛውንም ዓይነት የጥበብ ስራዎች ለታዳሚ ታቀርቡ ዘንድ ተጋብዛችኋል!
ማስፈንጠሪያውን በመጠቀም ቅጹን ይሙሉና የአውደርዕዩ አካል ይሁኑ።

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdSjNQ_xm8iKTDn_AzqyZwS2jd3e14CaU1TskMBy7GkLKqxbQ/viewform?usp=send_form

You can be part of the exhibition, if you have creative works related to the title "Who am I" and the subtitle "Telling Migrating Stories"

#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥበብበአደባባይ #TBA #tibeb2020 #tibebbeadebabay #gitemsitem #poeticsaturdays #digitalartfestival #artinaddis
የግጥም ሲጥም ወርሃዊ የስነ-ግጥም መጽሔትን ጥበብ በአደባባይ ላይ ባቀረብናቸው ስራዎች አንድ ብለን ለእናንተ ማድረስ ልንጀምር ነው። ገጻችንን ተከታተሉ፣ የድርሻችሁን ዝገኑ እንዲሁም ለግጥም ወዳጆች በማጋራት አጋዙን - እናመሰግናለን።

#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥበብበአደባባይ #የግጥምመጽሔት

We are about to launch our very first edition of the Gitem Sitem monthly poetry booklet. Stay tuned to our channel, get your copy and share with friends. Thank you!

#gietmsitem #poeticsaturdays #tibebbeadebabay #artinaddis #poetrybooklet
Gitem Sitem Monthly Booklet V1.pdf
17.5 MB
አንድ ብለን በመስከረም የጀመርነውን መጽሔት እንሆ አቅርበናል። በቀጣይ መጽሔታችን የእናንተኑ ስራ እንጠብቃለን። በ https://bit.ly/2GbwMgE ጎራ በሉና ቃኘት ቃኘት አድርጋችሁ ስታበቁ አስተያየት አቀብሉን።

ደ'ሞስ! . . . 'እኔ ማነኝ?' የሚለውን ጥያቄ እራሳችሁን ጠይቃችሁ በአንድ ቃል ወይም ሐረግ ብቻ መልሳችሁን ስጡንና ግጥማችን ውስጥ አግኙት ብለን ነበር እኮ . . .

#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥበብበአደባባይ #የግጥምመጽሔት
#gietmsitem #poeticsaturdays #tibebbeadebabay #artinaddis #poetrybooklet

Photo Credit: Poets portraits by Hermela (@AnimaHela) , Adey by Ribki (@Ribki), Picture for I Am or ነኝ። Lella (@Lellich)
Gitem Sitem Monthly Booklet V2.pdf
6.6 MB
የጥቅምትን ወር የግጥም መጽሔት እንሆ አቅርበናል።
በቀጣይ መጽሔታችን የእናንተኑ ስራ እንጠብቃለን።
shorturl.at/gwMO6 ገብታችሁ እዩልን፣ አውርዳችሁም የራሳችሁ ልታደርጉት ትችላላችሁ፣ አንብባችሁ ስታበቁ ግን አስተያየት አቀብሉን።

ግጥማቸውንና ምስሎቻቸውን እያቀበሉ ወሩን ላደመቁልን ሁሉ ምስጋና ይድረስ!!!
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥበብበአደባባይ #የግጥምመጽሔት
#gietmsitem #poeticsaturdays #artinaddis #poetrybooklet

Cover Photo Credit: ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል
ከመልካም በዓል ምኞት ጋር የወርኃ ታህሳስ የግጥም መጽሔትን ዘግየት ብለንም ቢሆን እንሆ አቅርበናል።
በቀጣይ መጽሔታችን የእናንተኑ ስራ እንጠብቃለን።
https://drive.google.com/file/d/1HushONVS9C8XU_xzalz55cis8Ol2KMK5/view?usp=drivesdk ገብታችሁ እዩልን፣ አውርዳችሁም የራሳችሁ ልታደርጉት ትችላላችሁ፣ አንብባችሁ ስታበቁ ግን አስተያየት አቀብሉን።

ግጥማቸውንና ምስሎቻቸውን እያቀበሉ ወሩን ላደመቁልን ሁሉ ምስጋና ይድረስ!!!

#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥበብበአደባባይ #የግጥምመጽሔት
#gietmsitem #poeticsaturdays #artinaddis #poetrybooklet

Cover Sketch Credit: Moon'it