#የኢትዮጵያ_የሃይማኖት_ተቋማት_ጉባኤ_በስልጤ_ዞን #ቅበት_ከተማ_በነዋሪዎች_መካከል_የተፈጠረውን_አለመግባባት_ለመቅረፍ_እየሰራ_መሆኑን_ተገለጸ።
ጉባኤው፤ አለመግባባቱ ከተፈጠረበት ጊዜ አንስቶ ችግሩን ለመፍታት ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አንስቷል፡፡
ረዕቡ ዕለትም የጉባኤው ጠቅላይ ጸሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለን ጨምሮ ሌሎችም የጉባኤው ከፍተኛ የስራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት በጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃዮችን፣ በስልጤ ዞን ቅበት ከተማ የሚገኙ ሀዘንተኛ ቤተሰቦችን እንዲሁም በሕክምና ላይ የሚገኙ ተጎጂዎችን ጎብኝተዋል፡፡
ጉባኤው፤ ለተፈናቃዮች እና ለተጎጂዎችም የገንዘብ እና የአይነት ድጋፍ አድርጓል፡፡
የተፈጠረውን ችግር በውይይት እና በቀደመ የአብሮነት ባህል መፍታት እንደሚገባ የተናገሩት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ፤ የኅብረተሰቡ ፍላጎት በጋራ መኖር እንጂ መለያየት አለመሆኑን በጉብኝታችን መረዳት ችለናል ብለዋል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎች ለዓመታት በመከባበር የኖሩ መሆናቸውን ያነሱት ጠቅላይ ጸሐፊው፤ ቅራኔ የሚፈጥሩ ነገሮችን ከማባባስ ይልቅ አንድነትን በሚያጠናክሩ መንገዶች ላይ ለመወያያት ዝግጁ ስለመሆናቸው አሳውቀዋል፡፡
ከጉብኝቱ በኋላ ከሃይማኖት አባቶች ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን በውይይቱ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው የሚመለሱበት፣ የአከባቢው መስተዳድር ለተፈናቃዮች የህይወት እና የንብረት ዋስትና
ውይይቱ፤ ዛሬ ሀሙስ ዕለትም ቀጥሎ እንደተካሄደ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ አሳውቋል።
ጉባኤው፤ አለመግባባቱ ከተፈጠረበት ጊዜ አንስቶ ችግሩን ለመፍታት ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አንስቷል፡፡
ረዕቡ ዕለትም የጉባኤው ጠቅላይ ጸሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለን ጨምሮ ሌሎችም የጉባኤው ከፍተኛ የስራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት በጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃዮችን፣ በስልጤ ዞን ቅበት ከተማ የሚገኙ ሀዘንተኛ ቤተሰቦችን እንዲሁም በሕክምና ላይ የሚገኙ ተጎጂዎችን ጎብኝተዋል፡፡
ጉባኤው፤ ለተፈናቃዮች እና ለተጎጂዎችም የገንዘብ እና የአይነት ድጋፍ አድርጓል፡፡
የተፈጠረውን ችግር በውይይት እና በቀደመ የአብሮነት ባህል መፍታት እንደሚገባ የተናገሩት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ፤ የኅብረተሰቡ ፍላጎት በጋራ መኖር እንጂ መለያየት አለመሆኑን በጉብኝታችን መረዳት ችለናል ብለዋል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎች ለዓመታት በመከባበር የኖሩ መሆናቸውን ያነሱት ጠቅላይ ጸሐፊው፤ ቅራኔ የሚፈጥሩ ነገሮችን ከማባባስ ይልቅ አንድነትን በሚያጠናክሩ መንገዶች ላይ ለመወያያት ዝግጁ ስለመሆናቸው አሳውቀዋል፡፡
ከጉብኝቱ በኋላ ከሃይማኖት አባቶች ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን በውይይቱ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው የሚመለሱበት፣ የአከባቢው መስተዳድር ለተፈናቃዮች የህይወት እና የንብረት ዋስትና
ውይይቱ፤ ዛሬ ሀሙስ ዕለትም ቀጥሎ እንደተካሄደ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ አሳውቋል።
👍2
#የኢትዮጵያ_የሃይማኖት_ተቋማት ጉባኤ #በኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ_ቤተክርስቲያን እና #በኢትዮጵያወንጌላዊት_ቤተክርስቲያን_መካነ_ኢየሱስ #ንጹሐን_አማኞች_ላይ_የተፈጸመውን_ግድያ በእጅጉ #አዉግዟል።
ጉባኤዉ “በንጹሐን ላይ የሚፈጸም ግድያ፣ ኢሰብአዊ ድርጊትና አያያዝ በሁሉም ሃይማኖቶች የሚወገዝ ወንጀል ነው” ብሏል።
ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ንፁሐን አማኞች ላይ ግድያ መፈጸሙን የሚገልጽ ከሁለቱ አባል ቤተ እምነቶች ካወጡት መግለጫ ተገንዝበናል ያለዉ ጉባኤዉ ድርጊቱ በእጅጉ የሚያሳዝን ከመሆኑም በላይ በሃይማኖት አገልግሎት ላይ የነበሩ ንፁሐን አማኞችን መግደል ደረቅ የወንጀል ተግባር በመሆኑ በእጅጉ የሚወገዝ ድርጊት ነው ብሏል።
በተጨማሪ ባለፈው ዓመት በተለያዩ ቦታዎች ላይ የቤተ ክርስቲኒቱ አማኞች ላይ ግድያ መፈጸሙን በመግለጫው ተገልፃል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ይህ አይነቱ የወንጀል ድርጊት በእጅጉ እያወገዘ የሚመለከተው የመንግስት አካልም የዜጎችንና የሃይማኖት ተቋማትን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅና የማስጠበቅ ሕገ መንግስታዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጉባኤው በአጽንኦት አሳስቧል።
በንጹሐን ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸሙትንም ወንጀለኞች በአፋጣኝ በሕግ ተጠያቂ እንዲያደርግና ፍትህን አንዲያስከብር ይጠይቃል፡፡
ከዚህም ባለፈ በሀገራችን የሚታየው ማንኛውንም ዓይነት ሕገ ወጥ ድርጊት እንዲታረም፣ የዜጎች ሕገ መንግስታዊ መብት ሳይሸራረፍ የመጠበቅ መንግስታዊ ሃላፊነተን ሕግንና መመሪያን መሠረት በማድረግ ሊሠራ ይገባል፡፡
ጉባኤዉ በንፁሀን ላይ ስለተፈጸመው ጥቃትና ግድያ በድጋሚ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በመግለፅ ለሟች ቤተሰቦች፣ ወዳጆች ዘመዶች እንዲሁም ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እና ለኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢያሱስ አባቶችና መሪዎች ልባዊ መጽናናትን ተመኝቷል።
#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -https://youtu.be/8f0kbYG0EJM
ቴሌግራም፦ https://tttttt.me/EGBCC
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!
ጉባኤዉ “በንጹሐን ላይ የሚፈጸም ግድያ፣ ኢሰብአዊ ድርጊትና አያያዝ በሁሉም ሃይማኖቶች የሚወገዝ ወንጀል ነው” ብሏል።
ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ንፁሐን አማኞች ላይ ግድያ መፈጸሙን የሚገልጽ ከሁለቱ አባል ቤተ እምነቶች ካወጡት መግለጫ ተገንዝበናል ያለዉ ጉባኤዉ ድርጊቱ በእጅጉ የሚያሳዝን ከመሆኑም በላይ በሃይማኖት አገልግሎት ላይ የነበሩ ንፁሐን አማኞችን መግደል ደረቅ የወንጀል ተግባር በመሆኑ በእጅጉ የሚወገዝ ድርጊት ነው ብሏል።
በተጨማሪ ባለፈው ዓመት በተለያዩ ቦታዎች ላይ የቤተ ክርስቲኒቱ አማኞች ላይ ግድያ መፈጸሙን በመግለጫው ተገልፃል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ይህ አይነቱ የወንጀል ድርጊት በእጅጉ እያወገዘ የሚመለከተው የመንግስት አካልም የዜጎችንና የሃይማኖት ተቋማትን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅና የማስጠበቅ ሕገ መንግስታዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጉባኤው በአጽንኦት አሳስቧል።
በንጹሐን ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸሙትንም ወንጀለኞች በአፋጣኝ በሕግ ተጠያቂ እንዲያደርግና ፍትህን አንዲያስከብር ይጠይቃል፡፡
ከዚህም ባለፈ በሀገራችን የሚታየው ማንኛውንም ዓይነት ሕገ ወጥ ድርጊት እንዲታረም፣ የዜጎች ሕገ መንግስታዊ መብት ሳይሸራረፍ የመጠበቅ መንግስታዊ ሃላፊነተን ሕግንና መመሪያን መሠረት በማድረግ ሊሠራ ይገባል፡፡
ጉባኤዉ በንፁሀን ላይ ስለተፈጸመው ጥቃትና ግድያ በድጋሚ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በመግለፅ ለሟች ቤተሰቦች፣ ወዳጆች ዘመዶች እንዲሁም ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እና ለኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢያሱስ አባቶችና መሪዎች ልባዊ መጽናናትን ተመኝቷል።
#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -https://youtu.be/8f0kbYG0EJM
ቴሌግራም፦ https://tttttt.me/EGBCC
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.