YeneTube
118K subscribers
31.4K photos
485 videos
79 files
3.87K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
#Update በስሜን #ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ ገደላማ አካባቢዎች የተከሰተውን ሰደድ #እሳት መቆጣጠር እንዳልተቻለ የኢትዮዽያ ዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። እስካሁን #በ343 ሄክታት ላይ ጉዳት #መድረሱንም ባለስልጣኑ ገልጿል።

የአካባቢው ወጣቶች፣ የጸጥታ አካላት እና የፓርክ ሰራተኞች እሳቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል እየሰሩ መሆኑን ባለስልጣኑ የገለጸ ሲሆን በስልጠና ላይ ያሉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የተለያዩ መሳሪያዎችን በመያዝ ወደ ስፍራው ማቅናታቸውንም አስታውቋል።

ምንጭ:- ElU
@YeneTube @FikerAssefa