YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የኢትዮጵያ የአየር መንገድ ከ41 ዓመታት በኋላ ወደ ሞቃዲሾ በረራ #ጀምሯል

የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ #ተወልደ ገብረማርያም አየር መንገዱ በዛሬው እለት ወደ #ሞቃዲሾ በይፋ በረራ መጀመሩን ተናግረዋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው እንደገለጹት የበረራው መጀመር #የሁለቱን ሀገራት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እና ንግድ ያጠናክረዋል።

በመላው ዓለም የሚገኘውን የሶማሊያ ዳያስፖራ ወደ ሃገራቸው እንዲገቡ በማድረግ #ሶማሊያን እንደገና ለመገንባት በሚደረገው ሂደት ትልቅ ሚና እንደሚኖረውም ነው የተናገሩት።
©FBC
@yenetube @mycase27