YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ የማብራት ሀይል ለሰራተኞች እና ለመንገደኞች እጃቸውን እንዲታጠብ እጅ መታጠቢያ ለሰራተኞች ግቢ ውስጥ ለተላላፊ እግረኞች ከግቢ ውጪ የእግረኛ መንገድ ጋር አዘጋጅተዋል።

@Yenetube @Fikerassefa
በ13ኛው ዙር እጣ የወጣባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች እየተከናወነ ያለው የውል ስምምነት የወሰን ወዝግብ ያለባቸውን ቤቶች አያካትትም፡፡

ሰሞኑን በተለያየ የግል ምክንያት እጣ ወጥቶላቸው ውል ያልተፈራረሙ እድለኞችን ውል የማፈራረም ስራ እተከናወነ ይገኛል፡፡

ቤቶቹን የማስተላለፍ አካል የሆነው የውል ሰምምነትም በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት እና አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መካከል የወሰን ጥያቄ የተነሳባቸውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች አያካትትም፡፡

የወሰን ጥያቄ የተነሳባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ጉዳይ በፌዴራል መንግስት በተቋቋመው ኮሚቴ ፤ በኦሮሚያ ክልል እና አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በኩል እየታየ ይገኛል፡፡

Via:- Mayor Office
@Yenetube @Fikerassefa
የዶ/ር ሊ ጉዳይ ዛሬ ይፋ ሆነ

የቻይና መንግስት እ.ኤ.አ. በየካቲት 7 ቀን በኮሮና ቫይረስ ሂወቱ ያለፈውና ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ ሌሎች ሰዎችን ለማስጠንቀቅ በመሞከር በ ዉሃን በፖሊስ ከተነቀፈው ሐኪም ጋር የተደረገው የምርመራ ውጤት የቻይና መንግሥት ሐሙስ ዕለት ይፋ አደረገ ። በዉሃን ሆስፒታል ውስጥ የሚሠራው የ 34 አመቱ ሊ በ 30 ዲሴምበር በደረሰው ወረርሽኝ ላይ የመንግስት ሰነዶችን በማኅበራዊ ሚዲያ በመላክና ሌሎችም ወደ ውጭ እንዳይወጡ ማስጠንቀቁን ብሔራዊ ባለሥልጣኖቹ አረጋግጠዋል፡፡

የወረርሽኙ ዋና ከተማ የሆነችው የዉሃን የአከባቢ ፖሊስ ከዚያን በኋላ ጥር 3 ቀን ሊን በመጥራት መደበኛ የሆነ ወቀሳ ሰጠው፡፡ የመንግሥት መርማሪዎችም ሊ በጠና ከታመመ ተገቢው ህክምና እንዳገኘና ሁሉም የሕክምና ሂደቶች በእሱ ወይም በቤተሰቡ ተቀባይነት እንዳገኙ ተናግረዋል፡፡

ባለ ሥልጣናቱ የአካባቢ ፖሊስ የፖሊሱን ወቀሳ አግባብ ያልሆነ የሕግ አተገባበር ላይ በመመርኮዝ “አግባብነት የለውም” ብለው ደምድመዋል፡፡

የመንግሥት መርማሪ አካላት የአካባቢውን ፖሊሶች ወቀሳውን እንዲተው እና ተገቢውን የሰራተኞች ተጠያቂነት እንዲኖራቸው አሳስበዋል።

Via:- CNN #YeneTube
@Yenetube @Fikerassefa
ኢትዮጵያ ውስጥ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው ዛሬ ሰባት ደርሷል ።

ምንጭ:- ፎርቹን አዲስ ጋዜጣ

@Yenetube @Fikerassefa
ኢትዮጵያን 7ተኛው በኮሮና ቫይረስ ተጠቂ ተገኘ

- ግለሰቡ አውስትራልያዊ መሆኑ ታውቋል

-ማርች 16 ነበር ወደ ኢትዮጵያ የገባው ከ ስዊዘርላንድ

- ግለሰብ እራሱን ለይቶ አቆይቶ ነበር የካ ኮተቤ ሆስፒታል እስኪ ደርስ

Via:- ፎርቹን አዲስ ጋዜጣ
@Yenetube @Fikerassefa
#CBE 10 ሚልዮን ብር ድጋፍ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ለሚደረገው ጥረት የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል። ባንኩ በዛሬው እለት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ለጤና ሚኒስቴር የ10 ሚሊየን ብር አስረክቧል።

@Yenetube @Fikerassefa
#Breaking ከዛሬ 5:00pm ጀምሮ በመላው አሜሪካ ሁሉም ተቋማት ለ2ሳምንት እንደሚዘጉና ሁሉም በየቤቱ ኳራንቲን በመሆን የኮሮና ቫይረስን ስርጭት ለመከላከል እንደታሰበ ስለሰማሁ በቀራችሁ 5 ሰዓት የጎደላችሁን በማሟላት ወደ ቤታችሁ እንድትሰባሰቡ ይሁን::

ራቅ ያለ መንገድ የጀመራችሁም ብትመለሱ ጥሩ ነው::

ይህንንም ለማስፈጸም በመላው አሜሪካ ወታደር ሊሰማራ መሆኑንም ሰምቻለሁ:: መጠንቀቅ እንጂ መደናገጥ ተገቢ እይደለም:: ተባብረን ይህንን ወረርሽን ለማቆም ከፍተኛ ጥረት ማድረግ አለብን::

Via:- Fistum Arega
@YeneTube @FikerAssefa
💥ማስታወቂያ💥
School of American English

📌ቻይንኛ
📌ፈረንሳይኛ
📌ጀርመንኛ
📌ጣልያንኛ
📌አፋን ኦሮሞ
📌አረብኛ

አንቱታን ባተፈሩ መምህራን እናስተምራለን

አድራሻዎቻችን ⬇️
ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ +251919913021
ፒያሳ ፒያሳ ገበያ ማዕከል +251919913023
22 ጎላጎል ህንፃ 6ተኛ ፎቅ +251919913022


💥💥💥10% Discount 💥💥💥💥

ቅናሹን ለመጠቀም
ይህንን ፓስት screenshot አድርገው መያዝና ስመጡ ማሣየት ይኖርብዎታል

T.me/SCHOOLOFAMERICAN
ለቅድመ ጥንቃቄ ሲባል እጅግ አስፈላጊ ከሆኑ ስብሰባዎች ወጪ ያሉ ስብሰባዎች እንዳይደረጉ መባሉ ይታወቃል።

ሆኖም በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች ስብሰባዎች እየተደረጉ መሆናቸውን መረጃዎች ደርሰውናል።

ስለሆነም ለቅድመ ጥንቃቄ ሲባል በከተማዋ ስብሰባዎች እንዳይደረጉና አስፈላጊ ናቸው ተብሎ ከታመነም ቁጥሩ እጅግ አነስተኛ ሰው እንዲሳተፍበትና ርቀቱን በጠበቀ መልኩ እንዲካሄድ እናሳስባለን።

@YeneTube @Fikerassefa
በኮሮና ቫይረስ ኢትዮጵያ ውስጥ የተያዙ ሰዎች ብዛት ዘጠኝ ደርሷል።
@Yenetube @Fikerassefa
ኢትዮጵያ በቫይረስ የተያዙ ቁጥር 9 ደርሷል

-አንደኛው 44 ጃፓናዊ ሲሆኑ ( ከመጀመሪያው ጋር ንክኪ ነበረው )

- ሁለተኛው የ85 አመት ዕድሜ ያላቸው ሲሆኑ የካቲት 23 ነበር ከውጪ የመጡት ከመጡበት ቀን ጀምሮ እራሳቸውን መለየታቸውም ተነግሯል።

- ሶስተኛው ግለሰብ 39 አመት ኦስትራዊ ዜጋ ሲሆን መጋቢት 6 ነበር ወደ ሀገር የገባ።

- ሁለቱ ታማሚዎች ጥሩ ሁኔታ ላይ ናቸው ከ85 አመቱ ዕድሜ ታማሚ ግን ከባድ የሚባል ህመም ሲኖራቸው እስፈላጊውን ክትትል እየተደረገላቸው ነው።

@Yenetube @fikerassefa
የኮሮና ወረርሽኝ በኢኮኖሚ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት በመለየት የሚቻለውን ለማድረግ መንግሥት እንቅስቃሴ ጀምሯል – ጠ/ሚ ዐቢይ

የኮሮና ወረርሽኝ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተጨባጭ ጉዳት ፈጥኖ በመለየት የሚቻለውን ሁሉ ለማድረግ መንግሥት እንቅስቃሴ መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት የጤና ባለሙያዎችን አመስግነው፥ “ጀግኖቹ የጤና ባለሙያዎቻችን ሕዝብን ከስቃይ ለመታደግ አያሌ መሥዋዕትነት ከፍለዋል፤ በሁሉም የጦር ግንባሮች ከመከላከያ ሠራዊታችን ጎን ተሰልፈው ለድንበራችን መከበርና ለሉዓላዊነታችን መረጋገጥ ሕይወታቸውን ሰጥተዋል” ብለዋል።

”እኛ ጤና እንድንሆን ሁሉም ጤና ይሁን” በሚለው መርሕ መሠረት፣ ሀገርን እና ሕዝብን ወክለው በኢቦላ ወረርሽኝ ወቅት፣ ከ150 በላይ የሚሆኑ የጤና ባለሙያዎቻችን ወደ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በመጓዝ አፍሪካውያን ወንድሞቻችንን አገልግለው በድል መመለሳቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ መሆኑንም አንስተዋል።

ተደምረን የማንሻገረው ፈተና፣ ተባብረን የማናልፈው መከራ አይኖርም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን የመከላከል ዘመቻ፣ የጤና ባለሙያዎቻችን ግምባር ቀደም ተሰላፊ በመሆን እስከ አሁን ላከናወኑት አኩሪ ገድል በኢፌዴሪ መንግሥትና በራሳቸው ስም ምስጋና አቅርበዋል።

“ፈተናውን በድል መወጣት እስከሚቻል ድረስ መንግሥት ሁሉንም ኃይሎች አስተባብሮ ከእናንተና ከቤተሰቦቻችሁ ጎን እስከ መጨረሻው የሚሰለፍ መሆኑን አረጋግጥላችኋለሁ” ሲሉም ገልፀዋል።

- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
የፊት ማስክ አጠቃቀም እና አወጋገድ

- የፊት ማስኮን ከማድረግ በፊት እጅም በሳሙና መታጠብ።

- በማስኩ አፍና አፍንጫን መሸፈን ምንም ክፍተት ሳይኖረው።

- ማስኩ አፍንጫዎ ላይ እንደተመጠ እንዲቆይ የአፍና የአፊንጫዎን ጠርዝ በጣቶ መጫን።

- ማስኩን በሚያወልቁበት ወቅት ክዳን ባለው ቆሻሻ መጣያ ውስጥ ይጣሉት ወይንም ያቃጥሉት።

- ማስኩን አድርገው እያለ ማስኩን በእጆ ባይነኩ ይመረጣል። ለመንካት ከፈለጉም እጆን በሳሙና ታጥበው መሆን አለበት


#ሼር ያድርጉ መልክቶቻችንን
@Yenetube @Fikerassefa
በማሊ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት 29 ወታደሮች ተገደሉ

በማሊ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት 29 ወታደሮች ተገደሉ። ጥቃቱ የተፈጸመው በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል ታርኪንት በሚገኘው የጦሩ ካምፕ ላይ መሆኑን መንግስት ገልጿል። በጥቃቱ ከሞቱት በተጨማሪ ሌሎች አምስት ወታደሮች መቁሰላቸው ተነግሯል። ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የሚነገርላቸው ታጣቂዎቹ በሰሀራ አካባቢ ባሉ ሀገራት ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት እያደረሱ እንደሚገኙ ተመላክቷል።

-FBC
@YeneTube @Fikerassefa
ካች የሰኘ አዲስ የራይድ አገልግሎት የሚሰጥ አፕሊኬሽን በዚህ ሳምንት ወደ ስራ ይገባል።

ካች ዋና መስሪያቤቱ ጅቡቲ መሆኑንም ሰምተናል።
@Yenetube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ትናንት ሌሊት በደረሱ የእሳት አደጋዎች 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር መውደሙ ተገልጿል።

የእሳት እና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን እንዳስታወቀው በትላንትናው እለት በደረሰ እሳት አደጋ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን አስታውቃል፡፡አደጋው በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ጎፋ ገብርኤል አካባቢ ባለ ጋራዥ ቤት የተፈጠረ ሲሆን በአደጋው 2 ነብ 5 ሚሊዮን ብር ወድሟል።አደጋውን ለመቆጣጠር ለአምስት ሰዓት እልክ አስጨራሽ ትግል መካሄዱን ኮሚሽኑ ገልጿል።በተደረገው ርብርብም 30 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ማዳን ተችሏል ተብሏል።

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ 20 ሚሊየን ብር መደበ

-FBC
@YeneTube @Fikerassefa
ኮሜዲያን ፍልፍሉ ባልተገባ ቦታ መኪናው አቁመሀል በሚል ዛሬ ቻርጅ ተፅፎበታል።

ፍልፍሉም "የማህበራዊ ሀላፊነቴን በመውጣት ላይ ነኝ ህብረተሰቡን እጁን እንዲታጠብ በማስተማር ላይ ነኝ " በማለት ተማፅኗት ነበር ትራፊኳን ነገር ግን ትራፊኳ #ቅጣት_ፅፋበታለች

በዚህ ሰዐት ፍልፍሉን መቅጣት ነው የሚቀድመው ወይስ #ህብረተሰብን_ስለ_ንፅህና_ማስተማር ?

Photo :- Samuel Getachew
@Yenetube @Fikerassefa
ተማሪዎች በራዲዮ ትምህርት መከታተል ይቻችላ።

በኮሮና ቫይረስ ምክኒያት ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ተማሪዎች በቤታቸው ሆነው የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያን መከታተል ይችላሉ ተብሏል፡፡ ትምህርት በሬዲዮ ሳምንታዊ የትምህርት ስርጭት ክፍለ ጊዜ ድልድል ይፋ ተደርጓል፡፡

@Yenetube @Fikerassefa