YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
70 አዳዲስ የአንበሳ አውቶብሶች ወደ ከተማዋ ገብተዋል።

እነዚህ አዳዲስ አውቶብሶች መጨናነቅን በመቀነስ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የሚደረጉ ጥረቶችን ለመከላከል ያግዛል ተብሏል።

ከገቡት ውስጥ 70 አውቶብሶች ዛሬ ወደ ስራ የገቡ ሲሆን ቀሪዎቹም በቀጣይ ቀናት ወደ ስራ እንደሚገቡ ከከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኢምባሲ በአዲስ አበባ የሚኖሩ የውጭ ዜጎች ላይ ጥቃት እየተሰነዘረ መሆኑን አስታወቀ።

ኢምባሲው በድረገጹ እንዳስታወቀው በአዲስ አበባ የውጭ አገራት ዜጎች ሲንቀሳቀሱ ኮሮና አመጣችሁብን፣በእናንተ ምክንያት ነው በቫይረሱ የተጠቃነው በሚል ነዋሪዎች ጥቃት እያደረሱ ነው ብሏል።

ጥቃቱ በድንጋይ ከመምታት ጀምሮ፣ወደ ታክሲ እንዳይገቡ መከልከል፣ መስደብ እና ሌሎች ድርጊቶች በነጮች ላይ እየተፈጸመ በመሆኑ አሜሪካዊያንን ጨምሮ ሁሉም ነጭ ዜጋ በቤታቸው እንዲቆየ መክሯል።

Via:- American Embassy - Ethio FM
@Yenetube @Fikerassefa
በሃዋሳ ከተማ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉ እና ባዕድ ነገር ቀላቅለው ለገበያ ባቀረቡ አካላት ላይ እርምጃ ተወሰደ

በሃዋሳ ከተማ የኮሮና ቫይረስን መከሰት ምክንያት በማድረግ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉ እና ባዕድ ነገር በመቀላቀል ለገበያ ሲያቀርቡ በነበሩ አካላት ላይ እርምጃ ተወሰደ። የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ደቡብ ቅርንጫፍ፣ የደቡብ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪና የሀዋሳ ከተማ ንግድ መምሪያ ባደረጉት ድንገተኛ አሰሳ ነው እርምጃ ሊወሰድባቸው የቻለው።

Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
የአማራ ክልል ምክር ቤት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል #150_ሚሊዮን ብር እንዲመደብ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡ ከተለያዩ አካላት በዓይነትና በገንዘብ ሀብት የሚያሰባስብ ኮሚቴ እንዲሁም ውሳኔ የሚያስተላልፍ ኮማንድ ፖስት አዋቅሯል፡፡

በተያያዘ መረጃ ከኮረና ተህዋሲ ጋር በተገናኘ በክልሉ በሚገኙ 82 ሆስፒታሎች የመለያ ቦታ መዘጋጀቱን የአማራ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር መልካሙ አብቴ ገልጸዋል። 132 የጤና ሙያተኞችም ተዘጋጅተዋል።

@Yenetube @Fikerassefa
የኮሮናን ተህዋሲ ለመከላከል የክልሉ ፍርድ ቤቶች ከመጋቢት 10-24/2012 ዓ.ም ድረስ ለ15 ቀናት በከፊል ዝግ ሆነው እንደሚቆዩ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ።

@Yenetube @Fikerassefa
#ህንድ

ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በህንድ ሀገር የሚገኙ የሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች የትኛውም የስልክ ጥሪ ከመጀመሩ በፊት ለ 30 ሴኮንድ ስለ ኮሮና ቫይረስ ትምህርት መስጠት ጀምረዋል።

@Yenetube @Fikerassefa
የኮሮና ቫይረስ ምልክቶች ሲታዩ የሚደረጉ ነገሮች እና ቫይረሱን ለመከላከል ስለሚደረጉ ጥንቃቄዎች በማወቅና በመተግበር ጤናዎን ይጠብቁ!

#የጤና_ሚንስትር
@Yenetube @Fikerassefa
ከ3 ሚሊየን ሊትር ቴክኒካል አልኮል መኖሩን አስታወቀ።

የስኳር ኮርፖሬሽን ለንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ማዘጋጃ የሚያገለግል ከ3 ሚሊየን ሊትር ቴክኒካል አልኮል መኖሩን አስታወቀ።

ኮርፖሬሽኑ ለጣቢያችን በላከው መግለጫ አልኮሉ በፊንጫ እና መተሐራ ስኳር ፋብሪካዎች እንደሚገኝ አስታውቋል።

አሁን ላይም ፋብሪካዎቹ በቀን 100 ሺህ ሊትር ቴክኒካል አልኮል በማምረት ላይ መሆናቸውን ጠቅሶ፥ አልኮሉ የዓለም ስጋት የሆነውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት የሚያግዙ የንጽህና መጠበቂያዎችን ለማምረት እንደሚውል ገልጿል።

በቂ የቴክኒካል አልኮል ክምችት መኖሩን የጠቀሰው ኮርፖሬሽኑ ከጤና እና ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር ከዚህ ቀደም ይወስዱ ከነበሩ ድርጅቶች በተጨማሪ ሰባት ድርጅቶች አልኮል እንዲወስዱ ተፈቅዷልም ነው ያለው።

ቴክኒካል አልኮል ለሳኒታይዘር፣ ለደረቅና ፈሳሽ ሳሙና እንዲሁም ለመጸዳጃ ቤት ማጽጃ መስሪያ በግብዓትነት ያገለግላል።

Via:- FBC
@YeneTube @Fikerassefa
በተፈጥሯዊ መንገድ በሽታ የመከላከል አቅምን እንዴት ማሳደግ ይቻላል?

1.ጭንቀትን መቀነስ

2. በቀን ቢያንስ 2 ሊትር ውሃ መጠጣት

3. የአልኮል መጠንን እጅጉን መቀነስ

4. ምግባችን ውስጥ አትክልት እና ፍራፍሬ ማዘውተር

5. ሰፕሊመንቶች መውሰድ

6. በቂ አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ

7. በቂ እንቅልፍ ማግኘት

8. ሲጋራ ማጨስን ማቆም

10. የፀሐይ ብርሀን ማግኘት

11. እጅን በሳሙና መታጠብ

ጤናችንን መጠበቅ ላይ ማተኮር መሠረታዊ ነው፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ከተያዙት አራቱ የህመም ምልክቶችን ማሳየት ማቆማቸው ተገለፀ

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ከተያዙት አራቱ የህመም ምልክቶችን ማሳየት ማቆማቸውን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለፁ።

-በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ተይዘው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው የሚገኙ 6 ታካሚዎች ናቸው።

-ከእነዚህም አራቱ የህመም ምልክቶችን ማሳየት ያቆሙና በደህና ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ተብሏል።

- ሁለቱ ታካሚዎች በማገገም ላይ በመሆናቸው የቅርብ ህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ነው ብለዋል።

Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
#ኮሮና ህፃናትን ያጠ ቃል?

የኮሮና ቫይረሱ ህጻናትን አያጠቃም በሚል እየተነገረ ያለው የተሳሳተ መረጃ ነው፡፡

ይህ ህጻናትን አያጠቃም የሚለው መረጃ የተሳሳተ መሆኑና ቫይረሱ በሁሉም የእድሜ ክልል ላይ ያለን ሰው እንደሚያጠቃ ባለሙያዎች በመግለጽ ላይ ናቸው፡፡

ለአብነትም በቻይና ከ2 ሺህ በላይ ልጆች እንደተጠቁና አንድ የ14 አመት ልጅም ህይወቱ እንዳለፈ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

በደቡብ አፍሪካም እንዲሁ እድሜያቸው ከ5 አመት በታች የሆኑ 4 ህጻናት በቫይረሱ እንደተጠቁ ታውቋል ።

ምንም እንኳን ቫይረሱ በዕድሜ የገፉ ሰዎችን በከፍተኛ ደረጃ እያጠቃ ነው ይባል እንጂ ህፃናትም በቫይረሱ በመያዝና ከሞት መትረፍ አለመቻላቸው ከተላያዩ የዜና ምጮች ያገኘናቸው መረጃዎች ጠቁመዋል።

ምንጭ:- ኢቢኤስ አዲስ ነገር
@Yenetube @Fikerassefa
የፊት ማስክ አጠቃቀም እና አወጋገድ

- የፊት ማስኮን ከማድረግ በፊት እጅም በሳሙና መታጠብ።

- በማስኩ አፍና አፍንጫን መሸፈን ምንም ክፍተት ሳይኖረው።

- ማስኩ አፍንጫዎ ላይ እንደተመጠ እንዲቆይ የአፍና የአፊንጫዎን ጠርዝ በጣቶ መጫን።

- ማስኩን በሚያወልቁበት ወቅት ክዳን ባለው ቆሻሻ መጣያ ውስጥ ይጣሉት ወይንም ያቃጥሉት።

- ማስኩን አድርገው እያለ ማስኩን በእጆ ባይነኩ ይመረጣል። ለመንካት ከፈለጉም እጆን በሳሙና ታጥበው መሆን አለበት


#ሼር ያድርጉ መልክቶቻችንን
@Yenetube @Fikerassefa
ናይ ኮሮና ሕማም ንምክልኻል ኣብ ከባቢና ብቀሊሉ ዝርከቡን ዋግኦም ብተመጣጣኒ ዋጋ ክንረኽቦም ንኽእል እታዎታት ክንጥቀም ንኽእል ኢና።

1. Disinfectant; እንጥቀመሎም ኣቑሑት፣ ከም ናይ በሪ መኽፈቲ ዝበሉ ነገራት ንምጽራይ በረኪና ምጥቃም ንኽእል ኢና።

1.1 ኣደላልዋ; ኣብ ሃገርና ብኣብዝሓ ዝርከብ በረኪና 70% ክሎሪን ዝሓዘ አዩ። እዚ ዓይነት በረኪና 1 ኢድ በረኪና 9 ኢድ ድማ ማይ ብምግባር ክነዳሉ ንክእል ኢና። ዘዳለናዮ ዉሁድ ኣብ ዘይንጥቀመሉ አዋን ብደንቢ ክንከድኖ ይግባእ።

2.Hand sanitizer; ኣእዳውና ኣዘውቲርና ክንሕፀበሉ ኣብ ዘይንኽእለሉ ኩነታት፣ ናይ ማይ ሕፅረት ኣብ ዝህልወሉ ኩነታትን ዝመሳሰሉ ግዚያትን hand sanitizer ምጥቃም ይምከር። ናይዞም ምህርትታት ሕፅረት ኣብ ዕዳጋ ብምህላዉ ኣማራጺታት ምጥቃም ንኽእል ኢና።
ኣልኮል; ብኣብዝሓ ኣብ ዕዳጋ ዘሎ ኣልኮል 70% ሕፍሰት (Concentration) ዘለዎ እዩ። CDC እንጥቀመሎም ናይ ኢድ መፅረዪ ኣልኮል መጠን 60%ን ካብኡ ንላዕሊን ክኮኑ ይመክር። ኣልኮል ንበይኑ ብተደጋጋሚ ምጥቃም ቆርበት ስለ ዘድርቕ ምስ ግሪሲሊን ምሕዋስ ይክኣል እዩ።

2.1 ኣደላልዋ; 9 ኢድ ኣልኮል ምስ ሓደ ኢድ ግሪሲሊን ምሕዋስ። ናይ ኣልኮል ሽታ ዘሸግሮ ሰብ ንእሽተይ ጨና ክውስኸሉ ይኽእል እዩ።

@YeneTube @Fikerassefa
Dhukkuba koroonaa ittisuudhaf haala salphaan naannoo keenyaatti kan argammani fi gaatii salphaa ta'een faayyadamu dandeenya
1. Disinfectant ; meeshaa itti faayyadamnu, qabanno balbala fi kaneen kan fakkaatan qulqullessudhaf barakina fayyadamu dandeenya.

1. 1 haala itti qophessan bayyinan fi barakinan biyya kessa jiru concentration 70% qaba. Barakina akkasi; barakina harka 1 bishaan harka 9 goone qopheessu dandeenya. Wantota walitti makamani qopha'an yeroo itti hin fayyadamne haalan qadadame ta'uu qaba.

2. Hand sanitizer harka keenya yeroo mara dhiqachuu yoo hin dandeenye, hanqina bishaani kan qabu fi kanen kan fakkatan yeroo hand sanitizer fayyadamu dandeenya. Omishni wareen kan gabarratti hanqinna qabachuun isaa filannoowwan gargar fayyadamu dandeenya.

Alkolin baayinan gaba irra jiru alkolii concentration 70% qabudha.CDC Qulqullina harkaaf kan fayyadamnu Alkoli 60% fi isaa ol akka ta'uu gorsa.
Alkoli qofa fayyadamun goga keenya waan gogsuuf girisilin dukka fayyadamu dandeenya .

2.1 Haala itti qophessan alkoli harka 9 girisilin harka 1 dukka walitti makudhan fooli alkolii nama jequuf shito xiqqo itti dabaluu hin damda'a.

Via:-samrawit
@Yenetube @Fikerassefa
#ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ_አህመድ_ያስተላለፉት መልክት

ህብረተሰቡ እነዚህን ምክሮች በመከተል እራሱን እና ቤተሰቦቹን ከበሽታው እንዲከላከል አሳስባለሁ።

* እጃችንን በውሃ እና በሳሙና አዘውትሮ መታጠብ

* የጉንፋን ምልክት ከታየብን ከቤት አለመውጣት፣ ሰው የሚበዛብት ቦታ አለመሄድ

* ንክኪ የሚያስፈልጋቸው የሰላምታ መንገዶችን መተው

* ሰው በብዛት የሚሰበሰብባቸው ቦታዎች ላይ የሚገኙ ከሆነ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ

* ህብረተሰቡ ሳይደናገጥ በንቃት የራሱን እና የቤተሰቡን ጤና መጠበቅ

Via:- አብይ አህመድ
@Yenetube @FikerAssefa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሰላም🙌

የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመቀነስ:

እባክዎን እጆቾን በሳሙና በደንብ ይታጠቡ። በሚያስሉበት ግዜ አፍ እና አፍንጫዎትን በክርኖ ይሸፍኑ።

አላስፈላጊ የእጅ መጨባበጥን ያስወግዱ።

የጤና ባለሞያዎችን ምክር በአንክሮ ይከታተላሉ።
@Yenetube @fikerassefa
#በኢራን በኮሮና ሳቢያ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ጨምሯል

የኢራን መንግስት ዜጎች የሚሰጣቸውን የጤና ምክር ካልሰሙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሀገሪቱ ዜጎች ሊሞቱ ይችላሉ አለ፡፡

ኢራን ከቻይናና ጣልያን ቀጥሎ በቫይረሱ ክፉኛ የተጠቃች ሀገር ስትሆን ቫይረሱ አሁን 147 ሰዎች ህይወትን የቀጠፈ ሲሆን አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 1135 ደርሷል፡፡

በኢራን በቫይረሱ የተያዙ ቁጥር ደግሞ 17 ሺ መድረሱን ነው የህክምና ባለስልጣናት የሚናገሩት፡፡

የጤና ባለሙያዎች እንደሚሉት በእድሜ የገፋና የቆየ የጤና እክል ያለባቸው ሰዎች በሽታውን የመቋቋም አቅማቸውም ደካማ መሆኑ ይገለፃሉ፡፡

ይህንን ተከትሎ በቫይረሱ ሳቢያ አንድ የእምነት ስፍራ በመንግስት እንዲዘጋ ተደርጓል።

ምንጭ:- ኢቢኤስ አዲስ ነገር
@Yenetube @Fikerassefa
ቀኑን ሙሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችን ተራረቃችሁ ተሰለፉ ስንል ውለን አሁን ከመሸ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ሰራተኖች ከ50 በላይ ተፋፍገው በገፃቸው ላይ ለቀዋል።

አረ ጎበዝ ከማን እንማር ?
@Yenetube @Fikerassefa
#በጣልያን ከፍተኛ ሞት ተመዘገበ!!

ጣልያን ዛሬ ከ4,207 ሰዎች በላይ በቫይረሱ ተጠቅተዋል እንዲሁም ዛሬ ከ475 ሰዎች በላይ ህይወታቸውን በቫይረሱ ምክንያት አጥተዋል።

በአጠቃላይ በጣልያን ከ3,5713 በላይ በቫይረሱ ተጠቅተዋል እንዲሁም በአጠቃላይ ከ2,978 ሰዎች ሞቷል።

@Yenetube @FikerAssefa