የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና ከሚያደርገው በርከት ያለ ቀጥተኛ በረራ አንፃር ቫይረሱን ወደ አፍሪካ ሊያስገባ የሚችልበት እድል ከፍተኛ ነው ተብሏል።
ከላይ በምስሉ ላይ እደምትመለከቱት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቻይናን ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር በማገናኘት ቀዳሚ ሆኖ ይታያል።
ምስሉ የቢቢሲ ነው!
@YeneTube @FikerAssefa
ከላይ በምስሉ ላይ እደምትመለከቱት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቻይናን ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር በማገናኘት ቀዳሚ ሆኖ ይታያል።
ምስሉ የቢቢሲ ነው!
@YeneTube @FikerAssefa
የጃዋር መሀመድ ጥበቃዎች መነሳታቸውን ኦቢኤን ዘገበ!
በቅርቡ ኦፌኮን የተቀላቀሉት ጃዋር መሃመድ የፌደራል ፖሊስ ሲያደርግላቸው የነበረውን ጥበቃ ከእሁድ ጥር 17/2012 ጀምሮ ማንሳቱን የኦሮሚያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን አስታወቀ፡፡ኦቢኤን በምሽት ሁለት ሰአት ዜናው ላይ አንዳስነበበው መንግስት ለማንኛውም ተፎካካሪ ፓርቲ አመራርም ሆነ አባል የግል ጥበቃ ስለማያደርግ እና አሰራሩም ስለማይፈቅድ ጥበቃዎቹ እንደተነሱ የፌደራል ፖሊስ አስታውቋል፡፡አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ደግሞ አደረኩት ባለው ማጣራት ጃዋር ጠባቂዎቻቸው ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ እንዲያደርጉ የፌደራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ዘርፍ በፃፈው ደብዳቤ ማስታወቁን አረጋግጫለው ብሏል፡፡የጋዜጣው ኤዲቶሪያል ክፍል ወደ ጃዋር መሃመድ በተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ ባደርግም ለግዜው አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል ብሏል፡፡
#Updated
ሁሉ ሰላም ነው ከፌዴራል ፖሊስ ጋር ተወያይተን የተስማማንበት ነው ብሏል ጃዋር መሃመድ
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
በቅርቡ ኦፌኮን የተቀላቀሉት ጃዋር መሃመድ የፌደራል ፖሊስ ሲያደርግላቸው የነበረውን ጥበቃ ከእሁድ ጥር 17/2012 ጀምሮ ማንሳቱን የኦሮሚያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን አስታወቀ፡፡ኦቢኤን በምሽት ሁለት ሰአት ዜናው ላይ አንዳስነበበው መንግስት ለማንኛውም ተፎካካሪ ፓርቲ አመራርም ሆነ አባል የግል ጥበቃ ስለማያደርግ እና አሰራሩም ስለማይፈቅድ ጥበቃዎቹ እንደተነሱ የፌደራል ፖሊስ አስታውቋል፡፡አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ደግሞ አደረኩት ባለው ማጣራት ጃዋር ጠባቂዎቻቸው ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ እንዲያደርጉ የፌደራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ዘርፍ በፃፈው ደብዳቤ ማስታወቁን አረጋግጫለው ብሏል፡፡የጋዜጣው ኤዲቶሪያል ክፍል ወደ ጃዋር መሃመድ በተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ ባደርግም ለግዜው አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል ብሏል፡፡
#Updated
ሁሉ ሰላም ነው ከፌዴራል ፖሊስ ጋር ተወያይተን የተስማማንበት ነው ብሏል ጃዋር መሃመድ
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
በባምባሲ ወረዳ ሰሞኑን ማንነታቸው ያልታወቁ አካላት ቦሽማ ቀርኪኪ ቀበሌ ገብተው ጉዳት ለማድረስ ቢሞክሩም በህብረተሰቡ ላይ የከፋ ጉዳት አለመድረሱ ተገለጸ፡፡
የባምባሲ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱላሂ መሀመድ ጉዳዩን አስመልክተው እንደገለጹት ባለፈው ጥር 25/2012 ዓ.ም ማንነታቸው ያልታወቁ አካላት በወረዳው ቦሽማ ቀርኪኪ ቀበሌ ገብተው እንደነበር ተናግረዋል፡፡እነዚህ አካላት በዚሁ ቀን ከጧቱ 1፡00 አካባቢ ወደ ቀበሌው ሲገቡ የተደራጀ መረጃ ይዘው እንደነበር ያስታወሱት አስተዳዳሪው፣ ከቀበሌ አመራሮች እና ከሚሊሻ አካላት የጦር መሳሪያ ለመዝረፍ የተለያዩ አስገዳጅ ሙከራ ማድረጋቸውን ነው የገለጹት፡፡
በዚህም በቀበሌው አስተዳዳሪ ላይ ድብደባ መፈጸማቸውን የሚናገሩት አቶ አብዱላሂ፣ በአስተዳዳሪው ላይ መጠነኛ የአካል ጉዳት ያደረሱ ሲሆን፣ ህክምና አግኝተው በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙም አመልክተዋል፡፡የወረዳው አስተዳዳሪ አክለውም፣ የጦር መሳሪያ እና ገንዘብ ለመዝረፍ ባደረጉት ሙከራ 1 የመኖሪያ ቤት ሙሉ በሙሉ መቃጠሉን ተናግረዋል፡፡ከዚህ ውጪ ምንም ዓይነት ጉዳት አለመድረሱን የሚናገሩት አቶ አብዱላሂ፣ "ሰዎች ታፍነው ተወስደዋል፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች አሉ" በሚል የሚናፈሰው መረጃ መሠረት የሌለው መሆኑ ሊታወቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
ችግሩ ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የክልሉ ጸጥታ አካላት እና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች በቦታው በመገኘት እየተሠራ ያለው ህብረተሰቡን የማወያዬትና የማረጋጋት ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ጠቁመዋል፡፡ በቀበሌው አሁን ሠላማዊ ሁኔታ መኖሩንም አክልው ገልጸዋል፡፡ በአካባቢው በተለይም የመሬት ወረራ እና መሠል ሌሎች ህገ-ወጥ ፍላጎት በመኖራቸው መንግስት በቀጣይ በዚሁ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ ከህብረተሰቡ ጥያቄ መነሳቱን የጠቀሱት አቶ አብዱላሂ፣ "ወረዳው ችግሮቹን ለመፍታት ትኩረት ሠጥቶ ይሠራል" ብለዋል፡፡
"ከተፈጠረው ክስተት ጋር በተያያዘ ሲገለጹ የነበሩት ህብረተሰቡን የሚያደናግሩ መሠረት የሌላቸው መረጃዎች ሊታረሙ ይገባል" የሚሉት ዋና አስተዳዳሪው፣ "አሁንም ህዝቡ ተረጋግቶ እንዳይኖር የሚፈልጉ አካላት በመኖራቸው፣ ህብረተሰቡ እነዚህን አካላት በመታገል ረገድ ከመንግስት ጎን መቆም ይጠበቅበታል" ሲሉ አሳስበዋል፡፡
ምንጭ: የቤ/ጉ/ብ/ክ/መ/መ/ኮ/ቢሮ
@YeneTube @FikerAssefa
የባምባሲ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱላሂ መሀመድ ጉዳዩን አስመልክተው እንደገለጹት ባለፈው ጥር 25/2012 ዓ.ም ማንነታቸው ያልታወቁ አካላት በወረዳው ቦሽማ ቀርኪኪ ቀበሌ ገብተው እንደነበር ተናግረዋል፡፡እነዚህ አካላት በዚሁ ቀን ከጧቱ 1፡00 አካባቢ ወደ ቀበሌው ሲገቡ የተደራጀ መረጃ ይዘው እንደነበር ያስታወሱት አስተዳዳሪው፣ ከቀበሌ አመራሮች እና ከሚሊሻ አካላት የጦር መሳሪያ ለመዝረፍ የተለያዩ አስገዳጅ ሙከራ ማድረጋቸውን ነው የገለጹት፡፡
በዚህም በቀበሌው አስተዳዳሪ ላይ ድብደባ መፈጸማቸውን የሚናገሩት አቶ አብዱላሂ፣ በአስተዳዳሪው ላይ መጠነኛ የአካል ጉዳት ያደረሱ ሲሆን፣ ህክምና አግኝተው በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙም አመልክተዋል፡፡የወረዳው አስተዳዳሪ አክለውም፣ የጦር መሳሪያ እና ገንዘብ ለመዝረፍ ባደረጉት ሙከራ 1 የመኖሪያ ቤት ሙሉ በሙሉ መቃጠሉን ተናግረዋል፡፡ከዚህ ውጪ ምንም ዓይነት ጉዳት አለመድረሱን የሚናገሩት አቶ አብዱላሂ፣ "ሰዎች ታፍነው ተወስደዋል፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች አሉ" በሚል የሚናፈሰው መረጃ መሠረት የሌለው መሆኑ ሊታወቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
ችግሩ ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የክልሉ ጸጥታ አካላት እና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች በቦታው በመገኘት እየተሠራ ያለው ህብረተሰቡን የማወያዬትና የማረጋጋት ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ጠቁመዋል፡፡ በቀበሌው አሁን ሠላማዊ ሁኔታ መኖሩንም አክልው ገልጸዋል፡፡ በአካባቢው በተለይም የመሬት ወረራ እና መሠል ሌሎች ህገ-ወጥ ፍላጎት በመኖራቸው መንግስት በቀጣይ በዚሁ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ ከህብረተሰቡ ጥያቄ መነሳቱን የጠቀሱት አቶ አብዱላሂ፣ "ወረዳው ችግሮቹን ለመፍታት ትኩረት ሠጥቶ ይሠራል" ብለዋል፡፡
"ከተፈጠረው ክስተት ጋር በተያያዘ ሲገለጹ የነበሩት ህብረተሰቡን የሚያደናግሩ መሠረት የሌላቸው መረጃዎች ሊታረሙ ይገባል" የሚሉት ዋና አስተዳዳሪው፣ "አሁንም ህዝቡ ተረጋግቶ እንዳይኖር የሚፈልጉ አካላት በመኖራቸው፣ ህብረተሰቡ እነዚህን አካላት በመታገል ረገድ ከመንግስት ጎን መቆም ይጠበቅበታል" ሲሉ አሳስበዋል፡፡
ምንጭ: የቤ/ጉ/ብ/ክ/መ/መ/ኮ/ቢሮ
@YeneTube @FikerAssefa
በቻይና የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ከ31 ሺህ ሲያልፍ ከ600 በላይ ሰዎች ለህልፈት ተዳርገዋል!
በቻይና በውሃን ግዛት በተቀሰቀሰ ኮሮና ቫይረስ የሚያዙ እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል።የቻይና ብሄራዊ የጤና ኮሚሽን በዛሬው እለት እንዳስታወቀው በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 636 ደርሷል።ከዚህ ውስጥ አዲስ የ73 ሰዎች ሞት የተመዘገበ ሲሆን፥ 69ኙ ቫይረሱ በተቀሰቀሰባት ሁቤይ ግዛት መሆኑን ኮሚሽኑ አስታውቋል።በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥርም ትናንት ከነበረው በ3 ሺህ 143 ጭማሪ ማሳየቱን እና አሁን ላይ በአጠቃላይ በቻይና በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር 31 ሺህ 161 ማድረሱን የኮሚሽኑ ሪፖርት ያመላክታል።
በቻይና በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸውን ካጡት ውስ፥ በሀገሪቱ የቫይረሱን መቀስቀስ ቀድሞ ያስጠነቀቀው የ34 ዓመቱ ዶክተር ሊ ዌንሊያንግ አንዱ ነው።የዶክተሩ ህልፈት በበርካቶች ዘንድ ቁጣን የቀሰቀሰ ሲሆን፥ የቻይና መንግስትም ምርመራ መጀመሩ ነው የተገለፀው።በተያያዘም የኮሮና ቫይረስ ከቻይና ውጭ በ25 ሀገራት መታየቱን እና በፊሊፒንስ እና በሆንግ ኮንግ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት።የዓለም ጤና ድርጅት የዓለም የጤና ስጋት የሆነውን የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል 675 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር እንድሚያስፈልግ ገልጿል። ሀገራትም ለዚህ ስራ ትብብር እንዲያደርጉም ጥሪውን አቅርቧል።
ቢቢሲን ጠቅሶ ኤፍ.ቢ.ሲ እንደዘገበው
@YeneTube @FikerAssefa
በቻይና በውሃን ግዛት በተቀሰቀሰ ኮሮና ቫይረስ የሚያዙ እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል።የቻይና ብሄራዊ የጤና ኮሚሽን በዛሬው እለት እንዳስታወቀው በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 636 ደርሷል።ከዚህ ውስጥ አዲስ የ73 ሰዎች ሞት የተመዘገበ ሲሆን፥ 69ኙ ቫይረሱ በተቀሰቀሰባት ሁቤይ ግዛት መሆኑን ኮሚሽኑ አስታውቋል።በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥርም ትናንት ከነበረው በ3 ሺህ 143 ጭማሪ ማሳየቱን እና አሁን ላይ በአጠቃላይ በቻይና በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር 31 ሺህ 161 ማድረሱን የኮሚሽኑ ሪፖርት ያመላክታል።
በቻይና በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸውን ካጡት ውስ፥ በሀገሪቱ የቫይረሱን መቀስቀስ ቀድሞ ያስጠነቀቀው የ34 ዓመቱ ዶክተር ሊ ዌንሊያንግ አንዱ ነው።የዶክተሩ ህልፈት በበርካቶች ዘንድ ቁጣን የቀሰቀሰ ሲሆን፥ የቻይና መንግስትም ምርመራ መጀመሩ ነው የተገለፀው።በተያያዘም የኮሮና ቫይረስ ከቻይና ውጭ በ25 ሀገራት መታየቱን እና በፊሊፒንስ እና በሆንግ ኮንግ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት።የዓለም ጤና ድርጅት የዓለም የጤና ስጋት የሆነውን የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል 675 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር እንድሚያስፈልግ ገልጿል። ሀገራትም ለዚህ ስራ ትብብር እንዲያደርጉም ጥሪውን አቅርቧል።
ቢቢሲን ጠቅሶ ኤፍ.ቢ.ሲ እንደዘገበው
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ረጅም ዓመት ያገለገሉ ምስጉን ሰራተኞቹን ሊሸልም ነው።
አየር መንገዱ እንዳስታወቀው በነገው ዕለት ከ20 እስከ 40 አመት ለሰሩ ለ1 ሺህ 200 ሰራተኞች እውቅና እና ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ገልጿል፡፡አየር መንገዱን ለረጅም ጊዜ እና በጡረታ ለተገለሉ ኢትዮጵያዊያን ሰራተኞቹን በነገው እለት ሊያመሰግን እንደሆነ ነው ለኢትዮ ኤፍ ኤም ያስታወቀው፡፡በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሳናድ ከተባለው የአውሮፕላን ጥገና አገልግሎት ሰጪ ኩባንያ ጋር በጋራ መስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድና በአውሮፕላን ሞተር ጥገና የሚታወቀው የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ሳናድ ኤሮቴክ የትብብር ስምምነት መፈራረማቸውን አየር መንገድ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግሯል፡፡የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረ ማሪያም እና የሳናድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ማንሱር ጃናሂ ስምምነቱን በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል።ሳናድ በአውሮፕላን ጥገና እና በአቪዬሽን አካዳሚ መቀመጫውን ዱባይ ያደረገ ረዥም ልምድና አቅም ያለው ተቋም እንደሆነ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
አየር መንገዱ እንዳስታወቀው በነገው ዕለት ከ20 እስከ 40 አመት ለሰሩ ለ1 ሺህ 200 ሰራተኞች እውቅና እና ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ገልጿል፡፡አየር መንገዱን ለረጅም ጊዜ እና በጡረታ ለተገለሉ ኢትዮጵያዊያን ሰራተኞቹን በነገው እለት ሊያመሰግን እንደሆነ ነው ለኢትዮ ኤፍ ኤም ያስታወቀው፡፡በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሳናድ ከተባለው የአውሮፕላን ጥገና አገልግሎት ሰጪ ኩባንያ ጋር በጋራ መስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድና በአውሮፕላን ሞተር ጥገና የሚታወቀው የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ሳናድ ኤሮቴክ የትብብር ስምምነት መፈራረማቸውን አየር መንገድ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግሯል፡፡የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረ ማሪያም እና የሳናድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ማንሱር ጃናሂ ስምምነቱን በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል።ሳናድ በአውሮፕላን ጥገና እና በአቪዬሽን አካዳሚ መቀመጫውን ዱባይ ያደረገ ረዥም ልምድና አቅም ያለው ተቋም እንደሆነ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ኖቬል ኮሮና ቫይረስን አስመልክቶ በህብረተሰብ ጤና ኢንስቲዩት የተዘጋጀ ሳምንታዊ መግለጫ!👇👇👇
➡️ እስከአሁን ድረስ 29 ጥቆማዎች በህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ውስጥ ለሚገኘው የድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ማስተባበሪያ ማዕከል (Emergency Operation Center) ደርሰዋል፡፡ 29ኙ ላይ በተደረገው ማጣራት፣ 14ቱ ምልክቶች ያሳዩ ስለነበረ (suspected cases ) ፤ በሽታው እንዳለባቸው ወይም እንሌለባቸው እስኪረጋገጥ ድረስ በለይቶ ማቆያ ክትትል እየተደረገላቸው ወደ መቆያ ስፍራ (Isolation center)) እንዲገቡ ተደርገዋል፡፡ወደ ደቡብ አፍሪካ 11 ናሙናዎች ተልከው ስምንቱ (8) ከቫይረሱ ነፃ መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን፣ 3 ናሙና ወደ ደቡብ አፍሪካ ተልኮ የምርምራው ውጤት እየተጠበቀ ሲሆን በቀጣዬቹ ቀናት 3 ናሙናዎች ለምርመራ የሚላኩ ይሆናል፡፡
➡️ ከቻይና ዉሃን ከተማ የሚመጡ ማናቸውም መንገደኞች ወደ ለይቶ ማቆያ ማእከል እንዲገቡ ተወስኗል በመሆኑም ወደ ሀገር እንደገቡ በተዘጋጀው ለይቶ ማቆያ ውስጥ ሆነው አስፈላጊው የህክምና ክትትል የሚደረግላቸው ይሆናል፡፡
➡️ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ከቻይና የሚመጡ መንገደኞች ከሌላው መንገደኛ ጋር ሳይቀላቀሉ የሙቀት ምርመራ የሚደረግላቸው ሲሆን በተጨማሪም ከቻይና ለሚመጡ መንገደኞች ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ የኢሚግሬሽን ልዩ መስኮት ተዘጋጅቶላቸዋል፡፡
➡️ ከቻይና የሚመጡ መንገደኞችን የጤና ሁኔታ መከታተል እንዲቻል ለባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቶ አገልግሎቱም ተጀምሯል፡፡
➡️ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ለሚሰሩ ሁሉም አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ እየተሰጠ ይገኛል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በነፃ የስልክ መስመር 8335 ወይም በመደበኛ የስልክ ቁጥር 0118276796 ወይም በኢሜል አድራሻችን
phemdatacenter@gmail.com ወይም ephieoc@gmail.com በመጠቀም ማግኘት ይቻላል፡፡
ምንጭ: ጤና ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
➡️ እስከአሁን ድረስ 29 ጥቆማዎች በህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ውስጥ ለሚገኘው የድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ማስተባበሪያ ማዕከል (Emergency Operation Center) ደርሰዋል፡፡ 29ኙ ላይ በተደረገው ማጣራት፣ 14ቱ ምልክቶች ያሳዩ ስለነበረ (suspected cases ) ፤ በሽታው እንዳለባቸው ወይም እንሌለባቸው እስኪረጋገጥ ድረስ በለይቶ ማቆያ ክትትል እየተደረገላቸው ወደ መቆያ ስፍራ (Isolation center)) እንዲገቡ ተደርገዋል፡፡ወደ ደቡብ አፍሪካ 11 ናሙናዎች ተልከው ስምንቱ (8) ከቫይረሱ ነፃ መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን፣ 3 ናሙና ወደ ደቡብ አፍሪካ ተልኮ የምርምራው ውጤት እየተጠበቀ ሲሆን በቀጣዬቹ ቀናት 3 ናሙናዎች ለምርመራ የሚላኩ ይሆናል፡፡
➡️ ከቻይና ዉሃን ከተማ የሚመጡ ማናቸውም መንገደኞች ወደ ለይቶ ማቆያ ማእከል እንዲገቡ ተወስኗል በመሆኑም ወደ ሀገር እንደገቡ በተዘጋጀው ለይቶ ማቆያ ውስጥ ሆነው አስፈላጊው የህክምና ክትትል የሚደረግላቸው ይሆናል፡፡
➡️ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ከቻይና የሚመጡ መንገደኞች ከሌላው መንገደኛ ጋር ሳይቀላቀሉ የሙቀት ምርመራ የሚደረግላቸው ሲሆን በተጨማሪም ከቻይና ለሚመጡ መንገደኞች ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ የኢሚግሬሽን ልዩ መስኮት ተዘጋጅቶላቸዋል፡፡
➡️ ከቻይና የሚመጡ መንገደኞችን የጤና ሁኔታ መከታተል እንዲቻል ለባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቶ አገልግሎቱም ተጀምሯል፡፡
➡️ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ለሚሰሩ ሁሉም አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ እየተሰጠ ይገኛል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በነፃ የስልክ መስመር 8335 ወይም በመደበኛ የስልክ ቁጥር 0118276796 ወይም በኢሜል አድራሻችን
phemdatacenter@gmail.com ወይም ephieoc@gmail.com በመጠቀም ማግኘት ይቻላል፡፡
ምንጭ: ጤና ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
የኤክስፖርት ዘርፍ ከአምናው የበጀት አመት አጋማሽ አንፃር መጠነኛ መሻሻል ቢያሳይም ማሳካት የተቻለው ግን የዕቅዱን 80 በመቶ ነው፣ በዚህም ባሳለፍነው 6 ወራት 1.33 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል። ከፍተኛ ውጤት ከታየባቸው ዘርፎች አንደኛው የአበባ ንግድ ሲሆን የእቅዱ 183% ማሳካት ተችሏል።
ምንጭ:Capital
@YeneTube @FikerAssefa
ምንጭ:Capital
@YeneTube @FikerAssefa
በደቡብ ክልል በሸካና ቤንች ማጂ ዞኖች የተፈጠረውን ግጭት ለማረጋጋት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ!
በደቡብ ክልል በሸካ እና ቤንች ማጂ ዞኖች የተፈጠረውን ግጭት ለማረጋጋት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ የፀጥታ እና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።ቢሮው እንደገለጸው፥ ባለፉት 2 ሳምንታት ቴፒ ከተማን ጨምሮ በተፈጠረው ግጭት የ7 ሰዎች ህይወት አልፏል።ግጭቱ በአካባቢው የመዋቅር አደረጃጀት ጥያቄን ወደ ግጭት ለመውሰድ በሞከሩ የተደራጁ ቡድኖች የተፈጠረ ስለመሆኑም ገልጿል።ከአንድ አመት ወዲህ በአካባቢው ተደጋጋሚ ግጭቶች ሲከሰቱ ይስተዋላል።
ተጨማሪ👇👇👇😒
https://telegra.ph/BenchiandSheka-02-07
በደቡብ ክልል በሸካ እና ቤንች ማጂ ዞኖች የተፈጠረውን ግጭት ለማረጋጋት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ የፀጥታ እና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።ቢሮው እንደገለጸው፥ ባለፉት 2 ሳምንታት ቴፒ ከተማን ጨምሮ በተፈጠረው ግጭት የ7 ሰዎች ህይወት አልፏል።ግጭቱ በአካባቢው የመዋቅር አደረጃጀት ጥያቄን ወደ ግጭት ለመውሰድ በሞከሩ የተደራጁ ቡድኖች የተፈጠረ ስለመሆኑም ገልጿል።ከአንድ አመት ወዲህ በአካባቢው ተደጋጋሚ ግጭቶች ሲከሰቱ ይስተዋላል።
ተጨማሪ👇👇👇😒
https://telegra.ph/BenchiandSheka-02-07
75 ኢትዮጵያውያን ከእስር ተፈትተው ዛር ሌሊት ከታንዛኒያ ተነስተው ነገ ጠዋት አዲስ አበባ ይገባሉ፤!
ከህገ-ወጥ ስደት ጋር በተያያዘ በታንዛኒያ መንግስት ቁጥጥር ስር ውለው በተለያዩ የታንዛኒያ ግዛቶች ውስጥ በሚገኙ እስር ቤቶች የሚገኙ 1443 ዜጎችን በማስፈታት ወደ አገር ቤት ለመመለስ ኤምባሲው በርካታ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል። በአሁኑ ሰዓትም አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ሁሉ በማጠናቀቅ ዜጎችን የመመለሱን ስራ በይፋ ጀምሯል።ለመጀመሪያ ዙር ጉዞ ዝግጁ የሆኑ 75 ዜጎች ሙትዋራ ሉሉንግዌ ከሚባል እስር ቤት ተፈትተው ዳሬ ሰላም የደረሱ ሲሆን ነገ ከጠዋቱ 1፡30 (7፡30) አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ይደርሳሉ። በቀጣዩ ሳምንትም ከረበዕ ጀምሮ የተቀሩትን ዜጎች የማጓጓዝ ስራው ይቀጥላል።
ዜጎችን ወደ አገር የመመለሱ ስራ በዋናነት በኢትዮጵያ መንግስት የሚከናወን ሲሆን ለ 1443 ዜጎች የአየር ትኬት አቅርቦት የኢትዮጵያ መንግስት ያደርጋል። የዓለም አቀፉ ልደተኞች ድርጅትና የአውሮፓ ህብረት የአገር ውስጥ መጓጓዣ በማቅረብና ወደ አገር ከተመለሱ በኋላ ባለው የመልሶ ሟቋቋም ስራ ውስጥ ይሳተፋሉ።በዳሬ ሰላም ኤምባሲ መከፈቱን ተከትሎ እስከ አሁን ድረስ 1100 የሚሆኑ ዜጎች በተለያየ ወቅት ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መደረጉ የሚታወስ ነው።
ምንጭ: በዳሬሰላም የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@YeneTube @FikerAssefa
ከህገ-ወጥ ስደት ጋር በተያያዘ በታንዛኒያ መንግስት ቁጥጥር ስር ውለው በተለያዩ የታንዛኒያ ግዛቶች ውስጥ በሚገኙ እስር ቤቶች የሚገኙ 1443 ዜጎችን በማስፈታት ወደ አገር ቤት ለመመለስ ኤምባሲው በርካታ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል። በአሁኑ ሰዓትም አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ሁሉ በማጠናቀቅ ዜጎችን የመመለሱን ስራ በይፋ ጀምሯል።ለመጀመሪያ ዙር ጉዞ ዝግጁ የሆኑ 75 ዜጎች ሙትዋራ ሉሉንግዌ ከሚባል እስር ቤት ተፈትተው ዳሬ ሰላም የደረሱ ሲሆን ነገ ከጠዋቱ 1፡30 (7፡30) አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ይደርሳሉ። በቀጣዩ ሳምንትም ከረበዕ ጀምሮ የተቀሩትን ዜጎች የማጓጓዝ ስራው ይቀጥላል።
ዜጎችን ወደ አገር የመመለሱ ስራ በዋናነት በኢትዮጵያ መንግስት የሚከናወን ሲሆን ለ 1443 ዜጎች የአየር ትኬት አቅርቦት የኢትዮጵያ መንግስት ያደርጋል። የዓለም አቀፉ ልደተኞች ድርጅትና የአውሮፓ ህብረት የአገር ውስጥ መጓጓዣ በማቅረብና ወደ አገር ከተመለሱ በኋላ ባለው የመልሶ ሟቋቋም ስራ ውስጥ ይሳተፋሉ።በዳሬ ሰላም ኤምባሲ መከፈቱን ተከትሎ እስከ አሁን ድረስ 1100 የሚሆኑ ዜጎች በተለያየ ወቅት ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መደረጉ የሚታወስ ነው።
ምንጭ: በዳሬሰላም የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@YeneTube @FikerAssefa
ጃፓን በጎዳናዋ የሚንቀሳቀስ መስኪድ ለሙስሊሞች አዘጋጀች።
የተንቀሳቀሽ መስጊዱ በ2020 በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ለሙስሊም ተሳታፊዎች ንፁህና ደህንነቱ የተጠበቀ የፀሎት ስፍራን ማዘጋጀትን አላማው ያደረገ ሲሆን በዚህ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ጃፖን ለሁሉም ሀይማኖት ተከታዮች በተለያዩ የውድድር ስፍራዎች አስፈላጊ መገልገያዎችን ለማዘጋጀት እየተሰናዳች መሆኑ ተጠቁሟል።ይሄ የመጀመሪያው ተንቀሳቃሽ መስጊድ 48 ስኩዌር ሜትር ስፋት ሲኖረው፥ ከመኪናው የኋላ ክፍል የሚከፈት የተሟላ የፀሎት ክፍል አለው 50 ሰወዎችን ማስተናገድ የሚችል ነው።
በጃፓን ከ100,000 እስከ 200,000 ሙስሊሞች እንደሚኖሩ የሚገመት ሲሆን 105 መስጊዶች እንደሚገኙ የሀገሪቱ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች አስታውቀዋል።
Via EOC-Tokyo 2020
@YeneTube @FikerAssefa
የተንቀሳቀሽ መስጊዱ በ2020 በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ለሙስሊም ተሳታፊዎች ንፁህና ደህንነቱ የተጠበቀ የፀሎት ስፍራን ማዘጋጀትን አላማው ያደረገ ሲሆን በዚህ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ጃፖን ለሁሉም ሀይማኖት ተከታዮች በተለያዩ የውድድር ስፍራዎች አስፈላጊ መገልገያዎችን ለማዘጋጀት እየተሰናዳች መሆኑ ተጠቁሟል።ይሄ የመጀመሪያው ተንቀሳቃሽ መስጊድ 48 ስኩዌር ሜትር ስፋት ሲኖረው፥ ከመኪናው የኋላ ክፍል የሚከፈት የተሟላ የፀሎት ክፍል አለው 50 ሰወዎችን ማስተናገድ የሚችል ነው።
በጃፓን ከ100,000 እስከ 200,000 ሙስሊሞች እንደሚኖሩ የሚገመት ሲሆን 105 መስጊዶች እንደሚገኙ የሀገሪቱ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች አስታውቀዋል።
Via EOC-Tokyo 2020
@YeneTube @FikerAssefa
የአፍሪካ ሀገራት እና መንግስታት መሪዎች ለአፍሪካ ህብረት መደበኛ የመሪዎች ጉባኤ አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል።
እስካሁንም የጅቡቲው ፕሬዚዳንት አስማኤል ኦማር ጌሌህ ገብተዋል። ፕሬዚዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደረሱም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ አቀባበል አድርገውላቸዋል።33ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የፊታችን እሁድ እና ሰኞ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ከዚያ ቀደም ብሎ የህብረቱ የስራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ጉባኤም ትናንት እና ዛሬ ተካሂዷል።ጉባኤው “ግጭትና ጦርነትን በማስቆም ለአፍሪካ ልማት ምቹ ሁኔታን ማመቻቸት”በሚል መሪ ቃል ነው በመካሄድ ላይ የሚገኘው።ለጉባኤው ከህብረቱ አባል ሀገራት መሪዎች በተጨማሪ የተመድ ዋና ፀሃፊ እና የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የተለያዩ ዓለም አቀፋዊ እና አህጉራዊ ድርጅቶች ሀላፊዎች ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
እስካሁንም የጅቡቲው ፕሬዚዳንት አስማኤል ኦማር ጌሌህ ገብተዋል። ፕሬዚዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደረሱም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ አቀባበል አድርገውላቸዋል።33ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የፊታችን እሁድ እና ሰኞ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ከዚያ ቀደም ብሎ የህብረቱ የስራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ጉባኤም ትናንት እና ዛሬ ተካሂዷል።ጉባኤው “ግጭትና ጦርነትን በማስቆም ለአፍሪካ ልማት ምቹ ሁኔታን ማመቻቸት”በሚል መሪ ቃል ነው በመካሄድ ላይ የሚገኘው።ለጉባኤው ከህብረቱ አባል ሀገራት መሪዎች በተጨማሪ የተመድ ዋና ፀሃፊ እና የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የተለያዩ ዓለም አቀፋዊ እና አህጉራዊ ድርጅቶች ሀላፊዎች ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሠላምና ፀጥታ ም/ቤት አባል ሆና ተመረጠች!
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሠላምና ፀጥታ ም/ቤት አባል በመሆኗ ለመጪዎቹ ሁለት ዓመታት ለማገልገል በአባልነት ተመርጣለች፡፡ ከምስራቅ አፍሪካ ክልል ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ጅቡቲ ለቀጣዩ ሁለት ዓመታት ለማገልገል ተመርጣለች፡፡የአፍሪካ የሠላምና የፀጥታ ም/ቤት 15 አበላት ያሉት ሲሆን በአፍሪካ ህብረት ግጭትን ለመከላከልና ለመፍታት የተቋቋመ አካል ነው፡፡
ምንጭ: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሠላምና ፀጥታ ም/ቤት አባል በመሆኗ ለመጪዎቹ ሁለት ዓመታት ለማገልገል በአባልነት ተመርጣለች፡፡ ከምስራቅ አፍሪካ ክልል ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ጅቡቲ ለቀጣዩ ሁለት ዓመታት ለማገልገል ተመርጣለች፡፡የአፍሪካ የሠላምና የፀጥታ ም/ቤት 15 አበላት ያሉት ሲሆን በአፍሪካ ህብረት ግጭትን ለመከላከልና ለመፍታት የተቋቋመ አካል ነው፡፡
ምንጭ: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
@YeneTube @FikerAssefa
አፍሪካዊቷ ሀገር ኢኳቶሪያል ጊኒ ቻይና ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ለምታደርገው ጥረት የሚያግዝ የ2 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አድርጋለች ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።
ከዚው ጋር በተገናኘ ቢቢሲ የሁለቱን ሀገራት GDP ለንፅፅር ያቀረበ ሲሆን የቻይና ጥቅል ሀገራዊ ምርት 13.6 ትሪሊዮን ዶላር ሲሆን የኢኳቶሪያክ ጊኒ 13.4 ቢሊዮን ዶላር ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
ከዚው ጋር በተገናኘ ቢቢሲ የሁለቱን ሀገራት GDP ለንፅፅር ያቀረበ ሲሆን የቻይና ጥቅል ሀገራዊ ምርት 13.6 ትሪሊዮን ዶላር ሲሆን የኢኳቶሪያክ ጊኒ 13.4 ቢሊዮን ዶላር ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
የመሰረት ድንጋዩ ዛሬ ይጣላል የተባለው የቡና ፓርክ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ፡፡
የቡና ፓርኩ በአዲስ አበባ በ30 ሄክታር መሬት ላይ በ50 ሚሊየን ዶላር እንደሚገነባ ባሳለፍነው ነሀሴ ላይ ነበር ይፋ የተደረገው።በ50 ሚሊየን ዶላር ይገነባል የተባለው የቡና ፓርክ የመሰረት ድንጋይ ዛሬ የቀመጣል ቢባልም ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያን እስፔሻሊቲ ቡና ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ ያስተዋውቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ የቡና ፓርክ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ማስቀመጥ መርሃ ግብር መራዘሙን ባለስልጣኑ ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል፡፡ባለስልጣኑ ይህ ፕሮግራም ለምን እንደተራዘመ እና የግንባታ መሰረተ ድንጋዩ መቼ እንደሚካሄድ ከመናገር ተቆጥቧል።
ምንጭ:Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የቡና ፓርኩ በአዲስ አበባ በ30 ሄክታር መሬት ላይ በ50 ሚሊየን ዶላር እንደሚገነባ ባሳለፍነው ነሀሴ ላይ ነበር ይፋ የተደረገው።በ50 ሚሊየን ዶላር ይገነባል የተባለው የቡና ፓርክ የመሰረት ድንጋይ ዛሬ የቀመጣል ቢባልም ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያን እስፔሻሊቲ ቡና ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ ያስተዋውቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ የቡና ፓርክ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ማስቀመጥ መርሃ ግብር መራዘሙን ባለስልጣኑ ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል፡፡ባለስልጣኑ ይህ ፕሮግራም ለምን እንደተራዘመ እና የግንባታ መሰረተ ድንጋዩ መቼ እንደሚካሄድ ከመናገር ተቆጥቧል።
ምንጭ:Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ባልተፈቀደ አግባብ የኢትዮጵያን ፓስፖርት በእጃቸው ያስገቡ 29 የውጭ ሀገር ዜጎች ፓስፖርቶችን እንደተሰረዘ የኢምግሬሽን ሃላፊዎች ማስታወቃቸውን ሸገር ዘግቧል፡፡ ፓስፖርት በገንዘብ የገዙ 3 የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር ተባረዋል፤ ሌላኛው ደሞ ሊወጣ ሲል ታስሯል፡፡ ፓስፖርት በሕ ወጥ መንገድ በመስጠት የተጠረጠረ የተቋሙ ሠራተኛ ታስሯል፡፡
Via Wazema Radio
@YeneTube @FikerAssefa
Via Wazema Radio
@YeneTube @FikerAssefa
ሀዲያ ሆሳዕና አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያምን አዲሱ የክለቡ አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ።
ከአሰልጣኝ ግርማ ታደሰ ጋር የተለያየው ሀዲያ ሆሳዕና የቀድሞውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲና አርባምንጭ ከተማ አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያን በምትካቸው ሾሟል።አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያም ዛሬ በክለቡ ጽህፈት ቤት በመገኘት እስከ ውድድር ዓመቱ መጨረሻ ድረስ የሚያቆያቸውን የኮንትራት ፊርማ አኑረዋል።
በቀሪዎቹ የሊጉ ጨዋታዎችም ጥሩ ውጤት በማስመዝገብ ክለቡን በሊጉ ለማቆየት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ክለቡ ከስፖርታዊ ጨዋነት ጋር በተያያዘ ቅጣት እንደተጣለበት ይታወሳል።ዘንድሮ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ያደገው ሀዲያ ሆሳዕና ካደረጋቸው 12 ጨዋታዎች በ7ቱ ተሸንፎ በ9 ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ከክለቡ የፌስ ገጽ ዋቢ አድርጎ ፋና ነው የዘገበው።
@YeneTube @FikerAssefa
ከአሰልጣኝ ግርማ ታደሰ ጋር የተለያየው ሀዲያ ሆሳዕና የቀድሞውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲና አርባምንጭ ከተማ አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያን በምትካቸው ሾሟል።አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያም ዛሬ በክለቡ ጽህፈት ቤት በመገኘት እስከ ውድድር ዓመቱ መጨረሻ ድረስ የሚያቆያቸውን የኮንትራት ፊርማ አኑረዋል።
በቀሪዎቹ የሊጉ ጨዋታዎችም ጥሩ ውጤት በማስመዝገብ ክለቡን በሊጉ ለማቆየት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ክለቡ ከስፖርታዊ ጨዋነት ጋር በተያያዘ ቅጣት እንደተጣለበት ይታወሳል።ዘንድሮ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ያደገው ሀዲያ ሆሳዕና ካደረጋቸው 12 ጨዋታዎች በ7ቱ ተሸንፎ በ9 ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ከክለቡ የፌስ ገጽ ዋቢ አድርጎ ፋና ነው የዘገበው።
@YeneTube @FikerAssefa
የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አቀባበል አድርገውላቸዋል።በቆይታቸው ከፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል።በዚህ ወቅት በሀገራቱ መካከል ሊኖር በሚችለው የኢንቨስትመንት እና ሌሎች የኢኮኖሚ ትብብሮች ዙሪያ ውይይት ይደረጋል።ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋርም የካናዳ ባለሀብቶችም አብረው አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን፥ በነገው እለት በሚካሄደው የቢዝነስ ፎረም ይካፈላሉ ተብሎም ነው የሚጠበቀው።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፈረንጆቹ የካቲት 6 ጀምረው እስከ የካቲት 14 ቀን 2020 በሚቆየው ጉብኝታቸው ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ወደ ሴኔጋል ያቀናሉ።
Via Fana
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አቀባበል አድርገውላቸዋል።በቆይታቸው ከፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል።በዚህ ወቅት በሀገራቱ መካከል ሊኖር በሚችለው የኢንቨስትመንት እና ሌሎች የኢኮኖሚ ትብብሮች ዙሪያ ውይይት ይደረጋል።ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋርም የካናዳ ባለሀብቶችም አብረው አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን፥ በነገው እለት በሚካሄደው የቢዝነስ ፎረም ይካፈላሉ ተብሎም ነው የሚጠበቀው።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፈረንጆቹ የካቲት 6 ጀምረው እስከ የካቲት 14 ቀን 2020 በሚቆየው ጉብኝታቸው ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ወደ ሴኔጋል ያቀናሉ።
Via Fana
@YeneTube @FikerAssefa
#Coronavirusupdate
የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ከሰላሳአንድ ሺህ ያለፈ ሲሆን የሟቾች ቁጥር ደግሞ 637 ደርሷል።
Via AFP
@YeneTube @FikerAssefa
የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ከሰላሳአንድ ሺህ ያለፈ ሲሆን የሟቾች ቁጥር ደግሞ 637 ደርሷል።
Via AFP
@YeneTube @FikerAssefa
#FakeNewsAlert
"ጀነራል ብርሀኑ ጁላ ባልታወቀ ታጣቂ ቆስለዋል" የሚል መልእክት በስፋት ሲሰራጭ ነበር።
ዛሬ ማታ የካናዳው ጠ/ሚር አቀባበል ፕሮግራም ላይ አየናቸው። ነው ወይስ ቶሎ ተሻላቸው? 😊
#StopFakeNews
Via Elias Meseret
@YeneTube @FikerAssefa
"ጀነራል ብርሀኑ ጁላ ባልታወቀ ታጣቂ ቆስለዋል" የሚል መልእክት በስፋት ሲሰራጭ ነበር።
ዛሬ ማታ የካናዳው ጠ/ሚር አቀባበል ፕሮግራም ላይ አየናቸው። ነው ወይስ ቶሎ ተሻላቸው? 😊
#StopFakeNews
Via Elias Meseret
@YeneTube @FikerAssefa
በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው አና በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ በተከሰተ ናዳ ለተፈናቀሉ ወገኖች መቋቋሚያ የሚሆን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳዳር ቃል በገባው መሰረት በዛሬው እለት በአካል በመገኘት የ500 ሺህ ብር ድጋፍ አበረከተ፡፡
በዛሬው እለት የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መስፍን ደነቀ በተገኙበት
➡️የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር በአርባምንጭ ዙርያ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው -የ300 ሺህ ብር
➡️ በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ በተከሰተ ናዳ ለተፈናቀሉ ወገኖች-የ200 ሺህ ብር
➡️የአርባምንጭ ከተማ የንግዱ ማህበረሰብ አካላት በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ በተከሰተ ናዳ ለተፈናቀሉ-በጥሬ ገንዘብ 50ሺህ ብር --የአርባምንጭ ከተማ የንግዱ ማህበረሰብ አካላት በአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው በአይነት 200 ኩንታል በቆሎ
➡️የኦሞቲክ ጄኔራል ትሬዲንግ ( ፓራዳይዝ ሎጂ ) በአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው በአይነት 500መቶ ብርድ ልብስ
➡️የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ በአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው በአይነት 100 ኩኒታል በቆሎ መቋቋሚያ እንዲሆን ድጋፍ አድርገዋል፡፡
ምንጭ: የከተማ አስተዳደሩ ኮ/ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
በዛሬው እለት የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መስፍን ደነቀ በተገኙበት
➡️የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር በአርባምንጭ ዙርያ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው -የ300 ሺህ ብር
➡️ በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ በተከሰተ ናዳ ለተፈናቀሉ ወገኖች-የ200 ሺህ ብር
➡️የአርባምንጭ ከተማ የንግዱ ማህበረሰብ አካላት በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ በተከሰተ ናዳ ለተፈናቀሉ-በጥሬ ገንዘብ 50ሺህ ብር --የአርባምንጭ ከተማ የንግዱ ማህበረሰብ አካላት በአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው በአይነት 200 ኩንታል በቆሎ
➡️የኦሞቲክ ጄኔራል ትሬዲንግ ( ፓራዳይዝ ሎጂ ) በአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው በአይነት 500መቶ ብርድ ልብስ
➡️የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ በአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው በአይነት 100 ኩኒታል በቆሎ መቋቋሚያ እንዲሆን ድጋፍ አድርገዋል፡፡
ምንጭ: የከተማ አስተዳደሩ ኮ/ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa