የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና ለሚበሩ ካፒቲኖች እና የበረራ አስተናጋጆች የሰርጂካል ጭንብል እንዲያጠልቁ አዟል።
ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ ወደ ቻይና የሚያደርገውን ጉዞ እንዲያቆም ግፊት እየተደረገበት ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከባለፈው እሮብ ጀምሮ ወደ ኤዥያ ፣አፍሪካ ፣እና መካከለኛው ምስራቅ ለሚበሩ ለ ካፒቲኖች እና የበረራ አስተናጋጆች የሰርጂካል ጭንብል እንዲያጠልቁ ያዘዘ ሲሆን መልሶ ግን ትናንት አርብ ባወጣው ማስታወቂያ የሰርጂካል ጭንብሉ መጋዘን ውስጥ በቂ ክምችት ስለሌለ ቻይና ለሚበረሩ የካቢን ክሪው አባላቱ ብቻ እንደሚሰጥና መደበኛው አፍ ላይ የሚደረገው ጭንብል ግን ህንድ ፣ጃፓን ፣ሲንጋፓር ፣ፊሊፔንስ ለሚበሩ የካቢን ክሪው አባላት ስራ ላይ ሲሰማሩ እንዲያደርጉ አዟል።
Via:- Fidel Post
@YeneTube @Fikerassefa
ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ ወደ ቻይና የሚያደርገውን ጉዞ እንዲያቆም ግፊት እየተደረገበት ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከባለፈው እሮብ ጀምሮ ወደ ኤዥያ ፣አፍሪካ ፣እና መካከለኛው ምስራቅ ለሚበሩ ለ ካፒቲኖች እና የበረራ አስተናጋጆች የሰርጂካል ጭንብል እንዲያጠልቁ ያዘዘ ሲሆን መልሶ ግን ትናንት አርብ ባወጣው ማስታወቂያ የሰርጂካል ጭንብሉ መጋዘን ውስጥ በቂ ክምችት ስለሌለ ቻይና ለሚበረሩ የካቢን ክሪው አባላቱ ብቻ እንደሚሰጥና መደበኛው አፍ ላይ የሚደረገው ጭንብል ግን ህንድ ፣ጃፓን ፣ሲንጋፓር ፣ፊሊፔንስ ለሚበሩ የካቢን ክሪው አባላት ስራ ላይ ሲሰማሩ እንዲያደርጉ አዟል።
Via:- Fidel Post
@YeneTube @Fikerassefa
የኮሮና ተዋህሲና በኢትዮጵያ የነዋሪዎች ስጋት
የኮሮና ተዋህሲ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ በኢትዮጵያ እስካሁን 29 ጥቆማዎች ታይተው በ14ቱ ላይ የበሽታው አጠራጣሪ ምልክቶች ስለታየባቸው በማቆያ ክትትል እየተደረግባቸው መሆኑን የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት አስታወቀ። ከነዚህ ውስጥ ስምንቱ የደም ናሙናቸው ደቡብ አፍሪካ ተልኮ በተደረገው ምርመራ ነጻ የሆኑ ሲሆን ሌሎች ስድስት ሰዎች ፣ አንዱ ቻይናዊ ፣ አምስቱ ደግሞ ኢትዮጵያዊያን በአሁኑ ወቅት የምርመራ ናሙናቸው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተልኳል ተብሏል።
በጉዳዩ ዙሪያ ዶይቸ ቬለ ያነጋገራቸው አስተያየት ሰጭዎች ቫይረሱ ኢትዮጵያ ውስጥ ይገባል የሚል ከፍተኛ ስጋት እንዳለባቸው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና የሚያደርገውን በረራ ቢያቆም ፍላጎታቸው እንደሆነ ገልጸዋል።
Via:- DW
@YeneTube @Yenetube
የኮሮና ተዋህሲ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ በኢትዮጵያ እስካሁን 29 ጥቆማዎች ታይተው በ14ቱ ላይ የበሽታው አጠራጣሪ ምልክቶች ስለታየባቸው በማቆያ ክትትል እየተደረግባቸው መሆኑን የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት አስታወቀ። ከነዚህ ውስጥ ስምንቱ የደም ናሙናቸው ደቡብ አፍሪካ ተልኮ በተደረገው ምርመራ ነጻ የሆኑ ሲሆን ሌሎች ስድስት ሰዎች ፣ አንዱ ቻይናዊ ፣ አምስቱ ደግሞ ኢትዮጵያዊያን በአሁኑ ወቅት የምርመራ ናሙናቸው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተልኳል ተብሏል።
በጉዳዩ ዙሪያ ዶይቸ ቬለ ያነጋገራቸው አስተያየት ሰጭዎች ቫይረሱ ኢትዮጵያ ውስጥ ይገባል የሚል ከፍተኛ ስጋት እንዳለባቸው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና የሚያደርገውን በረራ ቢያቆም ፍላጎታቸው እንደሆነ ገልጸዋል።
Via:- DW
@YeneTube @Yenetube
የአፍሪካ ሀገራት እና መንግስታት መሪዎች እንዲሁም የሌሎች ሀገራት መሪዎች ለአፍሪካ ህብረት መደበኛ የመሪዎች ጉባኤ ከትናንት ጀምሮ ወደ አዲስ አበባ እየገቡ ነው።
እስካሁንም የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ፣ የጅቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌህ እና የዚምባብዌ ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ አዲስ አበባ ገብተዋል።
በተጨማሪም የካናዳ እና የኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትሮች ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል።መሪዎቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል አድርገውላቸዋል።33ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የፊታችን እሁድ እና ሰኞ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ከዚያ ቀደም ብሎ የህብረቱ የስራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ጉባኤ ትናንት ተጠናቋል።ጉባኤው “ግጭትና ጦርነትን በማስቆም ለአፍሪካ ልማት ምቹ ሁኔታን ማመቻቸት” በሚል መሪ ቃል ነው በመካሄድ ላይ የሚገኘው።ለጉባኤው ከህብረቱ አባል ሀገራት መሪዎች በተጨማሪ የተመድ ዋና ፀሃፊ እና የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የተለያዩ ዓለም አቀፋዊ እና አህጉራዊ ድርጅቶች ሀላፊዎች ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ።
Via Fana
@YeneTube @FikerAssefa
እስካሁንም የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ፣ የጅቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌህ እና የዚምባብዌ ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ አዲስ አበባ ገብተዋል።
በተጨማሪም የካናዳ እና የኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትሮች ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል።መሪዎቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል አድርገውላቸዋል።33ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የፊታችን እሁድ እና ሰኞ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ከዚያ ቀደም ብሎ የህብረቱ የስራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ጉባኤ ትናንት ተጠናቋል።ጉባኤው “ግጭትና ጦርነትን በማስቆም ለአፍሪካ ልማት ምቹ ሁኔታን ማመቻቸት” በሚል መሪ ቃል ነው በመካሄድ ላይ የሚገኘው።ለጉባኤው ከህብረቱ አባል ሀገራት መሪዎች በተጨማሪ የተመድ ዋና ፀሃፊ እና የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የተለያዩ ዓለም አቀፋዊ እና አህጉራዊ ድርጅቶች ሀላፊዎች ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ።
Via Fana
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ እና ልዑካን ቡድናቸውን ዛሬ ማለዳ በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ትሩዶ ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው፣ ካናዳ በአያሌ መስኮች ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደ ሆነች ተናግረዋል።በኢትዮጵያ የሚካሄዱትን ለውጦች እና ሪፎርሞች እንደሚያደንቁና እንደ ወዳጅ፣ ደግሞም እንደ አጋር በጎን ሆነው ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉም አውስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድም በዲሞክራታይዜሽን እና ሁለተናዊ ብልጽግናን በመገንባት ላይ ስለተመሠረቱት ባለብዙ ገጽታ ቀጣይ የሪፎርም ሥራዎች ገልጸዋል።
ሁለቱ ጠቅላይ ሚኒስትሮች የጋራ ፍላጎት በሚስተዋልባቸው የልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ንግድ፣ የኢነርጂ ኢንቨስትመንት፣ አግሮ-ፕሮሰሲንግ፣ መድኃኒት እና ተያያዥ ግብአቶች ላይ በጋራ ስለመሥራት ተወያይተዋል። የቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ በጋራ መሥራትንም አንዱ የትብብር አቅጣጫ አድርገው አንስተዋል።
#PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ትሩዶ ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው፣ ካናዳ በአያሌ መስኮች ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደ ሆነች ተናግረዋል።በኢትዮጵያ የሚካሄዱትን ለውጦች እና ሪፎርሞች እንደሚያደንቁና እንደ ወዳጅ፣ ደግሞም እንደ አጋር በጎን ሆነው ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉም አውስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድም በዲሞክራታይዜሽን እና ሁለተናዊ ብልጽግናን በመገንባት ላይ ስለተመሠረቱት ባለብዙ ገጽታ ቀጣይ የሪፎርም ሥራዎች ገልጸዋል።
ሁለቱ ጠቅላይ ሚኒስትሮች የጋራ ፍላጎት በሚስተዋልባቸው የልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ንግድ፣ የኢነርጂ ኢንቨስትመንት፣ አግሮ-ፕሮሰሲንግ፣ መድኃኒት እና ተያያዥ ግብአቶች ላይ በጋራ ስለመሥራት ተወያይተዋል። የቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ በጋራ መሥራትንም አንዱ የትብብር አቅጣጫ አድርገው አንስተዋል።
#PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
በድሬደዋ ጅቡቲ መንገድ በደረሰ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ አስራ ስድስት ሰዎች ሞቱ!
በሶማሌ ክልል የሲቲ ዞን ትራፊክ ምርመራ ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ጉሌድ ገዲድ እንደገለጹት በድሬደዋ ጅቡቲ መንገድ ከድሬደዋ ሃያ ኪ.ሜ ርቀት ላይ በሚገኘው ላስዴሬ በተባለ ቦታ ንጋት አስራ አንድ ሰዓት ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ አስራ ስድስት ሰዎች ሞተዋል። ኃላፊው እንዳሉት በደረሰው አደጋ አምስት ሰዎች ከባድ እና ሰባት ሰዎች ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ። በግጭት አደጋው ሶስት ሚኒባስ እና ሁለት የጭነት ትራከር ተሽከርካሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። የአደጋው መንስዔ በከፍተኛ ፍጥነት ማሽከርከር እንደሆን የተናገሩት ምክትል ኢንስፔክተር ጉሌድ ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል። በቅርቡ ስራ የጀመረው የድሬደዋ ጅቡቲ የክፍያ መንገድ ከፍጥነት ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ ከፍተኛ አደጋ እያስተናገደ መሆኑን ምክትል ኢንስፔክተር በመግለጫቸው ጠቁመዋል። በደረሰው የትራፊክ አደጋ ሳቢያ ለሰዓታት ዝግ ሆኖ የነበረው የድሬደዋ ጅቡቲ መንገድ በአሁኑ ሰዓት ለትራፊክ ክፍት ተደርጓል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በሶማሌ ክልል የሲቲ ዞን ትራፊክ ምርመራ ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ጉሌድ ገዲድ እንደገለጹት በድሬደዋ ጅቡቲ መንገድ ከድሬደዋ ሃያ ኪ.ሜ ርቀት ላይ በሚገኘው ላስዴሬ በተባለ ቦታ ንጋት አስራ አንድ ሰዓት ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ አስራ ስድስት ሰዎች ሞተዋል። ኃላፊው እንዳሉት በደረሰው አደጋ አምስት ሰዎች ከባድ እና ሰባት ሰዎች ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ። በግጭት አደጋው ሶስት ሚኒባስ እና ሁለት የጭነት ትራከር ተሽከርካሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። የአደጋው መንስዔ በከፍተኛ ፍጥነት ማሽከርከር እንደሆን የተናገሩት ምክትል ኢንስፔክተር ጉሌድ ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል። በቅርቡ ስራ የጀመረው የድሬደዋ ጅቡቲ የክፍያ መንገድ ከፍጥነት ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ ከፍተኛ አደጋ እያስተናገደ መሆኑን ምክትል ኢንስፔክተር በመግለጫቸው ጠቁመዋል። በደረሰው የትራፊክ አደጋ ሳቢያ ለሰዓታት ዝግ ሆኖ የነበረው የድሬደዋ ጅቡቲ መንገድ በአሁኑ ሰዓት ለትራፊክ ክፍት ተደርጓል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
13 ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ!
በትላንትናው ምሽት 13 የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ስር ማዋሉን በሃላባ ዞን የዌራ ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገልጿል፡፡ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመከላከል ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በጋራ መስራት እንደሚገባ የሃላባ ዞን ፖሊስ መምሪያ አሳሰበ፡፡የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ በበኩሉ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ በተደራጀ መልኩ እየተሰራ መሆኑን አረጋግጧል፡፡
Via South TV
@YeneTube @FikerAssefa
በትላንትናው ምሽት 13 የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ስር ማዋሉን በሃላባ ዞን የዌራ ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገልጿል፡፡ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመከላከል ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በጋራ መስራት እንደሚገባ የሃላባ ዞን ፖሊስ መምሪያ አሳሰበ፡፡የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ በበኩሉ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ በተደራጀ መልኩ እየተሰራ መሆኑን አረጋግጧል፡፡
Via South TV
@YeneTube @FikerAssefa
የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፍወርቂ ትላንት ማታ በሀገራቸው ቴሌቪዝን በቀጥታ በተላለፈ ቃለ-መጠይቅ የኢትዮጵያና ኤርትራ የደንበር ውዝግብ ጉዳይ በከፋ ሁኔታ ላይ መሆኑ ገለፁ፡፡
በሌላ በኩል ፕሬዝደንቱ አዲሱ ምዕራፍ የኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነት በመልካም ሁኔታ ላይ መሆኑ ጠቁመዋል፡፡በፈረንጆቹ አዲሱ ዓመት የመጀመሪያ ቃለ መጠይቅ የሰጡት ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፍወርቂ በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት፣ የ2012 ምርጫ፣ እየተስተዋሉ ያሉ ብሄር ተኮር ግጭቶችና ሌሎች ጉዳዮች ዙርያም አስተያየታቸው ሰጥተዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር ከተያያዙ አጀንዳዎች ውጪ ኤርትራ አሁናዊ የሱዳን ፖለቲካዊ ሁኔታ በትኩረት እየተከታተለች መሆኑ የገለፁ ሲሆን የቀይባህር አካባቢ ሀገራት መርህ መሰረት ያደረገ ትብብር እንደሚያስፈልጋቸውም ተናግረዋል፡፡
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በሌላ በኩል ፕሬዝደንቱ አዲሱ ምዕራፍ የኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነት በመልካም ሁኔታ ላይ መሆኑ ጠቁመዋል፡፡በፈረንጆቹ አዲሱ ዓመት የመጀመሪያ ቃለ መጠይቅ የሰጡት ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፍወርቂ በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት፣ የ2012 ምርጫ፣ እየተስተዋሉ ያሉ ብሄር ተኮር ግጭቶችና ሌሎች ጉዳዮች ዙርያም አስተያየታቸው ሰጥተዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር ከተያያዙ አጀንዳዎች ውጪ ኤርትራ አሁናዊ የሱዳን ፖለቲካዊ ሁኔታ በትኩረት እየተከታተለች መሆኑ የገለፁ ሲሆን የቀይባህር አካባቢ ሀገራት መርህ መሰረት ያደረገ ትብብር እንደሚያስፈልጋቸውም ተናግረዋል፡፡
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
1650 በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ለአገር ውስጥ ገበያ ቀርቧል!
ኢትዮጵያ የራሷን የነዳጅ ምርት ለአገር ውስጥ ፍጆታ መጠቀም የጀመረች ሲሆን፤ የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ባለፉት 6 ወራት 1650 በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ለሀገር ውስጥ ገበያ መቅረቡን አስታውቋል፡፡በመጪው ሣምንት ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሊቀርብ በተዘጋጀው የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር የ6 ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት፤ በሶማሌ ክልል ኦጋዴን ከአንድ አመት ተኩል በፊት በሙከራ ደረጃ መመረት የጀመረው ነዳጅ፤ ባለፉት 6 ወራት ለሀገር ውስጥ ገበያ ሲቀርብ መቆየቱን ያመለክታል፡፡
‹‹ኒው ቢዝነስ ኢትዮጵያ›› የተሰኘው ድረ ገጽ፣ ማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴርን ጠቅሶ ባወጣው መረጃ፤ በሙከራ ደረጃ ካለፈው ሐምሌ 2011 ጀምሮ ላለፉት 6 ወራት 1650 በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ለሀገር ውስጥ ገበያ መቅረቡንና በዚህም ሀገሪቱ ከውጭ ተገዝቶ ለሚገባ ነዳጅ ታወጣ ከነበረው የውጭ ምንዛሪ፣ 55ሺህ 994 ዶላር ማዳን መቻሏን ጠቁሟል፡፡
በኦጋዴን ያለውን የነዳጅ ምርት ከሀገር ውስጥ ገበያ ባሻገር ወደ ውጪ ለመላክ፣ ከኦጋዴን እስከ ጅቡቲ የውስጥ ለውስጥ ነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ በቅርቡ እንደሚጀመርም ታውቋል፡፡የኢትዮጵያን ነዳጅ ከሚረከቡ 3 የውጭ ሀገር ኩባንያዎች ጋር ስምምነት መፈረሙም በሥራ አፈፃፀም ሪፖርቱ ላይ ተገልጿል፡፡ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በአመቱ ከ60ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጐች የስራ እድል መፈጠሩንም ለማወቅ ተችሏል፡፡
Via Addis Admas
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ የራሷን የነዳጅ ምርት ለአገር ውስጥ ፍጆታ መጠቀም የጀመረች ሲሆን፤ የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ባለፉት 6 ወራት 1650 በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ለሀገር ውስጥ ገበያ መቅረቡን አስታውቋል፡፡በመጪው ሣምንት ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሊቀርብ በተዘጋጀው የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር የ6 ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት፤ በሶማሌ ክልል ኦጋዴን ከአንድ አመት ተኩል በፊት በሙከራ ደረጃ መመረት የጀመረው ነዳጅ፤ ባለፉት 6 ወራት ለሀገር ውስጥ ገበያ ሲቀርብ መቆየቱን ያመለክታል፡፡
‹‹ኒው ቢዝነስ ኢትዮጵያ›› የተሰኘው ድረ ገጽ፣ ማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴርን ጠቅሶ ባወጣው መረጃ፤ በሙከራ ደረጃ ካለፈው ሐምሌ 2011 ጀምሮ ላለፉት 6 ወራት 1650 በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ለሀገር ውስጥ ገበያ መቅረቡንና በዚህም ሀገሪቱ ከውጭ ተገዝቶ ለሚገባ ነዳጅ ታወጣ ከነበረው የውጭ ምንዛሪ፣ 55ሺህ 994 ዶላር ማዳን መቻሏን ጠቁሟል፡፡
በኦጋዴን ያለውን የነዳጅ ምርት ከሀገር ውስጥ ገበያ ባሻገር ወደ ውጪ ለመላክ፣ ከኦጋዴን እስከ ጅቡቲ የውስጥ ለውስጥ ነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ በቅርቡ እንደሚጀመርም ታውቋል፡፡የኢትዮጵያን ነዳጅ ከሚረከቡ 3 የውጭ ሀገር ኩባንያዎች ጋር ስምምነት መፈረሙም በሥራ አፈፃፀም ሪፖርቱ ላይ ተገልጿል፡፡ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በአመቱ ከ60ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጐች የስራ እድል መፈጠሩንም ለማወቅ ተችሏል፡፡
Via Addis Admas
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ እዚሁ በተቋሙ ማድረግ ጀመረ::
ኢንስቲትዩት የኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ እዚሁ በተቋሙ ማድረግ የጀመረ ስሆን 6 የኮሮና ቫይረስ በሽታ ምልክት ታይቶባቸው በለይቶ ማቆያ ማዕከል ክትትል እየተደረገላቸው እንደሆነና ለኮሮና ቫይረስ ምርመራ ናሙና የተወሰደላቸው መሆኑንና የ3ቱ ናሙና ወደ ደቡብ አፍሪካ የተላከ መሆኑን በትላንትናው ዕለት መግለጹ ይታወሳል፡፡ በዛሬው ዕለት የ3ቱ ናሙናዎች ውጤት የደረሰ ሲሆን ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸዉ ተረጋግጧል፡፡ በተጨማርም እዚሁ በኢንስቲትዩቱ የተወስዱ 3ቱ ናሙና በተቋሙ ምርመራ ተደርጎ ነጻ መሆኑ ተረጋግጧል::
Via Ministry of Health
@YeneTube @FikerAssefa
ኢንስቲትዩት የኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ እዚሁ በተቋሙ ማድረግ የጀመረ ስሆን 6 የኮሮና ቫይረስ በሽታ ምልክት ታይቶባቸው በለይቶ ማቆያ ማዕከል ክትትል እየተደረገላቸው እንደሆነና ለኮሮና ቫይረስ ምርመራ ናሙና የተወሰደላቸው መሆኑንና የ3ቱ ናሙና ወደ ደቡብ አፍሪካ የተላከ መሆኑን በትላንትናው ዕለት መግለጹ ይታወሳል፡፡ በዛሬው ዕለት የ3ቱ ናሙናዎች ውጤት የደረሰ ሲሆን ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸዉ ተረጋግጧል፡፡ በተጨማርም እዚሁ በኢንስቲትዩቱ የተወስዱ 3ቱ ናሙና በተቋሙ ምርመራ ተደርጎ ነጻ መሆኑ ተረጋግጧል::
Via Ministry of Health
@YeneTube @FikerAssefa
#Coronavirusupdate
Updated 4hrs ago.
የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ከሰላሳአራት ሺህ ያለፈ ሲሆን የሟቾች ቁጥር ደግሞ 723 ደርሷል።
Via AFP
@YeneTube @FikerAssefa
Updated 4hrs ago.
የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ከሰላሳአራት ሺህ ያለፈ ሲሆን የሟቾች ቁጥር ደግሞ 723 ደርሷል።
Via AFP
@YeneTube @FikerAssefa
የአፍሪካ ኀብረት የመሪዎች ጉባዔ ዛሬ ይጀመራል
የአፍሪካ ኀብረት 33ኛው የመሪዎች መደበኛ ጉባዔ ዛሬና ነገ አዲስ አባበ በሚገኘው የኀብረቱ ዋና መስሪያ ቤት ይካሄዳል።
መሪዎቹ ለሁለት ቀናት በሚኖራቸው ጉባዔ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መክረው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ለአፍሪካ ልማት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ”የጦር መሳሪያ ድምጽን ማጥፋት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ሲጀመር ህብረቱን ለአንድ አመት በሊቀመንበርነት ያገለገሉት የግብጹ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ሃላፊነቱን ለሚቀጥለው አንድ አመት ለሚይዙት የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሳይሪል ራማፎሳ ያስረክባሉ።
የመክፈቻ ንግግሮች ከቀረቡና የጉባኤው መሪ ሃሳብ ይፋ ከተደረገ መሪዎቹ በዝግ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
መሪዎቹ በዝግ ይመክሩባቸዋል ተብለው ከሚጠበቁ ጉዳዮች መካከል የአፍሪካ ህብረት ተቋማዊ ለውጥ እና በአህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ዙሪያ የተሰሩ ስራዎችን የተመለከተ ሪፖርት ማዳመጥና ቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ እንደሚገኙበት መረጃዎች ያመለክታሉ።
ሰላምና ጸጥታን በተመለከተም የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤት እና አህጉራዊ የሰላምና ጸጥታ ሁኔታ ላይ ምክክር ይደረጋል።
በተጨማሪም እ.አ.አ በ2020 በአህጉሩ ጸጥታ ለማስፈን የተዘጋጀው የተግባር ፍኖተ ካርታ አፈጻጸም ላይ መሪዎቹ ይመክራሉ።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@YeneTube @Fikerassefa
የአፍሪካ ኀብረት 33ኛው የመሪዎች መደበኛ ጉባዔ ዛሬና ነገ አዲስ አባበ በሚገኘው የኀብረቱ ዋና መስሪያ ቤት ይካሄዳል።
መሪዎቹ ለሁለት ቀናት በሚኖራቸው ጉባዔ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መክረው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ለአፍሪካ ልማት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ”የጦር መሳሪያ ድምጽን ማጥፋት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ሲጀመር ህብረቱን ለአንድ አመት በሊቀመንበርነት ያገለገሉት የግብጹ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ሃላፊነቱን ለሚቀጥለው አንድ አመት ለሚይዙት የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሳይሪል ራማፎሳ ያስረክባሉ።
የመክፈቻ ንግግሮች ከቀረቡና የጉባኤው መሪ ሃሳብ ይፋ ከተደረገ መሪዎቹ በዝግ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
መሪዎቹ በዝግ ይመክሩባቸዋል ተብለው ከሚጠበቁ ጉዳዮች መካከል የአፍሪካ ህብረት ተቋማዊ ለውጥ እና በአህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ዙሪያ የተሰሩ ስራዎችን የተመለከተ ሪፖርት ማዳመጥና ቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ እንደሚገኙበት መረጃዎች ያመለክታሉ።
ሰላምና ጸጥታን በተመለከተም የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤት እና አህጉራዊ የሰላምና ጸጥታ ሁኔታ ላይ ምክክር ይደረጋል።
በተጨማሪም እ.አ.አ በ2020 በአህጉሩ ጸጥታ ለማስፈን የተዘጋጀው የተግባር ፍኖተ ካርታ አፈጻጸም ላይ መሪዎቹ ይመክራሉ።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@YeneTube @Fikerassefa
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ ለሚገኙት የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ማምሻውን ለክብራቸው የእራት ግብዣ አዘጋጅተዋል።
በግብዣውም ላይ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ትሩዶ ባለፈው አርብ ነበር ይፋዊ የስራ ጉበኝት ለማድረግ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት።
ትናንትናም ከፕሬዚዳንት ሳህለወረቅ ዘውዴ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ ጋር ተገናኝተው በሁለትዮሽ እና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
Photo: JustinTrudeau
Via:- FBC
@YeneTube @Fikerassefa
በግብዣውም ላይ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ትሩዶ ባለፈው አርብ ነበር ይፋዊ የስራ ጉበኝት ለማድረግ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት።
ትናንትናም ከፕሬዚዳንት ሳህለወረቅ ዘውዴ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ ጋር ተገናኝተው በሁለትዮሽ እና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
Photo: JustinTrudeau
Via:- FBC
@YeneTube @Fikerassefa
በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሪያድ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሰጠው ማሳሰቢያ👇👇
በሪያድ ከተማ ውስጥ ቱማማ፣ መኽረጅ 28፣ መኽረጅ 29 እና መኽረጅ 30 በሚባሉ ቦታዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች የሚታገቱበት ሁኔታ መኖሩንና ከዚህ በፊት ታግተው የነበሩ ሃያ የሚሆኑ ዜጎቻችንን ከእገታ ማዳን የተቻለ መሆኑን መግለጻችን ይታወሳል። በርካታ ቁጥር ያላቸው እህቶቻችን በደላሎች አማካኝነት ወደ እነዚህ አካባቢዎች ለሥራ ከሄዱ በኋላ ስልካቸውን ተነጥቀው ከማንም ጋር እንዳይገናኙ ተከልክለው እየታገቱ መሆኑን በተደጋጋሚ መረጃዎች ይደርሱናል።
አሁንም በተጠቀሰው አካባቢ ሄደው የሚሰሩ ኢቃማ ያላቸውና የሌላቸው ዜጎቻችን ተመሳሳይ እጣ ፈንታ እየገጠማቸው መሆኑን መረዳት ችለናል። የኢፌዲሪ ኤምባሲ ከሚመለከተው የሳዑዲ አረቢያ መንግስት ወገን ጋር በመተባበር የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ያለው መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ከሳዑዲ የህግ አስከባሪ አካላት ጋር በመሆን ጉዳዩን እየተከታተልን ያለንበት ሁኔታ ላይ የምንገኝ በመሆኑ፣ ዜጎቻችን ለጊዜው በተጠቀሱት አካባቢዎች ለሥራ እንዳይሄዱ ኤምባሲው ይመክራል።
ምንጭ: ኤምባሲው
@YeneTube @FikerAssefa
በሪያድ ከተማ ውስጥ ቱማማ፣ መኽረጅ 28፣ መኽረጅ 29 እና መኽረጅ 30 በሚባሉ ቦታዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች የሚታገቱበት ሁኔታ መኖሩንና ከዚህ በፊት ታግተው የነበሩ ሃያ የሚሆኑ ዜጎቻችንን ከእገታ ማዳን የተቻለ መሆኑን መግለጻችን ይታወሳል። በርካታ ቁጥር ያላቸው እህቶቻችን በደላሎች አማካኝነት ወደ እነዚህ አካባቢዎች ለሥራ ከሄዱ በኋላ ስልካቸውን ተነጥቀው ከማንም ጋር እንዳይገናኙ ተከልክለው እየታገቱ መሆኑን በተደጋጋሚ መረጃዎች ይደርሱናል።
አሁንም በተጠቀሰው አካባቢ ሄደው የሚሰሩ ኢቃማ ያላቸውና የሌላቸው ዜጎቻችን ተመሳሳይ እጣ ፈንታ እየገጠማቸው መሆኑን መረዳት ችለናል። የኢፌዲሪ ኤምባሲ ከሚመለከተው የሳዑዲ አረቢያ መንግስት ወገን ጋር በመተባበር የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ያለው መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ከሳዑዲ የህግ አስከባሪ አካላት ጋር በመሆን ጉዳዩን እየተከታተልን ያለንበት ሁኔታ ላይ የምንገኝ በመሆኑ፣ ዜጎቻችን ለጊዜው በተጠቀሱት አካባቢዎች ለሥራ እንዳይሄዱ ኤምባሲው ይመክራል።
ምንጭ: ኤምባሲው
@YeneTube @FikerAssefa
ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ሊቀመንበርነት ስፍራን ተረከበች!
ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ሊቀመንበርነት ስፍራን ተረከበች።ዛሬ በተጀመረው 33ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች መደበኛ ጉባኤ ላይ ነው ደቡብ አፍሪካ የፈረንጆቹ 2020 የህብረቱ የወቅቱ ሊቀመንበርነትን ስፍራ የተረከበችው።የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳም ከግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ኤልሲሲ ሊቀመንበርነቱን ተረክበዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ሊቀመንበርነት ስፍራን ተረከበች።ዛሬ በተጀመረው 33ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች መደበኛ ጉባኤ ላይ ነው ደቡብ አፍሪካ የፈረንጆቹ 2020 የህብረቱ የወቅቱ ሊቀመንበርነትን ስፍራ የተረከበችው።የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳም ከግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ኤልሲሲ ሊቀመንበርነቱን ተረክበዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ከደብረ ብርሀን ወደ ዓለም ከተማ የሚወስደው መንገድ በአካባቢው ወጣቶች መዘጋቱ ተገለጸ።
መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያትም ወደ መርሀቤቴ፣ ሚዳ ወረሞ እና እንሳሮ ወረዳዎች የሚሄዱ መንገደኞች መቸገራቸውን ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል።እንደ የአይን እማኞቹ አስተያየት ከሆነ መንገዱ የተዘጋው በአካባቢው ወጣቶች ሲሆን መንገዱ ወደ አስፓልት ይቀየርልን ብለን ለመንግስት ብናመለክትም የሚሰማን አጣን በሚል ምክንያት እንደዘጉት ተናግረዋል።በተለይም ህጻናት የያዙ ወላጆች ምግብና ውሀ በማጣታቸው ለእንግልት ተዳርገናል የሚመለከተው የመንግስት አካል መንገዱን በአፋጣኝ ያስከፍትልን ሲሉ ጠይቀዋል።የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ተፈራ ወንድምአገኝ በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ እንዲሰጡን ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካም።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያትም ወደ መርሀቤቴ፣ ሚዳ ወረሞ እና እንሳሮ ወረዳዎች የሚሄዱ መንገደኞች መቸገራቸውን ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል።እንደ የአይን እማኞቹ አስተያየት ከሆነ መንገዱ የተዘጋው በአካባቢው ወጣቶች ሲሆን መንገዱ ወደ አስፓልት ይቀየርልን ብለን ለመንግስት ብናመለክትም የሚሰማን አጣን በሚል ምክንያት እንደዘጉት ተናግረዋል።በተለይም ህጻናት የያዙ ወላጆች ምግብና ውሀ በማጣታቸው ለእንግልት ተዳርገናል የሚመለከተው የመንግስት አካል መንገዱን በአፋጣኝ ያስከፍትልን ሲሉ ጠይቀዋል።የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ተፈራ ወንድምአገኝ በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ እንዲሰጡን ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካም።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የኖርዌዩዋ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤርና ሶልበርግ በአዲስ አበባ ከተማ የካሳንቺስ ጤና ጣቢያን ጎብኝተዋል።
የኖርዌዩዋ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤርና ሶልበርግ በአዲስ አበባ ከተማ የካሳንቺስ ጤና ጣቢያን በጎበኙበት ወቅት እንደገለፁት ኢትዮጵያ በምዕተ ዓመቱ የጤና የልማት ግቦች በተለይ የእናቶችና የህፃናትን ሞት በመቀነሱ ረገድ ባለፉት ዓመታት አበረታች ስራዎችን ሰርታለች።
በወሊድ ወቅት በእናቶችና ህፃናት ላይ የሚደርሰውን የሞት እና ተያያዥ ችግሮችን ለመቀነስ በሚደረገው ጥረትም የኖርዌይ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤርና ሶልበርግ ተናግረዋል ።በኢትዮጵያ በፕሮጀክት ደረጃ ተግባራዊ ለሚደረጉ ሴፍ ሊትል ላይፍስ እና ካንጋሮ ማዘር ኬር ለተሰኙ የእናቶችና የህፃናት ጤናን ለመጠበቅ የኖርዌይ መንግሥት የአምስት ሚሊየን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል ።
ምንጭ: የአዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሬተሪያት
@YeneTube @FikerAssefa
የኖርዌዩዋ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤርና ሶልበርግ በአዲስ አበባ ከተማ የካሳንቺስ ጤና ጣቢያን በጎበኙበት ወቅት እንደገለፁት ኢትዮጵያ በምዕተ ዓመቱ የጤና የልማት ግቦች በተለይ የእናቶችና የህፃናትን ሞት በመቀነሱ ረገድ ባለፉት ዓመታት አበረታች ስራዎችን ሰርታለች።
በወሊድ ወቅት በእናቶችና ህፃናት ላይ የሚደርሰውን የሞት እና ተያያዥ ችግሮችን ለመቀነስ በሚደረገው ጥረትም የኖርዌይ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤርና ሶልበርግ ተናግረዋል ።በኢትዮጵያ በፕሮጀክት ደረጃ ተግባራዊ ለሚደረጉ ሴፍ ሊትል ላይፍስ እና ካንጋሮ ማዘር ኬር ለተሰኙ የእናቶችና የህፃናት ጤናን ለመጠበቅ የኖርዌይ መንግሥት የአምስት ሚሊየን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል ።
ምንጭ: የአዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሬተሪያት
@YeneTube @FikerAssefa
የዛሬው የNew York Times እትም ኢትዮጵያ እና ግብጽ ስለሚወዛገቡበት የአባይ ውኃ እና የታላቁ ህዳሴግድብ ሰፊ ዘገባ ይዞ ወጥቷል። ጋዜጣው በአሜሪካ እና ዓለም ባንክ አሸማጋይነት የሚደረገው ድርድር ግብጽ "ተስፋ ያደረገችውን ያህል አልተጓዘም" ሲል ጽፏል።
@YeneTube @Fikerassefa
@YeneTube @Fikerassefa
#Sport 🇪🇹 13ተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች
⏰ ጨዋታው ተጠናቋል
ሀዋሳ ከተማ 1-0 ጅማ አባጅፋር
ውልዋሎ አ.ዩ 1-4 ቅዱስ ጊዮርጊስ
ድሬደዋ ከተማ 1-1 ሰሑል ሽረ
ባህር ዳር ከተማ 3-2 ሰበታ ከተማ
@YeneTube @Fikerassefa
⏰ ጨዋታው ተጠናቋል
ሀዋሳ ከተማ 1-0 ጅማ አባጅፋር
ውልዋሎ አ.ዩ 1-4 ቅዱስ ጊዮርጊስ
ድሬደዋ ከተማ 1-1 ሰሑል ሽረ
ባህር ዳር ከተማ 3-2 ሰበታ ከተማ
@YeneTube @Fikerassefa
#Coronavirusupdate
Updated 1hr ago.
የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ከሰላሳሰባት ሺህ ያለፈ ሲሆን የሟቾች ቁጥር ደግሞ 813 ደርሷል።
በዚህም መሰረት ያለፈው 24 ሰዓት ከእስካሁኑ ትልቁ የሟቾች ቁጥር የተመዘገበበት ሆኗል።
Via AFP
@YeneTube @FikerAssefa
Updated 1hr ago.
የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ከሰላሳሰባት ሺህ ያለፈ ሲሆን የሟቾች ቁጥር ደግሞ 813 ደርሷል።
በዚህም መሰረት ያለፈው 24 ሰዓት ከእስካሁኑ ትልቁ የሟቾች ቁጥር የተመዘገበበት ሆኗል።
Via AFP
@YeneTube @FikerAssefa
በየኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኖቭል ኮሮና ቫይረስን አስመልክቶ የተዘጋጀ ወቅታዊ መግለጫ
➡️ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በኖቭል ኮሮና ቫይረስ በሽታ መያዙ የተረጋገጠም ሆነ በለይቶ ማቆያ ማዕከሉ ሆኖ ክትትል የሚደረግለት ሰው የለም፣
➡️ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኖቭል ኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ እዚሁ በተቋሙ ማድረግ የጀመረ በመሆኑ ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊላክ የነበረ የ3 ሰዎች ናሙና ምርመራ በማድረግ ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸውን ማረጋገጥ ችሏል፡፡ በተጨማሪም የ3ቱ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተልከው የነበሩ ናሙናዎች ውጤት የደረሰን ሲሆን ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸዉ ተረጋግጧል፡፡
➡️ የኖቭል ኮሮና ቫይረስን በሽታ የመከላከል ዝግጁነትን ለማጠናከር ኢንስቲትዩቱ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በአዲስ አበባ ለሚገኙ 13 ሆስፒታሎች የተለያዩ ግብዓቶችን አሰራጭቷል፤ እንዲሁም ለክልል ሆሲፒታሎች ለማሰራጨት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል፡፡
➡️ የቫይረሱን ስርጭት አስመልክቶ እስከ አሁን ድረስ 31 ጥቆማዎች ለኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ማስተባበሪያ ማዕከል (Emergency Operation Center) ደርሰው ማጣራት ተደርጎባቸዋል፣ ከነዚህ ውስጥ 14ቱ በልየታ ቆይተው ናሙናቸው ተመርምሮ ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው በመረጋገጡ ከለይቶ ማቆያ ማዕከሉ እንዲወጡ ተደርጓል፡፡
➡️ የበሽታውን ልየታ ስራ ለማጠናከር የልየታ ቡድኑን ለሚቀላቀሉ የጤና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
➡️ በሐዋሳ ቫይረሱን የመከላከል ዝግጁነትን ለመደገፍ ቡድን ተልኳል፡፡
➡️ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስተር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን የሚመራው ብሔራዊ ግብረ ሃይል ጥር 29/2012 ስብሰባ አካሂዷል፡፡
➡️ ለሆቴሎች፣ ታክሲ ሾፌሮች እና ለመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለመስጠት ዝግጅቶች ተጠናቀዋል፡፡
📌ጥንቃቄ መደረግ ያለባቸው ጉዳዮች
➡️ በተጨማሪም ሕብረተሰቡ በሀገራችን እስካአሁን በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠ ሰው አለመኖሩን አውቆ ሳይዘናጋ የበለጠ ጥንቃቄ ኢንዲያደርግ ኢንስቲትዩቱ ያሳስባል፡፡
➡️ የኖቭል ኮሮና ቫይረስ ከታየባቸው ሀገራት የመጡ መንገደኞች ወይም በዚህ ቫይረስ ከተያዙ ግለሰቦች ጋር ንክኪ የነበራቸው ሰዎች ላይ የበሽታው ምልክቶች (ትኩሳት፤ ሳል፤ የትንፋሽ መቆራረጥ፣ የመተንፈስ ችግር) ከታዩ፣ ማንኛውም የሕብረተሰቡ አካል በአስቸኳይ በ8335 ነጻ የስልክ መስመር ላይ በመደወል ሪፖርት እንዲያደርግ እናሳስባለን፡፡
➡️ የበሽታው ምልክት የታየባቸው ሰዎች በሚያስነሠጥሱበት እና በሚያስሉበት ወቅት አፍና አፍንጫቸውን በሶፍት ወይም በክንድ እንዲሸፍኑ፤ የተጠቀሙበትን ሶፍት ወደ ቆሻሻ ማጠራቀሚያ እንዲጥሉ እና እጃቸውን በውሃና ሳሙና በመታጠብ የቫይረሱን ስርጭት እንዲከላከሉ እንመክራለን፡፡
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
አዲስ አበባ
01/06/2012 ዓ.ም
@YeneTube @FikerAssefa
➡️ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በኖቭል ኮሮና ቫይረስ በሽታ መያዙ የተረጋገጠም ሆነ በለይቶ ማቆያ ማዕከሉ ሆኖ ክትትል የሚደረግለት ሰው የለም፣
➡️ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኖቭል ኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ እዚሁ በተቋሙ ማድረግ የጀመረ በመሆኑ ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊላክ የነበረ የ3 ሰዎች ናሙና ምርመራ በማድረግ ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸውን ማረጋገጥ ችሏል፡፡ በተጨማሪም የ3ቱ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተልከው የነበሩ ናሙናዎች ውጤት የደረሰን ሲሆን ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸዉ ተረጋግጧል፡፡
➡️ የኖቭል ኮሮና ቫይረስን በሽታ የመከላከል ዝግጁነትን ለማጠናከር ኢንስቲትዩቱ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በአዲስ አበባ ለሚገኙ 13 ሆስፒታሎች የተለያዩ ግብዓቶችን አሰራጭቷል፤ እንዲሁም ለክልል ሆሲፒታሎች ለማሰራጨት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል፡፡
➡️ የቫይረሱን ስርጭት አስመልክቶ እስከ አሁን ድረስ 31 ጥቆማዎች ለኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ማስተባበሪያ ማዕከል (Emergency Operation Center) ደርሰው ማጣራት ተደርጎባቸዋል፣ ከነዚህ ውስጥ 14ቱ በልየታ ቆይተው ናሙናቸው ተመርምሮ ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው በመረጋገጡ ከለይቶ ማቆያ ማዕከሉ እንዲወጡ ተደርጓል፡፡
➡️ የበሽታውን ልየታ ስራ ለማጠናከር የልየታ ቡድኑን ለሚቀላቀሉ የጤና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
➡️ በሐዋሳ ቫይረሱን የመከላከል ዝግጁነትን ለመደገፍ ቡድን ተልኳል፡፡
➡️ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስተር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን የሚመራው ብሔራዊ ግብረ ሃይል ጥር 29/2012 ስብሰባ አካሂዷል፡፡
➡️ ለሆቴሎች፣ ታክሲ ሾፌሮች እና ለመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለመስጠት ዝግጅቶች ተጠናቀዋል፡፡
📌ጥንቃቄ መደረግ ያለባቸው ጉዳዮች
➡️ በተጨማሪም ሕብረተሰቡ በሀገራችን እስካአሁን በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠ ሰው አለመኖሩን አውቆ ሳይዘናጋ የበለጠ ጥንቃቄ ኢንዲያደርግ ኢንስቲትዩቱ ያሳስባል፡፡
➡️ የኖቭል ኮሮና ቫይረስ ከታየባቸው ሀገራት የመጡ መንገደኞች ወይም በዚህ ቫይረስ ከተያዙ ግለሰቦች ጋር ንክኪ የነበራቸው ሰዎች ላይ የበሽታው ምልክቶች (ትኩሳት፤ ሳል፤ የትንፋሽ መቆራረጥ፣ የመተንፈስ ችግር) ከታዩ፣ ማንኛውም የሕብረተሰቡ አካል በአስቸኳይ በ8335 ነጻ የስልክ መስመር ላይ በመደወል ሪፖርት እንዲያደርግ እናሳስባለን፡፡
➡️ የበሽታው ምልክት የታየባቸው ሰዎች በሚያስነሠጥሱበት እና በሚያስሉበት ወቅት አፍና አፍንጫቸውን በሶፍት ወይም በክንድ እንዲሸፍኑ፤ የተጠቀሙበትን ሶፍት ወደ ቆሻሻ ማጠራቀሚያ እንዲጥሉ እና እጃቸውን በውሃና ሳሙና በመታጠብ የቫይረሱን ስርጭት እንዲከላከሉ እንመክራለን፡፡
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
አዲስ አበባ
01/06/2012 ዓ.ም
@YeneTube @FikerAssefa