ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.4K subscribers
69 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
ነጥብ ሁለት
“የወር አበባ”
አምላካችን አላህ “የተበከለ” ወይም “ቆሻሻ” የሚለው ሴቷን ሳይሆን ከሴቷ የሚወጠውን የወር አበባ ነው፤ በዚህ ጊዜ ተራክቦ ማድረግ ሃራም ነው፤ “ራቋቸው” እና “አትቅረቡዋቸው” የሚለው ቃል የ”ተገናኙዋቸው” ተቃራኒ ሆኖ ስለመጣ ራቁ ማለትና አትቅረቡ ማለት ተራክቦ አታድርጉ ማለት ነው፤ ለምሳሌ ዝሙት ማለት ከጋብቻ ውጪና በፊት የሚደረግ ተራክቦ ነው፤ ይህንን ተራክቦ “አትቅረቡ” ይላል፤ ያ ማለት “አትገናኙ” ማለት እንጂ ከሰው ጋር ጤናማ ግኑኝነት አይኑራችሁ ማለት እንዳልሆነ ሁሉ ሴት ራቁ ማለትና አትቅረቡ ማለት ተራክቦ አታድርጉ ማለት እንጂ አትቀፏቸው፣ አትሳሟቸው፣ አብራችሁ አትተኙ ማለት አይደለም፦
2፥222 ከወር አበባም ይጠይቁሃል፡፡ እርሱ “የተበከለ” ነው፡፡ ሴቶችንም በወር አበባ ጊዜ “ራቋቸው”፡፡ ንጹሕ እስከሚኾኑም ድረስ “አትቅረቡዋቸው”፡፡ ንጹሕ በኾኑም ጊዜ አላህ ካዘዛችሁ ስፍራ “ተገናኙዋቸው”፡፡ አላህ ከኃጢኣት ተመላሾችን ይወዳል፤ ተጥራሪዎችንም ይወዳል በላቸው وَيَسْـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلْمَحِيضِ ۖ قُلْ هُوَ أَذًۭى فَٱعْتَزِلُوا۟ ٱلنِّسَآءَ فِى ٱلْمَحِيضِ ۖ وَلَا تَقْرَبُوهُنَّ حَتَّىٰ يَطْهُرْنَ ۖ فَإِذَا تَطَهَّرْنَ فَأْتُوهُنَّ مِنْ حَيْثُ أَمَرَكُمُ ٱللَّهُ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ يُحِبُّ ٱلتَّوَّٰبِينَ وَيُحِبُّ ٱلْمُتَطَهِّرِينَ ፡፡
17፥32 ዝሙትንም “አትቅረቡ”፡፡ እርሱ በእርግጥ መጥፎ ሥራ ነውና፡፡ መንገድነቱም ከፋ وَلَا تَقْرَبُوا۟ ٱلزِّنَىٰٓ ۖ إِنَّهُۥ كَانَ فَٰحِشَةًۭ وَسَآءَ سَبِيلًۭا !

በተለይ ሱረቱል በቀራህ 2፥222 የወረደበት ምክንያት አይሁዳውያን ሴት በወር አበባ ጊዜ ስትሆን ምግብ አብረው አይበሉም በቤታቸውም አይኖሩም ስለነበርና ሰሃባዎችም ይህንን ጉዳይ ወደ ነብያችን”ﷺ” ጥያቄውን በማምራታቸው ነው፤ ነብያችንም”ﷺ” የመለሱት በወር አበባ ጊዜ ከተራክቦ በስተቀር ሁሉንም ማድረግ እንደሚቻል ነው፦
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 3 , ሐዲስ 16:
አነሥ”ረ.ዓ.” እንደተረከው፦
አይሁዳውያን ሴት በወር አበባ ጊዜ ስትሆን ምግብ አብረው አይበሉም በቤታቸውም አይኖሩም፤ የነብዩም”ﷺ” ባልደረቦች ነብዩን”ﷺ” ስለ ጉዳዩ ጠየቁ፤ ከሁሉ የላቀው አላህም ይህንን አንቀፅ አወረደ፦
2፥222 ከወር አበባም ይጠይቁሃል፡፡ እርሱ “የተበከለ” ነው፡፡ ሴቶችንም በወር አበባ ጊዜ “ራቋቸው”፡፡
የአላህም መልእክተኛ”ﷺ” አሉ፦ “ሁሉን ነገር አድርጉ ከተራክቦ በስተቀር” عَنْ أَنَسٍ، أَنَّ الْيَهُودَ، كَانُوا إِذَا حَاضَتِ الْمَرْأَةُ فِيهِمْ لَمْ يُؤَاكِلُوهَا وَلَمْ يُجَامِعُوهُنَّ فِي الْبُيُوتِ فَسَأَلَ أَصْحَابُ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم فَأَنْزَلَ اللَّهُ تَعَالَى ‏{‏ وَيَسْأَلُونَكَ عَنِ الْمَحِيضِ قُلْ هُوَ أَذًى فَاعْتَزِلُوا النِّسَاءَ فِي الْمَحِيضِ‏}‏ إِلَى آخِرِ الآيَةِ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ اصْنَعُوا كُلَّ شَىْءٍ إِلاَّ النِّكَاحَ ‏” ።

መደምደሚያ
ከላይ የቁርአኑ አናቅፅ ላይ የሴትን ክቡድና ክቡር መሆን የሚነካ ሀይለ ቃል ሽታው እንኳን ካልተገኘ አይሁዳውያንና ክርስቲያኖች ምንን ሚዛን አድርገው ነው ሂስ ሊሰጡ የቃጣቸው? ስንል፤ የራሳቸው ባይብል ሴት በወር አበባ ጊዜዋ “እርኩስ” ናት ስለሚል ነው፤ ምን እርሷ ብቻ በንክኪ እርሷን፣ የተኛችበትና የተቀመጠችበት የሚነካትም ሆነ የምትነካው ሁሉ እርኩስ ነው፤ የወር አበባዋ የፈራረሰ እንቁላል መሆኑ ተረስቶ “እርግማን” ነው ይለናል፦
ዘሌዋውያን 15፥25 #ሴትም #ከመርገም ቀን ሌላ ደምዋ ብዙ ቀን ቢፈስስ፥ ወይም ደምዋ #ከመርገምዋወራት የሚበልጥ ቢፈስስ፥ በመርገምዋ ወራት እንደ ሆነች እንዲሁ በፈሳሽዋ #ርኵስነት ወራት ትሆናለች፤ *#ርኩስ #ናት*።
ዘሌዋውያን 15፥19 *#ሴት ፈሳሽ ነገር ቢኖርባት* በሥጋዋም ያለው ፈሳሽ ነገር *#ደም ቢሆን*፥ *#በመርገምዋ* ሰባት ቀን ትቀመጣለች፤ የሚነካትም ሁሉ እስከ ማታ ድረስ *#ርኩስ* ነው።
ዘሌዋውያን 15፥20 #መርገምም ስትሆን #የምትተኛበት ነገር ሁሉ *#ርኩስ* ነው፤ #የምትቀመጥበትምነገር ሁሉ *#ርኩስ* ነው።
ዘሌዋውያን 15፥21 መኝታዋንም #የሚነካ ሁሉ ልብሱን ያጥባል፥ በውኃም ይታጠባል፥ እስከ ማታም ድረስ *#ርኩስ* ነው።
15፥22 #የምትቀመጥበትንም ነገር ሁሉ #የሚነካ ሁሉ ልብሱን ያጥባል፥ በውኃም ይታጠባል፥ እስከ ማታም *#ርኩስ* ነው።

ሙሽሪኪን ቢጠሉም አላህ መልክተኛውን በመምሪያ መጽሐፍ በእውነተኛው ሃይማኖትም በኢስላም ከሃይማኖት ሁሉ በላይ ይፋ ሊያደርገው የላከ ነው፦
48፥28 እርሱ ያ መልክተኛውን በመሪ መጽሐፍና በእውነተኛ ሃይማኖት በሃይማኖት ሁሉ ላይ ሊያልቀው የላከ ነው፡፡ መስካሪም በአላህ በቃ هُوَ ٱلَّذِىٓ أَرْسَلَ رَسُولَهُۥ بِٱلْهُدَىٰ وَدِينِ ٱلْحَقِّ لِيُظْهِرَهُۥ عَلَى ٱلدِّينِ كُلِّهِۦ ۚ وَكَفَىٰ بِٱللَّهِ شَهِيدًۭا ፡፡
9፥33 እርሱ ያ አጋሪዎቹ ቢጠሉም መልክተኛውን በቅን መንገድና በእውነተኛ ሃይማኖት ላይ ከሃይማኖት ሁሉ በላይ ይፋ ያደርገው ዘንድ የላከው ነው هُوَ ٱلَّذِىٓ أَرْسَلَ رَسُولَهُۥ بِٱلْهُدَىٰ وَدِينِ ٱلْحَقِّ لِيُظْهِرَهُۥ عَلَى ٱلدِّينِ كُلِّهِۦ وَلَوْ كَرِهَ ٱلْمُشْرِكُونَ ፡፡

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ሴቶች በባይብል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

መግቢያ
ክርስትና በአውሮፓ ላይ የተሸመነበት ድርና ማግ እንደሆነ ሁሉ የተዋረደበት ማቅ፣ የተገነዘበት በፍታ፣ የተከፈነበት ግምዣ ነው ብዬ ብናገር እብለትም ወይም ግነትም አሊያም ቅጥፈትም አይደለም። ሚሽነሪዎችም ማንኛውም ነገር ሲለኩ እና ሲመዝኑ ከባይብል ህግ ይልቅ ሰው ሰራሹን የምዕራባውያንን ህግ ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ነው፤ የኢስላም ህግ ስህተት እንዳለው ቧጦና ጓጦ ከመፈለግ ይልቅ የራሳቸውን ባይብል ላይ ስለ ሴቶች የተቀመጠውን ነገር ቅድሚያ ቢመለከቱ አባጣና ጎርባጣ ይሆንባቸዋል፤ ለዛ ነው ምዕራባውያን የክርስትና አህጉር የነበረው ዛሬ ተገልብጦ ከመቶ 65% አይደለም ሃይማኖት ሊኖረው ይቅርና በፈጣሪ መኖር እንኳን አይቀበልም። ምክንያቱም የክርስትና ሃይማኖት ህግ በጊዜው እንደጎረበጣቸው ይናገራሉ። ታዲያ ሚሽነሪዎች ሥርወ እምነታቸው ላይ የአውሮፓን ሥርወ መንግሥት ከለላ አድርገው ሂስ ከመስጠጣቸው በፊት በእማኝነትና በአስረጂነት ሴቶች በባይብል ያለባቸውን ደረጃና መብት ነጥብ በነጥብ እናያለን፦

ነጥብ አንድ
"ሴትና ደረጃዋ"
ሚስት ባልዋን "ጌታዬ" እያለች እንድትገዛ "ህጉ" ማለትም ኦሪት እርሱም *ገዥሽ* ነው ብሎ ያዛል፣ ለወንድ እንድትገዛ እንጂ እንድትናገር አልተፈቀደላትም፤ በዝግታ ትኑር እንጂ በወንድ ላይ ልትሰለጥን አይፈቀድም፤ በማህበር ማለትም ሰዎች በተሰበሰቡበት ልታስተምር ወይም ልትናገር አይፈቀድላትም፦
ዘፍጥረት3፤16 ለሴቲቱም አለ፦ በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ፤ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም *ገዥሽ* ይሆናል።
1ኛ ቆሮንቶስ 14፥34 ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ፤ ሕግ ደግሞ እንደሚል እንዲገዙ እንጂ እንዲናገሩ አልተፈቀደላቸውምና።
1ኛ ጴጥሮስ 3፤5-6 እንዲህ በቀድሞ ዘመን በእግዚአብሔር ተስፋ ያደረጉት ቅዱሳት ሴቶች ደግሞ *ለባሎቻቸው ሲገዙ* ተሸልመው ነበርና፤ እንዲሁም ሣራ ለአብርሃም፦ *ጌታ* ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት፤
1ኛ ጢሞቴዎስ 2፤11-12 ሴት በነገር ሁሉ *እየተገዛች* በዝግታ ትማር፤ ሴት ግን በዝግታ ትኑር እንጂ *ልታስተምር* ወይም በወንድ ላይ ልትሰለጥን አልፈቅድም።

ሚስት ባልዋን እንዴት ነው የምትገዛው ሲባል ልክ እንደ ፈጣሪ መገዛት አለባት። ሚስት ለፈጣሪዋ አምልኮ፣ ስግደት፣ ምስጋና፣ ውዳሴ፣ ማህሌት፣ የቀልብ፣ የነቢብ፣ የገቢር መገዛት የምታቀር ከሆነ ለባልዋም ማቅረብ አለባት፣ ምክንያቱም ሚስት ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ ተብሏልና፦
ኤፌሶን 5፣22 ሚስቶች ሆይ፥ ""ለጌታ እንደምትገዙ"" ለባሎቻችሁ ""ተገዙ""፤

ጥያቄአችን ሚስት ለባልዋ የምትገዛው እንደ ጌታዋ "ጌታዬ" እያለች ከሆነ ለሁለት ጌቶች መገዛት አይሆንምን?
ማቴዎስ 6፤24 ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም፤

ምክንያቱም ሴት ማለት ከሞት ይልቅ የመረረች፣ ልብዋ ወጥመድና መርበብ የሆነ፥ እጆችዋም እግር ብረት የሆኑ ናት፤ በእግዚአብሔር ፊት መልካም የሆነ ከእርስዋ ያመልጣል፥ ኃጢአተኛ ግን ይጠመድባታል ይለናል፦
መክብብ 7፥26 እኔም #ከሞት ይልቅ #የመረረ #ነገር መርምሬ አገኘሁ፤ እርስዋም ልብዋ ወጥመድና መርበብ የሆነ፥ እጆችዋም እግር ብረት የሆኑ #ሴት #ናት፤ በእግዚአብሔር ፊት መልካም የሆነ ከእርስዋ #ያመልጣል#ኃጢአተኛ ግን ይጠመድባታል።

ሴት በተፈጥሮዋ ደካማ እና የኃጢያትም ምንጭ እርሷ እንደሆነች እና የተታለለች እርሷ እንጂ ወንድ አይደለም ይለናል፦
1ኛ ጴጥሮስ 3፥7 እንዲሁም፥ እናንተ ባሎች ሆይ፥ ""ደካማ ፍጥረት ስለ ሆኑ"" ከሚስቶቻችሁ ጋር በማስተዋል አብራችሁ ኑሩ፤
ሲራክ 42:13-14 ከልብስ ብል ይገኛል፤ኃጢያትም ሁሉ
ከሴቶች ይገኛል።
1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥14 የተታለለም አዳም አይደለም፥ ሴቲቱ ግን ተታልላ በመተላለፍ ወደቀች፤