ሴቶች በባይብል
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
መግቢያ
ክርስትና በአውሮፓ ላይ የተሸመነበት ድርና ማግ እንደሆነ ሁሉ የተዋረደበት ማቅ፣ የተገነዘበት በፍታ፣ የተከፈነበት ግምዣ ነው ብዬ ብናገር እብለትም ወይም ግነትም አሊያም ቅጥፈትም አይደለም። ሚሽነሪዎችም ማንኛውም ነገር ሲለኩ እና ሲመዝኑ ከባይብል ህግ ይልቅ ሰው ሰራሹን የምዕራባውያንን ህግ ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ነው፤ የኢስላም ህግ ስህተት እንዳለው ቧጦና ጓጦ ከመፈለግ ይልቅ የራሳቸውን ባይብል ላይ ስለ ሴቶች የተቀመጠውን ነገር ቅድሚያ ቢመለከቱ አባጣና ጎርባጣ ይሆንባቸዋል፤ ለዛ ነው ምዕራባውያን የክርስትና አህጉር የነበረው ዛሬ ተገልብጦ ከመቶ 65% አይደለም ሃይማኖት ሊኖረው ይቅርና በፈጣሪ መኖር እንኳን አይቀበልም። ምክንያቱም የክርስትና ሃይማኖት ህግ በጊዜው እንደጎረበጣቸው ይናገራሉ። ታዲያ ሚሽነሪዎች ሥርወ እምነታቸው ላይ የአውሮፓን ሥርወ መንግሥት ከለላ አድርገው ሂስ ከመስጠጣቸው በፊት በእማኝነትና በአስረጂነት ሴቶች በባይብል ያለባቸውን ደረጃና መብት ነጥብ በነጥብ እናያለን፦
ነጥብ አንድ
"ሴትና ደረጃዋ"
ሚስት ባልዋን "ጌታዬ" እያለች እንድትገዛ "ህጉ" ማለትም ኦሪት እርሱም *ገዥሽ* ነው ብሎ ያዛል፣ ለወንድ እንድትገዛ እንጂ እንድትናገር አልተፈቀደላትም፤ በዝግታ ትኑር እንጂ በወንድ ላይ ልትሰለጥን አይፈቀድም፤ በማህበር ማለትም ሰዎች በተሰበሰቡበት ልታስተምር ወይም ልትናገር አይፈቀድላትም፦
ዘፍጥረት3፤16 ለሴቲቱም አለ፦ በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ፤ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም *ገዥሽ* ይሆናል።
1ኛ ቆሮንቶስ 14፥34 ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ፤ ሕግ ደግሞ እንደሚል እንዲገዙ እንጂ እንዲናገሩ አልተፈቀደላቸውምና።
1ኛ ጴጥሮስ 3፤5-6 እንዲህ በቀድሞ ዘመን በእግዚአብሔር ተስፋ ያደረጉት ቅዱሳት ሴቶች ደግሞ *ለባሎቻቸው ሲገዙ* ተሸልመው ነበርና፤ እንዲሁም ሣራ ለአብርሃም፦ *ጌታ* ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት፤
1ኛ ጢሞቴዎስ 2፤11-12 ሴት በነገር ሁሉ *እየተገዛች* በዝግታ ትማር፤ ሴት ግን በዝግታ ትኑር እንጂ *ልታስተምር* ወይም በወንድ ላይ ልትሰለጥን አልፈቅድም።
ሚስት ባልዋን እንዴት ነው የምትገዛው ሲባል ልክ እንደ ፈጣሪ መገዛት አለባት። ሚስት ለፈጣሪዋ አምልኮ፣ ስግደት፣ ምስጋና፣ ውዳሴ፣ ማህሌት፣ የቀልብ፣ የነቢብ፣ የገቢር መገዛት የምታቀር ከሆነ ለባልዋም ማቅረብ አለባት፣ ምክንያቱም ሚስት ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ ተብሏልና፦
ኤፌሶን 5፣22 ሚስቶች ሆይ፥ ""ለጌታ እንደምትገዙ"" ለባሎቻችሁ ""ተገዙ""፤
ጥያቄአችን ሚስት ለባልዋ የምትገዛው እንደ ጌታዋ "ጌታዬ" እያለች ከሆነ ለሁለት ጌቶች መገዛት አይሆንምን?
ማቴዎስ 6፤24 ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም፤
ምክንያቱም ሴት ማለት ከሞት ይልቅ የመረረች፣ ልብዋ ወጥመድና መርበብ የሆነ፥ እጆችዋም እግር ብረት የሆኑ ናት፤ በእግዚአብሔር ፊት መልካም የሆነ ከእርስዋ ያመልጣል፥ ኃጢአተኛ ግን ይጠመድባታል ይለናል፦
መክብብ 7፥26 እኔም #ከሞት ይልቅ #የመረረ #ነገር መርምሬ አገኘሁ፤ እርስዋም ልብዋ ወጥመድና መርበብ የሆነ፥ እጆችዋም እግር ብረት የሆኑ #ሴት #ናት፤ በእግዚአብሔር ፊት መልካም የሆነ ከእርስዋ #ያመልጣል፥ #ኃጢአተኛ ግን ይጠመድባታል።
ሴት በተፈጥሮዋ ደካማ እና የኃጢያትም ምንጭ እርሷ እንደሆነች እና የተታለለች እርሷ እንጂ ወንድ አይደለም ይለናል፦
1ኛ ጴጥሮስ 3፥7 እንዲሁም፥ እናንተ ባሎች ሆይ፥ ""ደካማ ፍጥረት ስለ ሆኑ"" ከሚስቶቻችሁ ጋር በማስተዋል አብራችሁ ኑሩ፤
ሲራክ 42:13-14 ከልብስ ብል ይገኛል፤ኃጢያትም ሁሉ
ከሴቶች ይገኛል።
1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥14 የተታለለም አዳም አይደለም፥ ሴቲቱ ግን ተታልላ በመተላለፍ ወደቀች፤
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
መግቢያ
ክርስትና በአውሮፓ ላይ የተሸመነበት ድርና ማግ እንደሆነ ሁሉ የተዋረደበት ማቅ፣ የተገነዘበት በፍታ፣ የተከፈነበት ግምዣ ነው ብዬ ብናገር እብለትም ወይም ግነትም አሊያም ቅጥፈትም አይደለም። ሚሽነሪዎችም ማንኛውም ነገር ሲለኩ እና ሲመዝኑ ከባይብል ህግ ይልቅ ሰው ሰራሹን የምዕራባውያንን ህግ ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ነው፤ የኢስላም ህግ ስህተት እንዳለው ቧጦና ጓጦ ከመፈለግ ይልቅ የራሳቸውን ባይብል ላይ ስለ ሴቶች የተቀመጠውን ነገር ቅድሚያ ቢመለከቱ አባጣና ጎርባጣ ይሆንባቸዋል፤ ለዛ ነው ምዕራባውያን የክርስትና አህጉር የነበረው ዛሬ ተገልብጦ ከመቶ 65% አይደለም ሃይማኖት ሊኖረው ይቅርና በፈጣሪ መኖር እንኳን አይቀበልም። ምክንያቱም የክርስትና ሃይማኖት ህግ በጊዜው እንደጎረበጣቸው ይናገራሉ። ታዲያ ሚሽነሪዎች ሥርወ እምነታቸው ላይ የአውሮፓን ሥርወ መንግሥት ከለላ አድርገው ሂስ ከመስጠጣቸው በፊት በእማኝነትና በአስረጂነት ሴቶች በባይብል ያለባቸውን ደረጃና መብት ነጥብ በነጥብ እናያለን፦
ነጥብ አንድ
"ሴትና ደረጃዋ"
ሚስት ባልዋን "ጌታዬ" እያለች እንድትገዛ "ህጉ" ማለትም ኦሪት እርሱም *ገዥሽ* ነው ብሎ ያዛል፣ ለወንድ እንድትገዛ እንጂ እንድትናገር አልተፈቀደላትም፤ በዝግታ ትኑር እንጂ በወንድ ላይ ልትሰለጥን አይፈቀድም፤ በማህበር ማለትም ሰዎች በተሰበሰቡበት ልታስተምር ወይም ልትናገር አይፈቀድላትም፦
ዘፍጥረት3፤16 ለሴቲቱም አለ፦ በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ፤ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም *ገዥሽ* ይሆናል።
1ኛ ቆሮንቶስ 14፥34 ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ፤ ሕግ ደግሞ እንደሚል እንዲገዙ እንጂ እንዲናገሩ አልተፈቀደላቸውምና።
1ኛ ጴጥሮስ 3፤5-6 እንዲህ በቀድሞ ዘመን በእግዚአብሔር ተስፋ ያደረጉት ቅዱሳት ሴቶች ደግሞ *ለባሎቻቸው ሲገዙ* ተሸልመው ነበርና፤ እንዲሁም ሣራ ለአብርሃም፦ *ጌታ* ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት፤
1ኛ ጢሞቴዎስ 2፤11-12 ሴት በነገር ሁሉ *እየተገዛች* በዝግታ ትማር፤ ሴት ግን በዝግታ ትኑር እንጂ *ልታስተምር* ወይም በወንድ ላይ ልትሰለጥን አልፈቅድም።
ሚስት ባልዋን እንዴት ነው የምትገዛው ሲባል ልክ እንደ ፈጣሪ መገዛት አለባት። ሚስት ለፈጣሪዋ አምልኮ፣ ስግደት፣ ምስጋና፣ ውዳሴ፣ ማህሌት፣ የቀልብ፣ የነቢብ፣ የገቢር መገዛት የምታቀር ከሆነ ለባልዋም ማቅረብ አለባት፣ ምክንያቱም ሚስት ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ ተብሏልና፦
ኤፌሶን 5፣22 ሚስቶች ሆይ፥ ""ለጌታ እንደምትገዙ"" ለባሎቻችሁ ""ተገዙ""፤
ጥያቄአችን ሚስት ለባልዋ የምትገዛው እንደ ጌታዋ "ጌታዬ" እያለች ከሆነ ለሁለት ጌቶች መገዛት አይሆንምን?
ማቴዎስ 6፤24 ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም፤
ምክንያቱም ሴት ማለት ከሞት ይልቅ የመረረች፣ ልብዋ ወጥመድና መርበብ የሆነ፥ እጆችዋም እግር ብረት የሆኑ ናት፤ በእግዚአብሔር ፊት መልካም የሆነ ከእርስዋ ያመልጣል፥ ኃጢአተኛ ግን ይጠመድባታል ይለናል፦
መክብብ 7፥26 እኔም #ከሞት ይልቅ #የመረረ #ነገር መርምሬ አገኘሁ፤ እርስዋም ልብዋ ወጥመድና መርበብ የሆነ፥ እጆችዋም እግር ብረት የሆኑ #ሴት #ናት፤ በእግዚአብሔር ፊት መልካም የሆነ ከእርስዋ #ያመልጣል፥ #ኃጢአተኛ ግን ይጠመድባታል።
ሴት በተፈጥሮዋ ደካማ እና የኃጢያትም ምንጭ እርሷ እንደሆነች እና የተታለለች እርሷ እንጂ ወንድ አይደለም ይለናል፦
1ኛ ጴጥሮስ 3፥7 እንዲሁም፥ እናንተ ባሎች ሆይ፥ ""ደካማ ፍጥረት ስለ ሆኑ"" ከሚስቶቻችሁ ጋር በማስተዋል አብራችሁ ኑሩ፤
ሲራክ 42:13-14 ከልብስ ብል ይገኛል፤ኃጢያትም ሁሉ
ከሴቶች ይገኛል።
1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥14 የተታለለም አዳም አይደለም፥ ሴቲቱ ግን ተታልላ በመተላለፍ ወደቀች፤