TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አስቸኳይ መረጃ‼️

(ሼር ይደረግ)

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ተፈናቅለው በምዕራብ ወለጋ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ከ70 ሺህ የማያንሱ ዜጎቻችንን አስቸኳይ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።

ከብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ጋር ባደረግነው ውይይት መሰረት ለኦሮሚያ አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ቢሮ በአፋጣኝ ሰብዓዊ እርዳታዎች ለማድረስ ተስማምተናል።

በዚህም መሰረት በአዲስ አበባና በአካባቢው የምትኖሩ ለሰብዓዊ እርዳታ ገር ልብ ያላችሁ ጽኑ ኢትዮጵያዊያን የተለመደው ርብርባችሁ ይጠበቃል።

#የማይበላሹ_ምግቦች

መኮረኒ
ሩዝ
ፉርኖ ዱቄት
ዘይት
ሴሪፋም /ፋፋ/
ብስኩት /ጋቤጣ/

#የንጽህና_ቁሳቁሶች

ሳሙና
ኦሞ
ሳኒታይዘር
የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ /ሞዴስ/

#አልባሳት

ብርድ ልብስ
ነጠላ ጫማ

የተለያዩ አልባሳት (ያገለገሉም ቢሆን)
እነዚህን ቁሳቁሶች ብቻ ለግዜው የፊታችን ሰኞ እና ማክሰኞ እኛ በምናዘጋጀው ግዜያዊ መረከቢያ ቦታ ታደርሱልን ዘንድ በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን።

ቦታው #የሀገር_ፍቅር_ቴአትር ቅጥር ግቢ (ሰኞና ማክሰኞ መስከረም 28 እና 29 ብቻ) ጫካ ያደሩ ህፃናትና እናቶች አረጋውያንና ደካሞች ከምንም በላይ "የኢትዮጵያዊያን ያለህ!" እያሉ ነው።

#ሰብዓዊነት_ይቅደም !!
(ከአንድ ግዜ በላይ ሼር በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነትዎን ይወጡ)

ከያሬድ ሹመቴ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ መረጃ‼️

(ሼር ይደረግ)

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ተፈናቅለው በምዕራብ ወለጋ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ከ70 ሺህ የማያንሱ ዜጎቻችንን አስቸኳይ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።

ከብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ጋር ባደረግነው ውይይት መሰረት ለኦሮሚያ አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ቢሮ በአፋጣኝ ሰብዓዊ እርዳታዎች ለማድረስ ተስማምተናል።

በዚህም መሰረት በአዲስ አበባና በአካባቢው የምትኖሩ ለሰብዓዊ እርዳታ ገር ልብ ያላችሁ ጽኑ ኢትዮጵያዊያን የተለመደው ርብርባችሁ ይጠበቃል።

#የማይበላሹ_ምግቦች

መኮረኒ
ሩዝ
ፉርኖ ዱቄት
ዘይት
ሴሪፋም /ፋፋ/
ብስኩት /ጋቤጣ/

#የንጽህና_ቁሳቁሶች

ሳሙና
ኦሞ
ሳኒታይዘር
የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ /ሞዴስ/

#አልባሳት

ብርድ ልብስ
ነጠላ ጫማ

የተለያዩ አልባሳት (ያገለገሉም ቢሆን)
እነዚህን ቁሳቁሶች ብቻ ለግዜው የፊታችን ሰኞ እና ማክሰኞ እኛ በምናዘጋጀው ግዜያዊ መረከቢያ ቦታ ታደርሱልን ዘንድ በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን።

ቦታው #የሀገር_ፍቅር_ቴአትር ቅጥር ግቢ (ሰኞና ማክሰኞ መስከረም 28 እና 29 ብቻ) ጫካ ያደሩ ህፃናትና እናቶች አረጋውያንና ደካሞች ከምንም በላይ "የኢትዮጵያዊያን ያለህ!" እያሉ ነው።

#ሰብዓዊነት_ይቅደም !!
(ከአንድ ግዜ በላይ ሼር በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነትዎን ይወጡ)

ከያሬድ ሹመቴ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Alert‼️

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በግቢው የጥበቃና ደህንነት አሠራር ላይ ያላቸው ከፍተኛ #ተቃውሞ ከምሽቱ 4:30 አንስቶ በማሰማት ላይ ይገኛሉ።

በተለይም የተቋሙ ሴት ተማሪዎች፦ መብታቸው እንዲከበር፤ ደህንነታቸው እንዲጠበቅ፤ በግቢ ውስጥ የሚፈፀሙ ዝርፊያዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ጠይቀዋል።

🔹በሌላ በኩል የተቋሙ ተማሪዎች በግቢ ውስጥ ከሚፈፀሙ ዝርፊያዎች በተጨማሪ በዩኒቨርሲቲው አካባቢ ያለው ዝርፊያ መንግስት በአስቸኳይ እንዲያስቆም እና ወንጀለኞችም ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቀዋል።

▫️በአሁን ሰዓት #የሀገር_መከላከያ_ሰራዊት እና #ፌደራል_ፖሊስ ወደ ዩኒቨርሲቲው በመግባት ተማሪዎችን ለማረጋጋት እና ለማነጋገር እየጣሩ ይገኛሉ። ከተማሪዎች እንደሰማነውም በነገው ዕለት ተማሪው የሚካፈልበት ስብሰባ ተጠርቷል።

ምንጭ፦በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የTIKVAH-ETHIOPIA ቤተሰብ አባላት
@tsegabwolde @tukvahethiopia
ነጭ ሳር🔝

በነጭ ሣር ፓርክ ላይ ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት ተነስቶ የነበረው እሳት #በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ የፓርኩ ሥራ አስኪያጅ አቶ #ሽመልስ_ዘነበ እንደገለፁት #የሀገር_መከላከያ_ሠራዊት እና #የፖሊስ_አባለት ባደረጉት ጥረት የተነሳው እሳት በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ እሳቱ የተነሳው "አርፋይዴ" ተብሎ በሚታወቀው የፓርኩ ክፍል ሲሆን 1ሺህ ሄክታር ያህል መውደሙን አቶ ሽመልስ ገልፀዋል ፡፡ #ጂቲዜድ የተባለው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የተነሳው እሳት በቁጥጥር ስር እንዲውል የቁሳቁስ አቅርቦት እና አስፈለገውን ወጪ መሸፈኑን ተናግረዋል፡፡

ምንጭ፦ Gamo Zone Adminstration office public Relation unit
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አብን‼️

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ለአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጠ።

የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት #ብርቱካን_ሚደቅሳ ለfbc እንዳረጋገጡት፥ ለአብን የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ከጥር 28 2011 ዓ.ም ተሰጥቷል።

በዚህም መሰረት ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ለአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) #የሀገር_አቀፍ_የፖለቲካ_ፓርቲ የምዝገባ እና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጥቷል።

ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ለሁለት ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ህጋዊ እውቅና መስጠቱንም ወይዘሪት ብርቱካን ተናግረዋል።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) ሰኔ 3 2010 ዓ.ም በይፋ ተቋቁሞ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ክብር ለጀግናው #የሀገር_መከላከያ_ሰራዊት! 7ኛው የመከላከያ ቀን! እንኳን አደረሳችሁ፤ እንኳን አደረሰን!

#ቲክቫህኢትዮጵያ #tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ግብፅ‼️

ግብፅ ከ5 ሺህ በላይ ተከታይ ያላቸው እና #የሀገር_ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥሉ ይዘቶችን የሚያሰራጩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲዘጉ የሚያስችል ህግ ይፋ አደረገች፡፡

የግብፅ የመገናኛ ብዙሃንን የሚቆጣጠረው አካል ይፋ ያደረገው ይህ አሰራር በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ከፍተኛ የሆነ ገደብ እንዳላው ነው የተነገረው፡፡

አዲሱ ህግ የሀገሪቱ ከፍተኛው የመገናኛ ብዙሃን ተቆጣጣሪ አካል ሀሰተኛ ዜናዎችን የሚያሰራጩ አካላትን ለማገድ እንደሚያሰችለውና ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ እስከ 14 ሺህ 400 ዶላር ቅጣት ለመጣል እንደሚያስችለው ተነግሯል፡፡

ይህ አዲስ አሰራር በትናንትናው ዕለት ተግባራዊ መደረግ የጀመረ ሲሆን፥ እርምጃው የኤል ሲ ሲ አስተዳደር ተቃዋሚዎችን ለመቆጣጠር እንደሚያስችለው ተጠቁሟል፡፡

በቅርብ ዓመታት ውስጥ ግብፅ በመገናኛ ብዙሃን እና ጋዜጠኞች ላይ የወሰደቸው እርምጃ መነጋገሪያ ሆኖ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን፥ በዚህም በርካታ ጋዜጠኞች ለእስር መዳረጋቸው የሚታወስ ነው፡፡

እርምጃው ኢ ህገ መንግስታዊ ነው ያሉት የግብፅ አንጋፋ ጋዜጠኞች የመገናኛ ብዙሃንን ነፃነት በመጋፋት የመንግስት ባለስልጣናት በመገናኛ ብዙሃንን ቁጥጥር እንዲያደርጉ የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የሀገሪቱ ከፍተኛው የሚዲያ ተቆጣጣሪ አካል ሃላፊ ሙሃመድ አህመድ በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡

ምንጭ፡- አልጀዚራ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአሸንድዬ ጨዋታ አከባበር በላልይበላ!

በአሸንድዬ በዓል #የሀገር ውስጥ እና #የውጭ ሀገራት ጎብኝዎች እየታደሙ ነው። የአሸንድዬ በዓል "የባህል እሴቶቻችን የአብሮነታችን መሠረት ናቸው" በሚል መሪ ሀሳብ እየተከበረ ነው።

የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የላልይበላና አካባቢው ነዋሪዎች በበዓሉ እየታደሙ ነው። የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገራት ጎብኝዎችም ተገኝተዋል። ይህም በዓሉን በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለማስተዋዎቅ እና ተጠቃሚ ለመሆን ያስችላል።

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA #GERD

" አሁን ላይ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም የኮንቮይ ጉዞ ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ ችሏል " - ኢ/ር በላቸው ካሳ

የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እየተካሄደ በሚገኝበት ቀጠና በተገኘው ሰላም የግድቡ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ ተገልጿል።

የግድቡ ምክትል ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኢንጂነር በላቸው ካሳ ፤ " በቀጠናው የተገኘው አስተማማኝ ሰላም የግድቡን የግንባታ ሂደት #እያፋጠነው ይገኛል " ሲሉ አሳውቀዋል።

" የፀጥታው ጉዳይ ለግድቡ ግንባታ መሠረታዊ ፍላጎት መሆኑን በመገንዘብ #የሀገር_መከላከያ_ሰራዊት ከሌሎች የፀጥታ ሃይሎች ጋር ተቀናጅቶ ተልዕኮውን በጀግንነት በመፈፀም በቀጠናው የከፈለው መስዋዕትነት የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ያኮራ በታሪክ የሚኖር ነው  " ብለዋል።

ኢ/ር በላቸው፤ በቀጠናው በነበረው የሰላም ችግር ምክንያት ወደ ግድቡ የሚመላለሱ ተሽከርካሪዎች ከሁለትና ከሶስት ቀን በላይ በመቆም መስተጓጎል ይፈጥር እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ የኮንቮይ ጉዞ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ መቻሉን አስረድተዋል።

የግድቡን ግንባታ ዳር ለማድረስ ሌት ተቀን ሃያ አራት ሰዓት ያለ ዕረፍት የሚተጉ የግንባታዉ ሰራተኞች የአካባቢውን የሙቀት ሁኔታ ተቋቁመው ታሪካዊ ሃላፊነታቸውን በደማቅ ሞራል እየተወጡ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።

በስፍራው ከሚገኙ የሀገር መከላከያ አባላት የቀጠናውን ዘላቂ ሰላም በአስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ በማረጋገጥ ሰራዊቱ የተሰጠውን ግዳጅ በሞራል እየተወጣ እነደሆነ ተናግረዋል።

ሰራዊቱ የሀገሪቱን ሰላም የማይፈልጉ ፀረሠላም የሆኑ ኃይሎችን ፍላጎት በማምከን የግድቡን የፍፃሜ ትንሳኤ ለማብሰር ደከመኝ ሳይል ሀገራዊ ተልዕኮዉን እየተወጣ ነው ብለዋል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
👍1.3K👎91🕊5336🙏32😢29🤔26🥰17😱15
#የምርመራ_ሪፖርት

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ፤ በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ ወለጋ ዞን ጎቡ ሰዮ ወረዳ አኖ ከተማ በጥር 25/ 2015 ዓ.ም. በዋናነት #የሀገር_ውስጥ_ተፈናቃዮችን ኢላማ በማድረግ በተፈጸመ ጥቃት በሰው ሕይወት ፣ በአካልና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን በተመለከተ ከጥር 25 እስከ ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም. ምስክሮችን፣ የመንግሥት አካላትን እና የተጎጂ ቤተሰቦችን በማነጋገር ምርመራ አድርጓል፡፡

ኮሚሽኑ የላከልን መግለጫ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
😢242👍141👎21🕊10😱43
#ፀድቋል

የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ በአብላጫ ድምፅ ፀደቀ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅን አስመልክቶ የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ በአንድ ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አጽድቋል።

የውሳኔ ሃሳቡን ያቀረቡት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ ፦ " የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ሁሉን አቀፍ፣ ወጥና አስተማማኝ የሀገሪቷ ነዋሪዎች የሚመዘገቡበት ሥርዓት በመዘርጋት እና የተመዝጋቢዎችን መረጃ በመያዝ የዲጂታል መታወቂያ አጠቃቀም ስርዓትን ሕጋዊ መሠረት እንዲኖረው ማድረግ ጠቀሜታው የጎላ ነው " ብለዋል።

መታወቂያውን በመጠቀም በሚሰጡ አገልግሎቶች ላይ የግልፅነትና ተጠያቂነት አሰራር ስርዓት እንዲዘረጋና የተሳለጠ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት እንዲኖር አመቺ ሁኔታዎችን እንደሚፈጥር አክለዋል።

በጉዳዩ ላይ አስተያየት የሰጡ የም/ ቤቱ አባላት ፥ የዲጂታል መታወቂያውን በተጭበረበረ መንገድ በሚሰጡ ግለ-ሰቦች እና ተቋማት ላይ #የሀገር_ክሕደት ወንጀል እንደፈፀሙ ታስቦ ከበድ ያለ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው በዝርዝር መቀመጥ አለበት ብለዋል።

ወ/ሮ እፀገነት አዋጁ ረዘም ላለ ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጥ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀው ፤ ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት የተጭበረበረ መታወቂያ ሰጥተው ከተገኙ ከበድ ያለ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው እና አስተማማኝነቱም በመርህ ላይ መመስረቱን አስረድተዋል።

ምክር ቤቱ በጉዳዩ ዙሪያ ከተወያየ በኋላ ረቂቅ አዋጁን አዋጅ ቁጥር 1284/2015 አድርጎ በአንድ ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አፅድቆታል።

ምንጭ፦ የህ/ተ/ም/ቤት

@tikvahethiopia
👍1.48K👎210124🙏37🕊23🤔21😱21😢13🥰10
ቪድዮ ፦ ከሞስኮ ወደ ሴንት ፒተርስበርግ ይበር የነበረ የግል አውሮፕለን ተከስክሶ በውስጡ የነበሩ ሁሉም ተሳፋሪዎች መሞታቸውን የሩስያ ሲቪል አቬሽን ባለስልጣን አስታወቀ።

አውሮፕላኑ ሰባት ተሳፋሪዎች እንዲሁም ሦስት የበረራ ሠራተኞችን አሳፍሮ ነበር ተብሏል።

በዚህ አውሮፕላን ውስጥ " ቫግነር " የተሰኘው ቅጥረኛ ቡድን መሪ የቭጌኒ ፕሪጎዢን ተሳፍሮበት ነበር ተብሏል። ከሱ በተጨማሪ ድሚትሪ ዩትኪን የተባለው ከቡድኑ መስራች አንድ ውስጥ ነበረበት ተብሏል።

ከቅጥረኛ ቡድኑ ቫግነር ጋር ግንኙነት ያለውና " ግሬይ ዞን " የተሰኘ የቴሌግራም ቻናል ፕሪጎዢን ተሳፍሮበት የነበረው ጄት በአየር መከላከያ ተመትቶ ወድቋል ብሏል።

አውሮፕላኑ የተመታው በሰሜናዊ ሞስኮ ቴቨር ክልል ውስጥ ነው ሲል ገልጿል።

ፕሪጎዢን የተባለው ግለሰብ አለበት ተብሎ የታመነው አውሮፕላን ሲከሰከስ የሚያሳዩ ቪድዮዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጩ ይገኛሉ።

ይኸው የቅጥረኛ ቡድኑ መሪ ከጥቂት ወራት በፊት በሩሲያ ጦር ላይ ያልተሳካ አመጽ መርቶ የነበረ ሲሆን በዚህም #የሀገር_ክህደት_ወንጀል ክስ ተመስርቶበት ነበር።

ከክሱ በኃላ ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ባደረገው ድርድር ክሱ ውድቅ ተደርጎለት ነበር።

ቫግነር ማነው ?

ይህ ቡድን እራሱን ‘የግል የጦር ኩባንያ’ ብሎ ይገልጻል። ነገር ግን ለሩሲያ መንግሥት ቅርበት ያለው ቅጥረኛ ተዋጊ ቡድን ነው።

መሥራቹ ደግመ የቀድሞው ወንጀለኛ የአሁኑ የቭላድሚር ፑቲን የቅርብ ወዳጅ የነበረው የቭጌኒ ፕሪጎዚን ነው።

የቡድኑ ዋና ተግባሩ ተቀጥሮ መዋጋት ሲሆን በዩክሬን ጦርነት ከሩሲያ ጎን በመሰለፍ ቁልፍ ሚና እንደተጫወተ ይነገራል።

በአፍሪካ ከ10 ባላነሱ አገራት ውስጥ ተሰማርቷል።

Via BBC / TSI
Video : Social Media

@tikvahethiopia
👍1.61K😢370214😱79🕊59👎34👏24🥰17🙏8
TIKVAH-ETHIOPIA
👏 በሀገር አቀፉ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከ600ው በተፈጥሮ እና በማህበራዊ ሳይንስ (575 እና 538) ከፍተኛውን ውጤት አምጥተው የሰቀሉት ሴት ተማሪዎች ናቸው። ከዚህ ባለፈ እጅግ በርካታ ሴት ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት በማምጣት የዘንድሮውን ፈተና ሰቅለዋል። በተመሳሳይ በትግራይ ክልል በተሰጠው ከ700 ፈተናም ሴቶች ከፍተኛ አኩሪ ውጤት ነው ያስመዘገቡት። ከላይ ለማሳያ የተወሰኑ…
#የሀገር_ተስፋዎች 👏

በ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡት አንዷ የአዲስ አበባ ፣ ብስራተ ገብርኤል ትምህርት ቤት ተማሪዋ ማዕዶት እስክንድር ናት ፤ ተማሪዋ በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600ው 573 በማምጣት ከሀገሪቱ 3ኛውን ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ሰቅላለች።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👏2.56K498🙏84🥰56😱22🕊17🤔12😡9😢6😭5
TIKVAH-ETHIOPIA
#የሀገር_ተስፋዎች 👏 በ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡት አንዷ የአዲስ አበባ ፣ ብስራተ ገብርኤል ትምህርት ቤት ተማሪዋ ማዕዶት እስክንድር ናት ፤ ተማሪዋ በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600ው 573 በማምጣት ከሀገሪቱ 3ኛውን ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ሰቅላለች። @tikvahethiopia
#የሀገር_ተስፋዎች 👏

በ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በማህበራዊ ሳይንስ ከ600ው ከመላ ሀገሪቱ ከፍተኛውን ውጤት ያመጣችው የኢትዮ ፓረንትስ ት/ቤት ተማሪዋ ዎይናብ ሰለሞን ስትሆን ከ600ው 538 በማስመዝገብ ነው የሰቀለችው።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1.67K👏980🙏87🥰70🤔48😱21🕊16😡15😢14😭11