TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ግብፅ‼️

ግብፅ ከ5 ሺህ በላይ ተከታይ ያላቸው እና #የሀገር_ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥሉ ይዘቶችን የሚያሰራጩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲዘጉ የሚያስችል ህግ ይፋ አደረገች፡፡

የግብፅ የመገናኛ ብዙሃንን የሚቆጣጠረው አካል ይፋ ያደረገው ይህ አሰራር በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ከፍተኛ የሆነ ገደብ እንዳላው ነው የተነገረው፡፡

አዲሱ ህግ የሀገሪቱ ከፍተኛው የመገናኛ ብዙሃን ተቆጣጣሪ አካል ሀሰተኛ ዜናዎችን የሚያሰራጩ አካላትን ለማገድ እንደሚያሰችለውና ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ እስከ 14 ሺህ 400 ዶላር ቅጣት ለመጣል እንደሚያስችለው ተነግሯል፡፡

ይህ አዲስ አሰራር በትናንትናው ዕለት ተግባራዊ መደረግ የጀመረ ሲሆን፥ እርምጃው የኤል ሲ ሲ አስተዳደር ተቃዋሚዎችን ለመቆጣጠር እንደሚያስችለው ተጠቁሟል፡፡

በቅርብ ዓመታት ውስጥ ግብፅ በመገናኛ ብዙሃን እና ጋዜጠኞች ላይ የወሰደቸው እርምጃ መነጋገሪያ ሆኖ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን፥ በዚህም በርካታ ጋዜጠኞች ለእስር መዳረጋቸው የሚታወስ ነው፡፡

እርምጃው ኢ ህገ መንግስታዊ ነው ያሉት የግብፅ አንጋፋ ጋዜጠኞች የመገናኛ ብዙሃንን ነፃነት በመጋፋት የመንግስት ባለስልጣናት በመገናኛ ብዙሃንን ቁጥጥር እንዲያደርጉ የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የሀገሪቱ ከፍተኛው የሚዲያ ተቆጣጣሪ አካል ሃላፊ ሙሃመድ አህመድ በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡

ምንጭ፡- አልጀዚራ
@tsegabwolde @tikvahethiopia