#ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ መገበያየት ይቻላል ? የብሔራዊ ባንክ መመሪያ በትክክል ምን ይላል ?
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ ባለፈው አመት 2016 ሐምሌ ወር ላይ የውጭ ምንዛሬ ግብይት በነፃ ገበያ እንዲመራ ከወሰነ በኋላ፣ አብሮ ይፋ በተደረገው መመሪያ በውጭ ምንዛሪ ግብይት ላይ አንዳንድ ማሻሻዎችን ማድረጉን አስታውቋል፡፡
በመመሪያው ላይ የተዘረዘሩትን ተግባራት መሰረት በማድረግም፣ ከህብረተሰቡ በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ መገበያየት ይቻላል ወይ ? የሚል ጥያቄ ይነሳል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ይህን በሚመለከት የባንክ ባለሙያዎች ማብራሪያ ጠይቋል፡፡
በዚህ ጉዳይ ዙርያ ማብራሪያቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የብሔራዊ ባንክ ባለሙያ ምን አሉ ?
" ኢትዮጵያ ውስጥ ከተፈቀደላቸው ሰዎች ውጪ፣ በውጭ ምንዛሪ መገበያየት አይፈቀድም፡፡ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በውጭ ምንዛሪ ወይም ዶላር መገበያየት አይችልም፡፡
ግብይትን በዶላር የሚፈፅሙ ሰዎች፣ የተፈቀደላቸው ብቻ ናቸው፡፡ እነዚህም ዶላር ይዘው ከውጭ የሚመጡ ቱሪስቶች፣ ዲያስፖራዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ከውጭ ሲመጡ እስከ 10 ሺህ ዶላር ይዘው እንዲገቡ ስለሚፈቀድላቸው፣ በጉምሩክ አስመዝግበው ባስገቡት ዶላር መገበያየት ይችላሉ፡፡ "
አገልግሎት ሰጭዎችስ በዶላር ማስከፈል ይችላሉ ?
" እነዚህ ሰዎች በዶላር መገበያየት የሚችሉት፣ አገልግሎታቸውን በውጭ ምንዛሪ እንዲሸጡ ከተፈቀደላቸው ተቋማት ብቻ ነው፡፡
ለምሳሌ ነጋዴዎችና አገልግሎት ሰጭዎች፣ ማለትም ሆቴሎችና አስጎብኝዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ለሰጡት አገልግሎተት በዶላር ክፍያ መቀበል እንዲችሉ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ያላቸው ናቸው፡፡ ኢትዮጵያዊ ሆኖ፣ በዶላር ግብይት መፈፀም አይችልም፣ ከተፈቀደላቸው ተቋማትም ቢሆን፡፡
እኔ ኢትዮጵያዊ ሆኜ በዶላር እንዲያስከፍል ወደ ተፈቀደለት ሆቴል ሄጄ በዶላር መጠቀም አልችልም፡፡ ዲያስፖራ ከሆነንክ ግን፣ የሆነ ሆቴል ሔደህ ለተሰጠህ አገልግሎት በዶላር መክፈል ትችላለህ፡፡ ሆቴል ደግሞ ለሰጠው አገልግሎት በዶላር የማስከፈል ፈቃድ ያለው መሆን ይጠበቅበታል፡፡ ከፋዩም፣ አስከፋዩም (ተጠቃሚውና አገልግሎት ሰጪው) በዶላር ለመገበያየት የተፈቀደላቸው ወይም እውቅና የተሰጣቸው መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
ከአንድ የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ ዶላር ማስተላለፍ ይቻላል ?
" የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፍን (ትራንስፈርን) በተመለከተ፣ ከአንድ የዶላር ሒሳብ ኢትዮጵያ ውስጥ ላለ ሌላ የዶላር ሒሳብ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፍ አይቻልም፡፡ ለምን ዓላማ ነው የሚተላለፈው ? የሚለው ይታያል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ዕቃ ገዝተህ በዶላር ልክፈል ብትል፣ አንተም በዶላር የመክፈል መብት የለህም፣ ሻጩም በዶላር ክፍያ የመቀበል ፈቃድ የለውም፣ ስለዚህ አይቻልም፡፡
ነገር ግን የዶላር አካውንት ኖሮህ፣ ከውጪ ሀገር እቃ ብትገዛ፣ ለእሱ በዶላር የመክፈል መብት አለህ፡፡ በቀጥታ ለእቃ ሻጩ ነው ዶላሩ የሚተለላለፈው፡፡ ውጭ ሀገር እቃ ወደገዛህበት መደብር ትራንስፈር ይደረጋል/ይተላለፋል፡፡ መረጃ አቅርበህ፣ ባንኩ ያንን መረጃ አይቶ አሳማኝ ሆኖ ካገኘው ይህንን ያደርግልሀል፡፡ ከራስህ ዶላር መፅሐፉን ለሸጠልህ ነጋዴ በቀጥታ ማስተላለፍ ይቻላል፡፡ ዋናው ነገር ለምን አላማ ነው የምታስተላልፈው የሚለው ነው፡፡ "
ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ ግብይት መቼ ሊጀመር ይችላል ?
" በውጭ ምንዛሪ ግብይት መቼም አይጀመርም፡፡ በየትም ሀገር በውጭ ምንዛሪ ግብይት አይደረግም፡፡ እንደዛ ከሆነ፣ የሚነግርህ ትርጉም የሀገርህን ብር አታምነውም ማለት ነው፡፡ ኢኮኖሚዋ ችግር ላይ የወደቀባት ዚምባብዌ እንኳን ያንን አላደረገችም፡፡
የውጭ ምንዛሪ ፍሰትን ለመጨመር፣ ኤክስፖርትን ለማበረታታት፣ የምታደርጋቸው ማስተካከያዎች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ከዛ ውጪ፣ ዜጎችህን በዶላር ተገበያዩ ልትል አትችልም፡፡
ለምሳሌ፣ ሪልስቴቶች ወይም አለምአቀፍ ት/ቤቶች የዋጋ እና የክፍያ ተመንን በዶላር ሲያወጡ ይታያል፡፡ ይህ ችግር የለውም፡፡ ክፍያው ሲፈፀም ግን በኢትዮጵያ ብር ነው የምትከፍለው፡፡ "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጣይ ፦
- ለውጭ ጉዞ ዶላር/የውጭ ምንዛሪ እንዴት ነው የሚሰጠው ?
- የባንኮች ቪዛ ካርዶች እንዴት ነው የምንጠቀምባቸው ?
- የባንኮች ቪዛ ካርዶች በሀገር ውስጥ የምንጠቀምበት ዕድል አለ ?
- የዶላር አካውንት/የውጭ ምንዛሪ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት ቅድመ ሁኔታ አለ ? በሚሉ ጥያቄዎች ላይ የባለሙያ ማብራሪያ ያቀርባል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ መገበያየት ይቻላል ? የብሔራዊ ባንክ መመሪያ በትክክል ምን ይላል ?
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ ባለፈው አመት 2016 ሐምሌ ወር ላይ የውጭ ምንዛሬ ግብይት በነፃ ገበያ እንዲመራ ከወሰነ በኋላ፣ አብሮ ይፋ በተደረገው መመሪያ በውጭ ምንዛሪ ግብይት ላይ አንዳንድ ማሻሻዎችን ማድረጉን አስታውቋል፡፡
በመመሪያው ላይ የተዘረዘሩትን ተግባራት መሰረት በማድረግም፣ ከህብረተሰቡ በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ መገበያየት ይቻላል ወይ ? የሚል ጥያቄ ይነሳል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ይህን በሚመለከት የባንክ ባለሙያዎች ማብራሪያ ጠይቋል፡፡
በዚህ ጉዳይ ዙርያ ማብራሪያቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የብሔራዊ ባንክ ባለሙያ ምን አሉ ?
" ኢትዮጵያ ውስጥ ከተፈቀደላቸው ሰዎች ውጪ፣ በውጭ ምንዛሪ መገበያየት አይፈቀድም፡፡ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በውጭ ምንዛሪ ወይም ዶላር መገበያየት አይችልም፡፡
ግብይትን በዶላር የሚፈፅሙ ሰዎች፣ የተፈቀደላቸው ብቻ ናቸው፡፡ እነዚህም ዶላር ይዘው ከውጭ የሚመጡ ቱሪስቶች፣ ዲያስፖራዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ከውጭ ሲመጡ እስከ 10 ሺህ ዶላር ይዘው እንዲገቡ ስለሚፈቀድላቸው፣ በጉምሩክ አስመዝግበው ባስገቡት ዶላር መገበያየት ይችላሉ፡፡ "
አገልግሎት ሰጭዎችስ በዶላር ማስከፈል ይችላሉ ?
" እነዚህ ሰዎች በዶላር መገበያየት የሚችሉት፣ አገልግሎታቸውን በውጭ ምንዛሪ እንዲሸጡ ከተፈቀደላቸው ተቋማት ብቻ ነው፡፡
ለምሳሌ ነጋዴዎችና አገልግሎት ሰጭዎች፣ ማለትም ሆቴሎችና አስጎብኝዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ለሰጡት አገልግሎተት በዶላር ክፍያ መቀበል እንዲችሉ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ያላቸው ናቸው፡፡ ኢትዮጵያዊ ሆኖ፣ በዶላር ግብይት መፈፀም አይችልም፣ ከተፈቀደላቸው ተቋማትም ቢሆን፡፡
እኔ ኢትዮጵያዊ ሆኜ በዶላር እንዲያስከፍል ወደ ተፈቀደለት ሆቴል ሄጄ በዶላር መጠቀም አልችልም፡፡ ዲያስፖራ ከሆነንክ ግን፣ የሆነ ሆቴል ሔደህ ለተሰጠህ አገልግሎት በዶላር መክፈል ትችላለህ፡፡ ሆቴል ደግሞ ለሰጠው አገልግሎት በዶላር የማስከፈል ፈቃድ ያለው መሆን ይጠበቅበታል፡፡ ከፋዩም፣ አስከፋዩም (ተጠቃሚውና አገልግሎት ሰጪው) በዶላር ለመገበያየት የተፈቀደላቸው ወይም እውቅና የተሰጣቸው መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
ከአንድ የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ ዶላር ማስተላለፍ ይቻላል ?
" የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፍን (ትራንስፈርን) በተመለከተ፣ ከአንድ የዶላር ሒሳብ ኢትዮጵያ ውስጥ ላለ ሌላ የዶላር ሒሳብ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፍ አይቻልም፡፡ ለምን ዓላማ ነው የሚተላለፈው ? የሚለው ይታያል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ዕቃ ገዝተህ በዶላር ልክፈል ብትል፣ አንተም በዶላር የመክፈል መብት የለህም፣ ሻጩም በዶላር ክፍያ የመቀበል ፈቃድ የለውም፣ ስለዚህ አይቻልም፡፡
ነገር ግን የዶላር አካውንት ኖሮህ፣ ከውጪ ሀገር እቃ ብትገዛ፣ ለእሱ በዶላር የመክፈል መብት አለህ፡፡ በቀጥታ ለእቃ ሻጩ ነው ዶላሩ የሚተለላለፈው፡፡ ውጭ ሀገር እቃ ወደገዛህበት መደብር ትራንስፈር ይደረጋል/ይተላለፋል፡፡ መረጃ አቅርበህ፣ ባንኩ ያንን መረጃ አይቶ አሳማኝ ሆኖ ካገኘው ይህንን ያደርግልሀል፡፡ ከራስህ ዶላር መፅሐፉን ለሸጠልህ ነጋዴ በቀጥታ ማስተላለፍ ይቻላል፡፡ ዋናው ነገር ለምን አላማ ነው የምታስተላልፈው የሚለው ነው፡፡ "
ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ ግብይት መቼ ሊጀመር ይችላል ?
" በውጭ ምንዛሪ ግብይት መቼም አይጀመርም፡፡ በየትም ሀገር በውጭ ምንዛሪ ግብይት አይደረግም፡፡ እንደዛ ከሆነ፣ የሚነግርህ ትርጉም የሀገርህን ብር አታምነውም ማለት ነው፡፡ ኢኮኖሚዋ ችግር ላይ የወደቀባት ዚምባብዌ እንኳን ያንን አላደረገችም፡፡
የውጭ ምንዛሪ ፍሰትን ለመጨመር፣ ኤክስፖርትን ለማበረታታት፣ የምታደርጋቸው ማስተካከያዎች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ከዛ ውጪ፣ ዜጎችህን በዶላር ተገበያዩ ልትል አትችልም፡፡
ለምሳሌ፣ ሪልስቴቶች ወይም አለምአቀፍ ት/ቤቶች የዋጋ እና የክፍያ ተመንን በዶላር ሲያወጡ ይታያል፡፡ ይህ ችግር የለውም፡፡ ክፍያው ሲፈፀም ግን በኢትዮጵያ ብር ነው የምትከፍለው፡፡ "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጣይ ፦
- ለውጭ ጉዞ ዶላር/የውጭ ምንዛሪ እንዴት ነው የሚሰጠው ?
- የባንኮች ቪዛ ካርዶች እንዴት ነው የምንጠቀምባቸው ?
- የባንኮች ቪዛ ካርዶች በሀገር ውስጥ የምንጠቀምበት ዕድል አለ ?
- የዶላር አካውንት/የውጭ ምንዛሪ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት ቅድመ ሁኔታ አለ ? በሚሉ ጥያቄዎች ላይ የባለሙያ ማብራሪያ ያቀርባል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
2❤403👏104🙏66😡52😭49🤔34🥰15🕊15😢14😱10💔4
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ መገበያየት ይቻላል ? የብሔራዊ ባንክ መመሪያ በትክክል ምን ይላል ? የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ ባለፈው አመት 2016 ሐምሌ ወር ላይ የውጭ ምንዛሬ ግብይት በነፃ ገበያ እንዲመራ ከወሰነ በኋላ፣ አብሮ ይፋ በተደረገው መመሪያ በውጭ ምንዛሪ ግብይት ላይ አንዳንድ ማሻሻዎችን ማድረጉን አስታውቋል፡፡ በመመሪያው ላይ የተዘረዘሩትን ተግባራት መሰረት በማድረግም፣ ከህብረተሰቡ…
#ኢትዮጵያ
" የዶላር ባንክ ሒሳብ ለመክፈት የዶላር ምንጭህ መታወቅ አለበት፡፡ ከዚሁ በጥቁር ገበያ እየለቃቀምክ ማስገባት አትችልም፡፡ ይህ ህገወጥ ነው " - የባንክ ባለሙያ
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከብሔራዊ ባንክ ባለሙያ ጋር ፦
- ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሬ መገበያያት ይቻላል ወይ ?
- አገልግሎት ሰጪዎች በዶላር ማስከፈል ይችላሉ ?
- ከአንድ የባንክ ሒሳብ ወደሌላ የባንክ ሒሳብ ዶላር ማስተላለፍ ይቻላል ?
- ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ ግብይት መቼ ሊጀመር ይችላል ?
የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ማብራሪያ ማቅረቡ ይታወሳል።
ለዛሬ ደሞ ከኚሁ ባለሙያ እንዲሁም ከአንድ ሌላ የባንክ ባለሙያ ጋር የተለያዩ ማብራሪያ የሚፈልጉ ጥያቄዎችን በማንሳት ያዘጋጀውን ማብራሪያ ያቀርባል።
ለውጭ ጉዞ ዶላር/የውጭ ምንዛሪ እንዴት ነው የሚሰጠው ?
" ለጉዞ ከሆነ ከራስህ ዶላር አካውንት ወይም ዶላር አካውንትም ባይኖርህ ከባንኮች ወይም ከተፈቀደላቸው የውጭ ምንዛሪ ሱቆች በግዢ እስከ 10 ሺህ ዶላር ይዘህ መውጣት ትችላለህ፡፡ ለዚህ ግን ማሳየት ያሉብህ ማስረጃዎች ይኖራሉ፣ የጉዞ ሰነዶች ማለት ነው፣ ለምሳሌ ቪዛ እና የአየር ቲኬት የመሳሰሉት፡፡ "
የባንኮች ቪዛ ካርዶች እንዴት ነው የምንጠቀምባቸው ?
" የንግድ ባንኮች ቪዛ/ማስተር ካርዶች ሁለት አላማ አላቸው፡፡
አንደኛው፣ ዳያስፖራዎች ከካርዳቸው በቀጥታ ወደ ሀገር ቤት በቀላሉ ዶላር እንዲልኩ ያስችላቸዋል፡፡ አሜሪካ ያለው ዳያስፖራ የአሜሪካ ባንክ ካርድ ይኖረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ተቀባይ ደግሞ የንግድ ባንክ ማስተር ካርድ ይኖረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ላለው ተቀባይ በካርዱ በቀላሉ ዶላር ሊያስተላልፍለት ይችላል፡፡ ተቀባዩ ደግሞ ከውጭ ዶላር ሊላክልኝ ስለሆነ የዶላር አካውንት ክፈቱልኝ ይላል፡፡ ከዛም ላኪው ከካርዱ በቀጥታ ወደ ተቀባዩ አካውንት ዶላር ያስተላልፍለታል፡፡
ሁለተኛው ጠቀሜታ፣ ከዚህ ወደ ውጭ ስትወጣ እስከ 10 ሺህ ዶላር መውሰድ ትችላለህ፡፡ ይህን በካሽ ከሚሰጡህ ይልቅ በካርድ ቢሰጡህ ይሻላል የሚል ነው፡፡ ስለዚህ ከባንክ ወደ ውጭ ይዘህ ለመውጣት የተፈቀደልህ ዶላር ማስተር ካርዱ ላይ ይጫናል ማለት ነው፡፡ ከዛም ካርዱን ይዘህ በመውጣት እንደ ኤቲኤም ትጠቀምበታለህ፡፡ "
ማስተር ካርዱን በውጭ ሀገራት ብቻ ነው የምንጠቀምበት ?
ስለዚህ ጉዳይ ያብራሩልን ማንነቴ አይጠቀስ ያሉን ሁለተኛ የባንክ ባለሙያ ፥ ቪዛ ካርዱ የሚጠቅመው ዶላር ይዞ ለመውጣት እና እዛው እንደ ኤቲኤም ለመጠቀም ነው ብለዋል፡፡
ካርዱ ላይ የሚጫነው ዶላር/የውጭ ምንዛሪ በባንክ የተፈቀደ ብቻ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ካርዱን ስላወጣህና አካውንትህ ውስጥ ዶላር ስላለህ ብቻ ካርዱ ላይ አይጫንም፡፡ አሳማኝ በሆነ ምክንያት የውጭ ጉዞ መኖሩ ከተረጋገጠ በኋላ ይዘህ እንድትወጣ የተፈቀደልህን ዶላር ካርዱ ላይ ይጭኑልሃል፡፡
ከውጭ ሀገር ከተመልስክ በኋላ፣ ካርድህ ውስጥ የተጫነውን ዶላር ካልጨረስከው ያልተጠቀምክበት ዶላር ካርዱ ውስጥ ካለ እዚህ ሀገር ካለ ኤቲኤም ማሽን ልታወጣው ትችላለህ፡፡ ግን ኤቲኤም ማሽኑ ዘርዝሮ ነው በብር የሚሰጥህ በዶላር አይሰጥህም፡፡
ለሀገር ውስጥ ግብይት ልትጠቀምበት አትችልም፡፡ ምክንያትም ቪዛ ካርድ የሚጠይቅ ግብይት የለም እዚህ ሀገር፡፡ ነገር ግን ካርድህ ውስጥ ያለውን ዶላር (ያልተጠቀምክበትን) ለውጭ ግብይት ልትጠቀምበት ትችላለህ፡፡ የካርድ ቁጥርህን በመናገር የፈለከውን ክፍያ ትፈፅምበታለህ፡፡ ለምሳሌ የቪዛ ክፍያ የሚጠይቁ ኤምባሲዎች አሉ ' በዶላር ክፈል ' ይሉሀል፡፡ ቪዛ ካርድ ካለህ (ቀድሞ ዶላር የተጫነበት) የካርድ ቁጥሩን ትነግራቸውና ከዛ መቀነስ ይችላሉ፡፡ "
የባንኮች ቪዛ ካርዶች በሀገር ውስጥ የምንጠቀምበት ዕድል አለ ?
" ቪዛ ካርዶቹ ብርም ሊጫንባቸው ይችላል፡፡ ንግድ ባንኮች ካርዶቹን ከዶላር በተጨማሪ ብርም ከጫኑባቸው እዚህ እንደ ኤቲኤም ልትጠቀምባቸው ትችላለህ፡፡ እንደዛ የሚያደርጉ ባንኮች አሉ፡፡
ለምሳሌ ፦ አንዳንድ ባንኮች በቪዛ ካርዳችሁ መጥታችሁ በፖስ ማሽን ተጠቀሙ የሚል ማስታወቂያ ሲያስነግሩ እንሰማለን፡፡ ይህ ማለት ቪዛ ካርዳቸው ከዶላር በተጨማሪ ብርም ተጭኖበታል ማለት ነው፡፡ ሁለቱንም አገልግሎት እንዲሰጥ ይደረጋል ቪዛ ካርዱ፡፡
ፖስ ማሽኑ እና ኤቲኤም ማሽኑ ቪዛ ካርዶችን ያነብባል፡፡ ይህ ግን እንደ ባንኩ ምርጫ ይወሰናል፡፡ ሁለቱንም እንዲያገለግል (ዱዋል ማለት ነው ብርም ዶላርም እንዲጫንበት) ሊያደርግ ይችላል ወይም ለውጭ ምንዛሪ አገልግሎት ብቻ እንዲሆን ሊያደርግ ይችላል።
ቪዛ ካርዱ ዱዋል (ለሁለቱም የሚያገለግል) ካልሆነ ግን አንዴ ከተጠቀምክበት በኋላ ከጥቅም ውጪ ነው የሚሆነው፡፡ ሁሌም ወደ ውጭ አትመላለስም፡፡ "
የዶላር አካውንት/የውጭ ምንዛሪ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት ቅድመ ሁኔታ አለ ?
" የዶላር ባንክ ሒሳብ ለመክፈት፣ የዶላር ምንጭህ መታወቅ አለበት፡፡ ከዚሁ በጥቁር ገበያ እየለቃቀምክ ማስገባት አትችልም፡፡ ይህ ህገወጥ ነው፡፡ ከውጭ የሚገባልህ የደመወዝ ወይም የስጦታ አለያም የክፍያ ዶላር እንዳለህ ማስረዳትና ለዚያ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅብሀል፡፡
በካሽ ይዘህ ስትሔድ ደግሞ ከውጭ ያስገባኸው ዶላር ስለመሆኑ፣ በጉምሩክ በህጋዊነት የገባ መሆኑን የሚያሳይ ሰነድ ማቅረብ አለብህ፡፡ ምክንያቱም ከውጭ ስትገባ አስመዝግበህ ነው እስከ 10 ሺህ ዶላር ድረስ ይዘህ የምትገባው፡፡ ስለሆነም የዶላር የባንክ ሒሳብ/ዶላር አካውንት ለመክፈት ቅድመ ሁኔታው፣ የዶላር ምንጭህን ማሳወቅ ነው፡፡ "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የዶላር ባንክ ሒሳብ ለመክፈት የዶላር ምንጭህ መታወቅ አለበት፡፡ ከዚሁ በጥቁር ገበያ እየለቃቀምክ ማስገባት አትችልም፡፡ ይህ ህገወጥ ነው " - የባንክ ባለሙያ
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከብሔራዊ ባንክ ባለሙያ ጋር ፦
- ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሬ መገበያያት ይቻላል ወይ ?
- አገልግሎት ሰጪዎች በዶላር ማስከፈል ይችላሉ ?
- ከአንድ የባንክ ሒሳብ ወደሌላ የባንክ ሒሳብ ዶላር ማስተላለፍ ይቻላል ?
- ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ ግብይት መቼ ሊጀመር ይችላል ?
የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ማብራሪያ ማቅረቡ ይታወሳል።
ለዛሬ ደሞ ከኚሁ ባለሙያ እንዲሁም ከአንድ ሌላ የባንክ ባለሙያ ጋር የተለያዩ ማብራሪያ የሚፈልጉ ጥያቄዎችን በማንሳት ያዘጋጀውን ማብራሪያ ያቀርባል።
ለውጭ ጉዞ ዶላር/የውጭ ምንዛሪ እንዴት ነው የሚሰጠው ?
" ለጉዞ ከሆነ ከራስህ ዶላር አካውንት ወይም ዶላር አካውንትም ባይኖርህ ከባንኮች ወይም ከተፈቀደላቸው የውጭ ምንዛሪ ሱቆች በግዢ እስከ 10 ሺህ ዶላር ይዘህ መውጣት ትችላለህ፡፡ ለዚህ ግን ማሳየት ያሉብህ ማስረጃዎች ይኖራሉ፣ የጉዞ ሰነዶች ማለት ነው፣ ለምሳሌ ቪዛ እና የአየር ቲኬት የመሳሰሉት፡፡ "
የባንኮች ቪዛ ካርዶች እንዴት ነው የምንጠቀምባቸው ?
" የንግድ ባንኮች ቪዛ/ማስተር ካርዶች ሁለት አላማ አላቸው፡፡
አንደኛው፣ ዳያስፖራዎች ከካርዳቸው በቀጥታ ወደ ሀገር ቤት በቀላሉ ዶላር እንዲልኩ ያስችላቸዋል፡፡ አሜሪካ ያለው ዳያስፖራ የአሜሪካ ባንክ ካርድ ይኖረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ተቀባይ ደግሞ የንግድ ባንክ ማስተር ካርድ ይኖረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ላለው ተቀባይ በካርዱ በቀላሉ ዶላር ሊያስተላልፍለት ይችላል፡፡ ተቀባዩ ደግሞ ከውጭ ዶላር ሊላክልኝ ስለሆነ የዶላር አካውንት ክፈቱልኝ ይላል፡፡ ከዛም ላኪው ከካርዱ በቀጥታ ወደ ተቀባዩ አካውንት ዶላር ያስተላልፍለታል፡፡
ሁለተኛው ጠቀሜታ፣ ከዚህ ወደ ውጭ ስትወጣ እስከ 10 ሺህ ዶላር መውሰድ ትችላለህ፡፡ ይህን በካሽ ከሚሰጡህ ይልቅ በካርድ ቢሰጡህ ይሻላል የሚል ነው፡፡ ስለዚህ ከባንክ ወደ ውጭ ይዘህ ለመውጣት የተፈቀደልህ ዶላር ማስተር ካርዱ ላይ ይጫናል ማለት ነው፡፡ ከዛም ካርዱን ይዘህ በመውጣት እንደ ኤቲኤም ትጠቀምበታለህ፡፡ "
ማስተር ካርዱን በውጭ ሀገራት ብቻ ነው የምንጠቀምበት ?
ስለዚህ ጉዳይ ያብራሩልን ማንነቴ አይጠቀስ ያሉን ሁለተኛ የባንክ ባለሙያ ፥ ቪዛ ካርዱ የሚጠቅመው ዶላር ይዞ ለመውጣት እና እዛው እንደ ኤቲኤም ለመጠቀም ነው ብለዋል፡፡
ካርዱ ላይ የሚጫነው ዶላር/የውጭ ምንዛሪ በባንክ የተፈቀደ ብቻ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ካርዱን ስላወጣህና አካውንትህ ውስጥ ዶላር ስላለህ ብቻ ካርዱ ላይ አይጫንም፡፡ አሳማኝ በሆነ ምክንያት የውጭ ጉዞ መኖሩ ከተረጋገጠ በኋላ ይዘህ እንድትወጣ የተፈቀደልህን ዶላር ካርዱ ላይ ይጭኑልሃል፡፡
ከውጭ ሀገር ከተመልስክ በኋላ፣ ካርድህ ውስጥ የተጫነውን ዶላር ካልጨረስከው ያልተጠቀምክበት ዶላር ካርዱ ውስጥ ካለ እዚህ ሀገር ካለ ኤቲኤም ማሽን ልታወጣው ትችላለህ፡፡ ግን ኤቲኤም ማሽኑ ዘርዝሮ ነው በብር የሚሰጥህ በዶላር አይሰጥህም፡፡
ለሀገር ውስጥ ግብይት ልትጠቀምበት አትችልም፡፡ ምክንያትም ቪዛ ካርድ የሚጠይቅ ግብይት የለም እዚህ ሀገር፡፡ ነገር ግን ካርድህ ውስጥ ያለውን ዶላር (ያልተጠቀምክበትን) ለውጭ ግብይት ልትጠቀምበት ትችላለህ፡፡ የካርድ ቁጥርህን በመናገር የፈለከውን ክፍያ ትፈፅምበታለህ፡፡ ለምሳሌ የቪዛ ክፍያ የሚጠይቁ ኤምባሲዎች አሉ ' በዶላር ክፈል ' ይሉሀል፡፡ ቪዛ ካርድ ካለህ (ቀድሞ ዶላር የተጫነበት) የካርድ ቁጥሩን ትነግራቸውና ከዛ መቀነስ ይችላሉ፡፡ "
የባንኮች ቪዛ ካርዶች በሀገር ውስጥ የምንጠቀምበት ዕድል አለ ?
" ቪዛ ካርዶቹ ብርም ሊጫንባቸው ይችላል፡፡ ንግድ ባንኮች ካርዶቹን ከዶላር በተጨማሪ ብርም ከጫኑባቸው እዚህ እንደ ኤቲኤም ልትጠቀምባቸው ትችላለህ፡፡ እንደዛ የሚያደርጉ ባንኮች አሉ፡፡
ለምሳሌ ፦ አንዳንድ ባንኮች በቪዛ ካርዳችሁ መጥታችሁ በፖስ ማሽን ተጠቀሙ የሚል ማስታወቂያ ሲያስነግሩ እንሰማለን፡፡ ይህ ማለት ቪዛ ካርዳቸው ከዶላር በተጨማሪ ብርም ተጭኖበታል ማለት ነው፡፡ ሁለቱንም አገልግሎት እንዲሰጥ ይደረጋል ቪዛ ካርዱ፡፡
ፖስ ማሽኑ እና ኤቲኤም ማሽኑ ቪዛ ካርዶችን ያነብባል፡፡ ይህ ግን እንደ ባንኩ ምርጫ ይወሰናል፡፡ ሁለቱንም እንዲያገለግል (ዱዋል ማለት ነው ብርም ዶላርም እንዲጫንበት) ሊያደርግ ይችላል ወይም ለውጭ ምንዛሪ አገልግሎት ብቻ እንዲሆን ሊያደርግ ይችላል።
ቪዛ ካርዱ ዱዋል (ለሁለቱም የሚያገለግል) ካልሆነ ግን አንዴ ከተጠቀምክበት በኋላ ከጥቅም ውጪ ነው የሚሆነው፡፡ ሁሌም ወደ ውጭ አትመላለስም፡፡ "
የዶላር አካውንት/የውጭ ምንዛሪ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት ቅድመ ሁኔታ አለ ?
" የዶላር ባንክ ሒሳብ ለመክፈት፣ የዶላር ምንጭህ መታወቅ አለበት፡፡ ከዚሁ በጥቁር ገበያ እየለቃቀምክ ማስገባት አትችልም፡፡ ይህ ህገወጥ ነው፡፡ ከውጭ የሚገባልህ የደመወዝ ወይም የስጦታ አለያም የክፍያ ዶላር እንዳለህ ማስረዳትና ለዚያ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅብሀል፡፡
በካሽ ይዘህ ስትሔድ ደግሞ ከውጭ ያስገባኸው ዶላር ስለመሆኑ፣ በጉምሩክ በህጋዊነት የገባ መሆኑን የሚያሳይ ሰነድ ማቅረብ አለብህ፡፡ ምክንያቱም ከውጭ ስትገባ አስመዝግበህ ነው እስከ 10 ሺህ ዶላር ድረስ ይዘህ የምትገባው፡፡ ስለሆነም የዶላር የባንክ ሒሳብ/ዶላር አካውንት ለመክፈት ቅድመ ሁኔታው፣ የዶላር ምንጭህን ማሳወቅ ነው፡፡ "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
6❤293😡141🙏52😭26🤔19👏17🕊13😱10💔10😢8🥰7
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኢትዮጵያ #ረቂቅአዋጅ
የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ መሬትን በሊዝ በባለቤትነት መያዝ የሚያስችላቸው የአዋጅ ረቂቅ ነገ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባል።
የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት " ባለቤት ' ወይም " ባለይዞታ " የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣው ይህ " የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበት " ወይም " ለመኖሪያ ቤት ግንባታ የሚውል መሬት የሚያገኙበትን " ህጋዊ አሰራር ለመዘርጋት ነው።
ረቂቅ አዋጁ ምን ይላል ?
- ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸው ግለሰቦች በኢትዮጵያ መሬትን፣ የመኖሪያ ቤትን ወይም ተያያዥ ግንባታዎችን በባለቤትነት ለመያዝ፤ ቢያንስ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ሊመድቡ እንደሚገባ ይደነግጋል።
- በውጭ ዜጋ " በሊዝ ባለይዞታነት " ወይም " ባለቤትነት " የሚያዝ መሬት ወይም የመኖሪያ ቤት፤ " የማይንቀሳቀስ ንብረት " ተደርጎ ይወሰዳል። " ሊዝ " ማለት " አግባብነት ባለው ህግ መሰረት በጊዜ በተገደበ ውል ለመኖሪያ ቤት ግንባታ ዓላማ የሚውል የከተማ ወይም የገጠር መሬት የሚገኝበት የመሬት ይዞታ ስሪት " ነው።
- ማንኛውም የውጭ ዜጋ በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ ሊሆን የሚችለው በአዋጁ የተዘረዘሩ ቅደመ ሁኔታዎችን ሲያሟላ ነው።
እነዚህም ፦
° የውጭ ዜጋው ስም፣ ዜግነት እና ሌሎችን ማንነትን የሚገልጹ ህጋዊ ሰነዶችን ማቅረብ አለበት።
° የውጭ ዜጋው የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለመብት ለመሆን የሚያስፈልግ አነስተኛ የገንዘብ መጠን ለማሟላት የሚያስችል በቂ አቅም ያለው መሆን አለበት።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ለመሆን፤ የሊዝ ዋጋውን ጨምሮ ለአንድ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሙሉ ዋጋ ወይም ለመኖሪያ ቤት ግዢ የሚመድበው አነስተኛ የገንዘብ መጠን ከ150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ያነሰ ሊሆን አይችልም።
° የውጭ ዜጋው የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆን ይገባዋል።
እነዚህን መስፈርቶች የሚያሟላ አንድ የውጭ ዜጋ ከከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የሚሰጥ ፈቃድ ሊያገኝ ይገባዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ " የፈቃድ ይሰጠኝ " ማመልከቻ ላቀረበ የውጭ ዜጋ፤ አስፈላጊውን ምርመራ በማድረግ በ15 ቀናት ውስጥ ውሳኔ መስጠት ይጠበቅበታል።
- የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከውጭ ዜጎች የሚጠበቀውን የአነስተኛ ገንዘብ መጠን ከፍ ወይም ዝቅ የሚያደርግ የእያንዳንዱን የሊዝ ቦታ ወይም ቤት ስፋት እንዲሁም የሊዝ ይዞታዎችን ወይም ቤቶችን አጠቃላይ ቁጥር የሚወስን መመሪያ የማውጣት ስልጣን በአዋጅ ረቂቁ ተሰጥቶታል። መመሪያውን የሚያወጣው፤ የቤቶች ገበያ ወቅታዊ ሁኔታን፣ የከተሞች የማይንቀሳቀስ ንብረት አማካይ ዋጋን፣ የውጭ ዜጎች በቤቶች ገበያ ያላቸውን የተሳትፎ መጠን እና የአዋጁን ዓላማ ለማሳካት የሚረዱ ሌሎች ምክንያቶችን መሰረት በማድረግ ነው።
- የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ፤ የተወሰኑ ሀገራት ዜጎችን ወይም ዜግነት የሌላቸው የውጭ ሀገር ሰዎችን በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ እንዳይሆኑ #ሊከልክል ይችላል።
- ለውጭ ዜጎች የተገደቡ ልዩ ቦታዎች እና የድንበር አካባቢዎችም እንዲሁ በሚያወጣ መመሪያ ይወሰናሉ።
- በውጭ ዜጎች ላይ የተጣሉ ሌሎች ገደቦችም አሉ።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ ለመሆን ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋም ወይም ምንጭ ገንዘብ መበደር ወይም ካፒታል ማሰባሰብ አይችልም።
° የውጭ ዜጎች ይህን ጉዳይ ለማስፈጸም የሚያስፈልጉ የሊዝ፣ የቤት ግዢ፣ የግንባታ ፈቃድ ወይም ተያያዥ የመንግስታዊ አገልግሎት ክፍያዎችን መክፈል ያለባቸው በኢትዮጵያ ተቀባይነት ባለው የውጭ ምንዛሬ ብቻ ነው።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ በመንግስት ቀጥተኛ ድጎማ ለዜጎች በሚሰሩ የጋራ መኖሪያ ህንጻዎች ውስጥ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት መሆን አይችልም። ይህ ገደብ በግል እና በመንግስት አጋርነት ወይም በተመሳሳይ የቤቶች ልማት ማዕቀፍ በፌደራል ወይም በክልል መንግስታት የሚገነቡ መኖሪያ ቤቶችን አያካትትም። ለውጭ ዜጎች የተቀመጠው ገደብ በእነዚህ አካላት አማካኝነት ለትርፍ ዓላማ ተገንብተው ለሽያጭ የሚቀርቡ ቤቶች ላይ ተፈጻሚ አይሆንም።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገጽ ነው።
@tikvahethiopia
የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ መሬትን በሊዝ በባለቤትነት መያዝ የሚያስችላቸው የአዋጅ ረቂቅ ነገ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባል።
የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት " ባለቤት ' ወይም " ባለይዞታ " የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣው ይህ " የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበት " ወይም " ለመኖሪያ ቤት ግንባታ የሚውል መሬት የሚያገኙበትን " ህጋዊ አሰራር ለመዘርጋት ነው።
ረቂቅ አዋጁ ምን ይላል ?
- ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸው ግለሰቦች በኢትዮጵያ መሬትን፣ የመኖሪያ ቤትን ወይም ተያያዥ ግንባታዎችን በባለቤትነት ለመያዝ፤ ቢያንስ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ሊመድቡ እንደሚገባ ይደነግጋል።
- በውጭ ዜጋ " በሊዝ ባለይዞታነት " ወይም " ባለቤትነት " የሚያዝ መሬት ወይም የመኖሪያ ቤት፤ " የማይንቀሳቀስ ንብረት " ተደርጎ ይወሰዳል። " ሊዝ " ማለት " አግባብነት ባለው ህግ መሰረት በጊዜ በተገደበ ውል ለመኖሪያ ቤት ግንባታ ዓላማ የሚውል የከተማ ወይም የገጠር መሬት የሚገኝበት የመሬት ይዞታ ስሪት " ነው።
- ማንኛውም የውጭ ዜጋ በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ ሊሆን የሚችለው በአዋጁ የተዘረዘሩ ቅደመ ሁኔታዎችን ሲያሟላ ነው።
እነዚህም ፦
° የውጭ ዜጋው ስም፣ ዜግነት እና ሌሎችን ማንነትን የሚገልጹ ህጋዊ ሰነዶችን ማቅረብ አለበት።
° የውጭ ዜጋው የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለመብት ለመሆን የሚያስፈልግ አነስተኛ የገንዘብ መጠን ለማሟላት የሚያስችል በቂ አቅም ያለው መሆን አለበት።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ለመሆን፤ የሊዝ ዋጋውን ጨምሮ ለአንድ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሙሉ ዋጋ ወይም ለመኖሪያ ቤት ግዢ የሚመድበው አነስተኛ የገንዘብ መጠን ከ150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ያነሰ ሊሆን አይችልም።
° የውጭ ዜጋው የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆን ይገባዋል።
እነዚህን መስፈርቶች የሚያሟላ አንድ የውጭ ዜጋ ከከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የሚሰጥ ፈቃድ ሊያገኝ ይገባዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ " የፈቃድ ይሰጠኝ " ማመልከቻ ላቀረበ የውጭ ዜጋ፤ አስፈላጊውን ምርመራ በማድረግ በ15 ቀናት ውስጥ ውሳኔ መስጠት ይጠበቅበታል።
- የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከውጭ ዜጎች የሚጠበቀውን የአነስተኛ ገንዘብ መጠን ከፍ ወይም ዝቅ የሚያደርግ የእያንዳንዱን የሊዝ ቦታ ወይም ቤት ስፋት እንዲሁም የሊዝ ይዞታዎችን ወይም ቤቶችን አጠቃላይ ቁጥር የሚወስን መመሪያ የማውጣት ስልጣን በአዋጅ ረቂቁ ተሰጥቶታል። መመሪያውን የሚያወጣው፤ የቤቶች ገበያ ወቅታዊ ሁኔታን፣ የከተሞች የማይንቀሳቀስ ንብረት አማካይ ዋጋን፣ የውጭ ዜጎች በቤቶች ገበያ ያላቸውን የተሳትፎ መጠን እና የአዋጁን ዓላማ ለማሳካት የሚረዱ ሌሎች ምክንያቶችን መሰረት በማድረግ ነው።
- የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ፤ የተወሰኑ ሀገራት ዜጎችን ወይም ዜግነት የሌላቸው የውጭ ሀገር ሰዎችን በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ እንዳይሆኑ #ሊከልክል ይችላል።
- ለውጭ ዜጎች የተገደቡ ልዩ ቦታዎች እና የድንበር አካባቢዎችም እንዲሁ በሚያወጣ መመሪያ ይወሰናሉ።
- በውጭ ዜጎች ላይ የተጣሉ ሌሎች ገደቦችም አሉ።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ ለመሆን ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋም ወይም ምንጭ ገንዘብ መበደር ወይም ካፒታል ማሰባሰብ አይችልም።
° የውጭ ዜጎች ይህን ጉዳይ ለማስፈጸም የሚያስፈልጉ የሊዝ፣ የቤት ግዢ፣ የግንባታ ፈቃድ ወይም ተያያዥ የመንግስታዊ አገልግሎት ክፍያዎችን መክፈል ያለባቸው በኢትዮጵያ ተቀባይነት ባለው የውጭ ምንዛሬ ብቻ ነው።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ በመንግስት ቀጥተኛ ድጎማ ለዜጎች በሚሰሩ የጋራ መኖሪያ ህንጻዎች ውስጥ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት መሆን አይችልም። ይህ ገደብ በግል እና በመንግስት አጋርነት ወይም በተመሳሳይ የቤቶች ልማት ማዕቀፍ በፌደራል ወይም በክልል መንግስታት የሚገነቡ መኖሪያ ቤቶችን አያካትትም። ለውጭ ዜጎች የተቀመጠው ገደብ በእነዚህ አካላት አማካኝነት ለትርፍ ዓላማ ተገንብተው ለሽያጭ የሚቀርቡ ቤቶች ላይ ተፈጻሚ አይሆንም።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገጽ ነው።
@tikvahethiopia
😡1.28K❤207😭88🤔72💔41🙏32👏21🕊18😢17😱10🥰6
#ኢትዮጵያ
በመንግሥት ብቻ ሲሰጥ የነበረው የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት የግል ዘርፍን ጨምሮ ሌሎች አካላት እንዲሳተፉ የሚያስችለው ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መተላለፉን የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስታወቀ።
በሀገሪቱ ባለፉት ዓመታት የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት በመንግሥት ብቻ ሲሰጥ መቆየቱን ያስታወሰው ምክር ቤቱ፣ ከዘርፉ እያደገ ከመጣው ፍላጎት አንፃር መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን፣ የግል ዘርፉን፣ የሕብረት ሥራ ማሕበራትንና የሙያ ማሕበራትን ማሳተፍ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝቧል።
ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በሙሉ ድምጽ ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 45ኛ መደበኛ ስብሰባው በበርካታ ጉዳዮች ላይ ከተወያየ በኋላ ውሳኔ ያሳለፈው ምክርቤቱ የስርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን በተጨማሪነት ለፓርላማው እንዲተላለፍ መወሰኑ ካፒታል ለመረዳት ተችሏል። #CAPITAL
@tikvahethiopia
በመንግሥት ብቻ ሲሰጥ የነበረው የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት የግል ዘርፍን ጨምሮ ሌሎች አካላት እንዲሳተፉ የሚያስችለው ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መተላለፉን የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስታወቀ።
በሀገሪቱ ባለፉት ዓመታት የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት በመንግሥት ብቻ ሲሰጥ መቆየቱን ያስታወሰው ምክር ቤቱ፣ ከዘርፉ እያደገ ከመጣው ፍላጎት አንፃር መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን፣ የግል ዘርፉን፣ የሕብረት ሥራ ማሕበራትንና የሙያ ማሕበራትን ማሳተፍ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝቧል።
ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በሙሉ ድምጽ ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 45ኛ መደበኛ ስብሰባው በበርካታ ጉዳዮች ላይ ከተወያየ በኋላ ውሳኔ ያሳለፈው ምክርቤቱ የስርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን በተጨማሪነት ለፓርላማው እንዲተላለፍ መወሰኑ ካፒታል ለመረዳት ተችሏል። #CAPITAL
@tikvahethiopia
😡230❤88👏29🤔19🥰11🕊10💔7😭2😢1🙏1
" ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘትን ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አንዱ አካል አድርጋ እየሰራችበት ነው።
ከቀጠናው ሀገራት ጋር ትብብር በመፍጠር ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ ጥረት እያደረገች ነው።
በጂኦግራፊያዊ አቀማመጣችን፣ በሕዝብ ብዛታችንና በታሪካችን የባህር በር ማግኘት ይገባናል።
ሁሉም ኢትዮጵያዊ ያለ ምንም ክፍፍል እና ልዩነት በመተባበር የተጀመረውን የባህር በር አጀንዳ ወደ ፊት ማስኬድ አለበት።
ሰላማዊ በሆነ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ ኢትዮጵያ እየሰራችበት የሚገኘው የባህር በር ጥያቄ ቅቡልነት ያለው ነው። " - የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ቀነአ ያደታ (ዶ/ር)
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.06K😡376👏112🕊54🤔44😭24🥰19😱15💔14😢7🙏1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Mpox #Ethiopia “ በሞያሌ በMpox የተያዙት ሦስት ሰዎች ናቸው፡፡ በጅማ ዞንም ተገኝቷል። ሁለት የተያዙ አሉ፡፡ በአጠቃላይ በኦሮሚያ አምስት ኬዞች ናቸው የተገኙት ” - የክልሉ ጤና ቢሮ በሞያሌ ከተያዙት በተጨማሪ በጅማ ዞንም ሁለት ሰዎች በዝንጀሮ ፈንጣጣ/Mpox መያዛቸውን፣ በአጠቃላይ በክልሉ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ብዛት አምስት መድረሱን የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።…
#ኢትዮጵያ
በMpox በሽታ የመጀመሪያው ሞት መመዝገቡን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
በኢትዮጵያ የMpox (የዝንጀሮ ፈንጣጣ) መገኘቱ ከተገለጸ በኃላ በዛሬው ዕለት የመጀመሪያው ሞት መመዝገቡን ሚኒስቴሩ ይፋ አድርጓል።
እስካሁን 15 የላብራቶሪ ምርመራ ተካሂዶ 6 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን የ1 ሰው ህይወት አልፏል ተብሏል።
ከቀናት በፊት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የMpox ኬዝ በሞያሌ ከተማ መገኘቱ ይፋ መደረጉ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በMpox በሽታ የመጀመሪያው ሞት መመዝገቡን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
በኢትዮጵያ የMpox (የዝንጀሮ ፈንጣጣ) መገኘቱ ከተገለጸ በኃላ በዛሬው ዕለት የመጀመሪያው ሞት መመዝገቡን ሚኒስቴሩ ይፋ አድርጓል።
እስካሁን 15 የላብራቶሪ ምርመራ ተካሂዶ 6 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን የ1 ሰው ህይወት አልፏል ተብሏል።
ከቀናት በፊት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የMpox ኬዝ በሞያሌ ከተማ መገኘቱ ይፋ መደረጉ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😭1.61K❤424😱189🙏80😢58💔49🕊34😡26👏24🤔23🥰11
#ኢትዮጵያ 🇪🇹 #ምርጫ
" በቀጣዩ ምርጫ በፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ እናደርጋለን " - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በዛሬው ዕለት በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ቅድመ-ዝግጅትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫው ላይ ሰብሳቢዋ በቀጣዩ ምርጫ ኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያን በተግባር ለማዋል መታቀዱን አንስተዋል።
በዚህም የመራጮች ምዝገባ በከፊል እንዲሁም የእጩዎች ምዝገባ ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) እንደሚከናወን ገልጸዋል።
ይህንንም ለማስቻል ከዚህ ቀደም የነበረው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ላይ ማሻሻያ ተደርጎበት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መላኩን አስረድተዋል።
ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ በምን መልኩ ነው በቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ተግባራዊ የሚደረገው ?
የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ፋይዳ መታወቂያ በተሻሻለው አዋጁ ማንነትን የሚገልጽ ሆኖ ተካቷል ብለዋል።
" ምርጫው በፋይዳ ብቻ ነው አይደለም። ፋይዳ አንድ ሰው አንድ ነው የሚለውን ይለይልናል በዛ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ እናደርጋለን። ያ የሌለው ደግሞ ከዚህ ቀደም በነበረው ሥርዓት የሚመዘገቡበት ሁኔታ ይኖራል። መራጮች የፋይዳ መታወቂያ ስለሌላቸው ከምዝገባ አይከለከሉም " ሲሉ ነው ያስረዱት።
ወደ ዲጂታል ምዝገባ ስለሚቀየረው የእጩዎች ምዝገባ ምን አሉ ?
ከዚህ ቀደም በምርጫ ክልል ደረጃ የሚሰጠው የእጩዎች ምዝገባ ተቀይሮ ሙሉ ለሙሉ እጩዎች ካሉበት ሆነው ራሳቸውን የሚመዘግቡበት ሥርዓት መዘጋጀቱን ገልጸዋል። ይህም ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ ወጪ ያስቀራል ነው ያሉት።
ከዚህ በተጨማሪም የምርጫ አስፈጻሚዎችም በተመሳሳይ መልኩ ኦላይን የሚመዘገቡበት እንዲሁም፤ ኦላይን ፈተና ወስደው ወደ ሥራ የሚገቡበት እንዲሁም ስለመገኘታቸው ሁሉ ማረጋገጫ የሚሰጥ ሥርዓት መበጀቱንም ነው ሰብሳቢዋ ያነሱት።
ክፍያን በተመለከተም ከዚህ ቀደም የነበሩ ክፍያ አልተፈጸመልንም የሚሉ ሰፊ ቅሬታዎችን ሊቀርፍ በሚችልና በፍጥነት ሊከፈልበት የሚችል ሥርዓት ተዘርግቷል ብለዋል።
" ፓርቲዎች አባሎቻቸውንም የሚመዘግቡበት ሶፍትዌር በማዘጋጀት ላይ ነን " ሲሉም የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ተናግረዋል።
ሁሉም ሶፍትዌሮች በራስ አቅም የተሰሩ መሆናቸውን ፤ ይህም በግዢ ቢሆን ኖሮ ብዙ ገንዘብ ይወጣ እንደነበር ገልጸዋል።
ቦርዱ በሰጠው መግለጫ በሚቀጥለው ምርጫ በስፋት የቴክኖሎጂ ውጤቶችን እንደሚጠቀም አስረድቷል።
በተጨማሪ ከ50 ሺህ በላይ የሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎችን " XY Coordinates " የመመዝገብ ስራ እየተሰራ መሆኑን የገለጸው ቦርዱ እስካሁን 12 ሺህ የምርጫ ጣቢያዎችን መመዝገባቸውን ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" በቀጣዩ ምርጫ በፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ እናደርጋለን " - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በዛሬው ዕለት በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ቅድመ-ዝግጅትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫው ላይ ሰብሳቢዋ በቀጣዩ ምርጫ ኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያን በተግባር ለማዋል መታቀዱን አንስተዋል።
በዚህም የመራጮች ምዝገባ በከፊል እንዲሁም የእጩዎች ምዝገባ ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) እንደሚከናወን ገልጸዋል።
ይህንንም ለማስቻል ከዚህ ቀደም የነበረው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ላይ ማሻሻያ ተደርጎበት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መላኩን አስረድተዋል።
ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ በምን መልኩ ነው በቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ተግባራዊ የሚደረገው ?
የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ፋይዳ መታወቂያ በተሻሻለው አዋጁ ማንነትን የሚገልጽ ሆኖ ተካቷል ብለዋል።
" ምርጫው በፋይዳ ብቻ ነው አይደለም። ፋይዳ አንድ ሰው አንድ ነው የሚለውን ይለይልናል በዛ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ እናደርጋለን። ያ የሌለው ደግሞ ከዚህ ቀደም በነበረው ሥርዓት የሚመዘገቡበት ሁኔታ ይኖራል። መራጮች የፋይዳ መታወቂያ ስለሌላቸው ከምዝገባ አይከለከሉም " ሲሉ ነው ያስረዱት።
ወደ ዲጂታል ምዝገባ ስለሚቀየረው የእጩዎች ምዝገባ ምን አሉ ?
ከዚህ ቀደም በምርጫ ክልል ደረጃ የሚሰጠው የእጩዎች ምዝገባ ተቀይሮ ሙሉ ለሙሉ እጩዎች ካሉበት ሆነው ራሳቸውን የሚመዘግቡበት ሥርዓት መዘጋጀቱን ገልጸዋል። ይህም ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ ወጪ ያስቀራል ነው ያሉት።
ከዚህ በተጨማሪም የምርጫ አስፈጻሚዎችም በተመሳሳይ መልኩ ኦላይን የሚመዘገቡበት እንዲሁም፤ ኦላይን ፈተና ወስደው ወደ ሥራ የሚገቡበት እንዲሁም ስለመገኘታቸው ሁሉ ማረጋገጫ የሚሰጥ ሥርዓት መበጀቱንም ነው ሰብሳቢዋ ያነሱት።
ክፍያን በተመለከተም ከዚህ ቀደም የነበሩ ክፍያ አልተፈጸመልንም የሚሉ ሰፊ ቅሬታዎችን ሊቀርፍ በሚችልና በፍጥነት ሊከፈልበት የሚችል ሥርዓት ተዘርግቷል ብለዋል።
" ፓርቲዎች አባሎቻቸውንም የሚመዘግቡበት ሶፍትዌር በማዘጋጀት ላይ ነን " ሲሉም የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ተናግረዋል።
ሁሉም ሶፍትዌሮች በራስ አቅም የተሰሩ መሆናቸውን ፤ ይህም በግዢ ቢሆን ኖሮ ብዙ ገንዘብ ይወጣ እንደነበር ገልጸዋል።
ቦርዱ በሰጠው መግለጫ በሚቀጥለው ምርጫ በስፋት የቴክኖሎጂ ውጤቶችን እንደሚጠቀም አስረድቷል።
በተጨማሪ ከ50 ሺህ በላይ የሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎችን " XY Coordinates " የመመዝገብ ስራ እየተሰራ መሆኑን የገለጸው ቦርዱ እስካሁን 12 ሺህ የምርጫ ጣቢያዎችን መመዝገባቸውን ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤530😡216🤔102😭38🙏25🕊10👏7😱5🥰2💔2
#ኢትዮጵያ
ለእንጀራ፣ ለዳቦ እና ለተለያዩ የሸቀጥ እቃዎች መጠቅለያነት የሚውለውን የአንድ ብሩን ፕላስቲክ ይዞ መገኘት ከ2,000 እስከ 5,000 ብር የሚያስቀጣው አዋጅ ጸደቀ፡፡
ማንኛውም ሰው አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል የፕላስቲክ ከረጢት ይዞ ከተገኘ ከ2,000 እስከ 5,000 ብር የሚያስቀጣው አዋጅ ፤ " ዜጎችን በማያውቁት ጉዳይ ለቅጣት የሚዳርግ ነው " የሚል ትችት ከምክር ቤት አባላት ቀርቦበታል፡፡
የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ የጸደቀው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ ፤ ማንኛውም ሰው አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል የፕላስቲክ ከረጢት ይዞ ከተገኝ ከ2,000 እስከ 5,000 ብር እንዲቀጣ ይደነግጋል፡፡
ያመረተ ወይም ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባ፣ ለገበያ ያቀረበ ወይም የሸጠ፣ ለንግድ ዓላማ ያከማቸ ወይም ይዞ የተገኘ ከ50,000 ብር በማያንስና ከ200,000 ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ እና ከ5 ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት እንዲቀጣ አዋጁ ያዝዛል፡፡
የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) የአዋጁን ይዘት በንባብ ከቀረቡ በኃላ የም/ቤት አባላት ጥያቄ አቅርበዋል።
የምክር ቤት አባሉ አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) ህዝባችን በፕላስቲክ እቃ ይዞ ወደ ቤቱ ከገባ ይጣለው ? ወይስ መልሶ ለአካባቢ ጥበቃ ያስረክበው ? የሚል ጥያቄ ጠይቀዋል።
አክለው የምናመርተው የፕላስቲክ ውጤት ዳግም እንድንጠቀምበት የሚያደርግ ቢሆን አይሻልም ወይ ? ምክንያቱም 10 ጊዜ የምጠቀምበትን ፕላስቲክ አንድ ጊዜ ብቻ ተጠቀም ማለት ተገቢ አይደለም፣ አዋጁ ፕላስቲኩን ከተጠቀምኩበት ወዲያ የት ማስቀመጥ እንዳለበት አላስቀመጠም ብለዋል፡፡
አዋጁ ይዞ የተገኝ እንዲቀጣ ይደነግጋል ህዝባችን የዚህ ግንዛቤ ይኖረዋል ወይ ? የትኛው ፕላስቲክ እንደሆነ የመለየት ግንዛቤስ አለው ወይ ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
ሌላ አንድ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው ማንኛውም ሰው ፕላስቲክ ይዞ ከተገኘ ከሁለት እስከ አምስት ሺህ ብር እንዲቀጣ ይደነግጋል፤ ይህ ከእኛ ነባራዊ ሁኔታ ጋር እንዴት ታየ ? በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያለው የማህበረሰብ ክፍል ሊጠቀመው ስለሚችል ጫና አይፈጥርም ወይ ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጡት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ(ዶ/ር) ለአንድ ጊዜ ብቻ አገልግሎት ላይ የሚውሉ ፌስታሎችን ዝቅተኛው የማህበረሰብ ክፍልም ስለሚጠቀማቸው ቅጣቱ ያን ግንዛቤ ውስጥ ያስገባ ነው ብለዋል፡፡
" ለምሳሌ አንዲት አሮጊት ወይም ሽማግሌ የሁለት ብር ዳቦ ወይም የአስር ብር ስኳር ገዝተው ሲሄዱ 5 ሺህ ብር ክፍሉ ቢባሉ ላይኖራቸው ስለሚችል ቅጣቱ ከ5 ሺህ ወደ 2 ሺህ ዝቅ እንዲል ተደርጓል ይህም የህብረተሰቡን የመክፈልም አቅም ከግንዛቤ ያስገባ ነው " ሲሉ አስረድተዋል፡፡
" የፕላስቲክ ከረጢቶች ከቅጣቱ በላይ ሀገርን የሚጎዱ ናቸው እስከ መቶ ዓመት ድረስም አይበሰብሱም " ያሉት ምክትል ሰብሳቢው፤ " ከዚህ አንጻር ቅጣቱ ሃያም ሰላሰም ሺህ ቢሆን ሀገርን ለማትረፍ ነው " ብለዋል፡፡
ለህዝቡ ግንዛቤ ለመስጠትም ከመጪው ሃሙስ ጀምሮ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ይካሄዳል ሲሉ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
አዋጁ የፕላስቲክ ጫማዎችን፣ የውሃ ኮዳዎችን እና ወፍራም የፕላስቲክ ውጤቶችን አይጨምርም ተብሏል።
አዋጁ ማንኛውም ሰው ከመኖሪያ ቤቱ ድንበር አንስቶ ከሃያ ሜትር በላይ አካባቢውን የማጽዳት ግዴታንም ያስቀምጣል፡፡
አዋጁ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከሚወጣበት ቀን ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM101.2
@tikvahethiopia
ለእንጀራ፣ ለዳቦ እና ለተለያዩ የሸቀጥ እቃዎች መጠቅለያነት የሚውለውን የአንድ ብሩን ፕላስቲክ ይዞ መገኘት ከ2,000 እስከ 5,000 ብር የሚያስቀጣው አዋጅ ጸደቀ፡፡
ማንኛውም ሰው አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል የፕላስቲክ ከረጢት ይዞ ከተገኘ ከ2,000 እስከ 5,000 ብር የሚያስቀጣው አዋጅ ፤ " ዜጎችን በማያውቁት ጉዳይ ለቅጣት የሚዳርግ ነው " የሚል ትችት ከምክር ቤት አባላት ቀርቦበታል፡፡
የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ የጸደቀው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ ፤ ማንኛውም ሰው አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል የፕላስቲክ ከረጢት ይዞ ከተገኝ ከ2,000 እስከ 5,000 ብር እንዲቀጣ ይደነግጋል፡፡
ያመረተ ወይም ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባ፣ ለገበያ ያቀረበ ወይም የሸጠ፣ ለንግድ ዓላማ ያከማቸ ወይም ይዞ የተገኘ ከ50,000 ብር በማያንስና ከ200,000 ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ እና ከ5 ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት እንዲቀጣ አዋጁ ያዝዛል፡፡
የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) የአዋጁን ይዘት በንባብ ከቀረቡ በኃላ የም/ቤት አባላት ጥያቄ አቅርበዋል።
የምክር ቤት አባሉ አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) ህዝባችን በፕላስቲክ እቃ ይዞ ወደ ቤቱ ከገባ ይጣለው ? ወይስ መልሶ ለአካባቢ ጥበቃ ያስረክበው ? የሚል ጥያቄ ጠይቀዋል።
አክለው የምናመርተው የፕላስቲክ ውጤት ዳግም እንድንጠቀምበት የሚያደርግ ቢሆን አይሻልም ወይ ? ምክንያቱም 10 ጊዜ የምጠቀምበትን ፕላስቲክ አንድ ጊዜ ብቻ ተጠቀም ማለት ተገቢ አይደለም፣ አዋጁ ፕላስቲኩን ከተጠቀምኩበት ወዲያ የት ማስቀመጥ እንዳለበት አላስቀመጠም ብለዋል፡፡
አዋጁ ይዞ የተገኝ እንዲቀጣ ይደነግጋል ህዝባችን የዚህ ግንዛቤ ይኖረዋል ወይ ? የትኛው ፕላስቲክ እንደሆነ የመለየት ግንዛቤስ አለው ወይ ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
ሌላ አንድ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው ማንኛውም ሰው ፕላስቲክ ይዞ ከተገኘ ከሁለት እስከ አምስት ሺህ ብር እንዲቀጣ ይደነግጋል፤ ይህ ከእኛ ነባራዊ ሁኔታ ጋር እንዴት ታየ ? በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያለው የማህበረሰብ ክፍል ሊጠቀመው ስለሚችል ጫና አይፈጥርም ወይ ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጡት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ(ዶ/ር) ለአንድ ጊዜ ብቻ አገልግሎት ላይ የሚውሉ ፌስታሎችን ዝቅተኛው የማህበረሰብ ክፍልም ስለሚጠቀማቸው ቅጣቱ ያን ግንዛቤ ውስጥ ያስገባ ነው ብለዋል፡፡
" ለምሳሌ አንዲት አሮጊት ወይም ሽማግሌ የሁለት ብር ዳቦ ወይም የአስር ብር ስኳር ገዝተው ሲሄዱ 5 ሺህ ብር ክፍሉ ቢባሉ ላይኖራቸው ስለሚችል ቅጣቱ ከ5 ሺህ ወደ 2 ሺህ ዝቅ እንዲል ተደርጓል ይህም የህብረተሰቡን የመክፈልም አቅም ከግንዛቤ ያስገባ ነው " ሲሉ አስረድተዋል፡፡
" የፕላስቲክ ከረጢቶች ከቅጣቱ በላይ ሀገርን የሚጎዱ ናቸው እስከ መቶ ዓመት ድረስም አይበሰብሱም " ያሉት ምክትል ሰብሳቢው፤ " ከዚህ አንጻር ቅጣቱ ሃያም ሰላሰም ሺህ ቢሆን ሀገርን ለማትረፍ ነው " ብለዋል፡፡
ለህዝቡ ግንዛቤ ለመስጠትም ከመጪው ሃሙስ ጀምሮ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ይካሄዳል ሲሉ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
አዋጁ የፕላስቲክ ጫማዎችን፣ የውሃ ኮዳዎችን እና ወፍራም የፕላስቲክ ውጤቶችን አይጨምርም ተብሏል።
አዋጁ ማንኛውም ሰው ከመኖሪያ ቤቱ ድንበር አንስቶ ከሃያ ሜትር በላይ አካባቢውን የማጽዳት ግዴታንም ያስቀምጣል፡፡
አዋጁ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከሚወጣበት ቀን ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM101.2
@tikvahethiopia
😡4.19K❤1.88K🤔237😭157👏99😢66💔50😱46🕊34🥰27🙏21
#ኢትዮጵያ🇪🇹
ኢትዮጵያ የCFA የምስራቅ አፍሪካ ቻርተርን ተቀላቀለች።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ተዋናዮችን እውቅና (Certification) የሚሰጠው ሲ.ኤፍ.ኤ (CFA) በኢትዮጵያ የፈተና ማዕከል መስጠት የሚያስችለውን ስምምነት አድርጓል።
ከዚህ ቀደም ይህንን ሰርተፊኬት ለማግኘት የሚሰጠውን ፈተና ናይሮቢ ወይም ሌሎች ቻርተሮች ወደ ሚገኙበት መሄድ ይጠበቅባቸው የነበረ ሲሆን ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ቻርተርን መቀላቀሏን ተከትሎ በአዲስ አበባ የመፈተኛ ማዕከል ይኖራል ተብሏል።
በምሥራቅ አፍሪካ ይሄን ሰርተፊኬት ያገኙ ባለሞያዎች ቁጥር ከ600 ቢልቅም በኢትዮጵያ ግን ሰርተፊኬቱን ያገኙት ባለሞያዎች ቁጥር 11 ብቻ ናቸው።
በዚህ መርሐግብር የተገኙት የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀና ተኸልኩ በዘርፉ ከፍተኛ የሆነ የክክሎትና እውቀት ክፍተት መኖሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በCFA እና መሰል ተቋማት የሚሰጡት ትምህርቶችና ሰርተፊኬቶች ክህሎት፤ እውቀት እና ዲሲፕሊን አብሮ የያዙ በመሆኑ ለገቢያው ጠቃሚ እንዲሁም ዓለም አቀፍ እና ወጥ የሆነ የእውቀት ደረጃ እንዲኖር እንደሚያግዝ አስረድተዋል።
በዘርፉ ያለው የሰው ኃይል እና እውቀት ክፍተት ምን ያህል ነው ? ምንስ እየተሰራ ነው? ስንል የጠየቅናቸው ዋና ዳይሬክተሯ " ሰፊ ክፍተት አለ " ሲሉ አመላክተዋል።
ዋና ዳይሬክተሯ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የፋይናንስ እና አኮኖሚ ዘርፉን፤ ካፒታል ማርኬትን እንዲሁም በካፒታል ማርኬት ያሉ ህጎችና ደንቦችን ከመረዳት እና የሚፈጠሩ ችግሮችን በአግባቡ የማስተዳደር (Risk management) ላይ ሰፊ ክፍተት አለ።
አሁን ላይ ከfsd ጋር በመተባበር በዘርፉ የሚያስፈልገው የሰው ኃይል አቅም (Human Capital Strategy ) እየሰራን እንገኛለን ወደ መጠናቀቁ ላይ ይገኛል። ይሄ ሲጠናቀቅ ያለው ክፍተት ምንድን ነው፤ የትኞቹ ተቋማት መካፈል አለባቸው የሚለውን ይመልሳል።
ከዚህ በተጨማሪ፤ ባለሥልጣኑ የካፒታል ማርኬት ስልጠና ተቋም እያቋቋመ ነው። አሁን ላይ ከፍ ያለ የስልጠና ማኑዋል በማዘጋጀት ላይ እንገኛለን ይሄ ሲጠናቀቅ ፕሮግራሙን በይፋ አስተዋውቀን ወደ ስልጠና እንገባለ።
CFA ወደ ሀገር ውስጥ የማምጣቱም ሂደት የጥረቱ አካል ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የዩኤን ዲ ፒ ፋይናንሻል ላብ አማካኝነት በኢትዮጵያ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሞያዎች ስፖንሰር ሺፕ እንደሚሰጥም ተገልጿል።
ይህ ስኮላርሺፕ እነማንን ይመለከታል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዩ ኤን ዲፒ ፋይናንሻል ላብ ዳይሬክተር የሆኑትን ዳግማዊት ሽፈራውን ጠይቋል።
ዳይሬክተሯ በምላሻቸውም፥ ይህ ስኮላርሺፕ በዘርፉ ልምድ ላላቸው የሚሰጥ እንደሆነ የገለጹ ሲሆን፥ ለምን ያህል ሰዎች እንዲሁም የብሩን መጠን ከመግለጽ ግን ተቆጥበዋል።
" በጣም ትጋት የሚፈልግ ነው ። ፈተናውን የማለፍ ምጣኔው 49 በመቶ ነው [Level 3] ለዚህ ደግሞ የውጤቱ መጠን ከፍ ያለ እንዲሆን ልምድ ላላቸው ሰዎች እድሉን እንሰጣለን " ሲሉ ነው ያስረዱን።
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀና ተኸልኩ ባንኮች፤ ኢንሹራንሶች፤ የመንግስት ተቋማት እንዲሁም የዘርፉ ተዋናዮች ለሰራተኞቻቸው ይህን መሰል ሥልጠና እንዲያመቻቹ ጥሪ አቅርበዋል።
የCFA ሰርተፊኬት ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ገቢያውን ለመቀላቀል የሚረዳ ነው ሲባል ኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬትን ማስተዋወቋን ተከትሎ ፍላጎቱ እንደሚጨምር ይታመናል።
ይንንን ሰርተፊኬሽን ለማግኘት ሦስት ደረጃዎች ሲኖሩት ለማጠናቀቅ ከ4100 ዶላር በላይ ይጠይቃል። ከዚህም በላይ 400 የጥናት ሰዓታት በየደረጃው ይፈልጋል ተብሎ ሲገለጽ ፈጣኑ የማጠናቀቂያ ጊዜ 2 ዓመት ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ የCFA የምስራቅ አፍሪካ ቻርተርን ተቀላቀለች።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ተዋናዮችን እውቅና (Certification) የሚሰጠው ሲ.ኤፍ.ኤ (CFA) በኢትዮጵያ የፈተና ማዕከል መስጠት የሚያስችለውን ስምምነት አድርጓል።
ከዚህ ቀደም ይህንን ሰርተፊኬት ለማግኘት የሚሰጠውን ፈተና ናይሮቢ ወይም ሌሎች ቻርተሮች ወደ ሚገኙበት መሄድ ይጠበቅባቸው የነበረ ሲሆን ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ቻርተርን መቀላቀሏን ተከትሎ በአዲስ አበባ የመፈተኛ ማዕከል ይኖራል ተብሏል።
በምሥራቅ አፍሪካ ይሄን ሰርተፊኬት ያገኙ ባለሞያዎች ቁጥር ከ600 ቢልቅም በኢትዮጵያ ግን ሰርተፊኬቱን ያገኙት ባለሞያዎች ቁጥር 11 ብቻ ናቸው።
በዚህ መርሐግብር የተገኙት የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀና ተኸልኩ በዘርፉ ከፍተኛ የሆነ የክክሎትና እውቀት ክፍተት መኖሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በCFA እና መሰል ተቋማት የሚሰጡት ትምህርቶችና ሰርተፊኬቶች ክህሎት፤ እውቀት እና ዲሲፕሊን አብሮ የያዙ በመሆኑ ለገቢያው ጠቃሚ እንዲሁም ዓለም አቀፍ እና ወጥ የሆነ የእውቀት ደረጃ እንዲኖር እንደሚያግዝ አስረድተዋል።
በዘርፉ ያለው የሰው ኃይል እና እውቀት ክፍተት ምን ያህል ነው ? ምንስ እየተሰራ ነው? ስንል የጠየቅናቸው ዋና ዳይሬክተሯ " ሰፊ ክፍተት አለ " ሲሉ አመላክተዋል።
ዋና ዳይሬክተሯ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የፋይናንስ እና አኮኖሚ ዘርፉን፤ ካፒታል ማርኬትን እንዲሁም በካፒታል ማርኬት ያሉ ህጎችና ደንቦችን ከመረዳት እና የሚፈጠሩ ችግሮችን በአግባቡ የማስተዳደር (Risk management) ላይ ሰፊ ክፍተት አለ።
አሁን ላይ ከfsd ጋር በመተባበር በዘርፉ የሚያስፈልገው የሰው ኃይል አቅም (Human Capital Strategy ) እየሰራን እንገኛለን ወደ መጠናቀቁ ላይ ይገኛል። ይሄ ሲጠናቀቅ ያለው ክፍተት ምንድን ነው፤ የትኞቹ ተቋማት መካፈል አለባቸው የሚለውን ይመልሳል።
ከዚህ በተጨማሪ፤ ባለሥልጣኑ የካፒታል ማርኬት ስልጠና ተቋም እያቋቋመ ነው። አሁን ላይ ከፍ ያለ የስልጠና ማኑዋል በማዘጋጀት ላይ እንገኛለን ይሄ ሲጠናቀቅ ፕሮግራሙን በይፋ አስተዋውቀን ወደ ስልጠና እንገባለ።
CFA ወደ ሀገር ውስጥ የማምጣቱም ሂደት የጥረቱ አካል ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የዩኤን ዲ ፒ ፋይናንሻል ላብ አማካኝነት በኢትዮጵያ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሞያዎች ስፖንሰር ሺፕ እንደሚሰጥም ተገልጿል።
ይህ ስኮላርሺፕ እነማንን ይመለከታል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዩ ኤን ዲፒ ፋይናንሻል ላብ ዳይሬክተር የሆኑትን ዳግማዊት ሽፈራውን ጠይቋል።
ዳይሬክተሯ በምላሻቸውም፥ ይህ ስኮላርሺፕ በዘርፉ ልምድ ላላቸው የሚሰጥ እንደሆነ የገለጹ ሲሆን፥ ለምን ያህል ሰዎች እንዲሁም የብሩን መጠን ከመግለጽ ግን ተቆጥበዋል።
" በጣም ትጋት የሚፈልግ ነው ። ፈተናውን የማለፍ ምጣኔው 49 በመቶ ነው [Level 3] ለዚህ ደግሞ የውጤቱ መጠን ከፍ ያለ እንዲሆን ልምድ ላላቸው ሰዎች እድሉን እንሰጣለን " ሲሉ ነው ያስረዱን።
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀና ተኸልኩ ባንኮች፤ ኢንሹራንሶች፤ የመንግስት ተቋማት እንዲሁም የዘርፉ ተዋናዮች ለሰራተኞቻቸው ይህን መሰል ሥልጠና እንዲያመቻቹ ጥሪ አቅርበዋል።
የCFA ሰርተፊኬት ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ገቢያውን ለመቀላቀል የሚረዳ ነው ሲባል ኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬትን ማስተዋወቋን ተከትሎ ፍላጎቱ እንደሚጨምር ይታመናል።
ይንንን ሰርተፊኬሽን ለማግኘት ሦስት ደረጃዎች ሲኖሩት ለማጠናቀቅ ከ4100 ዶላር በላይ ይጠይቃል። ከዚህም በላይ 400 የጥናት ሰዓታት በየደረጃው ይፈልጋል ተብሎ ሲገለጽ ፈጣኑ የማጠናቀቂያ ጊዜ 2 ዓመት ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤576👏32🤔19😡17🥰9🙏8😢6🕊4😱3😭2
#ኢትዮጵያ
ወደፊት ለሚቋቋመው “ የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ” ከመንግስት እና ከግል ተቋማት ሰራተኞች ደመወዝ መዋጮ እንዲሰበሰብ የሚያስገድደው የአዋጅ ድንጋጌ ተሰርዟል።
ዛሬ “የአደጋ ስጋት ስራ አመራር አዋጅ” በፓርላማ ፀድቋል።
ከመንግስት እና ከግል ተቋማት ሰራተኞች ደመወዝ መዋጮ እንዲሰበሰብ የሚያስገድደው የአዋጅ ድንጋጌ በሰራተኞች ላይ “ተደራራቢ ጫና እንዳያስከትል” በሚል ወጥቷል።
ባለፈው መጋቢት ወር መጀመሪያ ለተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ይኸው አዋጅ፤ የመንግስት እና የግል ተቋማት ከሚሰጧቸው 15 አይነት አገልግሎቶች “ለአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ” ገቢ እንዲሰበሰቡ የሚያስገድድ ድንጋጌ በውስጡ ይዞ ነበር።
መረጃው የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ነው።
@tikvahethiopia
ወደፊት ለሚቋቋመው “ የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ” ከመንግስት እና ከግል ተቋማት ሰራተኞች ደመወዝ መዋጮ እንዲሰበሰብ የሚያስገድደው የአዋጅ ድንጋጌ ተሰርዟል።
ዛሬ “የአደጋ ስጋት ስራ አመራር አዋጅ” በፓርላማ ፀድቋል።
ከመንግስት እና ከግል ተቋማት ሰራተኞች ደመወዝ መዋጮ እንዲሰበሰብ የሚያስገድደው የአዋጅ ድንጋጌ በሰራተኞች ላይ “ተደራራቢ ጫና እንዳያስከትል” በሚል ወጥቷል።
ባለፈው መጋቢት ወር መጀመሪያ ለተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ይኸው አዋጅ፤ የመንግስት እና የግል ተቋማት ከሚሰጧቸው 15 አይነት አገልግሎቶች “ለአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ” ገቢ እንዲሰበሰቡ የሚያስገድድ ድንጋጌ በውስጡ ይዞ ነበር።
መረጃው የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ነው።
@tikvahethiopia
❤549👏186🤔46😡39🙏29🕊14😭9🥰7💔7
#ኢትዮጵያ
የገቢ ግብር ምጣኔ ላይ ማሻሻያ ለማድረግ መንግስት ረቂቅ አዋጅ ማዘጋጀቱን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።
ሬድዮ ጣቢያው ከገንዘብ ሚኒስቴር አገኘሁት ባለው መረጃ በደመወዝተኛው ሆነ በንግድ የገቢ ግብር ምጣኔ ላይ ማሻሻያዎችን የያዘ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል።
በመጭው ሰኞም በረቂቅ አዋጁ ላይ ከባለሙያዎች ጋር ለመመካከር ጥሪ ማድረጉ ተሰምቷል።
የኢትዮጵያ ሰራተኞች ኮንፌዴሬሽንና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለሙያዎች በተለይ ቋሚ ደመወዝተኛው የኑሮ ጫናውን ለመቋቋም እንዲችል የሚቆረጥበት የገቢ ግብር ትርጉም ባለው መልኩ እንዲሻሻልለት ሲጠይቁ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡
ኢትዮጵያን ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሲነጻጸር ?
የኢትዮጵያ ብር እና የኬንያ ሽልንግ ከዶላር አንፃር የምንዛሪ ዋጋቸው እኩል ነው፡፡
በኢትዮጵያ ከ600 ብር ጀምሮ የሚያገኝ ደመወዝተኛ የገቢ ግብር ይቆረጥበታል፤ በኬንያ ደግሞ የገቢ ግብር የሚቆረጠው ከ24,000 ብር ደመወዝተኛ ጀምሮ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ደመወዙ 10,900 ብርና ከዚያ በላይ የሆነ ተቀጣሪ 35 በመቶ የገቢ ግብር ሲቆረጥበት፤ በኬንያ ከ800,000 ብር ደመወዝተኛ ጀምሮ ነው 35 በመቶ የገቢ ግብር የሚቆረጥበት፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
የገቢ ግብር ምጣኔ ላይ ማሻሻያ ለማድረግ መንግስት ረቂቅ አዋጅ ማዘጋጀቱን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።
ሬድዮ ጣቢያው ከገንዘብ ሚኒስቴር አገኘሁት ባለው መረጃ በደመወዝተኛው ሆነ በንግድ የገቢ ግብር ምጣኔ ላይ ማሻሻያዎችን የያዘ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል።
በመጭው ሰኞም በረቂቅ አዋጁ ላይ ከባለሙያዎች ጋር ለመመካከር ጥሪ ማድረጉ ተሰምቷል።
የኢትዮጵያ ሰራተኞች ኮንፌዴሬሽንና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለሙያዎች በተለይ ቋሚ ደመወዝተኛው የኑሮ ጫናውን ለመቋቋም እንዲችል የሚቆረጥበት የገቢ ግብር ትርጉም ባለው መልኩ እንዲሻሻልለት ሲጠይቁ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡
ኢትዮጵያን ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሲነጻጸር ?
የኢትዮጵያ ብር እና የኬንያ ሽልንግ ከዶላር አንፃር የምንዛሪ ዋጋቸው እኩል ነው፡፡
በኢትዮጵያ ከ600 ብር ጀምሮ የሚያገኝ ደመወዝተኛ የገቢ ግብር ይቆረጥበታል፤ በኬንያ ደግሞ የገቢ ግብር የሚቆረጠው ከ24,000 ብር ደመወዝተኛ ጀምሮ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ደመወዙ 10,900 ብርና ከዚያ በላይ የሆነ ተቀጣሪ 35 በመቶ የገቢ ግብር ሲቆረጥበት፤ በኬንያ ከ800,000 ብር ደመወዝተኛ ጀምሮ ነው 35 በመቶ የገቢ ግብር የሚቆረጥበት፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
❤1.49K👏274😭213🙏96🤔80💔31😡27😱22🥰10🕊9😢6
TIKVAH-ETHIOPIA
" አዲሱ በጀት የኑሮ ውድነትንና የዋጋ ግሽበትን በሚያረጋጉ ስራዎች ላይ መዋል አለበት " - የኢኮኖሚ ባለሙያ ለቀጣዩ አመት 2018 በሚኒስትሮች ምክር ቤት የቀረበው የሁለት ትሪሊዮን ብር በጀት ህዝቡን እያስጨነቁ ያሉትን የኑሮ ውድነትና የዋጋ ግሽበት ችግሮችን ለማረጋጋት መዋል እንዳለበት የኢኮኖሚ ባለሙያው ገለፁ፡፡ የኢኮኖሚ ባለሙያውና የፖሊሲ አማካሪው ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ በጉዳዩ ዙርያ…
#ኢትዮጵያ
ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር እንደሆነ ገንዘብ ሚኒስቴር አሳውቋል።
1 ትሪሊዮን ብር ወይም 73 በመቶውን ከታክስ ገቢ ለማግኘት መታቀዱ ተሰምቷል።
የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት በሰጡት ማብራሪያ ከ2018 ረቂቅ በጀት ፦
➡️ 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣
➡️ 415 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ፣
➡️ 315 ቢሊዮን ብር ለክልል መንግስታት ድጋፍ
➡️ 14 ቢሊዮን ብር ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ የሚውል እንደሆነ ገልጸዋል።
ከረቂቅ በጀቱ ፦
🔴 1 ትሪሊዮን ብር ወይም 73 በመቶውን ከታክስ ገቢ
🔴 236 ቢሊዮን ብር ከልማት አጋሮች ቀሪውን ደግሞ ከፕሮጀክቶች ድጋፍ እና ልዩ ልዩ ገቢዎች ለማግኘት መታቀዱን ተናግረዋል።
በረቂቅ በጀቱ ከጥቅል ሀገራዊ ምርት አንፃር ያልተጣራ የበጀት ጉድለት 2.2 በመቶ እንዲሁም የተጣራ የበጀት ጉድለት 1 በመቶ መሆኑንም የገንዘብ ሚኒስትሩ አስረድተዋል።
መንግስት የበጀት ጉድለቱን በቀጥታ ከብሔራዊ ባንክ ብድር በመውሰድ ሳይሆን በግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭ እንደሚሸፍን ፤ በ2018 በጀት ዓመት የ8.9 በመቶ የኢኮኖሚ እድገት እንደሚጠበቅ መናገራቸው ብሔራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
@tikvahethiopia
ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር እንደሆነ ገንዘብ ሚኒስቴር አሳውቋል።
1 ትሪሊዮን ብር ወይም 73 በመቶውን ከታክስ ገቢ ለማግኘት መታቀዱ ተሰምቷል።
የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት በሰጡት ማብራሪያ ከ2018 ረቂቅ በጀት ፦
➡️ 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣
➡️ 415 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ፣
➡️ 315 ቢሊዮን ብር ለክልል መንግስታት ድጋፍ
➡️ 14 ቢሊዮን ብር ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ የሚውል እንደሆነ ገልጸዋል።
ከረቂቅ በጀቱ ፦
🔴 1 ትሪሊዮን ብር ወይም 73 በመቶውን ከታክስ ገቢ
🔴 236 ቢሊዮን ብር ከልማት አጋሮች ቀሪውን ደግሞ ከፕሮጀክቶች ድጋፍ እና ልዩ ልዩ ገቢዎች ለማግኘት መታቀዱን ተናግረዋል።
በረቂቅ በጀቱ ከጥቅል ሀገራዊ ምርት አንፃር ያልተጣራ የበጀት ጉድለት 2.2 በመቶ እንዲሁም የተጣራ የበጀት ጉድለት 1 በመቶ መሆኑንም የገንዘብ ሚኒስትሩ አስረድተዋል።
መንግስት የበጀት ጉድለቱን በቀጥታ ከብሔራዊ ባንክ ብድር በመውሰድ ሳይሆን በግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭ እንደሚሸፍን ፤ በ2018 በጀት ዓመት የ8.9 በመቶ የኢኮኖሚ እድገት እንደሚጠበቅ መናገራቸው ብሔራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
@tikvahethiopia
😭735❤634😡149🤔49🙏36😱18😢17🕊12💔10
#ኢትዮጵያ
በግብይት ወቅት ከ 10,000 ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም፤ ለከፋዩ በወጪነት፣ ለተቀባዩ ደግሞ አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጣልበት ያደርጋል ተባለ።
አዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ሲጸድቅ ከ10,000 ብር በላይ ግብይትን በጥሬ ገንዘብ መፈጸም የሚያስቀጣ ይሆናል ተብሏል።
ረቂቅ አዋጁ ላይ ሃሳብ ለማዋጣት ከተሳተፉ ባለሙያዎች የተወሰኑት ተግባራዊ ይደረጋል በተባለው አሰራር ላይ ጥያቄ አንስተዋል።
የገንዘብ ሚኒስቴር የህግ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊው አቶ ተወዳጅ መሐመድ እንዳሉት አዋጁ ተግባራዊ የሚደረገው በጥሬ ገንዘብ የሚፈፀም ግብይትን መገደብን ታሳቢ አድርጎ ነው።
በአንድ ግብይት የሚፈፀም የጥሬ ገንዘብ ክፍያ ከ10ሺህ ብር ከበለጠ፣ ትርፉ ብር ለከፋዩ በወጪነት አይያዝም።
ገንዘቡን የተቀበለውም የትርፉን ገንዘብ እጥፍ አስተዳደራዊ ቅጣት እንደሚጣልበት ተቀምጧል።
ለምሳሌ ፦ የ20,000 ብር ግብይት በጥሬ ገንዘብ ቢፈፀም ለነጋዴው፣ ከ10 ሺህ ብር በላይ ያለው በወጪነት አይያዝም፣ ለተቀባዩ ደግሞ ከ10,000 በላይ ያለው ቀሪ 10,000 ብር እጥፍ ማለትም 20,000 ብር ይቀጣል እንደማለት ነው።
በረቂቅ አዋጁ ላይ የተሳተፉ፣ በጥሬ ገንዘብ ግብይት እንዲፈፀም ምክንያት የሚሆነውን በንግድ ስርዓቱ ውስጥ ያለውን ችግር መፍታት የተሻለ አማራጭ ሊሆን እንደሚችልና፣በሌሎች መመሪያዎች የጥሬ ገንዘብ ግብይት ስለሚፈቀድ አዋጁ የተናበበ እንዲሆን ጠይቀዋል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ባሰናዳው ረቂቅ አዋጅ መሰረት ከ10,000 ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ ግብይት እንዳይፈፀም የሚጣለው ግዴታ፣ በመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ በመንግስት የልማት ድርጅቶች፣ በባንኮችና በማይክሮ ፋይናንስ ድርጅቶች ላይ ተፈጻሚ አይሆንም ይላል።
ሌሎች አዋጁ ተፈፃሚ የማይሆንባቸው ግለሰቦችና ድርጅቶች የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ ዝርዝራቸው ይፋ ይሆናል ይላል ረቂቁ።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
በግብይት ወቅት ከ 10,000 ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም፤ ለከፋዩ በወጪነት፣ ለተቀባዩ ደግሞ አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጣልበት ያደርጋል ተባለ።
አዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ሲጸድቅ ከ10,000 ብር በላይ ግብይትን በጥሬ ገንዘብ መፈጸም የሚያስቀጣ ይሆናል ተብሏል።
ረቂቅ አዋጁ ላይ ሃሳብ ለማዋጣት ከተሳተፉ ባለሙያዎች የተወሰኑት ተግባራዊ ይደረጋል በተባለው አሰራር ላይ ጥያቄ አንስተዋል።
የገንዘብ ሚኒስቴር የህግ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊው አቶ ተወዳጅ መሐመድ እንዳሉት አዋጁ ተግባራዊ የሚደረገው በጥሬ ገንዘብ የሚፈፀም ግብይትን መገደብን ታሳቢ አድርጎ ነው።
በአንድ ግብይት የሚፈፀም የጥሬ ገንዘብ ክፍያ ከ10ሺህ ብር ከበለጠ፣ ትርፉ ብር ለከፋዩ በወጪነት አይያዝም።
ገንዘቡን የተቀበለውም የትርፉን ገንዘብ እጥፍ አስተዳደራዊ ቅጣት እንደሚጣልበት ተቀምጧል።
ለምሳሌ ፦ የ20,000 ብር ግብይት በጥሬ ገንዘብ ቢፈፀም ለነጋዴው፣ ከ10 ሺህ ብር በላይ ያለው በወጪነት አይያዝም፣ ለተቀባዩ ደግሞ ከ10,000 በላይ ያለው ቀሪ 10,000 ብር እጥፍ ማለትም 20,000 ብር ይቀጣል እንደማለት ነው።
በረቂቅ አዋጁ ላይ የተሳተፉ፣ በጥሬ ገንዘብ ግብይት እንዲፈፀም ምክንያት የሚሆነውን በንግድ ስርዓቱ ውስጥ ያለውን ችግር መፍታት የተሻለ አማራጭ ሊሆን እንደሚችልና፣በሌሎች መመሪያዎች የጥሬ ገንዘብ ግብይት ስለሚፈቀድ አዋጁ የተናበበ እንዲሆን ጠይቀዋል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ባሰናዳው ረቂቅ አዋጅ መሰረት ከ10,000 ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ ግብይት እንዳይፈፀም የሚጣለው ግዴታ፣ በመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ በመንግስት የልማት ድርጅቶች፣ በባንኮችና በማይክሮ ፋይናንስ ድርጅቶች ላይ ተፈጻሚ አይሆንም ይላል።
ሌሎች አዋጁ ተፈፃሚ የማይሆንባቸው ግለሰቦችና ድርጅቶች የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ ዝርዝራቸው ይፋ ይሆናል ይላል ረቂቁ።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
😡3.05K❤1.33K🤔191😭105👏48💔38😱34🥰31😢26🙏26🕊24
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይነበብ🚨 " በወንጀል የተገኘን ንብረት #ህጋዊ_ማስመሰልና #ሽብርተኝነትን_በገንዘብ_የመርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር " የወጣ ረቂቅ አዋጅ ለሕ/ተ/ም/ቤት ቀርቧል። በዚሁ ረቂቅ ላይ በክፍል 5 ' ስለ ምርመራ ' ሰፍሯል። ረቂቁ ስለ #ምርመራ ምን ይላል ? - በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ ማስመሰል ወይም ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ወይም የወንጀል ፍሬን ተከታትሎ ለመለየት…
#ኢትዮጵያ
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን የሚመረምር ሰው፤ በምርመራ ወቅት ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት ከ #ግድያ ውጪ የትኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢፈጽም ተጠያቂ የማያደርግ አዋጅ ጸደቀ፡፡
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል፡፡
አዋጁ በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራ (Under cover investigation) እንዲያስፈጽም የተመደበ ሰው፤ በግዴታ ላይ እያለ ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያትና ከፈቃዱ ውጪ በሆነ ከግድያ ወንጀል በስተቀር ለሚፈጽመው የወንጀል ድርጊት የወንጀል ክስ አይቀርብበትም ይላል።
የምክር ቤት አባሉ አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) በአዋጁ 5/15 ላይ የቀረበው ዐረፍተ ነገር ትንሽ ከባድ መስሎ እንደታያቸው ተናግረው አዋጁ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡
" እንደዚህ ዓይነት አዋጅ በተለይ ሽብርን ለመከላከል ለሀገራችን ያስፈልጋታል " ሲሉ የምክር ቤት አባሉ ተናግረዋል፡፡
‘’ የሆነው ሆኖ ግን ' አንድ ሰው በግዳጅ ላይ እያለ ከግድያ በስተቀር ለሚፈጽመው ወንጀል አይጠየቅም ' ይላል፡፡ አንደኛ ወንጀል ፈጽሟል ይላል፣ ወንጀል ፈጽሞ አለመጠየቅ ትክክለኛ አይመስለኝም፡፡ ወይም ድርጊቶቹ ተዘርዝረው ህጋዊ መብት የተሰጠው ሰው ሚወስዳቸው እርምጃዎች ወንጀል አይደሉም ብለን ማለፍ እንጂ አንድ ሰው በግዳጅ ላይ እያለ ለሚፈጽመው ወንጀል ከግድያ በስተቀር የሚለውን ሰው እንደፈለገ እንዲሆን የሚያደርግ ነው’ " ሲሉ አለሙ (ዶ/ር) ሃሳበቸውን አስረድተዋል፡፡
ሌላ ሙሉቀን አሰፋ የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " እኔ በግሌ እንደተፎካካሪ የፖለቲካ ሰው አዋጁ ባለሀብቶችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን እና የታዋቂ ሰዎችን መብት የሚገድብ ነው " ብለዋል፡፡
" እንዲያውም የመናገር መብትን ይከለክላል የሚል እምነት ነው እኔ ያለኝ " ያሉት የምክር ቤት አባሉ ‘" ምክንያቱም አዋጁን ስናየው በ10 ዓመት ገድቦ ነው የወጣው’ " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ህግ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ነው ተግባራዊ መደረግ ያለበት’ " ያሉት አቶ ሙሉቀን " ስለዚህ ከ10 ዓመት ወዲህ ብሎ ማውጣቱ የተወሰኑ ግለሰቦችን ወይም ቡድኖችን ለማጥቃት ያሰበ ስለሆነ ለሀገራችንም ጥሩ አይደለም የሚል እምነት አለኝ " ብለዋል፡፡
" በአለም አቀፍ ስምምነቶች ላይ እንደተገለጸው ሀይልን በመጠቀም፣ ንጹሃንን በማስገደድ አላማቸውን ለማስፈጽም የሚሳተፉ ተዋናዮችን ተጠያቂ ለማድረግ ሳይሆን አዋጁ እየዋለ ያለው በዋነኝነት የመንግስት ተቃዋሚዎችን፣ መንግስት ውስጥ ሆነው መንግስትን የሚተቹትን እና ጋዜጠኞችን ነው " ያሉት ደግሞ ሌላው የምክር ቤት አባል የሆኑት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ናቸው፡፡
" የአዋጁን ዝርዝር ካየንው በጣም አስገራሚ የሆኑ ድንጋጌዎችን ይዟል " ያሉት የምክር ቤት አባሉ " ለምሳሌ የፋይናንስ ድህንነት አገልግሎት አጠራጣሪ ግብይትን ለ7 ቀን አግዶ ማቆየት ይችላል ይላል ያውም ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ " ብለዋል፡፡
" አዋጁ በሽፋን ስር ምርመራ የሚያካሄድ መርማሪ ከግድያ ወንጀል ውጭ በሌላ ወንጀል አይጠየቅም ይላል " ያሉት ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) " ለምሳሌ መርማሪው በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ተደራድሮ ከሆነ ከወንጀለኛው ጋር መቀበሉን ብናውቅ አይጠየቅም ማለት ነው? ማሰቃየት ቢፈጽም፣ የመብት ጥሰት ቢፈጽም አይጠየቅም ማለት ነው? መሆን ያለበት ግን ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው አለም አቀፍ ድንጋጌዎች የተካተቱ ወንጀሎችን አለመፈጸሙ ነው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሌላው አቶ ዘካሪያስ የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " አዋጁ አንዳንድ የምክር ቤት አባላት እንደሚሉት ተቃዋሚን እና የሚዲያ ሰዎችን ለማፈን አይደለም " ብለዋል፡፡
አቶ ሳዲቅ አደም የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " አዋጁ ጠንከር ያለ መሆኑን ተናግረው ጠንከር ያለበት ምክንያትም ግልጽ ነው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ያለንበት ቀጠና አስቸጋሪ ነው፤ ሽብርተኝነት የሚበዛበት በመሆኑ የአዋጁ ከበድ ማለት ተገቢ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ከመብት አንፃር ሊታዩ የሚችሉ ነገሮች አሉ ያሉት አቶ ሳዲቅ ከህገ መንግስታችንም ስንነሳ ፍጹም የሚባል መብት የለም " ብለዋል፡፡
" ከመብቶች ሁሉ የላቀ ዋና መብት የሚባለው በህይወት የመኖር መብት ነው ይህ መብትም ፍጹም አይደለም " ሲሉ የተናገሩት የምክር ቤት አባሉ " ስለዚህ መብት የሚባለው ነገር ለህዝብ፣ ለማህበረሰብ እና ለሀገር ድህንነት ሲባል በየትኛውም ሀገር መብቶችን ፍጹማዊ አድርጎ የሚያስቀምጥ የለም " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ስጋት አድርጎ የሚወስድ ወገን ሊኖር ይችላል ግን ለምን ይሰጋል? " ሲሉ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ " ይህ አዋጅ ሲወጣ ለመጠርጠርም መሟላት ያለበት ነገር አለ ማንኛውም ወገን እነዚህ በአዋጁ የተቀመጡ ነገሮችን ካሟላ አይነካም ዋናው መስፈርቱን ማሟላት ነው " ብለዋል፡፡
" አዋጁ የወጣው በንድፍ ሃሳብ የምንፈራቸውን ለመከላከል ሳይሆን በተግባር እያየን እየኖርንበት ያለውን ነው " የሚሉት አቶ ሳደቅ " ሽብርተኝነት በሀገራችን በስፋት አለ ኤ ቤ ሲ ብለን ልንጠራቸው የምንችላቸው ግለሰቦች እና ወገኖች አሉ ስለዚህ ይህን ለመከላከል ለምን እንሰጋለን " ብለዋል፡፡
የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኢሳ ቦሮ በበኩላቸው በሰጡት ምላሽ የሚደረገው ምርመራ ልዩ መሆኑን ተናግረው አዋጁ አንድን ቡድን ለማጥቃት ታስቦ የወጣ አይደለም ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው በማሻሽያ ረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ በሶስት ተቃዉሞ በአንድ ድምጽ ተአቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን የሚመረምር ሰው፤ በምርመራ ወቅት ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት ከ #ግድያ ውጪ የትኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢፈጽም ተጠያቂ የማያደርግ አዋጅ ጸደቀ፡፡
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል፡፡
አዋጁ በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራ (Under cover investigation) እንዲያስፈጽም የተመደበ ሰው፤ በግዴታ ላይ እያለ ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያትና ከፈቃዱ ውጪ በሆነ ከግድያ ወንጀል በስተቀር ለሚፈጽመው የወንጀል ድርጊት የወንጀል ክስ አይቀርብበትም ይላል።
የምክር ቤት አባሉ አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) በአዋጁ 5/15 ላይ የቀረበው ዐረፍተ ነገር ትንሽ ከባድ መስሎ እንደታያቸው ተናግረው አዋጁ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡
" እንደዚህ ዓይነት አዋጅ በተለይ ሽብርን ለመከላከል ለሀገራችን ያስፈልጋታል " ሲሉ የምክር ቤት አባሉ ተናግረዋል፡፡
‘’ የሆነው ሆኖ ግን ' አንድ ሰው በግዳጅ ላይ እያለ ከግድያ በስተቀር ለሚፈጽመው ወንጀል አይጠየቅም ' ይላል፡፡ አንደኛ ወንጀል ፈጽሟል ይላል፣ ወንጀል ፈጽሞ አለመጠየቅ ትክክለኛ አይመስለኝም፡፡ ወይም ድርጊቶቹ ተዘርዝረው ህጋዊ መብት የተሰጠው ሰው ሚወስዳቸው እርምጃዎች ወንጀል አይደሉም ብለን ማለፍ እንጂ አንድ ሰው በግዳጅ ላይ እያለ ለሚፈጽመው ወንጀል ከግድያ በስተቀር የሚለውን ሰው እንደፈለገ እንዲሆን የሚያደርግ ነው’ " ሲሉ አለሙ (ዶ/ር) ሃሳበቸውን አስረድተዋል፡፡
ሌላ ሙሉቀን አሰፋ የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " እኔ በግሌ እንደተፎካካሪ የፖለቲካ ሰው አዋጁ ባለሀብቶችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን እና የታዋቂ ሰዎችን መብት የሚገድብ ነው " ብለዋል፡፡
" እንዲያውም የመናገር መብትን ይከለክላል የሚል እምነት ነው እኔ ያለኝ " ያሉት የምክር ቤት አባሉ ‘" ምክንያቱም አዋጁን ስናየው በ10 ዓመት ገድቦ ነው የወጣው’ " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ህግ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ነው ተግባራዊ መደረግ ያለበት’ " ያሉት አቶ ሙሉቀን " ስለዚህ ከ10 ዓመት ወዲህ ብሎ ማውጣቱ የተወሰኑ ግለሰቦችን ወይም ቡድኖችን ለማጥቃት ያሰበ ስለሆነ ለሀገራችንም ጥሩ አይደለም የሚል እምነት አለኝ " ብለዋል፡፡
" በአለም አቀፍ ስምምነቶች ላይ እንደተገለጸው ሀይልን በመጠቀም፣ ንጹሃንን በማስገደድ አላማቸውን ለማስፈጽም የሚሳተፉ ተዋናዮችን ተጠያቂ ለማድረግ ሳይሆን አዋጁ እየዋለ ያለው በዋነኝነት የመንግስት ተቃዋሚዎችን፣ መንግስት ውስጥ ሆነው መንግስትን የሚተቹትን እና ጋዜጠኞችን ነው " ያሉት ደግሞ ሌላው የምክር ቤት አባል የሆኑት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ናቸው፡፡
" የአዋጁን ዝርዝር ካየንው በጣም አስገራሚ የሆኑ ድንጋጌዎችን ይዟል " ያሉት የምክር ቤት አባሉ " ለምሳሌ የፋይናንስ ድህንነት አገልግሎት አጠራጣሪ ግብይትን ለ7 ቀን አግዶ ማቆየት ይችላል ይላል ያውም ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ " ብለዋል፡፡
" አዋጁ በሽፋን ስር ምርመራ የሚያካሄድ መርማሪ ከግድያ ወንጀል ውጭ በሌላ ወንጀል አይጠየቅም ይላል " ያሉት ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) " ለምሳሌ መርማሪው በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ተደራድሮ ከሆነ ከወንጀለኛው ጋር መቀበሉን ብናውቅ አይጠየቅም ማለት ነው? ማሰቃየት ቢፈጽም፣ የመብት ጥሰት ቢፈጽም አይጠየቅም ማለት ነው? መሆን ያለበት ግን ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው አለም አቀፍ ድንጋጌዎች የተካተቱ ወንጀሎችን አለመፈጸሙ ነው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሌላው አቶ ዘካሪያስ የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " አዋጁ አንዳንድ የምክር ቤት አባላት እንደሚሉት ተቃዋሚን እና የሚዲያ ሰዎችን ለማፈን አይደለም " ብለዋል፡፡
አቶ ሳዲቅ አደም የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " አዋጁ ጠንከር ያለ መሆኑን ተናግረው ጠንከር ያለበት ምክንያትም ግልጽ ነው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ያለንበት ቀጠና አስቸጋሪ ነው፤ ሽብርተኝነት የሚበዛበት በመሆኑ የአዋጁ ከበድ ማለት ተገቢ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ከመብት አንፃር ሊታዩ የሚችሉ ነገሮች አሉ ያሉት አቶ ሳዲቅ ከህገ መንግስታችንም ስንነሳ ፍጹም የሚባል መብት የለም " ብለዋል፡፡
" ከመብቶች ሁሉ የላቀ ዋና መብት የሚባለው በህይወት የመኖር መብት ነው ይህ መብትም ፍጹም አይደለም " ሲሉ የተናገሩት የምክር ቤት አባሉ " ስለዚህ መብት የሚባለው ነገር ለህዝብ፣ ለማህበረሰብ እና ለሀገር ድህንነት ሲባል በየትኛውም ሀገር መብቶችን ፍጹማዊ አድርጎ የሚያስቀምጥ የለም " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ስጋት አድርጎ የሚወስድ ወገን ሊኖር ይችላል ግን ለምን ይሰጋል? " ሲሉ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ " ይህ አዋጅ ሲወጣ ለመጠርጠርም መሟላት ያለበት ነገር አለ ማንኛውም ወገን እነዚህ በአዋጁ የተቀመጡ ነገሮችን ካሟላ አይነካም ዋናው መስፈርቱን ማሟላት ነው " ብለዋል፡፡
" አዋጁ የወጣው በንድፍ ሃሳብ የምንፈራቸውን ለመከላከል ሳይሆን በተግባር እያየን እየኖርንበት ያለውን ነው " የሚሉት አቶ ሳደቅ " ሽብርተኝነት በሀገራችን በስፋት አለ ኤ ቤ ሲ ብለን ልንጠራቸው የምንችላቸው ግለሰቦች እና ወገኖች አሉ ስለዚህ ይህን ለመከላከል ለምን እንሰጋለን " ብለዋል፡፡
የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኢሳ ቦሮ በበኩላቸው በሰጡት ምላሽ የሚደረገው ምርመራ ልዩ መሆኑን ተናግረው አዋጁ አንድን ቡድን ለማጥቃት ታስቦ የወጣ አይደለም ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው በማሻሽያ ረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ በሶስት ተቃዉሞ በአንድ ድምጽ ተአቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
❤1.04K😭959😡363🤔66😱28💔28😢20🕊16🙏14🥰5👏4
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ የገቢ ግብር ምጣኔ ላይ ማሻሻያ ለማድረግ መንግስት ረቂቅ አዋጅ ማዘጋጀቱን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል። ሬድዮ ጣቢያው ከገንዘብ ሚኒስቴር አገኘሁት ባለው መረጃ በደመወዝተኛው ሆነ በንግድ የገቢ ግብር ምጣኔ ላይ ማሻሻያዎችን የያዘ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል። በመጭው ሰኞም በረቂቅ አዋጁ ላይ ከባለሙያዎች ጋር ለመመካከር ጥሪ ማድረጉ ተሰምቷል። የኢትዮጵያ ሰራተኞች ኮንፌዴሬሽንና…
#ኢትዮጵያ
የሠራተኞች መነሻ የደመወዝ ወለል 8,384 ብር እንዲሆን ተጠይቋል።
ወርኃዊ ደመወዛቸው እስከ 8,384 ብር የሆነ ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን ገለጸ፡፡
የኢሠማኮ ፕሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፥ " ወርኃዊ ደመወዛቸው እስከ 8,384 ብር የሆነ ተቀጣሪ ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲደረጉ ለመንግሥት ጥያቄ አቅርበናል " ብለዋክ።
የገንዘብ ሚኒስቴር ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት በሥራ ላይ ቆይቷል የተባለውን የገቢ ግብር አዋጅ 979/2008ን ለማሻሻል ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ከተባሉ ባለድርሻዎች ጋር ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ እስከ ሁለት ሺሕ ብር የሚከፈለቸው ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ ተደንግጓል፡፡
ኢሠማኮ እስከ 8,384 ብር ድረስ የሚከፈለቸው ተቀጣሪዎች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ ለገንዘብ ሚኒስቴር በደብዳቤ እንደጠየቀ አስታውቋል፡፡
አቶ ካሳሁን በዓለም ባንክ መረጃ መሠረት ዕለታዊ ገቢው ከሦስት ዶላር በታች የሆነ ሰው ደሃ በመሆኑ፣ የመንግሥት የገቢ ግብር በዚህ ወለል ሥር ያሉ ተቀጣሪዎችን ታሳቢ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል፡፡
በማናቸውም ቀጣሪ ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞች በወር ከ8,384 ብር እስከ 22,974 ብር ደመወዝ የሚያገኙ ሠራተኞች፣ አሥር በመቶ ግብር እንዲጣልባቸው መንግሥትን መጠየቁን ኢሠማኮ ገልጿል፡፡
ከ22,975 እስከ 44,530 ብር ወርኃዊ ደመወዝ ተከፋዮች የ15 በመቶ፣ ከ44,531 እስከ 72,336 ብር የሚከፈለቸው ደግሞ 20 በመቶ፣ እንዲሁም ከ72,337 እስከ 107,449 ብር የ25 በመቶ ግብር እንዲጣልባቸው ኢሠማኮ በደብዳቤው አሳስቧል።
ከ107,450 እስከ 150,107 ብር ድረስ የሚከፈለቸው ሠራተኞች 30 በመቶ ግብር፣ እንዲሁም 150,108 ብር እና ከዚያ በላይ የሚከፈለቸው ተቀጣሪ ሠራተኞች ደግሞ 35 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ ለመንግሥት ባቀረበው ደብዳቤ ኢሠማኮ መጠየቁን ገልጿል።
አሁን በሥራ ላይ ባለው የሠራተኞች የገቢ ግብ አዋጅ መሠረት እስከ 600 ብር ድረስ የሚከፈላቸው ሠራተኞች ከግብር ነፃ ሲሆኑ፣ ከ10,900 ብር ጀምሮ ደግሞ 35 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ ይገደዳሉ፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር ከአንድ ሳምንት በፊት ለውይይት ይፋ ባደረገው የገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ 1,200 ብር፣ 1,600 ብር እና 2,000 ብር ወርኃዊ ደመወዝተኞች ከግብር ነፃ እንዲደረጉ ድንጋጌ መኖሩ ይታወሳል።
የመንግሥት የገቢ ግብር ማሻሻያው ሠራተኞች ያለባቸውን ወቅታዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ታሳቢ ያላደረገ እንደሆነ የተለያዩ የውይይት ተሳታፊዎች አስተያየት መስጠታቸው አይዘነጋም፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
#ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopia
የሠራተኞች መነሻ የደመወዝ ወለል 8,384 ብር እንዲሆን ተጠይቋል።
ወርኃዊ ደመወዛቸው እስከ 8,384 ብር የሆነ ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን ገለጸ፡፡
የኢሠማኮ ፕሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፥ " ወርኃዊ ደመወዛቸው እስከ 8,384 ብር የሆነ ተቀጣሪ ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲደረጉ ለመንግሥት ጥያቄ አቅርበናል " ብለዋክ።
የገንዘብ ሚኒስቴር ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት በሥራ ላይ ቆይቷል የተባለውን የገቢ ግብር አዋጅ 979/2008ን ለማሻሻል ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ከተባሉ ባለድርሻዎች ጋር ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ እስከ ሁለት ሺሕ ብር የሚከፈለቸው ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ ተደንግጓል፡፡
ኢሠማኮ እስከ 8,384 ብር ድረስ የሚከፈለቸው ተቀጣሪዎች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ ለገንዘብ ሚኒስቴር በደብዳቤ እንደጠየቀ አስታውቋል፡፡
አቶ ካሳሁን በዓለም ባንክ መረጃ መሠረት ዕለታዊ ገቢው ከሦስት ዶላር በታች የሆነ ሰው ደሃ በመሆኑ፣ የመንግሥት የገቢ ግብር በዚህ ወለል ሥር ያሉ ተቀጣሪዎችን ታሳቢ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል፡፡
በማናቸውም ቀጣሪ ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞች በወር ከ8,384 ብር እስከ 22,974 ብር ደመወዝ የሚያገኙ ሠራተኞች፣ አሥር በመቶ ግብር እንዲጣልባቸው መንግሥትን መጠየቁን ኢሠማኮ ገልጿል፡፡
ከ22,975 እስከ 44,530 ብር ወርኃዊ ደመወዝ ተከፋዮች የ15 በመቶ፣ ከ44,531 እስከ 72,336 ብር የሚከፈለቸው ደግሞ 20 በመቶ፣ እንዲሁም ከ72,337 እስከ 107,449 ብር የ25 በመቶ ግብር እንዲጣልባቸው ኢሠማኮ በደብዳቤው አሳስቧል።
ከ107,450 እስከ 150,107 ብር ድረስ የሚከፈለቸው ሠራተኞች 30 በመቶ ግብር፣ እንዲሁም 150,108 ብር እና ከዚያ በላይ የሚከፈለቸው ተቀጣሪ ሠራተኞች ደግሞ 35 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ ለመንግሥት ባቀረበው ደብዳቤ ኢሠማኮ መጠየቁን ገልጿል።
አሁን በሥራ ላይ ባለው የሠራተኞች የገቢ ግብ አዋጅ መሠረት እስከ 600 ብር ድረስ የሚከፈላቸው ሠራተኞች ከግብር ነፃ ሲሆኑ፣ ከ10,900 ብር ጀምሮ ደግሞ 35 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ ይገደዳሉ፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር ከአንድ ሳምንት በፊት ለውይይት ይፋ ባደረገው የገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ 1,200 ብር፣ 1,600 ብር እና 2,000 ብር ወርኃዊ ደመወዝተኞች ከግብር ነፃ እንዲደረጉ ድንጋጌ መኖሩ ይታወሳል።
የመንግሥት የገቢ ግብር ማሻሻያው ሠራተኞች ያለባቸውን ወቅታዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ታሳቢ ያላደረገ እንደሆነ የተለያዩ የውይይት ተሳታፊዎች አስተያየት መስጠታቸው አይዘነጋም፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
#ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopia
❤3.78K👏674🙏169😭76😡47🕊45🥰36🤔36😱22😢11💔9
#ኢትዮጵያ🇪🇹
ኢትዮጵያ የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት የአባልነት ማረጋገጫ ተቀበለች።
ኢትዮጵያ 105 አገራትን ባቀፈው የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት (PKD) አባል መሆኗን የሚያረጋግጥ ሰርተፍኬት ከተቋሙ ዋና መቀመጫ ከሆነችው ካናዳ ሞንትሪያል ከሚገኘዉ አለም አቀፉ የሲቪል አቬሽን ተቋም ተቀብላለች።
ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ አባል መሆኗ የኢትዮጵያን ፓስፖርት የያዙ ዜጎች በአባል አገራቱ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ያለምንም እንግልት እንዲጓጓዙ የሚያስችል ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ በየብስም ሆነ በአየር በተጭበረበረ የጉዞ ሰነድ ለመምጣት የሚሞክሩ አካላትን በቀላሉ ለመለየት የሚረዳና በአገር ላይ ሊቃጣ የሚችል የደህንነት ስጋትን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያግዝ ነው።
ኢትዮጵያ ወደዚህ ማዕቀፍ በይፋ መቀላቀሏን ተከትሎ የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት አባል አገራት ተወካዮችና የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች አካላት በተገኙበት አገሪቱ ያላትን ሁለንተናዊ አቅም የሚያስተዋውቅ መድረክ ተዘጋጅቷል።
በዚህ ወቅትም የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ገፅታ፣ የኢሚግሬሽን ስርዓትና አሁናዊ ሁኔታ እንዲሁም የኢትዮጵያን የቱሪዝምና የቢዝነስ አቅሞች የሚያስተዋውቁ ገለፃዎች ተደርገዋል።
በስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት " ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ (PKD) አባል መሆኗ ዜጎች በሚሄዱበት አገር ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ከማድረጉ ባሻገር የአገርን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ አይነተኛ ሚና የሚጫወት ይጫወታል " ብለዋል።
" ኢትዮጵያ ጠንካራ በሆነው የአለም አቀፍ አቪዬሽን ትብብር ስርዓት ውስጥ የላቀ ቴክኖሎጂን መጠቀሟ ድንበሯን ከመጠበቅ ባለፈ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ የጋራ ደኅንነት መጠበቅ ያላትን ቁርጠኝነትም የሚያሳይ ውሳኔ ነው " ሱሉ ጠቁመዋል።
የካናዳ ትራንስፖርት ሚኒስትር ምክትል ሚኒስትር ኒኮላስ ሮብሰን " ኢትዮጵያ ወደዚህ ስርዓት በይፋ መቀላቀሏ በአቪዬሽን መስክ የምትሰራውን ስራ በዓለም የታመነ እንዲሆን ያደርጋል " ብለዋል።
" በተለይም በርካታ ዜጎችን ወደ ተለያዩ ክፍለ-ዓለማት የሚያጓጉዝ የግዙፍ አየር መንገድ ባለቤት በመሆኗ ይህን ማዕቀፍ መቀላቀሏ የሚደነቅ ውሳኔ ነው " ሲሉ ጠቁመዋል።
የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ፕሬዝዳንት ሳልቫቶሬ ሻኪታኖ ኢትዮጵያ ወደ ማዕቀፉ በመግባት የተሰማቸውን ደስታ በመግለፅ ተቋማቸው የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
መረጃው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት የአባልነት ማረጋገጫ ተቀበለች።
ኢትዮጵያ 105 አገራትን ባቀፈው የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት (PKD) አባል መሆኗን የሚያረጋግጥ ሰርተፍኬት ከተቋሙ ዋና መቀመጫ ከሆነችው ካናዳ ሞንትሪያል ከሚገኘዉ አለም አቀፉ የሲቪል አቬሽን ተቋም ተቀብላለች።
ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ አባል መሆኗ የኢትዮጵያን ፓስፖርት የያዙ ዜጎች በአባል አገራቱ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ያለምንም እንግልት እንዲጓጓዙ የሚያስችል ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ በየብስም ሆነ በአየር በተጭበረበረ የጉዞ ሰነድ ለመምጣት የሚሞክሩ አካላትን በቀላሉ ለመለየት የሚረዳና በአገር ላይ ሊቃጣ የሚችል የደህንነት ስጋትን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያግዝ ነው።
ኢትዮጵያ ወደዚህ ማዕቀፍ በይፋ መቀላቀሏን ተከትሎ የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት አባል አገራት ተወካዮችና የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች አካላት በተገኙበት አገሪቱ ያላትን ሁለንተናዊ አቅም የሚያስተዋውቅ መድረክ ተዘጋጅቷል።
በዚህ ወቅትም የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ገፅታ፣ የኢሚግሬሽን ስርዓትና አሁናዊ ሁኔታ እንዲሁም የኢትዮጵያን የቱሪዝምና የቢዝነስ አቅሞች የሚያስተዋውቁ ገለፃዎች ተደርገዋል።
በስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት " ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ (PKD) አባል መሆኗ ዜጎች በሚሄዱበት አገር ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ከማድረጉ ባሻገር የአገርን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ አይነተኛ ሚና የሚጫወት ይጫወታል " ብለዋል።
" ኢትዮጵያ ጠንካራ በሆነው የአለም አቀፍ አቪዬሽን ትብብር ስርዓት ውስጥ የላቀ ቴክኖሎጂን መጠቀሟ ድንበሯን ከመጠበቅ ባለፈ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ የጋራ ደኅንነት መጠበቅ ያላትን ቁርጠኝነትም የሚያሳይ ውሳኔ ነው " ሱሉ ጠቁመዋል።
የካናዳ ትራንስፖርት ሚኒስትር ምክትል ሚኒስትር ኒኮላስ ሮብሰን " ኢትዮጵያ ወደዚህ ስርዓት በይፋ መቀላቀሏ በአቪዬሽን መስክ የምትሰራውን ስራ በዓለም የታመነ እንዲሆን ያደርጋል " ብለዋል።
" በተለይም በርካታ ዜጎችን ወደ ተለያዩ ክፍለ-ዓለማት የሚያጓጉዝ የግዙፍ አየር መንገድ ባለቤት በመሆኗ ይህን ማዕቀፍ መቀላቀሏ የሚደነቅ ውሳኔ ነው " ሲሉ ጠቁመዋል።
የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ፕሬዝዳንት ሳልቫቶሬ ሻኪታኖ ኢትዮጵያ ወደ ማዕቀፉ በመግባት የተሰማቸውን ደስታ በመግለፅ ተቋማቸው የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
መረጃው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤484😡43👏23🕊13😢8🙏7🤔5
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoPR🇪🇹 " በዝቋላ አቦና በተለያዩ ገዳማት ምንም መሳሪያ ያልታጠቁ መናኞች እና የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ከሞት እና ከድብደባ ለመታደግ አግባብ ያለው የጸጥታ ሃይል የማይመድበው ለምንድነው ? " - የምክር ቤት አባሉ አበባው ደሳለው (ዶ/ር) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉና አማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባሉ አበባው ደሳለው (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ን ምን ጠየቁ…
#ኢትዮጵያ🇪🇹
" የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል፤ ከ40 ወራት በኋላም ተጠናቅቆ ስራ ይጀምራል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
" ኢትዮጵያ ከፍተኛ የማዕድን አቅም ያላት ሀገር ናት፤ በአፍሪካ ውስጥ ትላልቅ የማዕድን አቅም ካላቸው ሀገራት አንዷ ናት ፤ እስካሁን የትክረት የአመራር፣ የዕይታ ማነስ ስለነበረ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ማገዝ ይችል ነበር። አሁን እያነቃቃነው ነው።
ወርቅ ባለፈው ዓመት በዚህ ዓመት 37 ቶን ወርቅ ኤክስፖርት አድርገነዋል። 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ኤክስፖርት ዓመት ያገኘነውም ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተን ስለሰራን ነው። ይህ በየትኛውም ዘመን ያልነበረ ስኬተ ነው። ሌላው ጋዝ ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በጋዝ ላይ የሚሰማሩ ኩባንያወች ፈቃድ አውጥተው ወደ ተጨባጭ ስራ አይገቡም ነበር።
ኢትዮጵያ የጋዝ ምርት በቅርቡ ለገበያ ማቅረብ ትጀምራለች። በዚህም ሰርቶ አዳሪ እንጂ አውርቶ አዳሪ አለመሆናችንንም በተከታታይ እያሳየን እንቀጥላለን። የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል፤ ከ40 ወራት በኋላም ተጠናቅቆ ስራ ይጀምራል። "
Credit : PMO Ethiopia
@tikvahethiopia
" የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል፤ ከ40 ወራት በኋላም ተጠናቅቆ ስራ ይጀምራል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
" ኢትዮጵያ ከፍተኛ የማዕድን አቅም ያላት ሀገር ናት፤ በአፍሪካ ውስጥ ትላልቅ የማዕድን አቅም ካላቸው ሀገራት አንዷ ናት ፤ እስካሁን የትክረት የአመራር፣ የዕይታ ማነስ ስለነበረ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ማገዝ ይችል ነበር። አሁን እያነቃቃነው ነው።
ወርቅ ባለፈው ዓመት በዚህ ዓመት 37 ቶን ወርቅ ኤክስፖርት አድርገነዋል። 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ኤክስፖርት ዓመት ያገኘነውም ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተን ስለሰራን ነው። ይህ በየትኛውም ዘመን ያልነበረ ስኬተ ነው። ሌላው ጋዝ ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በጋዝ ላይ የሚሰማሩ ኩባንያወች ፈቃድ አውጥተው ወደ ተጨባጭ ስራ አይገቡም ነበር።
ኢትዮጵያ የጋዝ ምርት በቅርቡ ለገበያ ማቅረብ ትጀምራለች። በዚህም ሰርቶ አዳሪ እንጂ አውርቶ አዳሪ አለመሆናችንንም በተከታታይ እያሳየን እንቀጥላለን። የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል፤ ከ40 ወራት በኋላም ተጠናቅቆ ስራ ይጀምራል። "
Credit : PMO Ethiopia
@tikvahethiopia
😡917❤717😭54👏33🤔31🙏15🕊14😱13💔10🥰8😢5
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia🇪🇹 " አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም ! " - የምክር ቤት አባል በገቢ ግብር ማሻሽያ አዋጅ ላይ ዝቅተኛ የግብር ከፋይ መነሻ ደመወዝ 5,000 ብር እንዲሆን በምክር ቤት ተጠየቀ፡፡ ይህ ጥያቄ የተጠየቀው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዛሬ ከሰዓት በጠራው ልዩ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡ አሁን በስራ ላይ…
#ኢትዮጵያ🇪🇹
የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ፣ የኑሮ ውድነትን ታሳቢ በማድረግ የገቢ ግብር መነሻ ገቢ ከ2,000 ብር ወደ 5,000 ብር ከፍ እንዲል ጠንካራ ጥያቄ ቀርቧል።
ጥያቄው የቀረበው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ በፓርላማው የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ባደረገዉ ዉይይት ላይ ነው።
በአሁኑ ረቂቅ አዋጅ መሰረት፣ ከ2,000 ብር በላይ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር እንዲከፈል የሚለው ሀሳብ ቀርቧል።
ይህ የገቢ ግብር አዋጅ ከዘጠኝ ዓመታት በላይ ስራ ላይ መዋሉ የተገለጸ ሲሆን፣ አሁን በማሻሻያው ከግብር ነፃ የሚሆነው ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ በ300% በማሳደግ ወደ 2,000 ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል።
በተጨማሪም፣ ከፍተኛው የማስከፈያ መጣኔ የሆነው 35% ግብር የሚያርፍበት ገቢ ደግሞ ወደ 14,000 ብር ከፍ እንዲል ሆኗል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ፣ የአዋጁ መሻሻል መንግስት ግብር በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እንደሚረዳ ገልጸዋል።
ከግብር ከፋዩ ህብረተሰብ የሚነሱ " ግብር በዝቷል ይቀነስ " የሚሉ ሀሳቦች ሚዛናዊ በሆነ መልኩ እንደሚታዩም አክለዋል።
በውይይት መድረኩ ከተነሱት አስተያየቶች መካከል፣፦
- የገቢ ግብር መነሻው ከአምስት ሺህ ብር ጀምሮ እንዲሆን፣
- ለአካል ጉዳተኞች በተለየ መልኩ ግብር እንዲቀነስ፣
- በተለያዩ የሙያና የንግድ ዘርፎች አንፃር በደንብ እንዲታይ የሚሉ ሀሳቦች ቀርበዋል።
የመረጃው ባለቤት የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ፣ የኑሮ ውድነትን ታሳቢ በማድረግ የገቢ ግብር መነሻ ገቢ ከ2,000 ብር ወደ 5,000 ብር ከፍ እንዲል ጠንካራ ጥያቄ ቀርቧል።
ጥያቄው የቀረበው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ በፓርላማው የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ባደረገዉ ዉይይት ላይ ነው።
በአሁኑ ረቂቅ አዋጅ መሰረት፣ ከ2,000 ብር በላይ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር እንዲከፈል የሚለው ሀሳብ ቀርቧል።
ይህ የገቢ ግብር አዋጅ ከዘጠኝ ዓመታት በላይ ስራ ላይ መዋሉ የተገለጸ ሲሆን፣ አሁን በማሻሻያው ከግብር ነፃ የሚሆነው ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ በ300% በማሳደግ ወደ 2,000 ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል።
በተጨማሪም፣ ከፍተኛው የማስከፈያ መጣኔ የሆነው 35% ግብር የሚያርፍበት ገቢ ደግሞ ወደ 14,000 ብር ከፍ እንዲል ሆኗል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ፣ የአዋጁ መሻሻል መንግስት ግብር በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እንደሚረዳ ገልጸዋል።
ከግብር ከፋዩ ህብረተሰብ የሚነሱ " ግብር በዝቷል ይቀነስ " የሚሉ ሀሳቦች ሚዛናዊ በሆነ መልኩ እንደሚታዩም አክለዋል።
በውይይት መድረኩ ከተነሱት አስተያየቶች መካከል፣፦
- የገቢ ግብር መነሻው ከአምስት ሺህ ብር ጀምሮ እንዲሆን፣
- ለአካል ጉዳተኞች በተለየ መልኩ ግብር እንዲቀነስ፣
- በተለያዩ የሙያና የንግድ ዘርፎች አንፃር በደንብ እንዲታይ የሚሉ ሀሳቦች ቀርበዋል።
የመረጃው ባለቤት የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤981👏119😭84😡80🕊32🙏24😢11🤔10🥰4😱1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ዛሬ ወሬ የለም " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የሃይማኖት አባቶች ልዑክ በመቐለ ! ከአዲስ አበባ ተነስቶ በጥዋቱ ትግራይ ክልል መቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ የደረሰው የሃይማኖት አባቶች ልዑክ ከሁሉም የሃይማኖት ተቋማት የተወጣጣ ሲሆን አጠቃላይ ልዑኩ ከ20 በላይ አባላት አሉት። የሰላም ልኡኩ ከአውሮፕላን ማረፍያ በቀጥታ ወደ መቐለ ፕላኔት ሆቴል አዳራሽ በማመራት በፕሬዜዳንት…
#ኢትዮጵያ🇪🇹
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ፥ " በአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች የሚደረግ ምክክርና እርቀ ሰላም ፍሬው ጣፋጭ ነው " አሉ።
ትናንት ሀምሌ 10/2017 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ያቀኑት የትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ዛሬ ሀምሌ 11/2017 ዓ.ም ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) መክረዋል።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ከትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ስለተካሄደው የሰላም ውይይት አስመልከተው በማህበራዊ የትስስር ገፃቸው በትግርኛ ባጋሩት መረጃ " የኢፌዲሪ መንግስት በሽምግልና እና ምክክር ችግሮች እንዲፈቱ ቅድምያ ሰጥቶ እንደሚሰራ በተለያዩ ጊዚያት በተግባር አሳይቷል " ብለዋል።
" በረጅሙ የአገሪቱ የአገረ መንግስት ስርዓት አገራዊ እርቅ ፣ አገራዊ ምክክር ፣ ፓለቲካዊ ውይይት የሚሉ ማህበራዊ አምዶች በኢትዮጵያ ፓለቲካ ውይይት በይፋ እንዲተገበሩ ያደረገው የአሁኑ መንግስት መሆኑ መካድ የለበትም " ብለዋል።
" ግጭት ሌላ ግጭት እየወለደ በችግር አዙሪት ከመኖር ያለፈ ሌላ ፋይዳ የለውም " ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ " በውይይትና መግባባት ችግሮቻችን በመፍታት ሰላምን በፅኑ መሰረት እናኑር " ብለዋል።
" ከተለያዩ የትግራይ የማህበረሰብ ክፍሎች ከተውጣጡ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አካላት ለቀጣይ መደረክ ምቹ መደላድል የሚፈጥር ውይይት አካሂደናል " ሲሉ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተካሄደው ጥልቅ ውይይት በጥያቄና መልስ የታጀቡ በርካታ ጉዳዮች እንደተነሱ ገልጸዋል።
በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አተገባበር ያሉት ተግዳሮቶች እንዴት መታረም አለባቸው ፣ ግጭት ቀስቃሽ የሆኑ ንግግሮች መቆምና መታረም እንዳለባቸው በተለይ የተፈናቃዮችና ትግራይን መልሶ መገንባት ጉዳይ የምክክሩ ዋነኛ ነጥቦች ነበሩ ብለዋል።
የትግራይ ህዝብና ልሂቃን በአገሪቱ ፓለቲካና ኢኮኖሚ በብርቱ ተዋናይ የሚሆኑበት ሁኔታ መፍጠር እጅግ አስፈላጊ እንደሆነና ሌሎች ጉዳዮች ተነስው መግባባት ተደርሶባቸዋል ብለዋል።
" የፌደራል መንግስት ከህዝብ ፣ ከጊዚያዊ አስተዳደሩና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በፓለቲካ በፀጥታና ኢኮኖሚ እንዲሁም በትግራይ መልሶ ግንባታ ዙሪያ ተቀራርበን እንደምንሰራ ደገመን እረጋግጠንላችኋለን " ብለዋል።
የትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ትናንት ሀምሌ 10/2017 ዓ.ም በመቐለ ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ከተወያዩ በኋላ ወደ አዲስ አበባ በማቅናት ነው ዛሬ ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር ) ጋር ውይይት ያደረጉት ሲል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyAA
ፎቶ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ፥ " በአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች የሚደረግ ምክክርና እርቀ ሰላም ፍሬው ጣፋጭ ነው " አሉ።
ትናንት ሀምሌ 10/2017 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ያቀኑት የትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ዛሬ ሀምሌ 11/2017 ዓ.ም ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) መክረዋል።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ከትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ስለተካሄደው የሰላም ውይይት አስመልከተው በማህበራዊ የትስስር ገፃቸው በትግርኛ ባጋሩት መረጃ " የኢፌዲሪ መንግስት በሽምግልና እና ምክክር ችግሮች እንዲፈቱ ቅድምያ ሰጥቶ እንደሚሰራ በተለያዩ ጊዚያት በተግባር አሳይቷል " ብለዋል።
" በረጅሙ የአገሪቱ የአገረ መንግስት ስርዓት አገራዊ እርቅ ፣ አገራዊ ምክክር ፣ ፓለቲካዊ ውይይት የሚሉ ማህበራዊ አምዶች በኢትዮጵያ ፓለቲካ ውይይት በይፋ እንዲተገበሩ ያደረገው የአሁኑ መንግስት መሆኑ መካድ የለበትም " ብለዋል።
" ግጭት ሌላ ግጭት እየወለደ በችግር አዙሪት ከመኖር ያለፈ ሌላ ፋይዳ የለውም " ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ " በውይይትና መግባባት ችግሮቻችን በመፍታት ሰላምን በፅኑ መሰረት እናኑር " ብለዋል።
" ከተለያዩ የትግራይ የማህበረሰብ ክፍሎች ከተውጣጡ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አካላት ለቀጣይ መደረክ ምቹ መደላድል የሚፈጥር ውይይት አካሂደናል " ሲሉ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተካሄደው ጥልቅ ውይይት በጥያቄና መልስ የታጀቡ በርካታ ጉዳዮች እንደተነሱ ገልጸዋል።
በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አተገባበር ያሉት ተግዳሮቶች እንዴት መታረም አለባቸው ፣ ግጭት ቀስቃሽ የሆኑ ንግግሮች መቆምና መታረም እንዳለባቸው በተለይ የተፈናቃዮችና ትግራይን መልሶ መገንባት ጉዳይ የምክክሩ ዋነኛ ነጥቦች ነበሩ ብለዋል።
የትግራይ ህዝብና ልሂቃን በአገሪቱ ፓለቲካና ኢኮኖሚ በብርቱ ተዋናይ የሚሆኑበት ሁኔታ መፍጠር እጅግ አስፈላጊ እንደሆነና ሌሎች ጉዳዮች ተነስው መግባባት ተደርሶባቸዋል ብለዋል።
" የፌደራል መንግስት ከህዝብ ፣ ከጊዚያዊ አስተዳደሩና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በፓለቲካ በፀጥታና ኢኮኖሚ እንዲሁም በትግራይ መልሶ ግንባታ ዙሪያ ተቀራርበን እንደምንሰራ ደገመን እረጋግጠንላችኋለን " ብለዋል።
የትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ትናንት ሀምሌ 10/2017 ዓ.ም በመቐለ ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ከተወያዩ በኋላ ወደ አዲስ አበባ በማቅናት ነው ዛሬ ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር ) ጋር ውይይት ያደረጉት ሲል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyAA
ፎቶ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤931😡320🕊101🤔32🙏30😭17🥰10💔7😢4😱3
TIKVAH-ETHIOPIA
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ምንድነው ያሉት ? 🔴 ፕሬዝዳንቱ አብዛኛው ንግግራቸው ስለ ሀገራቸው ኤርትራ የውስጥ ጉዳይ ሳይሆን ስለ ኢትዮጵያ እና ሌሎች ሀገራት ጉዳይ ነበር ! ኤርትራ ትላንት ቅዳሜ 34ኛ ዓመት የነፃነት በዓሏን አክብራለች። ለ34 ዓመታት አገሪቷን በብቸኝነት እያስተዳደሩ ያሉት ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለ34ኛ ጊዜ ንግግር አድርገዋል። ፕሬዜዳንቱ 20 ደቂቃ ርዝማኔ ባለው ንግግራቸው…
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ስለ #ኢትዮጵያ 🇪🇹 ምን እያሉ ነው ?
ከሀገራቸው ጉዳይ ይልቅ ስለ ሰው ሀገር ጉዳዮች ሰፊ ጊዜ ወስደው በመናገርና በመተንተን የሚታወቁት የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ትላንት ምሽት በሀገራቸው ብቸኛው ቴሌቪዥን በተላለፈ ቃለ መጠይቅ #የኢትዮጵያን ስም ደጋግመው ሲያነሱ ታይተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ከወራት በፊት በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ከሀገራቸው ጉዳይ ይልቅ ስለ ኢትዮጵያ እና ቀጠናው ጉዳይ ትንታኔ ሲሰጡ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም። በወቅቱም ኢትዮጵያ ስሟን እያነሱ ለተናገሩት ነገር ሁሉ በቀጥታ አንዳችም ምላሽ ሳትሰጣቸው በዝምታ አልፋቸዋለች።
ትላንት በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ደግሞ ንዴትን በቀላቀለ ሁኔታ በማይመጥኑ ቃላት የኢትዮጵያን ስም ሲያነሱ ነበር።
በተለይም ኢትዮጵያ ያነሳችውን የባህር በር ጥያቄ ሲያጣጥሉት ነው ያመሹት።
የኢትዮጵያን የወደብ እና የባህር በር ጥያቄ " የህጻን ጨዋታ ነው፣ ማሳሳቻ ነው፣ የረከሰ ውሸት ነው ፣ የውስጥ ጉዳይ ማዳፈኛ ነው ፣ ጀርባው የተባበሩት አረብ ኤሜራት የወደብ ማስፋፋት አጀንዳ ነው " የሚሉ ቃላቶችን በመጠቀም ኢትዮጵያን ለማጣጣል ሞክረዋል።
ኢትዮጵያ የባህር በርን ጉዳይ አለም አቀፍ አጀንዳ ማድረጓን ተከትሎ በርካታ ሀገራት ለጥያቄዋ ድጋፍ ማድረጋቸውም ፕሬዝዳንቱን እንዳላስደሰተ የሚጠቁም ንግግርም ሲናገሩ ነበር።
" ፈረንሳይ ከኛ ጋር ናት፣ አሜሪካ ፣ ኤማራት፣ አውሮፓ ህብረት ከኛ ጎን ናቸው ማለት ጭንቅ እንጂ የድል መንገድ አይደለም " በማለት " ኢትዮጵያውያን የውስጥ ችግራችሁን ፍቱ " ሲሉ ተደምጠዋል።
በኢትዮጵያ በኩል ሀገራቸው ላይ የጦርነት ስጋትና ዛቻ እንዳለ በማመላከትም " እራሳችንን እንጠብቃለን " ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለባሕር ስትል ኤርትራንም ሆነ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር የመውጋት አንዳችም ፍላጎት እንደሌላት በተደጋጋሚ ማሳወቋ ይታወሳል። ነገር ግን የባህር በር ጉዳይ ህልውናዋ መሆኑን ለዓለም ህዝብ አስረግጣ ተናግራለች።
ሌላው ፕሬዜዳንቱ ኢትዮጵያ ተመድ ሄዳ ከሳናለች (ክሱ ፦ ድንበር አካባቢ አሁንም የኤርትራ ጦር ግፍ እየፈጸመ ስለመሆኑ) " ያሉም ሲሆን " ክሱ አስነዋሪና አሳፋሪ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
ስለ ፕሪቶሪያ ስምምነትም ሲያነሱ ነበር።
ገና የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሲፈረም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት እንዳሻከረች በይፋ የሚታወቅ ቢሆንም " ኤርትራን ከመክሰሳችሁ በፊት የፕሪቶሪያን ውል ተግብሩ ፤ የውስጥ ችግራችሁን መፍታት አስቀድሙ ፤ ለምን ስምምነቱ በቅን ልቦና አልተተገበርም ለምን ፋኖ ላይ ጦርነት ከፈታችሁ ? " የሚል ንግግርም ተናግረዋል።
ሌላው የፖለቲካ ፓርቲዎች የሌለባት ፣ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የማይታወቅባት ኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያን በተመለከተ ንግግራቸው " በኢትዮጵያ መታየት ጀምሮ የነበረው የለውጥ ተስፋ ጨልሟል ፤ የፖለቲካ ፓርቲ ብሎ የለም " የሚል ንግግር አሰምተዋል።
ያለአንዳች ተቀናቃኝ ከ30 ዓመት በላይ ኤርትራን እየገዙ ያሉት ኢሳያስ አፈወርቂ እንደ ሁል ጊዜው የትላንት ምሽቱ ቃለ ምልልሳቸው ስለ ሀገራቸው ጉዳይ ሳይሆን ስለ ኢትዮጵያ እንዲሁም ስለ ሌሎች ሀገራት ጉዳይ በመተንተን ነው ያለፈው።
ከዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ተነሳሽነት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ሰላም እንዲወርድ ከተደረገ በኃላ የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እስኪፈረም ድረስ ኢትዮጵያን እና አስተዳደሯን ሲያሞካሹ እንደቆዩ በአደባባይ የሚታወቅ ሀቅ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyMekelle
@tikvahethiopia
ከሀገራቸው ጉዳይ ይልቅ ስለ ሰው ሀገር ጉዳዮች ሰፊ ጊዜ ወስደው በመናገርና በመተንተን የሚታወቁት የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ትላንት ምሽት በሀገራቸው ብቸኛው ቴሌቪዥን በተላለፈ ቃለ መጠይቅ #የኢትዮጵያን ስም ደጋግመው ሲያነሱ ታይተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ከወራት በፊት በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ከሀገራቸው ጉዳይ ይልቅ ስለ ኢትዮጵያ እና ቀጠናው ጉዳይ ትንታኔ ሲሰጡ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም። በወቅቱም ኢትዮጵያ ስሟን እያነሱ ለተናገሩት ነገር ሁሉ በቀጥታ አንዳችም ምላሽ ሳትሰጣቸው በዝምታ አልፋቸዋለች።
ትላንት በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ደግሞ ንዴትን በቀላቀለ ሁኔታ በማይመጥኑ ቃላት የኢትዮጵያን ስም ሲያነሱ ነበር።
በተለይም ኢትዮጵያ ያነሳችውን የባህር በር ጥያቄ ሲያጣጥሉት ነው ያመሹት።
የኢትዮጵያን የወደብ እና የባህር በር ጥያቄ " የህጻን ጨዋታ ነው፣ ማሳሳቻ ነው፣ የረከሰ ውሸት ነው ፣ የውስጥ ጉዳይ ማዳፈኛ ነው ፣ ጀርባው የተባበሩት አረብ ኤሜራት የወደብ ማስፋፋት አጀንዳ ነው " የሚሉ ቃላቶችን በመጠቀም ኢትዮጵያን ለማጣጣል ሞክረዋል።
ኢትዮጵያ የባህር በርን ጉዳይ አለም አቀፍ አጀንዳ ማድረጓን ተከትሎ በርካታ ሀገራት ለጥያቄዋ ድጋፍ ማድረጋቸውም ፕሬዝዳንቱን እንዳላስደሰተ የሚጠቁም ንግግርም ሲናገሩ ነበር።
" ፈረንሳይ ከኛ ጋር ናት፣ አሜሪካ ፣ ኤማራት፣ አውሮፓ ህብረት ከኛ ጎን ናቸው ማለት ጭንቅ እንጂ የድል መንገድ አይደለም " በማለት " ኢትዮጵያውያን የውስጥ ችግራችሁን ፍቱ " ሲሉ ተደምጠዋል።
በኢትዮጵያ በኩል ሀገራቸው ላይ የጦርነት ስጋትና ዛቻ እንዳለ በማመላከትም " እራሳችንን እንጠብቃለን " ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለባሕር ስትል ኤርትራንም ሆነ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር የመውጋት አንዳችም ፍላጎት እንደሌላት በተደጋጋሚ ማሳወቋ ይታወሳል። ነገር ግን የባህር በር ጉዳይ ህልውናዋ መሆኑን ለዓለም ህዝብ አስረግጣ ተናግራለች።
ሌላው ፕሬዜዳንቱ ኢትዮጵያ ተመድ ሄዳ ከሳናለች (ክሱ ፦ ድንበር አካባቢ አሁንም የኤርትራ ጦር ግፍ እየፈጸመ ስለመሆኑ) " ያሉም ሲሆን " ክሱ አስነዋሪና አሳፋሪ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
ስለ ፕሪቶሪያ ስምምነትም ሲያነሱ ነበር።
ገና የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሲፈረም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት እንዳሻከረች በይፋ የሚታወቅ ቢሆንም " ኤርትራን ከመክሰሳችሁ በፊት የፕሪቶሪያን ውል ተግብሩ ፤ የውስጥ ችግራችሁን መፍታት አስቀድሙ ፤ ለምን ስምምነቱ በቅን ልቦና አልተተገበርም ለምን ፋኖ ላይ ጦርነት ከፈታችሁ ? " የሚል ንግግርም ተናግረዋል።
ሌላው የፖለቲካ ፓርቲዎች የሌለባት ፣ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የማይታወቅባት ኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያን በተመለከተ ንግግራቸው " በኢትዮጵያ መታየት ጀምሮ የነበረው የለውጥ ተስፋ ጨልሟል ፤ የፖለቲካ ፓርቲ ብሎ የለም " የሚል ንግግር አሰምተዋል።
ያለአንዳች ተቀናቃኝ ከ30 ዓመት በላይ ኤርትራን እየገዙ ያሉት ኢሳያስ አፈወርቂ እንደ ሁል ጊዜው የትላንት ምሽቱ ቃለ ምልልሳቸው ስለ ሀገራቸው ጉዳይ ሳይሆን ስለ ኢትዮጵያ እንዲሁም ስለ ሌሎች ሀገራት ጉዳይ በመተንተን ነው ያለፈው።
ከዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ተነሳሽነት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ሰላም እንዲወርድ ከተደረገ በኃላ የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እስኪፈረም ድረስ ኢትዮጵያን እና አስተዳደሯን ሲያሞካሹ እንደቆዩ በአደባባይ የሚታወቅ ሀቅ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyMekelle
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.37K😡174🕊72🤔46👏39🙏16🥰10😭8😢7💔6😱4