ለምን አልሰለምኩም?
3.01K subscribers
52 photos
10 videos
42 files
187 links
ይህ ቻነል ቅዱሱ የአምላካችን ቃል በ1ኛ ጴጥ 3:15 ላይ ባዘዘን መሠረት ሙስሊም ወገኖቻችን በክርስትና ላይ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች እና ትችቶች ምላሽ የምንሰጥበት፣ ጥያቄዎቻቸውን ከነመልሳቸው በየጊዜው እያዘጋጀን የምንለጥፍበት፣ ለምን እንዳልሰለምን ፣ እንደማንሰልምም የምንገልጥበት ፣ የኢስላምን የጨለማ መንገድነት በእውነት ብርሀን የሚገልጡ ፅሁፎችን የምናስነብብበት መድረክ ነው።
Download Telegram
📌ከ እስልምና በፊት ከነበሩት እምነቶች ይተኮረጁ📌
👹የ ሙሓመድ ሸይጠኖች 2 👹

ከ መቀጠላችን በፊት ጂኒዎች የ ሰይጣን(ዲያብሎስ/ኢብሊስ) ጎሳ መሆናቸውን የሚገልጽ ሱራ እናንብብ
ሱረቱል ካፍ (18):50
"ለመላእክትም ለአደም ስገዱ፥ ባልናቸው ጊዜ (የሆነውን አስታውስ)። ወዲያውም ሰገዱ፤ ኢብሊስ ብቻ ሲቀር፤ ከጋኔን/ጂን (ጎሳ) ነበር፤ ከጌታውም ትእዛዝ ወጣ፤ እርሱንና ዘሮቹን እነሱ ለናንተ ጠላቶች ሲኾኑ፥ ከኔ ሌላ ረዳቶች አድርጋችሁ ትይዛላችሁን? ለበዳዮች ልዋጭነቱ ከፋ!" ....ስለዚህ ክፉ መናፍስት እንጅ ቁሳዊ እንዳልሆኑ ግልጽ ነው።

ክፍል አንድ ላይ ነ.ሙሓመድ ሰይጣኖች እንደሚበሉ አስተምረውናል። እንግዲህ ማንም ሰው ይህንን ትምህርት ከተማረ በኊላ የሚጠይቀው ጥያቄ ቢኖር "ጂኒዎቹ ምንድነው የሚበሉት??" የሚል ጥያቄ ይሆናል ብዬ አስባለው። እስኪ እሳቸው (ሙሓመድ) ምን ይላሉ??

Bukhari - Volume 5, Book 58, Number 200:
Narrated Abu Huraira:
 አንድ ወቅት ላይ አቡ ሁረይራ ለ ነብዩ ሙሓመድ  ሓፍረተ ስጋቸውን የሚታጠቡበት ውሃ (ከተጽዳዱ በኊላ የሚደረግ)  ይሸከምላቸው ነበር። አንድ ቀን እየተከተላቸው እያለ ነብዩ "ማን ነው" ብለው ይጠይቃሉ። እሱም "አቡ ሁረይራ ነኝ" ብሎ ይመልስላቸዋል። ሙሓመድም "ሒድና ብልቴን የማፀዳበትን #ድንጋይ አምጣልኝ። የ እንስሳን #ኩበት ወይም #አጥንት ግን እንዳታመጣ" አሉት። አቡ ሁረይራም ዘገባውን ቀጥሎ እንዲህ አለ " እኔም በ ጎን ኪሴ ድንጋይ አመጣሁለት።....ሲጨርሱም "ኩበትና አጥንት ለምን ተከለከለ??" ብዬ ጠየኩ። ነብዩም "እነኛ ሁለቱም የ #ጂኒዎች #ምግብ ናቸው፣ ብለው መለሱ።..." 

 ጃሚ አት ቲርሚዚ 3258

"...(በ ኩበት ወይም በ አጥንት)ብልቶቻቹን አታፅዱ።እነሱ ለ ጂን ወንድሞቻቹ ምግብ ናቸው።"

ጥያቄዎቻችን
1. ሙስሊሞች እነኚን የ ጂኒዎችን ምግብ እንዳይጠቀሙ ከታዘዙ ጂኒዎችን እየመገቡ ምሆኑ አይሆንምን?? ክፉ መናፍስት ልክ እንደሰው የሚመገቡ ከሆነ የሰው ጠላት (ሱራ 35:6) እስከሆኑ ድረስ የነሱን ምግብ እየተጽዳዳንበት በ ረሃብ ብንጨርሳቸው አይሻልምን??

ሙስሊሞች እንግዲህ እነኚን ጥቅሶች ስንስጣቸው.. "አይ! ሰይጣን እንደሰው ይበላል ማለት አይደለም..." እያሉ ለመግለፅ ይፍጨረጨራሉ። ችግሩ፣ አንድ ሙስሊም ተነስቶ የራሱን ፊቺ ለዬትኛውም የእስልምና መፅሓፍ ሊሰጥ አይችልም። ምክኒያቱም ቀደምት  የ እስልምና አዋቂዎች፣ ሙፈሲሮች ትርጉሞቹን በ መፅሓፍቶቻቸው አስቀምጦውልናል። ስለዚ ከላይ ያነበብናቸው ሓድዞች ትርጒሜያቸው ምን እንደሆነ ቀጥለን እናያለን

ኢብን ሓጀር፦ "ሰይጣን ይበላል የተባለው ምንም የማያከራክር ሓቅ ነው።ይሄን ለመቃወም የሚያስችለን ምንም የ አይምሮ ብቃት የለንም። ይህ ቃል የተረጋገጠ ስለሆነ ምንም ትርጉም አያስፈልገውም።" ይላል
And that Satan eats is a fact. It is not for our intellect to reject that, and it is already proven from the report with no need for interpretation. (Fath al-Bari 9/522)

ኢማም ነወዊም  ይህንን ሓሳብ ይጋራሉ (Sharh Sahih Muslim 13/204)

ወገኖቼ፣ የ እስልምና ሰይጣኖች ልክ እንደሰው የሚዳሰሱ የሚጨበጡ  ወ.ዘ.ተ  እንደሆነ ግልፅ ነው።
ለምሳሌ፦ሳሂህ አል-ቡኻሪ ቅጽ  4  መፅሓፍ 54 ቁጥር 495  ላይ አቡ ሁረይራ አንድን ሰይጣን ምግብ እየሰረቀ አግኝቶት እንደያዘውን ሰይጣኑም "ቸግሮኝ ነው ባክህ ልቀቀኝ" ብሎ ሲለምነው እንደለቀቀው ተጽፎ እናገኛለን።

ውድ አንባቢዋቼ፣ ነብዩ ሙሓመድ ይህንን የ "ስነ-ሰይጣን" አስተምህሮ ከዬት አምጥተውት ነው ብላቹ አስባቹ ይሆናል። መልሱ ሙስሊሞች እንደሚነግሩን ከ አላህ #አይደለም!!!"

መልሱ፣ነብዩ ሙሓመድ ይህንን ሁሉ (ስለ ሰይጣን መብላት፣መጠጣት፣መሽናት፣መጋባትና መራባት ወ.ዘ.ተ) ያስተማሩት ሙሉ ለ ሙሉ ከ ዕስልምና በፊት በ አራቢያ ውስጥ ከ ነበሩ እምነቶች ቀድተው ነው። ይህንን ለ መረዳት አንድ ሰው "The Evolution of the Concept of Jinn" የሚል በ Amira El-Zein
የተፃፈ መጽሓፍ ማንበብ ይጠበቅበታል!!
......ይቀጥላል
@Jesuscrucified
@Jesuscrucified
📌አምላክ እንዴት አምላክ ይኖረዋል?📌

ሙሓመዳውያን ስለ እየሱስ አምላክነት ሲጠይቁን ውሃ ከማይቋጥሩ ሙግታቸው መካከል አንዱ "እየሱስ እራሱ እግዚያብሔር አብን አምላኬ ብሏል፤ታድያ እናንተ እየሱስን አምላክ የምትሉት ከዬት አምጥታችሁት ነው?? አምላክስ አምላክ ሊኖረው ይችላልን??" የሚል ነው።

በመጀመሪያ ደረጃ እኛ እግዚያብሔር አብ የ እየሱስ አምላክ ("የሰውነት ማንነቱ") መሆኑን ጠንቅቀን እናውቃለን።  እየሱስም ወደ ምድር ሲመጣ በ አምላክነት ማንነቱ የ ሰውነት ማንነተ ስለተዋሃደ  ጠቅልለን "የ እየሱስ ክርስቶስ አባትና አምላክ" እንላለን።

ሙግት አንድ

እየሱስ መጽሓፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚያብሔር አብን "አምላኬ" ብሎ ጠርቶታል (ማቴዎስ 27:46)፤ ጳውሎስም "የእየሱስ ክርስቶስ አባትና አምላክ" ብሏል።
" በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1:3)። እየሱስ ካረገ በኋላም "አምላኬ" ብሏል። (ራእይ 3:2)


ታድያ እየሱስ አማላክ ከሆነ እንዴት አምላክ ይኖረዋል??

" እነሆ፥ እኔ የሥጋ ለባሽ ሁሉ አምላክ  "יְהוָ֔ה" እግዚአብሔር "אֱלֹהֵ֖י" ነኝ"(ትንቢተ ኤርምያስ 32:27)
"27 Behold, I [am] the LORD ""  , the God of all flesh: is there any thing too hard for me?"
(Jeremiah 32:27)

በዚህ በክፍል ላይ እግዚአብሔር ያህዌ #የስጋ #ለባሽ ሁሉ አምላክ እንደሆነ ግልፅ ነው። እየሱስ ደግሞ ወደ ምድር ሲመጣ ስጋን ለብሷል። ልበ በል "ማንነቱን (essence) ቀየረ" ሳይሆን፤ ሌላ ማንነትን (ሰውነትን) ጨመረ ማለት ነው። ስለዚህ እየሱስ ሁለት ማንነት በ አንድ አካል (one person) ሆኖ ተገልጧል ማለት ነው። ስለዚህ እየሱስን በ አረፍተ ነገር ውስጥ ስናመለክት ሁለቱ ማንነቶች የተለያዩ ቢሆኑም ለይተን አንጠራም ማለት ነው። ስለዚህ እየሱስ የሰውነት ማንነት(human nature) ስላለው፣ በ ኤርሚያስ 32:27 መሰረት፣ ስጋ ያልለበሰውን እግዚያብሔር አብን "አምላኬ" ብሎ መጥራት ነበረበት። ስለዚህ እየሱስ እግዚያብሔር አብን አምላኬ ስላለ እየሱስ አምላክ አይደለም ማለት አይደለም። ምክኒያቱም በአምላክነት ማነቱ ለዘለአለም ከ አብ ገር " አንድ ማንነት (one being)" ኖሮት ይኖር ስለነበረ። 

" #አሁንም፥ አባት ሆይ፥ #ዓለም #ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ #በነበረኝ #ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ።"(የዮሐንስ ወንጌል 17:5)፤  

(የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 1)
----------
1፤ በመጀመሪያው ቃል ነበረ( En arche(ልብ በል "ኤጌኔቶ" አይልም) en o logos)፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።

2፤ ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ።

(የዚህን ክፍል ጥልቅ ማብራሪያ በ ግሪክ ሰዋስውና ፊሎሶፊ በቅርብ ቀን እናያለን።)

ስለዚህ እየሱስ እግዚያብሔር አብን "አምላኬ" ብሎ እንዲጠራው ያደረገው የሰውነት ባህሪይ ነው እንጂ ፍጡር ስለሆነ #አይደለም

ሙግት ሁለት፦ ካረገ በኋላስ??

እየሱስ ካረገ በኋላም በሁለቱ ማንነቶቹ ይኖራል። ሲጀመር የትንሳኤ ሃሳብ እራሱ የስጋ ማንነትን "pre suppose"  ያደረገ ነው።(ሉቃስ 24:39)
ለዚያም ነው ጳውሎስ ሲናገር "አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤"(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:5) ብሎ የሰውነት ማንነቱን ብቻ የ ገለፀው። የ እየሱስ ክርስቶስ መካከለኛነት በ ስጋዊ ባህሪው (በመሞት) የተፈፀመ ስለሆን "ሰው የሆነው" ብሎም ተናግሯል። ልብ በሉ "ሰው ብቻ" አላለም። ከሁለቱ ማንነቱ አንዱን በ አውዱ (መካከለኛ መሆን) መርጦ ተናግሯል። ጳውሎስም በ ኤፌሶን 1፡3 "የ እየሱስ አባትና አምላክ" ያለው አሁንም እየሱስ በ ሁለት ማንነቱ ስላለ ነው።

ሙግት ሶስት፦ አንተ ብቻ እውነተኛ አምላክ

" እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።"(የዮሐንስ ወንጌል 17:3)
"3 And this is life eternal, that they might know thee the only true God, and Jesus Christ, whom thou hast sent."(John 17:3)

እግዚያብሔር አብ ብቻ እውነተኛ አምላክ ከተባለ እየሱስ እንዴት እምላክ ይሆናል??

መልሱ " ስላሴ ውስጥ ነው። ሎጂኩን ላሳያቹ

1. ስላሴ ብቻ እውነተኛ አምላክ ነው
2 ስላሴ በ አንድ አምለክ ማንነት ( in only one being=God) ሶስት አካል (person) ለዘለአለም በአምላክነት ባህሪያቸው እኩልና አንድ የሆኑ አብ፣ወልድና መንፈስ ቅዱስ አሉ። ስለዚህ እያንዳንዱ የስላሴ አካል በ ነጠላም ብቸኛ እውነተኛ አምላክ ነው

መደምደሚያ። አብ ብቸኛ እውነተኛ አምላክ ነው፤ ወልድ ብቸኛ እውነተኛ አምላክ ነው፣ መንፈስ ቅዱስ ብቸኛ እውነተኛ አምላክ ነው። ልብ በል፤ "እውነተኘ አምላክ" አንድ "essence" ነው፤ "አካል" (person) አይደለም። ሶስቱ ደግሞ "አካል ናቸው"።

ስለዚህ በ ስላሴ አውድ "አብ ብቸኛ እውነተኛ አምላክ ነው" ማለት ወልድ #አይደለም ማለት አይደለም

ይቀጥላል...
@Jesuscrucified
@Jesuscrucified
1👍1
ግራንቪል ሻርፕ በ ቲቶ 2:13

የ ሙሓመዳውያን ኡሥታዞች ከ ስላሴ ትምህርት ተቃዋሚያን ፅሁፍ በሚቃርሙት የተሳሳተ መረጃና እጅጉን አሳፋሪ በሆነ አለመረዳትና አለማወቅ የክርስቶስን አምላክነት ለመቃወም በ ፅሁፎቻቸው እራሳችውን ማዋረድና ማውረድ ከጀመሩ ሰንብቷል። ከነኚህ ትችህቶች ውስጥ ዛሬ የምናየው ቲቶ 2:13 ላይ የተነሱትን ይሆናል።

" ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም #የታላቁን #የአምላካችንንና #የመድኃኒታችንን #የኢየሱስ #ክርስቶስን ክብር #መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤"
(ወደ ቲቶ 2:12-13)
προσδεχόμενοι τὴν μακαρίαν ἐλπίδα καὶ ἐπιφάνειαν τῆς δόξης τοῦ μεγάλου #θεοῦ καὶ #σωτῆρος ἡμῶν #Χριστοῦ #Ἰησοῦ,

while we wait for the blessed hope—the appearing of the glory of our great #God and #Savior, #Jesus Christ ( tou megaluo #Theou kai #Soteros hemon Christou 'Iesou)

ከላይ እንዳነበባችሁት ክፍሉ እየሱስን # θεοῦ God ወይም #እግዚያብሔር ብሎ እየጠራ እንደሆነ ግልፅ ነው። ነገር ግን አንዳንድ ከንቱ ተቺዎች "θεοῦ" የሚለው ለ እየሱስ ሳይሆን #ለአብ ነው ብሎ ሙግት አቅርቧል። ሙግቱም አንድ የ ግሪክ ቋንቋ ምሁር (Scholar)፣ ስሙም "ግራንቪል ሻርፕ" የተባለ ሰው ባስቀመጠው የ ሰዋሰው ሕግ ላይ የተመሰረተ ነው። ይሁን እንጂ ይህንን ሙግት ያቀረበው 'ተቺ'፥ ሕጉንና ቲቶ 2:13'ን  አንድ ላይ ቢያጠና ኖሮ፣ ክፍሉ እንዲያውም የ ክርስቶስን አምላክነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ስለሚረዳ አፉን ይዞ ቁጭ ይል ነበር። የሚገርመው ግራምቪል እራሱ ሕጉን ተጠቅሞ ቲቶ 2:13 እየሱስ አምላክ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ ፅፏል።

1ኛው የ ግራንቪል ሕግ ምን ይላል??

“When the copulative kai connects two nouns of the same case, [viz. nouns (either substantive or adjective, or participles) of personal description, respecting office, dignity, affinity, or connexion, and attributes, properties, or qualities, good or ill], if the article ho, or any of its cases, precedes the first of the said nouns or participles, and is not repeated before the second noun or participle, the latter always relates to the same person that is expressed or described by the first noun or participle”

καὶ(kai, 'እና') የተሰኘች መስተፃምር ሁለት ተመሳሳይ ሙያ ያላቸውን ስሞች ለማያያዝ ስትገባና ከመጀመሪያው ስም በፊት ho ወይም τοῦ ("The") የሚለው definite article ከገባ  ግን ሁለተኛው ስም(noun) በፊት ሳይገባ ከቀረ እነኚህ ሁለቱ ስሞች የሚናገሩት(የሚገልፁት) ስለ አንድ ሰው ነው።
(Remarks on the Uses of the Definitive Article, 3)
(ይህንን ካላሟላ ግን ሁለት የተለያዩ አካላትን ለመግለፅ ነው የሚለው ሙግት ከዚህ የመጣ ነው፤ሁል ግዜ ትክክል ባይሆንም)

ይሁን እንጂ ይሄ ሕግ ከላይ የተገለፀውን የ አርፍተ ነገር አወቃቀር ለሚያሟሉ  ሁሉ ይሰራል ማለት #አይደለም። ሕጉ የሚሰራው ቀጥለን ይምንዘረዝራቸውን ቅድመ ሁኔታ ለሚያሟሉ #ብቻ ነው።

1. ስሞቹ ሕልውና ላላቸው (ለሰው, ለ አምላክ) ብቸ የተጠቀሙ መሆን አለባቸው (they must refer to a person;not a thing)

2. የተፀውኦ ስም (Proper name) መሆን #የለባቸውም

3. ተመሳሳይ ሙያ መሆን አለባቸው (The same case)

4. ነጠላ መሆን አለባቸው (singular in number)

ዋቢ መፅሓፍት

ሀ. A Reexamination of the Granville Sharp rule by Daniel B.Wallace, Ph.D. Associate professor of New Testament Studies;

ለ. Wallace, Greek Grammar, 280-290

ሐ. Robertson, Grammar, 785-90

ስለዚህ በዚህ ሕግ መሰረት ቲቶ 2:13 "እየሱስ አምላክ ነው" ይላል?? መልሱን የምንሰጠው ክፍሉ የ ግራንቪልን ሕግ ሙሉ ለሙሉ ማሟላቱን ነጥብ በ ነጥብ እያየን ይሆናል።

1. 'tou' 'The' የሚለውን definite article የተጠቀመው በ መጀመሪየ ስም ላይ ብቻ ነውን?
መልስ- #አዎ
#tou megaluo #Theou kai #Soteros hemon Christou 'Iesou (ቲቶ 2:13)
θεοῦ(Theou, አምላክ, God) የሚለው የመጀመሪያ ስም ሲሆን σωτῆρος(Soteros, አዳኝ ወይም መድሃኒት, saviour) ሁለተኛ ስም ነው። tou' የሚለው የገባው በ θεοῦ ፊትለፊት ብቻ ነው።

2. ስሞቹ የተጠቀሙት(Theou እና Soteros) "ህልውና ላለው( personal) ነውን??
መልስ፦አዎ። ምክንኒያቱም ሁለቱም እየሱስን ለመግለፅ ነው የገቡት።
"..የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን #የኢየሱስ #ክርስቶስን.."

3. θεοῦ እና σωτῆρος ሁለቱም የተፀውኦ ስም (Proper name) #አይደሉም። ስለዚህ አሁንም ክፍሉ 2ኛውን  ቅድመ ሁኔታ ያሟላል ማለት ነው።

4. θεοῦ እና σωτῆρος ተመሳሳይ ሙያ ናቸውንህ??

θεοῦ=Noun #Genetive masculine singular
σωτῆρος=Noun #Genetive masculine Singular
ስለዚህ መልሱ "አዎ! ሁለቱም ተመሳሳይ ሙያ ናቸው።"

5. θεοῦ እና σωτῆρος ሁለቱም #ነጠላ (singular) ናቸው። ስለዚህ የመጨረሻውንም ቅድመ ሁኔታ ያሟላል።

ስለዚህ፤ ቲቶ 2:13 ሁሉንም የ ግራንቪል የ ሰዋሰው ሕግ ያሟላል። ማለትም θεοῦ እና σωτῆρος ( God and saviour, አምላካችንና መድሓኒታችን) ብሎ የተቀመጠው ሁለቱም #እየሱስን ለመግለፅ ነው ማለት ነው። ስለዚህ እየሱስ 'አምላክ" እና "መድሃኒት" ነው ማለት ነው።

ሙስሊሙ 'ተቺ"ይህንን ክፍል ለማክሸፍ የተጠቀማቸው ጥቅሶች ሁለት ናቸው።

1. ማቴ 21:12 ኢየሱስም ወደ መቅደስ ገባና በመቅደስ *የሚሸጡትን* እና *የሚገዙትን* ሁሉ አወጣ። "እነኚህ ሁለቱ ስሞች የተለያዩ ሰዎችን ይገልፃሉ" ብሎ ፅፏል።

ይሄ ክፍል በ አረፍተ ነገር አወቃቀሩ ቲቶ 2:13ን ቢመስልም (τοὺς πωλοῦντας καὶ ἀγοράζοντας*Those selling and buying) ግን ቅድመሁኔታዎችን ስለማያሟላ ውድቅ ነው። ምክኒያቱም "የሚሸጡትን* እና *የሚገዙትን" የሚሉ ሁለቱም ቃላት #ነጠላ አይደሉም።የ ግራምቪልን ሕግ አያሟሉም። ስለዚህ ክፍሉን እንደማስረጃ ማቅረብ በራሱ አሳፋሪ ነው።

2. ኤፌሶን 2:20 *በሐዋርያት* እና *በነቢያት* መሠረት ላይ ታንጻችኋል፥

አሁንም በዚህ ክፍል "በሐዋርያት* እና *በነቢያት"  የተባሉት ሁለቱም ብዛትን የሚያሳዩ እንጂ ነጠላ አይደሉም። ስለዚህ አሁንም ማስረጃው የ ግራንቪልን ሕግ ስለማያሟላ  ውድቅ ይሆናል
@Jesuscrucified
ብዙ ሚስት በባይብል??

"፤ የጌታህንም ቤት ሰጠሁህ፥ የጌታህንም #ሚስቶች በብብትህ ጣልሁልህ፤ የእስራኤልንና የይሁዳን ቤት ሰጠሁህ፤ ይህም አንሶ ቢሆን ኖሮ ከዚህ የበለጠ እጨምርልህ ነበር።"
(መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ 12: 8)

አንዳንድ ንቀን የተውናቸው ሙሓመዳውያን ስናፍጭ በምታክለው ጭንቅላታቸው መፅሓፍ ቅዱስን ወደ እራሳቸው የወረደ ደረጃ ሲጎትቱና በየ ቻነሎቻቸው የወደቀ ትርጉም ሲፈላሰፉለት እያየን ነው። ከላይ ያነበብነውን የመፅሓፍ ቅዱስ ክፍል፣አንዱ እንዲህ ብሎ ትርጉም ሰጥቶታል። እስኪ የሱን ትርጉም ላስነብባቹ፤

"........አንዳንድ ክርስቲያን ወገኖች የዳዊትና የልጁ ሰለሞንን ከመጠን ያለፈ የሚስት ብዛት ለማስተባበል የሚጠቀሙት ቃል "እግዚአብሄር ሳያዛቸው በፍቃዳቸው የሰሩት ነው በዚህም ተወቅሰዋል" የሚል ነው። በመጀመሪያ ነገር በሚስት ማብዛታቸው ምክንያት ተቀጡ የሚል የለም። ሲቀጥል መጀመሪያውኑ እግዚአብሄር አይደል እንዴ በጅምላ እንዲያገቡ ያመቻቸው?...." ብሎ 2ሳሙኤል 12:8 ጠቅሷል።እስኪ ክፍሉን እናጥናው፤

1. #የጌታህንም_ሚስቶች your master's wives

ለዳዊት ጌታው(master) የነበረው #ሳኦል ነው። በመጀመሪያ ደረጃ፣ሳኦል ብዙ ሚስት አለው የሚል መፅሓፍ ቅዱስ ውስጥ የለም። ሳኦል #አንድ_ሚስት(1ሳም 14:49-50) እና "ሪጽፋን" የምትባል አንድ #ቁባት(concubine)(2ሳም 3:6-7)ብቻ ነበረው። "ሚስቶች" የተባለውም እሷን ጨምሮ ነው።በ ኢስራኤልም ሆነ በ ድሮ ምስራቃዉያን አለም፣ የ አንድ ንጉስ ሚስትም ሆነ ቁባት፣ ንጉሱ ከሞተ፣ የቀጣዩ ንጉስ ይሆናሉ። ንጉሱ ሊያገባትም ላያገባትም ይችላል። ብቻ እጣ ፈንታቸውን የሚወስነው ቀጣዩ ንጉስ ነው ማለት ነው።  የሚገርመው ነገር፣ መፅሓፍ ቅዱስን ከ ጫፍ እስከ ጫፍ ብታነብ፣ ዳዊት የሳኦልን ሚስት እንዳገባ የሚናገር #አንድም_ማስረጃ_የለም። ሌላው አስገራሚው ነገር ደግሞ፣ የሳኦልን ቁባት የወሰደው ዳዊት ሳይሆን #አበኔርም የሚባል ሰው ነው(2ሳም 3:7)። የቀረችው አንድ የሳኦል ሚስት ናት፤እሷንም ዳዊት እንዳገባት የሚናገር ጥቅሥም ማስረጃም የለም። ታዲያ ሙስሊሞች የሚሉት 'የትኞቹን የሳኦል ሚስቶች ናቸው ዳዊት ያገባው??'
ይልቁንስ ክፍሉ ላይ '... የጌታህንም #ሚስቶች በብብትህ ጣልሁልህ፤..' ለሚለው  ተቀባይነት ያለው ትርጉም "በራሱ በሳኦል ሚስቶች ላይ መብት ሰጠሁ፤" ይሄ ማለት የፈለገውን ማግባት ይችላል ነው እንጂ 'ሁሉንም ማግባት ይችላል'  ማለተም አይደለም። ለዳዊት ይሄ መብት ተሰቶታል ማለት ግን "አግብቷል" ማለት #አይደለም። ማስረጃም የለም። ስለዚህ በ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ 'እግዚያብሔር  ወንዶች ብዙ ሚስቶችን እንዲያገቡ ፈቅዷል' የሚል ሙግት ውድቅ ይሆናል ማለት ነው።

2. "..ከዚህ የበለጠ እጨምርልህ ነበር.."

ሙሓመዳውያን በዚህኛው ደግሞ እጅግ የሚያስቅ ሙግት ሰርቷል። ሙግታቸውም "..ለዳዊት አንሶት ቢሆን ኖሮ እግዚያብሔር ለዳዊት ብዙ ሚስቶችንም ይጨምርለት ነበር.." የሚል ነው። አንድ ፊደል የቆጠረ ሰው ይሄንን ክፍል መረዳት ያቅተዋል ብዬ አላስብም ነበር( apparently i was wrong 😂)።

በዚህ ክፍል ላይ፣እግዚያብሔር ለዳዊት የሰጠውን ነገር በዝርዝር እያስቀመጠ ነው ያለው፤ እንመልከት
1. የጌታህንም ቤት..
2. የጌታህንም ሚስቶች..
3.የእስራኤልንና የይሁዳን ቤት..
 ሰጠሁህ፤
..ይህም አንሶ ቢሆን ኖሮ ከዚህ የበለጠ እጨምርልህ ነበር።"
ስለዚህ፣ እግዚያብሔር "እጨምራለው" እያለ ያለው፣ ዝርዝሩን (e.g 4.ብር፣ 5.ወርቅ ወ ዘ ተ) እንጂ  #ሚስቶችን ወይም የተጠቀሱ ነገሮችን 'በብዛት' እጨምራለው' ማለት አይደለም

ይልቁንስ፣ ቀጥለን በምናነበው ክፍል ላይ እግዚያብሔር በግልጽ #የትኛውም የእስራኤል ንጉስ ብዙ ሚስት እንዳያገባ ከልክሎ እናገኛለን። ስለዚህ ዳዊትም ሆነ ሶሎሞን ብዙ ሚስት ቢያገቡም እግዚያብሔር ፈቅዷል ማለት አይደለም



(ኦሪት ዘዳግም ምዕራፍ 17)
----------
15፤ አምላክህ እግዚአብሔር የመረጠውን በላይህ ታነግሣለህ፤ ከወንድሞችህ መካከል የሆነውን በአንተ ላይ ንጉሥ ታነግሣለህ፤ ወንድምህ ያልሆነውን ከሌላ ወገን ሰው በላይህ ንጉሥ ታደርግ ዘንድ አይገባህም።

16፤ ነገር ግን ለእርሱ ፈረሶችን አያበዛም፤ እግዚአብሔር። በዚያ መንገድ ደግማችሁ አትመለሱም ብሎአችኋልና ፈረሶችን ለማብዛት ሕዝቡን ወደ ግብፅ አይመልስም።

17፤ ልቡም እንዳይስት #ሚስቶችን_ለእርሱ_አያበዛም፤ ወርቅና ብርም ለእርሱ እጅግ አያበዛም።

"17 Neither shall he multiply wives to himself, that his heart turn not away: neither shall he greatly multiply to himself silver and gold."

የኢስልምና አፖሎጂስቶችን ሎጂክ እናስተምር እንዴ?
@Jesuscrucified
@Jesuscrucified