#የማታ_ቀጠሮ 🕊
እና .....እንደነገርኩሽ !!
አዲስ ቀን ተስፋ ጥሎ .....ከሚሰነቅ ስንቅ
የራእይ ወቅቱ ፥ በበነጋ ሲርቅ
እስትንፋሰ እድሜ ተኮላሽቶ
ሬሳ ለቃሚ ፥ ከየ ስርፋው በዝቶ
እምነታችን መንገድ ሳተ ....አካሄዱ ተሸረፈ
መኖር መሰንበቱ ፥ ፍርሀት ሸከፈ
ሰው እንደ ባህር ዛፍ ፥ በምሳር ታጠፈ
ሀሳባችን ታጥሮ
የተስፋችን ፋኖስ አይሆኑ ተሰብሮ
በኔና ባንቺ አገር ፥ መሞት ዋዛ ቀረ
የለትተለት ዜና
ልጅ አሞራ በላው ፥ ወላጅ ተሸበረ
የተማረው ብሶ
ወደ እናት አባት ቤት ፥ ሳጥን ተሳፈረ።
አየሽ !!
በግብሬ ፣ በክፍሌ ፥ በስጋ ላደረ
ሰብነት ሸክፎ
በህላዌ ተስፋ ፥ ኑሮ ለመተረ
ከሊቅ እስከ ደቂቅ ፥ ለትልቅ ትንሹ
ለነ ንዋይ ዘገን !!
ለነ አመድ አፋሹ !!
እኩል እንደ አቅሙ ፥ ብስራተ ጥሞና
የመኝታ ደወል ፥ የህልም መዲና
ከምሽቱ በላይ ፥ ፅልመታም ጀበርና
ከሚታወጅበት...
የውድቅት ጀምበር ፥ የጨለማ ጋራ
ገላጣና ግልፁን ፥ ቀኑን ነው ምፈራ !!
ቀኑን ነው ምፈራ !!
አለሰአት ስንጦሎጦል.... ከሚያገኘኝ አውሬ
በለሊት ከሚያፍን ፥ ከቅጥረኛ ካድሬ
ሌት ከሾመው ፥ ኪስ አውላቂ ፥ ንብረተ ወዝ ከሚጋራ
ድንቡሎ ላየገኝ ፥ ደሜን የሚዘራ
ማጅራት ከሚመታ
በድቡልቡል ድንጋይ ፥ በሰላ ቆንጨራ
ከውድቅት ልክፍት ፥ ከቄሳር አሞራ
ከዚህ ....ከዚህ በላይ
ባማረበት ጀምበር ፥ በገላጣው ፀሀይ
በኔና አንቺ ሰማይ
ክልክል ባረጉብኝ ፥ በጋረዱኝ ቦታ
ነቃይ
አስነቃዩ
ባለ መሬት ጋንታ
በጠራራ ፀሀይ ፥ የሰየመው ሽፍታ
ቀለሀውን ዘግኖ
እርሳስ በሰው ገላ ፥ ቃታውን ሲፈታ
የሰፈር ተጠሪ ፥ ቀን የሰጠው ጌታ
ሮንድ የሚቃርም ፥ አለሁ ባይ ኮማንዶ
በዘረኛ ምላስ ፥ መቃቃር ሞርዶ
እንደ መብረቅ መአት ፥ ደቦ ጎኔ ወርዶ
መታወቂያ አውጣ !!
የሚለኝ ኮበሌ
በብሄር መታደን
የፈቀደ ገዢ፥ ያወጀ ቀበሌ
ደፍቶ መጣያውን ፥
አቅም አደርጅቶ ፥ ቀብር አስተካክሎ
በስመኔ ...ለኔ
በገዛ ፈቃዱ ፥ ራሱን ወክሎ
የናቴን ልጅ....... እቴን
በነገር ጥላሸት
በበቀል ስንደዶ ፥ አይነስቧን ኩሎ
ለወንድሜ ባዳ
ለህቴ ባይተዋር ፥ አዲስ ችካል ተክሎ
ባላንጣ !!
ደመኛ !!
ቀበኛ !! ያረገኝ
ጥማዴን ሻሽጬ ፥ ክላሽ ያስታጠቀኝ
ሰላም ሰልፍ ጠርቶ ፥ ሰላሜን የነሳ
ዝጋ !!
ክፈት !! ብሎ ፥ አርጩሜ ያነሳ
መንግስትለይ የሚሸፍት.... አለቃላይ የሚነሳ
እረ'ፍ... የሚል ብርቱ !!
ማስታረቂያ ገመድ ፥ ከስጋንት ያጣ
አሻግሮ ከማየት
በደንጋዛ ግዜ ፥ መነፀር ደርቦ ፥ እራሱን የቀጣ
ፅድቅ ያላጀገነው ፥ ኩነኔ ያልፈራ
የዘመን ውልክፍክፍ ፥ ከንቱ የሰው ተራ
ይህንን ያቀፈ ፥ ቀን ነው የምፈራ !!
እናልሽ ውዴዋ....
ከገነተ ምድር ፥ የፍቅራችን ጠበል
በሰማዩ ጎማ ፥ በእግዜሩ ተጠልፎ
በድንግል መቀነት
በራማ ወገብ ላይ ፥ ቁልቁል ተሰልፎ
ለፍቅራችን አፈር
የሰላም እርጥበት ፥ ከላይ እስኪደፋ
ቀን ከሚሮጡት ጋራ
አብረን ተሯሩጠን ፥ ሞሰብ እንዳንደፋ
ወድቀን እንዳንጋጥ ፥ በርግጫ እንዳንጠፋ
ለዚህ ነው...
ቀን ቀን ላይ ፥ ስልኬን የምዘጋ ፥ ድምጤን የማጠፋ።
እኔ ያንቺ አፍቃሪ ፥
ጭን ፍለጋ መስሎሽ ፥ነይ ማታ ማለቴ
ዋልጌ ነው አትበይ ሳይገባሽ ስጋቴ
የአራዊቶቹን ቀን ፥ ጨለማን አውቄ
እለቱን ጠልቼ ፥ ፅልመቱን ታርቄ
ቢጨንቀኝ ነው እንጂ እኔስ ማስጨነቄ
ጥንታዊ አዋዋል
ኢትዮጵያዊ ቀኔን ፥ ዛሬ መናፈቄ
አንቺም ታውቂዋለሽ ፥ የቀደመውን ቀን
ጨቅላነት ሲጥመን ፥ ጉዲፈቻ ሲያቅፈን
ድክ ድክ ስንል
እስላም ክርስቲያኑ ፥ አዝሎ ሲታቀፈን
በልጅ ቡረቃችን ፥ ዝምድና ሳንፈራ
ጎረቤት በሙሉ
ጡት እያጎረሰን ፥ በለት እለት ተራ
እንኳን ሰው ሊገደል ፥ አይናችን እያየ
ምንኛ በዳዩ ፥ አፈሩን ሲቀምሰው
ነብስ ይማር !! ብለን ነው ፥ ደጁን የምናልፈው
ደስታችን ሰው አይመርጥ ሀዘኑ የጋራ
ልእለ ሰውነት ነው !! ኢትዮጵያዊ ዳራ
ለማያውቁት ማዘን
ለእግዚሀር እንግዳ ፥ ላይ እታች መባዘን
ፀዲቅ እና ዘካ ፥ ወንጌል ቁርአኑ ፥ ከቀዲም ያዘዘን።
እኔ ብቻ አይደለሁ
እንቺም ታውቂዋለሽ ፥ እንዴት እንደነበር
ወረንጦ ፍቅራችን
ከጥላቻ እሾህ ፥ ፈውሶ ያስታርቀን።
እስከዛው ድረስ ግን.....
ለምንመኘው ቀን ፥ ፍቅርን ዘውሪ
አቅምሽ እስከቻለ
ትንፋሽሽ እስካለ ፥ ሰላምን ዘምሪ
ገራ ገር ማንነት
ጥቂት ፀበል ቢያጣ ፥ ተለከፈ ብለሽ አትደናገሪ
ወዶ ማን ሰው ያብዳል ፥ በዲያቢሎስ ጋሪ ??
እኔም በፈቀደ ፥ እድሌ በሰጠኝ
እምነቴን የበላ ፥ ፍርሀቴ እስኪለቀኝ
ከወራት ግርግር ፥ እራሴን መንጭቄ
ያቻዬን አብሮነት ፥ ፍስሀ ናፍቄ
ፈረሰች ለሚለኝ !!
ወደቀች ለሚለኝ !!
የሀገር ሟርተኛ ፥ እሬት እየጋትኩኝ
ማዕልት ሳላጎል ፥ ፍቅር እየዳርኩኝ
ሰርክ ማታ ማታ እጠብቅሻለው
አንቺም መውደድ አለሽ ፥ ሀበሻም ቀልብ አለው።
እስከዛው ድረስ ግን....ሲመሽ እንገናኝ !!
#ያንቺው_አፍቃሪ !!
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
✍ #አብርሀም_ተክሉ
contact ፦ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
እና .....እንደነገርኩሽ !!
አዲስ ቀን ተስፋ ጥሎ .....ከሚሰነቅ ስንቅ
የራእይ ወቅቱ ፥ በበነጋ ሲርቅ
እስትንፋሰ እድሜ ተኮላሽቶ
ሬሳ ለቃሚ ፥ ከየ ስርፋው በዝቶ
እምነታችን መንገድ ሳተ ....አካሄዱ ተሸረፈ
መኖር መሰንበቱ ፥ ፍርሀት ሸከፈ
ሰው እንደ ባህር ዛፍ ፥ በምሳር ታጠፈ
ሀሳባችን ታጥሮ
የተስፋችን ፋኖስ አይሆኑ ተሰብሮ
በኔና ባንቺ አገር ፥ መሞት ዋዛ ቀረ
የለትተለት ዜና
ልጅ አሞራ በላው ፥ ወላጅ ተሸበረ
የተማረው ብሶ
ወደ እናት አባት ቤት ፥ ሳጥን ተሳፈረ።
አየሽ !!
በግብሬ ፣ በክፍሌ ፥ በስጋ ላደረ
ሰብነት ሸክፎ
በህላዌ ተስፋ ፥ ኑሮ ለመተረ
ከሊቅ እስከ ደቂቅ ፥ ለትልቅ ትንሹ
ለነ ንዋይ ዘገን !!
ለነ አመድ አፋሹ !!
እኩል እንደ አቅሙ ፥ ብስራተ ጥሞና
የመኝታ ደወል ፥ የህልም መዲና
ከምሽቱ በላይ ፥ ፅልመታም ጀበርና
ከሚታወጅበት...
የውድቅት ጀምበር ፥ የጨለማ ጋራ
ገላጣና ግልፁን ፥ ቀኑን ነው ምፈራ !!
ቀኑን ነው ምፈራ !!
አለሰአት ስንጦሎጦል.... ከሚያገኘኝ አውሬ
በለሊት ከሚያፍን ፥ ከቅጥረኛ ካድሬ
ሌት ከሾመው ፥ ኪስ አውላቂ ፥ ንብረተ ወዝ ከሚጋራ
ድንቡሎ ላየገኝ ፥ ደሜን የሚዘራ
ማጅራት ከሚመታ
በድቡልቡል ድንጋይ ፥ በሰላ ቆንጨራ
ከውድቅት ልክፍት ፥ ከቄሳር አሞራ
ከዚህ ....ከዚህ በላይ
ባማረበት ጀምበር ፥ በገላጣው ፀሀይ
በኔና አንቺ ሰማይ
ክልክል ባረጉብኝ ፥ በጋረዱኝ ቦታ
ነቃይ
አስነቃዩ
ባለ መሬት ጋንታ
በጠራራ ፀሀይ ፥ የሰየመው ሽፍታ
ቀለሀውን ዘግኖ
እርሳስ በሰው ገላ ፥ ቃታውን ሲፈታ
የሰፈር ተጠሪ ፥ ቀን የሰጠው ጌታ
ሮንድ የሚቃርም ፥ አለሁ ባይ ኮማንዶ
በዘረኛ ምላስ ፥ መቃቃር ሞርዶ
እንደ መብረቅ መአት ፥ ደቦ ጎኔ ወርዶ
መታወቂያ አውጣ !!
የሚለኝ ኮበሌ
በብሄር መታደን
የፈቀደ ገዢ፥ ያወጀ ቀበሌ
ደፍቶ መጣያውን ፥
አቅም አደርጅቶ ፥ ቀብር አስተካክሎ
በስመኔ ...ለኔ
በገዛ ፈቃዱ ፥ ራሱን ወክሎ
የናቴን ልጅ....... እቴን
በነገር ጥላሸት
በበቀል ስንደዶ ፥ አይነስቧን ኩሎ
ለወንድሜ ባዳ
ለህቴ ባይተዋር ፥ አዲስ ችካል ተክሎ
ባላንጣ !!
ደመኛ !!
ቀበኛ !! ያረገኝ
ጥማዴን ሻሽጬ ፥ ክላሽ ያስታጠቀኝ
ሰላም ሰልፍ ጠርቶ ፥ ሰላሜን የነሳ
ዝጋ !!
ክፈት !! ብሎ ፥ አርጩሜ ያነሳ
መንግስትለይ የሚሸፍት.... አለቃላይ የሚነሳ
እረ'ፍ... የሚል ብርቱ !!
ማስታረቂያ ገመድ ፥ ከስጋንት ያጣ
አሻግሮ ከማየት
በደንጋዛ ግዜ ፥ መነፀር ደርቦ ፥ እራሱን የቀጣ
ፅድቅ ያላጀገነው ፥ ኩነኔ ያልፈራ
የዘመን ውልክፍክፍ ፥ ከንቱ የሰው ተራ
ይህንን ያቀፈ ፥ ቀን ነው የምፈራ !!
እናልሽ ውዴዋ....
ከገነተ ምድር ፥ የፍቅራችን ጠበል
በሰማዩ ጎማ ፥ በእግዜሩ ተጠልፎ
በድንግል መቀነት
በራማ ወገብ ላይ ፥ ቁልቁል ተሰልፎ
ለፍቅራችን አፈር
የሰላም እርጥበት ፥ ከላይ እስኪደፋ
ቀን ከሚሮጡት ጋራ
አብረን ተሯሩጠን ፥ ሞሰብ እንዳንደፋ
ወድቀን እንዳንጋጥ ፥ በርግጫ እንዳንጠፋ
ለዚህ ነው...
ቀን ቀን ላይ ፥ ስልኬን የምዘጋ ፥ ድምጤን የማጠፋ።
እኔ ያንቺ አፍቃሪ ፥
ጭን ፍለጋ መስሎሽ ፥ነይ ማታ ማለቴ
ዋልጌ ነው አትበይ ሳይገባሽ ስጋቴ
የአራዊቶቹን ቀን ፥ ጨለማን አውቄ
እለቱን ጠልቼ ፥ ፅልመቱን ታርቄ
ቢጨንቀኝ ነው እንጂ እኔስ ማስጨነቄ
ጥንታዊ አዋዋል
ኢትዮጵያዊ ቀኔን ፥ ዛሬ መናፈቄ
አንቺም ታውቂዋለሽ ፥ የቀደመውን ቀን
ጨቅላነት ሲጥመን ፥ ጉዲፈቻ ሲያቅፈን
ድክ ድክ ስንል
እስላም ክርስቲያኑ ፥ አዝሎ ሲታቀፈን
በልጅ ቡረቃችን ፥ ዝምድና ሳንፈራ
ጎረቤት በሙሉ
ጡት እያጎረሰን ፥ በለት እለት ተራ
እንኳን ሰው ሊገደል ፥ አይናችን እያየ
ምንኛ በዳዩ ፥ አፈሩን ሲቀምሰው
ነብስ ይማር !! ብለን ነው ፥ ደጁን የምናልፈው
ደስታችን ሰው አይመርጥ ሀዘኑ የጋራ
ልእለ ሰውነት ነው !! ኢትዮጵያዊ ዳራ
ለማያውቁት ማዘን
ለእግዚሀር እንግዳ ፥ ላይ እታች መባዘን
ፀዲቅ እና ዘካ ፥ ወንጌል ቁርአኑ ፥ ከቀዲም ያዘዘን።
እኔ ብቻ አይደለሁ
እንቺም ታውቂዋለሽ ፥ እንዴት እንደነበር
ወረንጦ ፍቅራችን
ከጥላቻ እሾህ ፥ ፈውሶ ያስታርቀን።
እስከዛው ድረስ ግን.....
ለምንመኘው ቀን ፥ ፍቅርን ዘውሪ
አቅምሽ እስከቻለ
ትንፋሽሽ እስካለ ፥ ሰላምን ዘምሪ
ገራ ገር ማንነት
ጥቂት ፀበል ቢያጣ ፥ ተለከፈ ብለሽ አትደናገሪ
ወዶ ማን ሰው ያብዳል ፥ በዲያቢሎስ ጋሪ ??
እኔም በፈቀደ ፥ እድሌ በሰጠኝ
እምነቴን የበላ ፥ ፍርሀቴ እስኪለቀኝ
ከወራት ግርግር ፥ እራሴን መንጭቄ
ያቻዬን አብሮነት ፥ ፍስሀ ናፍቄ
ፈረሰች ለሚለኝ !!
ወደቀች ለሚለኝ !!
የሀገር ሟርተኛ ፥ እሬት እየጋትኩኝ
ማዕልት ሳላጎል ፥ ፍቅር እየዳርኩኝ
ሰርክ ማታ ማታ እጠብቅሻለው
አንቺም መውደድ አለሽ ፥ ሀበሻም ቀልብ አለው።
እስከዛው ድረስ ግን....ሲመሽ እንገናኝ !!
#ያንቺው_አፍቃሪ !!
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
✍ #አብርሀም_ተክሉ
contact ፦ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
👍1
#ያንቺው_ደቂቅ
:
:
ከቅዱስ ተራራ እንደመነጨ ኩልል ብሎ እንደጠራ
እንደ ጎበዝ ገበሬ ዘር እልፍ አላፍ የሚያፈራ
ልክ እንደ ፀደይ ሰማይ
ወለል ብሎ እንደሚታይ
ልዩ ስሜት እንከን የለሽ ያደባባይ ጥዑም ሚስጥር
ጨቅላ እፃናት የሚረዱት እሷ ለኔ አላት ፍቅር።
:
:
ጨቅላ እፃናት ሚገባቸው ሰሙም ወርቁም ማያሻማ
ለልብ ሀሴት መጠንሰሻ ሳትናገር የሚሰማ
ሁሉ ፈጥኖ የሚረዳው ግልፅ ስሜት ቀላል ቅኔ
ላዋቂው ሰው ላስተዋዩ ተሰወረ ምነው ከኔ።
:
:
የፍቅርን ታንኳ ቀዝፋ ከኔ ዘንዳ ስትመጣ
እንደ እፃን ስትቦርቅ በደስታ ጮቤ ረግጣ
ምትይዝ ምትለቀው ጠፍቷት ጥርሷ ሳይከደን አምሽቶ
ከርታታ ዓይኗ ሲስለመለም በእንቅልፍ አጀብ ተረቶ
ደረት ክንዴን ተንተርሳ ሰላም እንቅልፍ ተኝታለች
ከ አንዴም አንድ ሺህ ግዜ ፍቅሬ አንተነህ ብላኛለች።
:
:
ያ ፍም ስሜት ነበልባሉ ባይኗ ዘልቆ የሚያወራው
ቀልብ የሚስብ እጅግ ደማቅ እንደ ሩቢ የሚያበራው
ዋጋ ተመን የማይሰፍረው የከበረው ከቀይ እንቁ
የቀለም ቀንድ ከሆንኩት ሰው ምነው ከኔ መደበቁ።
:
:
ለኔ ያላት ጥልቅ ፍቅር ልብ ዘልቆ የሚያረካ
ንዋይ ከቶ የማይገዛው ባለም ሚዛን የማይለካ
መሰረቱ ወለል ጣራው የታነፀ በፅኑ ቃል
እንደሆነ እንኳን ሊቁ ደቂቁም ሰው በደንብ ያውቃል።
:
:
ሸክላ ፈራሽ ገላን ቀርቶ ነብሷን ለኔ አትሰስትም
እኔ ካለው አጠገቧ ግራዋውም አይመራትም
መታያዋም መደበቂያ እኔ እንደሆንኩ ህዝብ ያወራል
ልቤ ብቻ ከእውነታው ላይተያይ ተሰውሯል።
:
:
ቀን ከሌሊት ቢያዳምጡት በማይጠገብ አንደበቷ
እማሬውም ፍካሬውም አቻ ፍቺ የቃላቷ
እኔ ብቻ ሆኜ ሳለው የሷ ድርሰት ነፀብራቁ
ታዲያ ምነው ከእውነታው ልባም ልቤ መራራቁ።
:
:
የጭንቀቷ ማራገፊያ ወደቧ ነው ዓይኔን መሳም
አንገቴ ስር ስትወሸቅ ይሰማታል ልዩ ሰላም።
ዘቢብ ስሜት የማይነጥፍ ቀን ሲገፋ ውሎ ሲያድር
ደርሶ ሚስጥር ሆኖብኛል የሚታየው ገሀድ ፍቅር።
:
:
ሌላን ነገር ለመረዳት ቅፅበት እንኳን ማይወስድብኝ
ግልፁ ፍቅሯ ለምን ይሆን እንዲ ስውር የሆነበኝ።
ልጅ አዋቂው የተረዳው ያደባባይ ግልብ ነገር
ባለ ማዕረግ የሆንኩት ሰው እንዴት እኔ ልደናገር?
እያልኩ ሁሌ ደጋግሜ እኔው እኔን ጠይቄያለው
ቀለም ቁጥር አመክንዮ አይገልፃትም አውቄያለው።
:
:
ለካ ፍቅርን ለመረዳት ሊቅ ደቂቅን አያካትም
ስሜት ስሌት የሆነበት መቼም ቢሆን አያውቃትም።
ለኔ ካለት ፍቅር ጋራም የገባኝን ሳነፃፅር
የሰናፍጭ ቅንጣት ያክል ኢምንት ነው የሚያሳፍር።
እናም ለምን እንዳልገባኝ ደጋግሜ ሳውጠነጥን
ስሌት እንጂ ስሜት የለኝ የሷን ፍቅር የሚመጥን።
ጠቢቧ ሴት አስተዋዩዋ ረቂቋ የኔ አፍቃሪ
ለሌላ ሰው የቀለም ቀንድ ላንቺ ደቂቅ ነኝ ተማሪ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henokbirhanu
@getem
@getem
@getem
:
:
ከቅዱስ ተራራ እንደመነጨ ኩልል ብሎ እንደጠራ
እንደ ጎበዝ ገበሬ ዘር እልፍ አላፍ የሚያፈራ
ልክ እንደ ፀደይ ሰማይ
ወለል ብሎ እንደሚታይ
ልዩ ስሜት እንከን የለሽ ያደባባይ ጥዑም ሚስጥር
ጨቅላ እፃናት የሚረዱት እሷ ለኔ አላት ፍቅር።
:
:
ጨቅላ እፃናት ሚገባቸው ሰሙም ወርቁም ማያሻማ
ለልብ ሀሴት መጠንሰሻ ሳትናገር የሚሰማ
ሁሉ ፈጥኖ የሚረዳው ግልፅ ስሜት ቀላል ቅኔ
ላዋቂው ሰው ላስተዋዩ ተሰወረ ምነው ከኔ።
:
:
የፍቅርን ታንኳ ቀዝፋ ከኔ ዘንዳ ስትመጣ
እንደ እፃን ስትቦርቅ በደስታ ጮቤ ረግጣ
ምትይዝ ምትለቀው ጠፍቷት ጥርሷ ሳይከደን አምሽቶ
ከርታታ ዓይኗ ሲስለመለም በእንቅልፍ አጀብ ተረቶ
ደረት ክንዴን ተንተርሳ ሰላም እንቅልፍ ተኝታለች
ከ አንዴም አንድ ሺህ ግዜ ፍቅሬ አንተነህ ብላኛለች።
:
:
ያ ፍም ስሜት ነበልባሉ ባይኗ ዘልቆ የሚያወራው
ቀልብ የሚስብ እጅግ ደማቅ እንደ ሩቢ የሚያበራው
ዋጋ ተመን የማይሰፍረው የከበረው ከቀይ እንቁ
የቀለም ቀንድ ከሆንኩት ሰው ምነው ከኔ መደበቁ።
:
:
ለኔ ያላት ጥልቅ ፍቅር ልብ ዘልቆ የሚያረካ
ንዋይ ከቶ የማይገዛው ባለም ሚዛን የማይለካ
መሰረቱ ወለል ጣራው የታነፀ በፅኑ ቃል
እንደሆነ እንኳን ሊቁ ደቂቁም ሰው በደንብ ያውቃል።
:
:
ሸክላ ፈራሽ ገላን ቀርቶ ነብሷን ለኔ አትሰስትም
እኔ ካለው አጠገቧ ግራዋውም አይመራትም
መታያዋም መደበቂያ እኔ እንደሆንኩ ህዝብ ያወራል
ልቤ ብቻ ከእውነታው ላይተያይ ተሰውሯል።
:
:
ቀን ከሌሊት ቢያዳምጡት በማይጠገብ አንደበቷ
እማሬውም ፍካሬውም አቻ ፍቺ የቃላቷ
እኔ ብቻ ሆኜ ሳለው የሷ ድርሰት ነፀብራቁ
ታዲያ ምነው ከእውነታው ልባም ልቤ መራራቁ።
:
:
የጭንቀቷ ማራገፊያ ወደቧ ነው ዓይኔን መሳም
አንገቴ ስር ስትወሸቅ ይሰማታል ልዩ ሰላም።
ዘቢብ ስሜት የማይነጥፍ ቀን ሲገፋ ውሎ ሲያድር
ደርሶ ሚስጥር ሆኖብኛል የሚታየው ገሀድ ፍቅር።
:
:
ሌላን ነገር ለመረዳት ቅፅበት እንኳን ማይወስድብኝ
ግልፁ ፍቅሯ ለምን ይሆን እንዲ ስውር የሆነበኝ።
ልጅ አዋቂው የተረዳው ያደባባይ ግልብ ነገር
ባለ ማዕረግ የሆንኩት ሰው እንዴት እኔ ልደናገር?
እያልኩ ሁሌ ደጋግሜ እኔው እኔን ጠይቄያለው
ቀለም ቁጥር አመክንዮ አይገልፃትም አውቄያለው።
:
:
ለካ ፍቅርን ለመረዳት ሊቅ ደቂቅን አያካትም
ስሜት ስሌት የሆነበት መቼም ቢሆን አያውቃትም።
ለኔ ካለት ፍቅር ጋራም የገባኝን ሳነፃፅር
የሰናፍጭ ቅንጣት ያክል ኢምንት ነው የሚያሳፍር።
እናም ለምን እንዳልገባኝ ደጋግሜ ሳውጠነጥን
ስሌት እንጂ ስሜት የለኝ የሷን ፍቅር የሚመጥን።
ጠቢቧ ሴት አስተዋዩዋ ረቂቋ የኔ አፍቃሪ
ለሌላ ሰው የቀለም ቀንድ ላንቺ ደቂቅ ነኝ ተማሪ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henokbirhanu
@getem
@getem
@getem
👍1
#ዘመንኛ_ዘማች ❤️❤️❤️
በፊት ድሮ....ድሮ..
ከወንዶች ለይቶ ...ሀሞቱ ኮስትሮ...
ድግን መትረየሱን ..
በዝናር ሸልሞ...ከፈፉ ወድሮ
ባላንጣውን ለቅሞ ...በጥይት የቆላ
የዱር የገደሉ...የሀገሬው ጥላ
ሞት አልያ ጡረታ ...እስኪገላግለው
ግዳጁ... ግንባር ነው
ግንባሩን ...አይነሳም...ግንባር ለለመነው
ክብሩ ለሌላንጂ...
በሱ ደም ጠብታ...ለሚንዘባነነው
ብለን #እያመመን ...ስለሱ ሲነሳ
የተገላቢጦሽ
በኔና ባንች አገር...
ቅቤ ጠባሹ ነው ...የሚያገኘው ምሳ
የሞተልሽ እማ....
ሲሞት ኖሮ ኖሮ...
እንደቀደሙቱ ፥ አያገኝም ካሳ
ብንል ስናወጋ.... ከቀናቶች ቀድሞ
#ግዳጅ...
የወቶ አደር...የሚዋደቅ ቆሞ
አልያም የሀክሙ...
መድህን ለሚሆን ፥ ለሚማቅቅ ታሞ
የተተወላቸው ...አርገን ስንሟገት
ግዜ ጨከነና ... #ገደደን_መጓተት ።
ታዲያ ..ዛሬ...ዛሬ
እኔም ..አንቺም...ሌላው...
መሰንበቻው ጠፍቶን
ጭራቅ መአልት ወርዶ ...አለሙን ሲበላው
ሳልነካሽ መዋሉ ፥ እንዲሆንሽ ገዴ
ጦስ እንዳቶኝብኝ...ሰበብ ለዘመዴ
ግዳጅ ላይ ....ነን #እኛ ...
ወግ ደርሶን ለዜጋ
ቤት መሽቀን ሆኗል..
ስውር ጠላታችን...ከርሞው #የሚናጋ ።
እናም...ጓዴ....ውዴ ❤️❤️❤️
#ዘግተሽ ተቀመጪ ...
አልያ #ተሸፍነሽ... #ተጣጥበሽ ባግባቡ
እጆችሽ ለመንካት ... #ፊትሽ አካባቢ ሳይርገበገቡ
#ሳትተፋፈጊ...!!
#ሳትጨናነቂ...!!
ከሰው ሳትጠጊ ...ካምላክሽ ሳትርቂ
ምን ቢሳሳ ጎኔ......እንዴት ብትናፍቂ
ለኔም ላንቺ ሆነ
ለተቀረቅ ዜጋ ... #ግዳጁን_ጠብቂ!!!
#ያንቺው.... #ጓድ ❤️❤️❤️
#አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
✍ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
በፊት ድሮ....ድሮ..
ከወንዶች ለይቶ ...ሀሞቱ ኮስትሮ...
ድግን መትረየሱን ..
በዝናር ሸልሞ...ከፈፉ ወድሮ
ባላንጣውን ለቅሞ ...በጥይት የቆላ
የዱር የገደሉ...የሀገሬው ጥላ
ሞት አልያ ጡረታ ...እስኪገላግለው
ግዳጁ... ግንባር ነው
ግንባሩን ...አይነሳም...ግንባር ለለመነው
ክብሩ ለሌላንጂ...
በሱ ደም ጠብታ...ለሚንዘባነነው
ብለን #እያመመን ...ስለሱ ሲነሳ
የተገላቢጦሽ
በኔና ባንች አገር...
ቅቤ ጠባሹ ነው ...የሚያገኘው ምሳ
የሞተልሽ እማ....
ሲሞት ኖሮ ኖሮ...
እንደቀደሙቱ ፥ አያገኝም ካሳ
ብንል ስናወጋ.... ከቀናቶች ቀድሞ
#ግዳጅ...
የወቶ አደር...የሚዋደቅ ቆሞ
አልያም የሀክሙ...
መድህን ለሚሆን ፥ ለሚማቅቅ ታሞ
የተተወላቸው ...አርገን ስንሟገት
ግዜ ጨከነና ... #ገደደን_መጓተት ።
ታዲያ ..ዛሬ...ዛሬ
እኔም ..አንቺም...ሌላው...
መሰንበቻው ጠፍቶን
ጭራቅ መአልት ወርዶ ...አለሙን ሲበላው
ሳልነካሽ መዋሉ ፥ እንዲሆንሽ ገዴ
ጦስ እንዳቶኝብኝ...ሰበብ ለዘመዴ
ግዳጅ ላይ ....ነን #እኛ ...
ወግ ደርሶን ለዜጋ
ቤት መሽቀን ሆኗል..
ስውር ጠላታችን...ከርሞው #የሚናጋ ።
እናም...ጓዴ....ውዴ ❤️❤️❤️
#ዘግተሽ ተቀመጪ ...
አልያ #ተሸፍነሽ... #ተጣጥበሽ ባግባቡ
እጆችሽ ለመንካት ... #ፊትሽ አካባቢ ሳይርገበገቡ
#ሳትተፋፈጊ...!!
#ሳትጨናነቂ...!!
ከሰው ሳትጠጊ ...ካምላክሽ ሳትርቂ
ምን ቢሳሳ ጎኔ......እንዴት ብትናፍቂ
ለኔም ላንቺ ሆነ
ለተቀረቅ ዜጋ ... #ግዳጁን_ጠብቂ!!!
#ያንቺው.... #ጓድ ❤️❤️❤️
#አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
✍ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
#ያንቺው_ደቂቅ
:
:
ከቅዱስ ተራራ እንደመነጨ ኩልል ብሎ እንደጠራ
እንደ ጎበዝ ገበሬ ዘር እልፍ አላፍ የሚያፈራ
ልክ እንደ ፀደይ ሰማይ
ወለል ብሎ እንደሚታይ
ልዩ ስሜት እንከን የለሽ ያደባባይ ጥዑም ሚስጥር
ጨቅላ እፃናት የሚረዱት እሷ ለኔ አላት ፍቅር።
:
:
ጨቅላ እፃናት ሚገባቸው ሰሙም ወርቁም ማያሻማ
ለልብ ሀሴት መጠንሰሻ ሳትናገር የሚሰማ
ሁሉ ፈጥኖ የሚረዳው ግልፅ ስሜት ቀላል ቅኔ
ላዋቂው ሰው ላስተዋዩ ተሰወረ ምነው ከኔ።
:
:
የፍቅርን ታንኳ ቀዝፋ ከኔ ዘንዳ ስትመጣ
እንደ እፃን ስትቦርቅ በደስታ ጮቤ ረግጣ
ምትይዝ ምትለቀው ጠፍቷት ጥርሷ ሳይከደን አምሽቶ
ከርታታ ዓይኗ ሲስለመለም በእንቅልፍ አጀብ ተረቶ
ደረት ክንዴን ተንተርሳ ሰላም እንቅልፍ ተኝታለች
ከ አንዴም አንድ ሺህ ግዜ ፍቅሬ አንተነህ ብላኛለች።
:
:
ያ ፍም ስሜት ነበልባሉ ባይኗ ዘልቆ የሚያወራው
ቀልብ የሚስብ እጅግ ደማቅ እንደ ሩቢ የሚያበራው
ዋጋ ተመን የማይሰፍረው የከበረው ከቀይ እንቁ
የቀለም ቀንድ ከሆንኩት ሰው ምነው ከኔ መደበቁ።
:
:
ለኔ ያላት ጥልቅ ፍቅር ልብ ዘልቆ የሚያረካ
ንዋይ ከቶ የማይገዛው ባለም ሚዛን የማይለካ
መሰረቱ ወለል ጣራው የታነፀ በፅኑ ቃል
እንደሆነ እንኳን ሊቁ ደቂቁም ሰው በደንብ ያውቃል።
:
:
ሸክላ ፈራሽ ገላን ቀርቶ ነብሷን ለኔ አትሰስትም
እኔ ካለው አጠገቧ ግራዋውም አይመራትም
መታያዋም መደበቂያ እኔ እንደሆንኩ ህዝብ ያወራል
ልቤ ብቻ ከእውነታው ላይተያይ ተሰውሯል።
:
:
ቀን ከሌሊት ቢያዳምጡት በማይጠገብ አንደበቷ
እማሬውም ፍካሬውም አቻ ፍቺ የቃላቷ
እኔ ብቻ ሆኜ ሳለው የሷ ድርሰት ነፀብራቁ
ታዲያ ምነው ከእውነታው ልባም ልቤ መራራቁ።
:
:
የጭንቀቷ ማራገፊያ ወደቧ ነው ዓይኔን መሳም
አንገቴ ስር ስትወሸቅ ይሰማታል ልዩ ሰላም።
ዘቢብ ስሜት የማይነጥፍ ቀን ሲገፋ ውሎ ሲያድር
ደርሶ ሚስጥር ሆኖብኛል የሚታየው ገሀድ ፍቅር።
:
:
ሌላን ነገር ለመረዳት ቅፅበት እንኳን ማይወስድብኝ
ግልፁ ፍቅሯ ለምን ይሆን እንዲ ስውር የሆነበኝ።
ልጅ አዋቂው የተረዳው ያደባባይ ግልብ ነገር
ባለ ማዕረግ የሆንኩት ሰው እንዴት እኔ ልደናገር?
እያልኩ ሁሌ ደጋግሜ እኔው እኔን ጠይቄያለው
ቀለም ቁጥር አመክንዮ አይገልፃትም አውቄያለው።
:
:
ለካ ፍቅርን ለመረዳት ሊቅ ደቂቅን አያካትም
ስሜት ስሌት የሆነበት መቼም ቢሆን አያውቃትም።
ለኔ ካለት ፍቅር ጋራም የገባኝን ሳነፃፅር
የሰናፍጭ ቅንጣት ያክል ኢምንት ነው የሚያሳፍር።
እናም ለምን እንዳልገባኝ ደጋግሜ ሳውጠነጥን
ስሌት እንጂ ስሜት የለኝ የሷን ፍቅር የሚመጥን።
ጠቢቧ ሴት አስተዋዩዋ ረቂቋ የኔ አፍቃሪ
ለሌላ ሰው የቀለም ቀንድ ላንቺ ደቂቅ ነኝ ተማሪ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henockb
@getem
@getem
@getem
:
:
ከቅዱስ ተራራ እንደመነጨ ኩልል ብሎ እንደጠራ
እንደ ጎበዝ ገበሬ ዘር እልፍ አላፍ የሚያፈራ
ልክ እንደ ፀደይ ሰማይ
ወለል ብሎ እንደሚታይ
ልዩ ስሜት እንከን የለሽ ያደባባይ ጥዑም ሚስጥር
ጨቅላ እፃናት የሚረዱት እሷ ለኔ አላት ፍቅር።
:
:
ጨቅላ እፃናት ሚገባቸው ሰሙም ወርቁም ማያሻማ
ለልብ ሀሴት መጠንሰሻ ሳትናገር የሚሰማ
ሁሉ ፈጥኖ የሚረዳው ግልፅ ስሜት ቀላል ቅኔ
ላዋቂው ሰው ላስተዋዩ ተሰወረ ምነው ከኔ።
:
:
የፍቅርን ታንኳ ቀዝፋ ከኔ ዘንዳ ስትመጣ
እንደ እፃን ስትቦርቅ በደስታ ጮቤ ረግጣ
ምትይዝ ምትለቀው ጠፍቷት ጥርሷ ሳይከደን አምሽቶ
ከርታታ ዓይኗ ሲስለመለም በእንቅልፍ አጀብ ተረቶ
ደረት ክንዴን ተንተርሳ ሰላም እንቅልፍ ተኝታለች
ከ አንዴም አንድ ሺህ ግዜ ፍቅሬ አንተነህ ብላኛለች።
:
:
ያ ፍም ስሜት ነበልባሉ ባይኗ ዘልቆ የሚያወራው
ቀልብ የሚስብ እጅግ ደማቅ እንደ ሩቢ የሚያበራው
ዋጋ ተመን የማይሰፍረው የከበረው ከቀይ እንቁ
የቀለም ቀንድ ከሆንኩት ሰው ምነው ከኔ መደበቁ።
:
:
ለኔ ያላት ጥልቅ ፍቅር ልብ ዘልቆ የሚያረካ
ንዋይ ከቶ የማይገዛው ባለም ሚዛን የማይለካ
መሰረቱ ወለል ጣራው የታነፀ በፅኑ ቃል
እንደሆነ እንኳን ሊቁ ደቂቁም ሰው በደንብ ያውቃል።
:
:
ሸክላ ፈራሽ ገላን ቀርቶ ነብሷን ለኔ አትሰስትም
እኔ ካለው አጠገቧ ግራዋውም አይመራትም
መታያዋም መደበቂያ እኔ እንደሆንኩ ህዝብ ያወራል
ልቤ ብቻ ከእውነታው ላይተያይ ተሰውሯል።
:
:
ቀን ከሌሊት ቢያዳምጡት በማይጠገብ አንደበቷ
እማሬውም ፍካሬውም አቻ ፍቺ የቃላቷ
እኔ ብቻ ሆኜ ሳለው የሷ ድርሰት ነፀብራቁ
ታዲያ ምነው ከእውነታው ልባም ልቤ መራራቁ።
:
:
የጭንቀቷ ማራገፊያ ወደቧ ነው ዓይኔን መሳም
አንገቴ ስር ስትወሸቅ ይሰማታል ልዩ ሰላም።
ዘቢብ ስሜት የማይነጥፍ ቀን ሲገፋ ውሎ ሲያድር
ደርሶ ሚስጥር ሆኖብኛል የሚታየው ገሀድ ፍቅር።
:
:
ሌላን ነገር ለመረዳት ቅፅበት እንኳን ማይወስድብኝ
ግልፁ ፍቅሯ ለምን ይሆን እንዲ ስውር የሆነበኝ።
ልጅ አዋቂው የተረዳው ያደባባይ ግልብ ነገር
ባለ ማዕረግ የሆንኩት ሰው እንዴት እኔ ልደናገር?
እያልኩ ሁሌ ደጋግሜ እኔው እኔን ጠይቄያለው
ቀለም ቁጥር አመክንዮ አይገልፃትም አውቄያለው።
:
:
ለካ ፍቅርን ለመረዳት ሊቅ ደቂቅን አያካትም
ስሜት ስሌት የሆነበት መቼም ቢሆን አያውቃትም።
ለኔ ካለት ፍቅር ጋራም የገባኝን ሳነፃፅር
የሰናፍጭ ቅንጣት ያክል ኢምንት ነው የሚያሳፍር።
እናም ለምን እንዳልገባኝ ደጋግሜ ሳውጠነጥን
ስሌት እንጂ ስሜት የለኝ የሷን ፍቅር የሚመጥን።
ጠቢቧ ሴት አስተዋዩዋ ረቂቋ የኔ አፍቃሪ
ለሌላ ሰው የቀለም ቀንድ ላንቺ ደቂቅ ነኝ ተማሪ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henockb
@getem
@getem
@getem
👍6🔥1
#ያንቺው_ደቂቅ
:
:
ከቅዱስ ተራራ እንደመነጨ ኩልል ብሎ እንደጠራ፤
እንደ ጎበዝ ገበሬ ዘር እልፍ አላፍት የሚያፈራ፤
ልክ እንደ ፀደይ ሰማይ፤
ወለል ብሎ እንደሚታይ፤
ልዩ ስሜት እንከን የለሽ ያደባባይ ጥዑም ሚስጥር፤
ጨቅላ እፃናት የሚረዱት እሷ ለኔ አላት ፍቅር።
:
:
ጨቅላ እፃናት ሚገባቸው ሰሙም ወርቁም ማያሻማ፤
ለልብ ሀሴት መጠንሰሻ ሳትናገር የሚሰማ፤
ሁሉ ፈጥኖ የሚረዳው ግልፅ ስሜት ቀላል ቅኔ፤
ላዋቂው ሰው ላስተዋዩ ተሰወረ ምነው ከኔ።
:
:
የፍቅርን ታንኳ ቀዝፋ ከኔ ዘንዳ ስትመጣ፤
እንደ እፃን ስትቦርቅ በደስታ ጮቤ ረግጣ፤
ምትይዝ ምትለቀው ጠፍቷት ጥርሷ ሳይከደን አምሽቶ፤
ከርታታ ዓይኗ ሲስለመለም በእንቅልፍ አጀብ ተረቶ፤
ደረት ክንዴን ተንተርሳ ሰላም እንቅልፍ ተኝታለች፤
ከ አንዴም አንድ ሺህ ግዜ ፍቅሬ አንተነህ ብላኛለች።
:
:
ያ ፍም ስሜት ነበልባሉ ባይኗ ዘልቆ የሚያወራው፤
ቀልብ የሚስብ እጅግ ደማቅ እንደ ሩቢ የሚያበራው፤
ዋጋ ተመን የማይሰፍረው የከበረው ከቀይ እንቁ፤
የቀለም ቀንድ ከሆንኩት ሰው ምነው ከኔ መደበቁ?
:
:
ለኔ ያላት ጥልቅ ፍቅር ልብ ዘልቆ የሚያረካ፤
ንዋይ ከቶ የማይገዛው ባለም ሚዛን የማይለካ፤
መሰረቱ ወለል ጣራው የታነፀ በፅኑ ቃል፤
እንደሆነ እንኳን ሊቁ ደቂቁም ሰው በደንብ ያውቃል።
:
:
ሸክላ ፈራሽ ገላን ቀርቶ ነብሷን ለኔ አትሰስትም፤
እኔ ካለው አጠገቧ ግራዋውም አይመራትም፤
መታያዋም መደበቂያ እኔ እንደሆንኩ ህዝብ ያወራል፤
ልቤ ብቻ ከእውነታው ላይተያይ ተሰውሯል።
:
:
ቀን ከሌሊት ቢያዳምጡት በማይጠገብ አንደበቷ፤
እማሬውም ፍካሬውም አቻ ፍቺ የቃላቷ፤
እኔ ብቻ ሆኜ ሳለው የሷ ድርሰት ነፀብራቁ፤
ታዲያ ምነው ከእውነታው ልባም ልቤ መራራቁ።
:
:
የጭንቀቷ ማራገፊያ ወደቧ ነው ዓይኔን መሳም፤
አንገቴ ስር ስትወሸቅ ይሰማታል ልዩ ሰላም፤
ዘቢብ ስሜት የማይነጥፍ ቀን ሲገፋ ውሎ ሲያድር፤
ደርሶ ሚስጥር ሆኖብኛል የሚታየው ገሀድ ፍቅር።
:
:
ሌላን ነገር ለመረዳት ቅፅበት እንኳን ማይወስድብኝ፤
ግልፁ ፍቅሯ ለምን ይሆን እንዲ ስውር የሆነበኝ?
ልጅ አዋቂው የተረዳው ያደባባይ ግልብ ነገር፤
ባለ ማዕረግ የሆንኩት ሰው እንዴት እኔ ልደናገር?
እያልኩ ሁሌ ደጋግሜ እኔው እኔን ጠይቄያለው፤
ቀለም ቁጥር አመክንዮ አይገልፃትም አውቄያለው።
:
:
ለካ ፍቅርን ለመረዳት ሊቅ ደቂቅን አያካትም፤
ስሜት ስሌት የሆነበት መቼም ቢሆን አያውቃትም።
ለኔ ካለት ፍቅር ጋራም የገባኝን ሳነፃፅር፤
የሰናፍጭ ቅንጣት ያክል ኢምንት ነው የሚያሳፍር።
እናም ለምን እንዳልገባኝ ደጋግሜ ሳውጠነጥን፤
ስሌት እንጂ ስሜት የለኝ የሷን ፍቅር የሚመጥን።
ጠቢቧ ሴት አስተዋዩዋ ረቂቋ የኔ አፍቃሪ፤
ለሌላ ሰው የቀለም ቀንድ ላንቺ ደቂቅ ነኝ ተማሪ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@getem
@getem
@getem
:
:
ከቅዱስ ተራራ እንደመነጨ ኩልል ብሎ እንደጠራ፤
እንደ ጎበዝ ገበሬ ዘር እልፍ አላፍት የሚያፈራ፤
ልክ እንደ ፀደይ ሰማይ፤
ወለል ብሎ እንደሚታይ፤
ልዩ ስሜት እንከን የለሽ ያደባባይ ጥዑም ሚስጥር፤
ጨቅላ እፃናት የሚረዱት እሷ ለኔ አላት ፍቅር።
:
:
ጨቅላ እፃናት ሚገባቸው ሰሙም ወርቁም ማያሻማ፤
ለልብ ሀሴት መጠንሰሻ ሳትናገር የሚሰማ፤
ሁሉ ፈጥኖ የሚረዳው ግልፅ ስሜት ቀላል ቅኔ፤
ላዋቂው ሰው ላስተዋዩ ተሰወረ ምነው ከኔ።
:
:
የፍቅርን ታንኳ ቀዝፋ ከኔ ዘንዳ ስትመጣ፤
እንደ እፃን ስትቦርቅ በደስታ ጮቤ ረግጣ፤
ምትይዝ ምትለቀው ጠፍቷት ጥርሷ ሳይከደን አምሽቶ፤
ከርታታ ዓይኗ ሲስለመለም በእንቅልፍ አጀብ ተረቶ፤
ደረት ክንዴን ተንተርሳ ሰላም እንቅልፍ ተኝታለች፤
ከ አንዴም አንድ ሺህ ግዜ ፍቅሬ አንተነህ ብላኛለች።
:
:
ያ ፍም ስሜት ነበልባሉ ባይኗ ዘልቆ የሚያወራው፤
ቀልብ የሚስብ እጅግ ደማቅ እንደ ሩቢ የሚያበራው፤
ዋጋ ተመን የማይሰፍረው የከበረው ከቀይ እንቁ፤
የቀለም ቀንድ ከሆንኩት ሰው ምነው ከኔ መደበቁ?
:
:
ለኔ ያላት ጥልቅ ፍቅር ልብ ዘልቆ የሚያረካ፤
ንዋይ ከቶ የማይገዛው ባለም ሚዛን የማይለካ፤
መሰረቱ ወለል ጣራው የታነፀ በፅኑ ቃል፤
እንደሆነ እንኳን ሊቁ ደቂቁም ሰው በደንብ ያውቃል።
:
:
ሸክላ ፈራሽ ገላን ቀርቶ ነብሷን ለኔ አትሰስትም፤
እኔ ካለው አጠገቧ ግራዋውም አይመራትም፤
መታያዋም መደበቂያ እኔ እንደሆንኩ ህዝብ ያወራል፤
ልቤ ብቻ ከእውነታው ላይተያይ ተሰውሯል።
:
:
ቀን ከሌሊት ቢያዳምጡት በማይጠገብ አንደበቷ፤
እማሬውም ፍካሬውም አቻ ፍቺ የቃላቷ፤
እኔ ብቻ ሆኜ ሳለው የሷ ድርሰት ነፀብራቁ፤
ታዲያ ምነው ከእውነታው ልባም ልቤ መራራቁ።
:
:
የጭንቀቷ ማራገፊያ ወደቧ ነው ዓይኔን መሳም፤
አንገቴ ስር ስትወሸቅ ይሰማታል ልዩ ሰላም፤
ዘቢብ ስሜት የማይነጥፍ ቀን ሲገፋ ውሎ ሲያድር፤
ደርሶ ሚስጥር ሆኖብኛል የሚታየው ገሀድ ፍቅር።
:
:
ሌላን ነገር ለመረዳት ቅፅበት እንኳን ማይወስድብኝ፤
ግልፁ ፍቅሯ ለምን ይሆን እንዲ ስውር የሆነበኝ?
ልጅ አዋቂው የተረዳው ያደባባይ ግልብ ነገር፤
ባለ ማዕረግ የሆንኩት ሰው እንዴት እኔ ልደናገር?
እያልኩ ሁሌ ደጋግሜ እኔው እኔን ጠይቄያለው፤
ቀለም ቁጥር አመክንዮ አይገልፃትም አውቄያለው።
:
:
ለካ ፍቅርን ለመረዳት ሊቅ ደቂቅን አያካትም፤
ስሜት ስሌት የሆነበት መቼም ቢሆን አያውቃትም።
ለኔ ካለት ፍቅር ጋራም የገባኝን ሳነፃፅር፤
የሰናፍጭ ቅንጣት ያክል ኢምንት ነው የሚያሳፍር።
እናም ለምን እንዳልገባኝ ደጋግሜ ሳውጠነጥን፤
ስሌት እንጂ ስሜት የለኝ የሷን ፍቅር የሚመጥን።
ጠቢቧ ሴት አስተዋዩዋ ረቂቋ የኔ አፍቃሪ፤
ለሌላ ሰው የቀለም ቀንድ ላንቺ ደቂቅ ነኝ ተማሪ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@getem
@getem
@getem
❤26👍15🔥5