ተነስ !
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።
ወንድሜ ሆይ !
ይኸው እንዳየሁህ ፥ የጫማህ መርገጫ
ምላስ ሆኖ ሳስቷል
አካልህ ኮስምኖ ...
ኑሮ የደበተው ፥ አይንህ እንባን አዝሏል ።
#ከዚህ ሁሉ ጀርባ
ቅዱስ ፍጥረትህን ፥ ሰውነትህን ሽሮ
በብሄር ቱማታ ፥ በቃሉ ጠፍሮ
በል ... በል በሚል ድንፋት ፥ በፌስቡክ ፉከራ
ግለሰብ አያለሁ !
ከዳር ተቀምጦ ፥ ስሙን የሚሰራ ።
።።።።።።
#አያለሁ ከጀርባህ !
ባንተው ተጠልሎ ፥ ተስፋ ጓዙን ጥሎ
አንጓች ቅቤ አዝሎ ...
ዘር እየቆጠረ ፥ ዘመድ እያስጠቃ
ባንተ ጉስቁልና ፥ ኪሱን ያጠረቃ
።።።።።።
#አያለሁ ከጀርባህ !
ደጀን ሁነኝ ብሎ ፥ ደረት የለመነ
አንተ ስትቆስል ፥ እርሱ የጀገነ
የጥል እርሾ ቅመም ፥ ፅዋውን ጠማቂ
ባንተ እሪታ ጩኸት ፥ ከጠርዝ ቆሞ ሳቂ
።።።።።
#አያለሁ አንድ ሰው !
አያለሁ ታዋቂ ....
ውብ ቃላት አርቃቂ
የሰይጣን ውልድ ጭፍራ
መሬቱ ልብህ ላይ ስሜት የሚዘራ
በል ተዋጋ 'ሚልህ
መንገድ ዝጋ 'ሚልህ
ከእህትህ ድርሻ ፥ ቆርሰህ ጉረስ 'ሚልህ
የህሊና ስንኩል!
ዛሬም ይታየኛል.. .
በሞትህ ሀውልት ገፅ ፥ ስሙን ቀርፆ ሲውል ።
።።።።
#እንግዲያስ ወንድሜ
የእናቴ ልጅ ደሜ ...
ፌዝ ቧልቱ አይጣለን ፥ በዚህች አጭር ዕድሜ
እኔም ቁርሾ ልፋቅ ፥ ከጥል ቀን ቀድሜ
ቀሰቀስሁህ ተነስ ፥ ማሸለቡ ይብቃን
የወጣት ደም ፍላት ፥ ስሜት እንዳይገዛን
በክልል ሲያጠቡን.. .
ሀገር ሆነን ሰፍተን ፥ ከመሞት እንዳን ።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።
ወንድሜ ሆይ !
ይኸው እንዳየሁህ ፥ የጫማህ መርገጫ
ምላስ ሆኖ ሳስቷል
አካልህ ኮስምኖ ...
ኑሮ የደበተው ፥ አይንህ እንባን አዝሏል ።
#ከዚህ ሁሉ ጀርባ
ቅዱስ ፍጥረትህን ፥ ሰውነትህን ሽሮ
በብሄር ቱማታ ፥ በቃሉ ጠፍሮ
በል ... በል በሚል ድንፋት ፥ በፌስቡክ ፉከራ
ግለሰብ አያለሁ !
ከዳር ተቀምጦ ፥ ስሙን የሚሰራ ።
።።።።።።
#አያለሁ ከጀርባህ !
ባንተው ተጠልሎ ፥ ተስፋ ጓዙን ጥሎ
አንጓች ቅቤ አዝሎ ...
ዘር እየቆጠረ ፥ ዘመድ እያስጠቃ
ባንተ ጉስቁልና ፥ ኪሱን ያጠረቃ
።።።።።።
#አያለሁ ከጀርባህ !
ደጀን ሁነኝ ብሎ ፥ ደረት የለመነ
አንተ ስትቆስል ፥ እርሱ የጀገነ
የጥል እርሾ ቅመም ፥ ፅዋውን ጠማቂ
ባንተ እሪታ ጩኸት ፥ ከጠርዝ ቆሞ ሳቂ
።።።።።
#አያለሁ አንድ ሰው !
አያለሁ ታዋቂ ....
ውብ ቃላት አርቃቂ
የሰይጣን ውልድ ጭፍራ
መሬቱ ልብህ ላይ ስሜት የሚዘራ
በል ተዋጋ 'ሚልህ
መንገድ ዝጋ 'ሚልህ
ከእህትህ ድርሻ ፥ ቆርሰህ ጉረስ 'ሚልህ
የህሊና ስንኩል!
ዛሬም ይታየኛል.. .
በሞትህ ሀውልት ገፅ ፥ ስሙን ቀርፆ ሲውል ።
።።።።
#እንግዲያስ ወንድሜ
የእናቴ ልጅ ደሜ ...
ፌዝ ቧልቱ አይጣለን ፥ በዚህች አጭር ዕድሜ
እኔም ቁርሾ ልፋቅ ፥ ከጥል ቀን ቀድሜ
ቀሰቀስሁህ ተነስ ፥ ማሸለቡ ይብቃን
የወጣት ደም ፍላት ፥ ስሜት እንዳይገዛን
በክልል ሲያጠቡን.. .
ሀገር ሆነን ሰፍተን ፥ ከመሞት እንዳን ።
@getem
@getem
@getem
ለውብ ቀን!
💚
#ለምን ዛሬ ውብ ቀናችንን ለየት አናረገውም.....#ቅኔ ያለው ትውልድ የሚል እዚሁ ቴሌግራም መንደር የሚገኝ ቻናል እና የመወያያ ግሩፕ አለ .....ሁለቱም ጋር ብትገቡ በብዙ ታተርፋላቹ ነብስ ያላቸው ሀሳቦች ይነሱበታል.....እናም ለውይይት በሚነሱ ሀሳቦች ላይ እኔም መሳተፍ እፈልጋለው ፣ እኔም የዚህ ቤተሰብ አባል መሆን እሻለው ፣ ማን እንደዚህ አይነት እድል ገጥሞት እንቢ ይላል .....ይኼ አይደለም ወይ የተጠፋው የምትሉ ከሆነ ደስ ደስ እያላቸው ያስተናግዳሉ።
# የናንተን ምርጥ ምርጥ ሀሳቦች ይፈልጋሉ እና አካፍሏቸው።
#ከዚህ በታች ወደ ቴሌግራም ቤቱ የሚያደርሰውን ሊንክ ጀባ እላለሁኝ....መሄድና መግባት ለፈለገ ቤቱ ሁሌም ክፍት ነው.....
ውብ ቀን!💚
👇👇👇👇
💚
#ለምን ዛሬ ውብ ቀናችንን ለየት አናረገውም.....#ቅኔ ያለው ትውልድ የሚል እዚሁ ቴሌግራም መንደር የሚገኝ ቻናል እና የመወያያ ግሩፕ አለ .....ሁለቱም ጋር ብትገቡ በብዙ ታተርፋላቹ ነብስ ያላቸው ሀሳቦች ይነሱበታል.....እናም ለውይይት በሚነሱ ሀሳቦች ላይ እኔም መሳተፍ እፈልጋለው ፣ እኔም የዚህ ቤተሰብ አባል መሆን እሻለው ፣ ማን እንደዚህ አይነት እድል ገጥሞት እንቢ ይላል .....ይኼ አይደለም ወይ የተጠፋው የምትሉ ከሆነ ደስ ደስ እያላቸው ያስተናግዳሉ።
# የናንተን ምርጥ ምርጥ ሀሳቦች ይፈልጋሉ እና አካፍሏቸው።
#ከዚህ በታች ወደ ቴሌግራም ቤቱ የሚያደርሰውን ሊንክ ጀባ እላለሁኝ....መሄድና መግባት ለፈለገ ቤቱ ሁሌም ክፍት ነው.....
ውብ ቀን!💚
👇👇👇👇
ጀመኣው ነገ ቅዳሚትም አይደለች..❤ እና ለቅዳሚት ድምቀት "ሰው ፍቅር ናፍቆት" የተሰኘ ቅዳሜን የመሰለ የግጥም መድብል ወጥቷል ለግጥም አፍቃሪያን......#መፅሐፉ በጃፋር መፅሐፍት መደብር እና በኤዞፕ (ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ወረድ ብላቹ ይገኛል )....
#ከዚህ በታች የወሎው አድባር ሙሀመድ ሙፍቲ ስለ ፀሐፊው የከተበው አለው...እንካቹ...
ግጥምን ቅኔን እንዲሁ በያዝ ለቀቅ እንደቧልት የሚገጠም የሚዘረፍ ሳይሆን ፣ ለአፈር ገላችን ምንዳ (በረካ) ይሆነን ዘንድ ለነፍሳችን በነፍሳችን ቀለም የሚከተብ የህወይት ግብራችን ነው ። ስንፈቅድ ሲሻን የምናነሳው ፣ ሳይሻን የምንተወው አንድ የፊዚካል እንቅስቃሴ ዘርፍ እይደለም ። ይልቅ ጌትዬው ደጅ የሚፈስ የፍቅር ወንጌል ፣ በሓድራ እየከነፉ በሙሃባ እየሰገሩ ተውበትና ንስሃን አዝለው የሚንዘምትበት ላይታገድ እስካለይኛው ቀዬ የሚዘረጋ ዘላለማዊ ኪታብ ነው ። ለዚህም ከፍታ ባለቅኔው ሙሉጌታ ተስፋዬ ያበክራል ።
.
እኔም ቅኔ ልዝረፍ ... እስኪ ይመርብኝ
ያፈር ግብር አስራት ... የሥጋ‘ዳ አለብኝ...
.
ገጣሚ በሀይማኖት አጥር ሳለ ፣ ግን ሰውነትን ፍቅር ትተው የሀይማኖት ንፅፅር ተጠምደው የሰውን ልብ ገመና ከሚያዜሙ ከንቱ ሰባኪዎች የማይወረስ ፣ ለጀሊሉ ያደረውን ልብህን ነፍስህን ገፍተው በወሎህና ባዳርህ የሚተምኑ ፣ የጀነትን ቁልፍ በእጃቸው ያለ ይመስል ጀነትን እና ጀሀነምን ከሚተምኑ ቀድሞ ቀመስ ዳኢዎች ሸውራራ ተፍሲር የማይማርከው ነው ። ገጣሚው ገና በጥንስሱ ኪነትን ለፍቅር በፍቅር ብሎ በመውላናው የታደለች ናት ። ነፍሱእንደ ቧልት እንዲሁ ስሜቱን ሊሸነግለው አይቻለውም ። ብርቱ የነፍስ ጥሪ ጥበበ ደወል አድያው ከላይ ነውና ።
ይልቁን ያየውን ሀቅ ላያፈገፍግ በቀለሙ ሊገስፅ ይታገላል ። ለሌላው ሊጠቁም በቅኔ መሰላል ይሻገራል ።
ቅንነት ነው ቅኔው ፣ ቅንነት ነው ቀኑ ፣ ሰው ቂም ውሎ ካሳደረ ጀባ ያሉት አወል ቡና እንኳን አይሰባም ። ቢመርቅ ላያደርስ ፣ ቢለግስ በረከት ላይገመጥመው ፣ በሊግስ እንኳ ቂም ካለ በውስጡ እንኳም ለእሱ ለተመፅዋቹም አይበረክትለትም ። ባብጀው የሀጃ ሰታቴ ምን ቢያንፈቀፍቁ የሻቱት ላይበስል አሻዋ ነው የጣዱት ሙራድ ። የከፈተው ላይከድን አድሮ ገርበብ ነው ። ኢማን እንደዋዛ አሉ ... ወዲህም ለውስጣችን ለነፍስ ተክህኖ ( ካባ ) እንጂ ለፈራሽ ገላ መልበሱ ክንቱ ነው ። ይህን የሰውነት ድካ አይያ ሙሌም ሲለኩሰው እንዲህ ነው ። አዎና « ቁርሾ ያዘለች ነፍስ ቅኔ አይቀናትም ። »
.
ጠኔ ሲያጥመነምን ...
መገን ይሄ ቅኔ ... በምን ይገለጣል
ስትሹ " እሹ ! " እያለ የወዳጃ አበጋር ...
ቁርሾ ካንቀራጨ ... መች ሓጃ ያወጣል ።
.
.
.
ሊቀ ካህናቱ ... በከንቱ ውዕቱ ፣
መርተው ሲነርቱ ...
በብር መቋሚያ ፣ በወርቅ ፅናጵል
ደበሎ ለብሼ ...
ሚስጥረ ህቡኀን ድጎን ብቀጵል..
" በህግ አምላክ ብሎ !" ብሎ ማን ሊያቆመኝ ኑሯል?
ለራሱ ሊወናኝ ... ዘርፎ ቢቀኝ እንጂ
በነብሱ " ተክህኖ " ማን ማንን አስምሯል !
.
.
----
እናም ይህንን አይነት ሀቅ ከብላቴናው ገጣሚ ዳግም ደጀኔ (ሔራን) የፊታችን አርብና ቅዳሜ ገደማ ከምትወጣው ( ሰው - ፍቅር - ናፍቆት ) አድስ የግጥም መድብል ላይ አየናትና ነው ብዙ ማለቴ ።
.
የለምን ጥያቄ
።።
የያመነው ኪዳን
ባልታመነ ካህን በአማኝ ነኝ ልሳን ፣
በአርጅቷል ማዘዣ
ሰርክ እየታደሰ አውደ ‘ዳሱ ድርሳን ።
እውነት ቅቡ ሃሰን
ገዝፎ ለመታየት የክፍ እርካብ ሽቶ ፣
ከመሆን ዘመን ላይ
ወደ ቅጥፈት ደጃፍ
ሀቅ ይንከባለላል በመምሰል ተገፍቶ ።
በገፊዎች ግፊት
የእውነት እውነት ወዙ ሲገረጣ ፣
እውነት አምላኪ ሰው
በሀሰት ገዢዎች ሰውነቱን አጣ ።
.
ታዳ እንድህ እንዳለ ...
ተገፊው ይሄ ሰው ፣
ለምን ነው እምገፋ
ብሎ ለመጠየቅ ለ ማለት ሲጀምር ፣
ዝምበል አትናገር
የሚል መልስ ያገኛል ከገፊው መምህር ።
ለምን ሲል ለእንደዚህ
እንደት ሲል እንደዚህ
ምድራዊ መገፋት
አየለማዊ ልፋት
ሩህን ቢያርዳት የልፋቱ ቀንበር ፣
ዝም ብለህ አትናገር
የፈተነህ ጌታ
አንተን ሊመርጥ ነው ለሰማዩ መምበር ።
ይህ ማለት ምንድን ነው ...
.
.
.
.
ታዳ ልክ እንደዚህ
አማኝ አለማኙም
እውነት ለመቀርጠፍ ቅጥፈት ከታቀፈ ፣
አምንም ያለ ሰው
በአማኞች ህብረት ለምን ተነቀፈ ።
.
.
.
.
-----
( ሰው ፍቅር ናፍቆት )ገፅ 83
ሰኞም ትወጣለችና እንሸምታት ።
---
በመጨረሻም.
--
በሰው ልጅ የሕይወት ሂደት ውስጥ ጥበብ ወይም የእርሱ ዘርፍ ውስጥ የሆነው ልክ እንደ ግጥም ቋሚ ቅርሶች ሁሉ የማህበረሰቡን ወግ ፣ ልማድ ፣ ባህል ... ወ ዘ ተ ይዞ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ ይኖራል ። እስልምናም ለዚህ የጥበብ ዘርፍ የራሱ የሆነ አስተዋፅኦ አለው ። ከረሱል አሚን ( ሶ ዐ ወ ) መላክ በስተፊት አንስቶ ድንቅ ገጣሚያን በአረቢያን ምድር ነበሩ ። ግጥም እጅግ ትልቅ ሀይል እንደነበረው የተለያዪ የታሪክ መዛግብት ይናገራሉ ። እጅግ ያማረና ውብ የሆኑ ግጥሞችን ያስነበበ ደግሞ ለክብሩ ሲባል በካዕባ ይንጠለጠል እንደነበር ታሪክ ያስረዳል ። ሲለኝ በአደብ አደምጨዋለሁ " ኪታቡን " የግጥም መፅሓፍ መግቢያ ።
-
አሁን አሁን የግጥም መፀሐፍ በየወሩ ቢወጡም ሳለ ፣ በእርቃን የታጀበ ክሊፕ ብቻ ሰርተው " ዘፈን ነው አደምጡ " ብለው ጆሯችንን እንደሚቀልዱበት ሙዚቃ ተብዬ ግርግር አይደለም ። አዎ አንድ የግጥም መፀሐፍ ሲወጣ ተነቦ እንደገጣሚው አቅምና መድረስ እንጂ የሚለካው ከሌሎች ከፍ ካሉ ስራዎች ጋር አይወደዳደርም ። ሲጀመር ያን መፀሀፍ ይጣፍ አይጣፍጥ መች ገዝተን አንብበንው ነው ። ይህ ትልቅ በሽታ ነው ። ስም ያላቸውን ገጣሚያን ግን ሳናነበው ለማድነቅ መሯሯጡ ነው አመላችን ። በተዋቂ ስም ለመድመቅ ከጀርባ ከፊት ሽፋን መለጠፉ ክፉ በሽታ ነው ። በዛው ልክም ሳያነቡ የማይመሰክሩ ሸጋ አንባቢም አሉ ። አዎ ለነፍስ ወደ ነፍስ የነፍስን ስራ የሚያደርሱ የሚጀቡ እንደነ Shalom Desalegn Fuddy Man Cj አይነትም አይነት የለሽ አሉ ።
.
እንጂማ ...
የነ YadEl Tizazu -- ( ሕልም ብሀርን አድሜ )
የነ ዲበኩሉ ጌታ --( የምድር ዘላለም )
የነ Andualem Mesfin ... ( ሰበከት )
ወ
ዘ
ተ
ሸጋ የግጥም መፀሓፍ ተነቦ ሊገን ሊከበር በተገባው ነበር ። ግን ስንገዛ ፣ ስንጋብዝ አልታየንም ።
---
ምን ማለት ፈልጌ ነው -- እንግዛ እናንብብና ይውደቅ ። " አንባቢ ከብዶታል " አንበል መጀመሪያ እናድርስው ። #ኸላስ
---
ሸጋ የቅዳሚት መዳረሻ ምሽት❤
@getem
@getem
@Nagayta
#ከዚህ በታች የወሎው አድባር ሙሀመድ ሙፍቲ ስለ ፀሐፊው የከተበው አለው...እንካቹ...
ግጥምን ቅኔን እንዲሁ በያዝ ለቀቅ እንደቧልት የሚገጠም የሚዘረፍ ሳይሆን ፣ ለአፈር ገላችን ምንዳ (በረካ) ይሆነን ዘንድ ለነፍሳችን በነፍሳችን ቀለም የሚከተብ የህወይት ግብራችን ነው ። ስንፈቅድ ሲሻን የምናነሳው ፣ ሳይሻን የምንተወው አንድ የፊዚካል እንቅስቃሴ ዘርፍ እይደለም ። ይልቅ ጌትዬው ደጅ የሚፈስ የፍቅር ወንጌል ፣ በሓድራ እየከነፉ በሙሃባ እየሰገሩ ተውበትና ንስሃን አዝለው የሚንዘምትበት ላይታገድ እስካለይኛው ቀዬ የሚዘረጋ ዘላለማዊ ኪታብ ነው ። ለዚህም ከፍታ ባለቅኔው ሙሉጌታ ተስፋዬ ያበክራል ።
.
እኔም ቅኔ ልዝረፍ ... እስኪ ይመርብኝ
ያፈር ግብር አስራት ... የሥጋ‘ዳ አለብኝ...
.
ገጣሚ በሀይማኖት አጥር ሳለ ፣ ግን ሰውነትን ፍቅር ትተው የሀይማኖት ንፅፅር ተጠምደው የሰውን ልብ ገመና ከሚያዜሙ ከንቱ ሰባኪዎች የማይወረስ ፣ ለጀሊሉ ያደረውን ልብህን ነፍስህን ገፍተው በወሎህና ባዳርህ የሚተምኑ ፣ የጀነትን ቁልፍ በእጃቸው ያለ ይመስል ጀነትን እና ጀሀነምን ከሚተምኑ ቀድሞ ቀመስ ዳኢዎች ሸውራራ ተፍሲር የማይማርከው ነው ። ገጣሚው ገና በጥንስሱ ኪነትን ለፍቅር በፍቅር ብሎ በመውላናው የታደለች ናት ። ነፍሱእንደ ቧልት እንዲሁ ስሜቱን ሊሸነግለው አይቻለውም ። ብርቱ የነፍስ ጥሪ ጥበበ ደወል አድያው ከላይ ነውና ።
ይልቁን ያየውን ሀቅ ላያፈገፍግ በቀለሙ ሊገስፅ ይታገላል ። ለሌላው ሊጠቁም በቅኔ መሰላል ይሻገራል ።
ቅንነት ነው ቅኔው ፣ ቅንነት ነው ቀኑ ፣ ሰው ቂም ውሎ ካሳደረ ጀባ ያሉት አወል ቡና እንኳን አይሰባም ። ቢመርቅ ላያደርስ ፣ ቢለግስ በረከት ላይገመጥመው ፣ በሊግስ እንኳ ቂም ካለ በውስጡ እንኳም ለእሱ ለተመፅዋቹም አይበረክትለትም ። ባብጀው የሀጃ ሰታቴ ምን ቢያንፈቀፍቁ የሻቱት ላይበስል አሻዋ ነው የጣዱት ሙራድ ። የከፈተው ላይከድን አድሮ ገርበብ ነው ። ኢማን እንደዋዛ አሉ ... ወዲህም ለውስጣችን ለነፍስ ተክህኖ ( ካባ ) እንጂ ለፈራሽ ገላ መልበሱ ክንቱ ነው ። ይህን የሰውነት ድካ አይያ ሙሌም ሲለኩሰው እንዲህ ነው ። አዎና « ቁርሾ ያዘለች ነፍስ ቅኔ አይቀናትም ። »
.
ጠኔ ሲያጥመነምን ...
መገን ይሄ ቅኔ ... በምን ይገለጣል
ስትሹ " እሹ ! " እያለ የወዳጃ አበጋር ...
ቁርሾ ካንቀራጨ ... መች ሓጃ ያወጣል ።
.
.
.
ሊቀ ካህናቱ ... በከንቱ ውዕቱ ፣
መርተው ሲነርቱ ...
በብር መቋሚያ ፣ በወርቅ ፅናጵል
ደበሎ ለብሼ ...
ሚስጥረ ህቡኀን ድጎን ብቀጵል..
" በህግ አምላክ ብሎ !" ብሎ ማን ሊያቆመኝ ኑሯል?
ለራሱ ሊወናኝ ... ዘርፎ ቢቀኝ እንጂ
በነብሱ " ተክህኖ " ማን ማንን አስምሯል !
.
.
----
እናም ይህንን አይነት ሀቅ ከብላቴናው ገጣሚ ዳግም ደጀኔ (ሔራን) የፊታችን አርብና ቅዳሜ ገደማ ከምትወጣው ( ሰው - ፍቅር - ናፍቆት ) አድስ የግጥም መድብል ላይ አየናትና ነው ብዙ ማለቴ ።
.
የለምን ጥያቄ
።።
የያመነው ኪዳን
ባልታመነ ካህን በአማኝ ነኝ ልሳን ፣
በአርጅቷል ማዘዣ
ሰርክ እየታደሰ አውደ ‘ዳሱ ድርሳን ።
እውነት ቅቡ ሃሰን
ገዝፎ ለመታየት የክፍ እርካብ ሽቶ ፣
ከመሆን ዘመን ላይ
ወደ ቅጥፈት ደጃፍ
ሀቅ ይንከባለላል በመምሰል ተገፍቶ ።
በገፊዎች ግፊት
የእውነት እውነት ወዙ ሲገረጣ ፣
እውነት አምላኪ ሰው
በሀሰት ገዢዎች ሰውነቱን አጣ ።
.
ታዳ እንድህ እንዳለ ...
ተገፊው ይሄ ሰው ፣
ለምን ነው እምገፋ
ብሎ ለመጠየቅ ለ ማለት ሲጀምር ፣
ዝምበል አትናገር
የሚል መልስ ያገኛል ከገፊው መምህር ።
ለምን ሲል ለእንደዚህ
እንደት ሲል እንደዚህ
ምድራዊ መገፋት
አየለማዊ ልፋት
ሩህን ቢያርዳት የልፋቱ ቀንበር ፣
ዝም ብለህ አትናገር
የፈተነህ ጌታ
አንተን ሊመርጥ ነው ለሰማዩ መምበር ።
ይህ ማለት ምንድን ነው ...
.
.
.
.
ታዳ ልክ እንደዚህ
አማኝ አለማኙም
እውነት ለመቀርጠፍ ቅጥፈት ከታቀፈ ፣
አምንም ያለ ሰው
በአማኞች ህብረት ለምን ተነቀፈ ።
.
.
.
.
-----
( ሰው ፍቅር ናፍቆት )ገፅ 83
ሰኞም ትወጣለችና እንሸምታት ።
---
በመጨረሻም.
--
በሰው ልጅ የሕይወት ሂደት ውስጥ ጥበብ ወይም የእርሱ ዘርፍ ውስጥ የሆነው ልክ እንደ ግጥም ቋሚ ቅርሶች ሁሉ የማህበረሰቡን ወግ ፣ ልማድ ፣ ባህል ... ወ ዘ ተ ይዞ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ ይኖራል ። እስልምናም ለዚህ የጥበብ ዘርፍ የራሱ የሆነ አስተዋፅኦ አለው ። ከረሱል አሚን ( ሶ ዐ ወ ) መላክ በስተፊት አንስቶ ድንቅ ገጣሚያን በአረቢያን ምድር ነበሩ ። ግጥም እጅግ ትልቅ ሀይል እንደነበረው የተለያዪ የታሪክ መዛግብት ይናገራሉ ። እጅግ ያማረና ውብ የሆኑ ግጥሞችን ያስነበበ ደግሞ ለክብሩ ሲባል በካዕባ ይንጠለጠል እንደነበር ታሪክ ያስረዳል ። ሲለኝ በአደብ አደምጨዋለሁ " ኪታቡን " የግጥም መፅሓፍ መግቢያ ።
-
አሁን አሁን የግጥም መፀሐፍ በየወሩ ቢወጡም ሳለ ፣ በእርቃን የታጀበ ክሊፕ ብቻ ሰርተው " ዘፈን ነው አደምጡ " ብለው ጆሯችንን እንደሚቀልዱበት ሙዚቃ ተብዬ ግርግር አይደለም ። አዎ አንድ የግጥም መፀሐፍ ሲወጣ ተነቦ እንደገጣሚው አቅምና መድረስ እንጂ የሚለካው ከሌሎች ከፍ ካሉ ስራዎች ጋር አይወደዳደርም ። ሲጀመር ያን መፀሀፍ ይጣፍ አይጣፍጥ መች ገዝተን አንብበንው ነው ። ይህ ትልቅ በሽታ ነው ። ስም ያላቸውን ገጣሚያን ግን ሳናነበው ለማድነቅ መሯሯጡ ነው አመላችን ። በተዋቂ ስም ለመድመቅ ከጀርባ ከፊት ሽፋን መለጠፉ ክፉ በሽታ ነው ። በዛው ልክም ሳያነቡ የማይመሰክሩ ሸጋ አንባቢም አሉ ። አዎ ለነፍስ ወደ ነፍስ የነፍስን ስራ የሚያደርሱ የሚጀቡ እንደነ Shalom Desalegn Fuddy Man Cj አይነትም አይነት የለሽ አሉ ።
.
እንጂማ ...
የነ YadEl Tizazu -- ( ሕልም ብሀርን አድሜ )
የነ ዲበኩሉ ጌታ --( የምድር ዘላለም )
የነ Andualem Mesfin ... ( ሰበከት )
ወ
ዘ
ተ
ሸጋ የግጥም መፀሓፍ ተነቦ ሊገን ሊከበር በተገባው ነበር ። ግን ስንገዛ ፣ ስንጋብዝ አልታየንም ።
---
ምን ማለት ፈልጌ ነው -- እንግዛ እናንብብና ይውደቅ ። " አንባቢ ከብዶታል " አንበል መጀመሪያ እናድርስው ። #ኸላስ
---
ሸጋ የቅዳሚት መዳረሻ ምሽት❤
@getem
@getem
@Nagayta
👍2