#ንግስተ_ምላስ
…………………………………
ሁሉ ተነጫናጭ…ሁሉ ተናጋሪ፡
አለቃቃሽ ብቻ…የውስጥ ብሶት አውሪ፡
የራስ ጆሮ ሸጦ…በሠው ጆሮ ኗሪ፡
ያላዳምጥም ባይ…የልናገር ዘመን፡
አመዛዝኘ ነው…ብሎ ሲሠጥ ስልጣን፡
ለምላስ ንግስና…ኩሊ አድርጎ ጆሮን፡
ትክክል ነኝ ይላል…አሹሎ ምላሱን፡
እናም በዚህ ዘመን…የኔ አዳማጭነት፡
ሊያሠማኝ ካልሆነ…የሁሉንም ብሶት፡
ለኔ ጥቅም የለው
ምላሴ ካልጮኸ…ምኞቴን ለማግኘት፡
ነገር ግን…………
ያዳማጭ ምላስ…ለተናጋሪ አጭር ነው ብለው፡
የኔ እሪ ማለት ካልተሠማቸው፡
ልክ እንደነሡ እለፈልፍ ዘንድ፡
ምላሴ ይርዘም ይሁን ፩ ክንድ፡
ጆሮየን ልቁረጥ ልቀጥል ከሡ፡
ሆኗልና አሁን…
የሠው ማንነት…ጥቁር ምላሱ።
✍ #ተፃፈ_በዳዊት_ሠለሞን
ለግጥሙ አስተያየት @davaye
@getem
@getem
@gebriel_19
…………………………………
ሁሉ ተነጫናጭ…ሁሉ ተናጋሪ፡
አለቃቃሽ ብቻ…የውስጥ ብሶት አውሪ፡
የራስ ጆሮ ሸጦ…በሠው ጆሮ ኗሪ፡
ያላዳምጥም ባይ…የልናገር ዘመን፡
አመዛዝኘ ነው…ብሎ ሲሠጥ ስልጣን፡
ለምላስ ንግስና…ኩሊ አድርጎ ጆሮን፡
ትክክል ነኝ ይላል…አሹሎ ምላሱን፡
እናም በዚህ ዘመን…የኔ አዳማጭነት፡
ሊያሠማኝ ካልሆነ…የሁሉንም ብሶት፡
ለኔ ጥቅም የለው
ምላሴ ካልጮኸ…ምኞቴን ለማግኘት፡
ነገር ግን…………
ያዳማጭ ምላስ…ለተናጋሪ አጭር ነው ብለው፡
የኔ እሪ ማለት ካልተሠማቸው፡
ልክ እንደነሡ እለፈልፍ ዘንድ፡
ምላሴ ይርዘም ይሁን ፩ ክንድ፡
ጆሮየን ልቁረጥ ልቀጥል ከሡ፡
ሆኗልና አሁን…
የሠው ማንነት…ጥቁር ምላሱ።
✍ #ተፃፈ_በዳዊት_ሠለሞን
ለግጥሙ አስተያየት @davaye
@getem
@getem
@gebriel_19
#ተረጅልኝ ግጥሜን
………………………………
…………ልክ እኮ ነው ያልሽው፡
ግጥሜ ሀዘንን እንጅ…
ደስታን አይነግርሽም፡
አይኔ አለቀሰ እንጅ…
ጥርሴ ሳቀ አይልሽም፡
መጎዳቴን እንጅ…
ባንች መደሰቴን አያሳውቅሽም፡
፩ነቴን እንጅ…
ሠው እንዳለኝ ጭራሽ…እንድታምኝ አይሻም፡
ግን……አትናደጅብኝ ተረጅልኝ ግጥሜን፡
ቢከብደኝ ጊዜ እንጅ…
ብዕር አስነብቸ…ለመንገር ደስታየን፡
ብፈልግማ ኮ……
የሳቅሁትን ሳይሆን ልስቅ ያሠብኩትን፡
ውስጤ ጭንቁን ትቶ የልቤ ሀሴቱን፡
ቅሬታውን ረስቶ ባንች መደሰቱን፡
ይነግርሽ ነበረ…………
ግን……እባክሽን ውዴ ተረጅልኝ ግጥሜን፡
ከዘመኑ ሠው ጋ…እንባ ከሚያስቀው፡
መሀረብን ነፍጎ…ከንፈር ከሚመጠው፡
ያንተ መውደቅ ለኔ ከሚል መነሻ ነው፡
ሊመደብ አይሻም ሊያጣ ህሊናውን፡
በብእሩ ዕንባ…ሊነግርሽ ደስታውን።
✍#ተፃፈ_በዳዊት_ሠለሞን
@getem
@getem
@gebriel_19
………………………………
…………ልክ እኮ ነው ያልሽው፡
ግጥሜ ሀዘንን እንጅ…
ደስታን አይነግርሽም፡
አይኔ አለቀሰ እንጅ…
ጥርሴ ሳቀ አይልሽም፡
መጎዳቴን እንጅ…
ባንች መደሰቴን አያሳውቅሽም፡
፩ነቴን እንጅ…
ሠው እንዳለኝ ጭራሽ…እንድታምኝ አይሻም፡
ግን……አትናደጅብኝ ተረጅልኝ ግጥሜን፡
ቢከብደኝ ጊዜ እንጅ…
ብዕር አስነብቸ…ለመንገር ደስታየን፡
ብፈልግማ ኮ……
የሳቅሁትን ሳይሆን ልስቅ ያሠብኩትን፡
ውስጤ ጭንቁን ትቶ የልቤ ሀሴቱን፡
ቅሬታውን ረስቶ ባንች መደሰቱን፡
ይነግርሽ ነበረ…………
ግን……እባክሽን ውዴ ተረጅልኝ ግጥሜን፡
ከዘመኑ ሠው ጋ…እንባ ከሚያስቀው፡
መሀረብን ነፍጎ…ከንፈር ከሚመጠው፡
ያንተ መውደቅ ለኔ ከሚል መነሻ ነው፡
ሊመደብ አይሻም ሊያጣ ህሊናውን፡
በብእሩ ዕንባ…ሊነግርሽ ደስታውን።
✍#ተፃፈ_በዳዊት_ሠለሞን
@getem
@getem
@gebriel_19
👍1