ለምሽታችን!
💚
“
´✍ከላይ ያለች እጅ ከታች ካለች እጅ የተሻለች ናት!
በአንድ የገጠር ከተማ በርካታ ተማሪዎችን ሰብስበው የሚያስቀሩ አንድ ሸይኽ ነብሩ።አንድ ቀን ከነዚህ ተማሪዎች ውስጥ አንዱ ለሸይኹ ገንዘብ እንደሚያስፈልገውና ወደ ከተማ ሄዶ ይህንን ለቀለብ የሚያስፈልገውን ገንዘብ ማፈላለግ እንዳለበት ይነግራቸዋል። #ሼይኹም ለተማሪያቸው ከፈቀዱለትና ስንቅ ካዘጋጁለት በኋላ መንገዱን ይጀምራል። ወደ እሚሄድበት ከተማ ለመድረስም ከመንገድ ያለን በረሀ ማቋረጥ ነበረበት። ይህንንም በረሃ አቋርጦ በሚሄድበት ወቅት አንድ የቆሰለ አሞራ ከመሬት ላይ መብረር የማይችል ሆኖ ይመለከተዋል። ታድያ ይህ ደረሳ በዚህ አሞራ ተፈኩር(ማስተንተን) ማድረግ ይጀምራል።
#በዚህ_በረሀ ውስጥ ምንም የሚቀመስ በሌለበት ይህ አሞራ ምን እየበላ ይሆን!?
#እንዴት_በህይወት መቆየትስ ቻለ!?
በዚህ መልኩ በተፈኩር ውስጥ ሳለ ከወደ ሰማይ ሌላ አሞራ ድንገት ከወደ ሰማይ ዱብ ይላል።
#ይህ_አሞራ የሚበላ ነገር በእግሮቹ አንጠልጥሎ ነበርና ለተጎዳው አሞራ ጥሎለት ሄደ። ያ የተጎዳው አሞራም የተጣለለትን ምግብ መመገብ ይጀምራል።
ተማሪውም በጣም ተገረመ። (መቼስ ፈጣሪ ነፍስን ከሪዝቋ ጋር እንጂ መች በባዶ ፈጠራት እና!) ብቻ ነገሩ እጅግ አስገርሞት እና አስደንቆት የሚሄድበትን በመሰረዝ ወደ ሸይኹ መመለስ ጀመረ። ለመመለሱ ምክንያትም ይህንን የተጎዳ አሞራ በዚህ በረሃ ውስጥ የሚመግብ እና የሚረዝቀው ፈጣሪ እኔንም ይመግበኛል ችግሬን ያስወግድልኛል የሚል ነበር። ወደ ሸይኹም እንደደረሰ የተመለሰበትን ምክንያት ይጠይቁታል።
ተማሪውም ያጋጠመውን ሁሉ ይነግራቸውና ፈጣሪው እሱንም ልክ እንደ አሞራው ሁሉ ከችሮታው እንደሚለግሰው ተስፋ አድርጎ መመለሱን ነገራቸው።
#ሸይኹም- ምነው !? እንደው እንተጎዳውና እርዳታ ፈላጊው አሞራ መሆንን ከመመኘት ለምን እንደ ረጂው እና ምግብን ተሸክሞ እንደተባበረው አሞራ መሆንን አልተመኘህም አሉት ይባላል።
---------------------------------------
#ሁሌም ቢሆን ትብብር እና እርዳታን ፈላጊ ከመሆን አንተው እራስህ ረጂ እና ተባባሪ መሆንን ምረጥ።
ከላይ ያለች እጅ ታች ካለች እጅ በላጭስ አይደለች!
#አሁን ወቅቱ ከመቼውም በላይ ቁጭ ብለን ለመረዳት ወይም ከመንግስት ብቻ መፍትሔ የምንጠብቅበት ጊዜ ላይ አይደለንም ሀገራችንን ፣ ወገኖቻችን ፣ ቤተሰቦቻችን ፣ ወገኖቻችን እንዴት ነው ከዚህ ችግር ልንከላከል የምንችለው ብለን በደንብ የምናስብበትና ወደ ተግባር የምንገባበት ጊዜ ነው....እናም ወንድምና እህቶቼ እቤት ከመቀመጥ በዘለለ ደሞ ማድረግ ስላለብን ነገሮች አስቡልኝ የኛ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች አሉ በየአካባቢው አይደል..? አቅም የሌላቸው የንፅህና ሳኒታይዘር ሆነ ምግብ መግዣ የሌላቸው ብዙ አሉ በየአካባቢያችን ስለዚህ እዚህ ቻናል ወንድሞችና እህቶች የምንችለውን እንርዳቸው ይሄን በሽታ የሚከላከሉበት ማቴሪያል እንርዳቸው ፣ የሚበሉትን ገዝተን እንስጣቸው በአቅማችን #ይሄኔ እኛም ለሀገራችን የበኩላችንን አስተዋጽኦ እናደርጋለን.....ለምን አንድ ሳሙና አይሆንም ....
#ይሄን የምታነቡ ሰዎች ይሄን እንደምታደርጉ እናንተም የመፍትሔ አካል እንደምትሆኑ እምነት አለኝ🙏🙏🙏
ውብ ምሽት ትሁንላቹ!❤🙏
@getem
@getem
@Nagayta
💚
“
´✍ከላይ ያለች እጅ ከታች ካለች እጅ የተሻለች ናት!
በአንድ የገጠር ከተማ በርካታ ተማሪዎችን ሰብስበው የሚያስቀሩ አንድ ሸይኽ ነብሩ።አንድ ቀን ከነዚህ ተማሪዎች ውስጥ አንዱ ለሸይኹ ገንዘብ እንደሚያስፈልገውና ወደ ከተማ ሄዶ ይህንን ለቀለብ የሚያስፈልገውን ገንዘብ ማፈላለግ እንዳለበት ይነግራቸዋል። #ሼይኹም ለተማሪያቸው ከፈቀዱለትና ስንቅ ካዘጋጁለት በኋላ መንገዱን ይጀምራል። ወደ እሚሄድበት ከተማ ለመድረስም ከመንገድ ያለን በረሀ ማቋረጥ ነበረበት። ይህንንም በረሃ አቋርጦ በሚሄድበት ወቅት አንድ የቆሰለ አሞራ ከመሬት ላይ መብረር የማይችል ሆኖ ይመለከተዋል። ታድያ ይህ ደረሳ በዚህ አሞራ ተፈኩር(ማስተንተን) ማድረግ ይጀምራል።
#በዚህ_በረሀ ውስጥ ምንም የሚቀመስ በሌለበት ይህ አሞራ ምን እየበላ ይሆን!?
#እንዴት_በህይወት መቆየትስ ቻለ!?
በዚህ መልኩ በተፈኩር ውስጥ ሳለ ከወደ ሰማይ ሌላ አሞራ ድንገት ከወደ ሰማይ ዱብ ይላል።
#ይህ_አሞራ የሚበላ ነገር በእግሮቹ አንጠልጥሎ ነበርና ለተጎዳው አሞራ ጥሎለት ሄደ። ያ የተጎዳው አሞራም የተጣለለትን ምግብ መመገብ ይጀምራል።
ተማሪውም በጣም ተገረመ። (መቼስ ፈጣሪ ነፍስን ከሪዝቋ ጋር እንጂ መች በባዶ ፈጠራት እና!) ብቻ ነገሩ እጅግ አስገርሞት እና አስደንቆት የሚሄድበትን በመሰረዝ ወደ ሸይኹ መመለስ ጀመረ። ለመመለሱ ምክንያትም ይህንን የተጎዳ አሞራ በዚህ በረሃ ውስጥ የሚመግብ እና የሚረዝቀው ፈጣሪ እኔንም ይመግበኛል ችግሬን ያስወግድልኛል የሚል ነበር። ወደ ሸይኹም እንደደረሰ የተመለሰበትን ምክንያት ይጠይቁታል።
ተማሪውም ያጋጠመውን ሁሉ ይነግራቸውና ፈጣሪው እሱንም ልክ እንደ አሞራው ሁሉ ከችሮታው እንደሚለግሰው ተስፋ አድርጎ መመለሱን ነገራቸው።
#ሸይኹም- ምነው !? እንደው እንተጎዳውና እርዳታ ፈላጊው አሞራ መሆንን ከመመኘት ለምን እንደ ረጂው እና ምግብን ተሸክሞ እንደተባበረው አሞራ መሆንን አልተመኘህም አሉት ይባላል።
---------------------------------------
#ሁሌም ቢሆን ትብብር እና እርዳታን ፈላጊ ከመሆን አንተው እራስህ ረጂ እና ተባባሪ መሆንን ምረጥ።
ከላይ ያለች እጅ ታች ካለች እጅ በላጭስ አይደለች!
#አሁን ወቅቱ ከመቼውም በላይ ቁጭ ብለን ለመረዳት ወይም ከመንግስት ብቻ መፍትሔ የምንጠብቅበት ጊዜ ላይ አይደለንም ሀገራችንን ፣ ወገኖቻችን ፣ ቤተሰቦቻችን ፣ ወገኖቻችን እንዴት ነው ከዚህ ችግር ልንከላከል የምንችለው ብለን በደንብ የምናስብበትና ወደ ተግባር የምንገባበት ጊዜ ነው....እናም ወንድምና እህቶቼ እቤት ከመቀመጥ በዘለለ ደሞ ማድረግ ስላለብን ነገሮች አስቡልኝ የኛ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች አሉ በየአካባቢው አይደል..? አቅም የሌላቸው የንፅህና ሳኒታይዘር ሆነ ምግብ መግዣ የሌላቸው ብዙ አሉ በየአካባቢያችን ስለዚህ እዚህ ቻናል ወንድሞችና እህቶች የምንችለውን እንርዳቸው ይሄን በሽታ የሚከላከሉበት ማቴሪያል እንርዳቸው ፣ የሚበሉትን ገዝተን እንስጣቸው በአቅማችን #ይሄኔ እኛም ለሀገራችን የበኩላችንን አስተዋጽኦ እናደርጋለን.....ለምን አንድ ሳሙና አይሆንም ....
#ይሄን የምታነቡ ሰዎች ይሄን እንደምታደርጉ እናንተም የመፍትሔ አካል እንደምትሆኑ እምነት አለኝ🙏🙏🙏
ውብ ምሽት ትሁንላቹ!❤🙏
@getem
@getem
@Nagayta