#በእውቀቱ_ስዩም
.
እንደ ጊዜው መክፋት
እንደ ግፉ መስፋት
እንዳገሩ ክስመት
እንዳገሬው ጥመት
እንደሰው ጭካኔ፤ እንደ ልቡ ፍሬ
ታምር ነው መትረፍሽ ፤ ታምር ነው መኖሬ::
የበጎ ሰው ሀሳብ ፤ ሲካድ እለት በለት
ጉድጏድ ተምሶለት
ሰብእና ሲቀበር፤
በዚህ ምድር መኖር ፤ አያስመኝም ነበር::
ምድሩ ሳር ቅጠሉ፤ በስጋት ተሞልቶ
የማለዳው ሰማይ፤ እንዳንቀልባ ቀልቶ
ታረደ
ነደደ
ከዘብጥያ ወጥቶ
ዘብጥያ ወረደ
የሚል ዜና ብቻ አየሩን ሲሞላው
ሰው በገዛ ጥላው
በርግጎ ሲሸበር
በዚህ ምድር መኖር ፤አያስመኝም ነበር::
አዎ
ለጊዜውም ቢሆን፤ ግፍ ያደነዝዛል
በደል ያስተክዛል
ጊዜም ጠብን ሽሮ፤ ወደ ፊት ይጏዛል
በልብ ሰሌዳ ላይ ፤ቂም ይደበዝዛል
በነገ ያመነ
ልጁን ቀብሮ መጥቶ፤ ሚስቱን ያስረግዛል::
ይቅርታና ምህረት
ፍቅርና ህብረት
ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው ፤ ቢሆን የሞት ሽረት
ዳገት ይወጣሉ ፤ በንጥፍጣፊ አቅም
የመኖር ፍላጎት
ዘመም ይላል እንጂ ፤ ተገርስሶ አይወድቅም::
@getem
@getem
@getem
.
እንደ ጊዜው መክፋት
እንደ ግፉ መስፋት
እንዳገሩ ክስመት
እንዳገሬው ጥመት
እንደሰው ጭካኔ፤ እንደ ልቡ ፍሬ
ታምር ነው መትረፍሽ ፤ ታምር ነው መኖሬ::
የበጎ ሰው ሀሳብ ፤ ሲካድ እለት በለት
ጉድጏድ ተምሶለት
ሰብእና ሲቀበር፤
በዚህ ምድር መኖር ፤ አያስመኝም ነበር::
ምድሩ ሳር ቅጠሉ፤ በስጋት ተሞልቶ
የማለዳው ሰማይ፤ እንዳንቀልባ ቀልቶ
ታረደ
ነደደ
ከዘብጥያ ወጥቶ
ዘብጥያ ወረደ
የሚል ዜና ብቻ አየሩን ሲሞላው
ሰው በገዛ ጥላው
በርግጎ ሲሸበር
በዚህ ምድር መኖር ፤አያስመኝም ነበር::
አዎ
ለጊዜውም ቢሆን፤ ግፍ ያደነዝዛል
በደል ያስተክዛል
ጊዜም ጠብን ሽሮ፤ ወደ ፊት ይጏዛል
በልብ ሰሌዳ ላይ ፤ቂም ይደበዝዛል
በነገ ያመነ
ልጁን ቀብሮ መጥቶ፤ ሚስቱን ያስረግዛል::
ይቅርታና ምህረት
ፍቅርና ህብረት
ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው ፤ ቢሆን የሞት ሽረት
ዳገት ይወጣሉ ፤ በንጥፍጣፊ አቅም
የመኖር ፍላጎት
ዘመም ይላል እንጂ ፤ ተገርስሶ አይወድቅም::
@getem
@getem
@getem
❤1👍1
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሠላም አደረሳችሁ
__ለአባቴ______
ሰው ብቻ አይደለህም፥ካፈር ወጥተህ ላፈር
መልእክ ነህ ሉሲፈር*
ክብርህ ማንነትህ ባመጽ የሚታፈር
የማትንበረከክ
የማትርመጠመጥ
ከባለጌ ዙፋን ፥በርጩማ የምትመርጥ፣
ያለ ባሕር ሰርጓጅ፥ያለ ሙሴ በትር
በመታገስ ብቻ ፥ባሕር የምትመትር
ካዘልከኝ ጀምሮ፥እንኮኮ ጫንቃህ ላይ
ከፍታውን እንጂ፥ዝቅታውን ላላይ
እንደንስር መጠቅሁ፥እንደ ምስራቅ በራሁ
የገዛ ክንፎቼን፥እንደ ዳንቴል ሠራሁ፤
በርግጥ ደሀ ነበርክ
ከሰላምታ በቀር፥የማታበረክት
ነጠላህ መናኛ፥ሰውነትህ የክት፤
በርግጥ ደሀ ነበርክ፥የነጣህ የጠራህ
ከጦር ሜዳ ይልቅ፥ገበያ ሚያስፈራህ
ቤሳ ባታወርሰኝ፥አወረስከኝ ትግል
የትም እንዳይጥለኝ፥ሕይወት እንደ ፈንግል፤
አባዬ ብርሃን
አባ የምስራቅ በር
ገመና ሸሻጊ፥እንደ ካባ ገበር
አባቴ ባትሆን፥ምን ይውጠኝ ነበር።
(*'ሉሲፈር' አጥቢያ ኮከብም እንደማለት ነው)
#በእውቀቱ ሥዩም
የማለዳ ድባብ
ገፅ 72
@getem
@getem
@beckyalexander
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሠላም አደረሳችሁ
__ለአባቴ______
ሰው ብቻ አይደለህም፥ካፈር ወጥተህ ላፈር
መልእክ ነህ ሉሲፈር*
ክብርህ ማንነትህ ባመጽ የሚታፈር
የማትንበረከክ
የማትርመጠመጥ
ከባለጌ ዙፋን ፥በርጩማ የምትመርጥ፣
ያለ ባሕር ሰርጓጅ፥ያለ ሙሴ በትር
በመታገስ ብቻ ፥ባሕር የምትመትር
ካዘልከኝ ጀምሮ፥እንኮኮ ጫንቃህ ላይ
ከፍታውን እንጂ፥ዝቅታውን ላላይ
እንደንስር መጠቅሁ፥እንደ ምስራቅ በራሁ
የገዛ ክንፎቼን፥እንደ ዳንቴል ሠራሁ፤
በርግጥ ደሀ ነበርክ
ከሰላምታ በቀር፥የማታበረክት
ነጠላህ መናኛ፥ሰውነትህ የክት፤
በርግጥ ደሀ ነበርክ፥የነጣህ የጠራህ
ከጦር ሜዳ ይልቅ፥ገበያ ሚያስፈራህ
ቤሳ ባታወርሰኝ፥አወረስከኝ ትግል
የትም እንዳይጥለኝ፥ሕይወት እንደ ፈንግል፤
አባዬ ብርሃን
አባ የምስራቅ በር
ገመና ሸሻጊ፥እንደ ካባ ገበር
አባቴ ባትሆን፥ምን ይውጠኝ ነበር።
(*'ሉሲፈር' አጥቢያ ኮከብም እንደማለት ነው)
#በእውቀቱ ሥዩም
የማለዳ ድባብ
ገፅ 72
@getem
@getem
@beckyalexander
ድሎት እየዘሩ
#በእውቀቱ ስዩም
ይቅርብኝ ፍሪዳው፥
አልጠግብ- ባይ ይብላው
ወይኑም በፅዋ ላይ ፤ እንደ እንኮይ የቀላው
ግዴለም ይለፈኝ !
ጊዜ ምቾት ነስቶ
ምንጣፉን አንስቶ ፤
ፅናቱን ያውሰኝ
በመጋዝ ጠርዝ ላይ፤
መራመድ ከተማርኩ፤ ማንም አይመልሰኝ::
አውቃለሁ
አሳር አሻራውን፣ ግንባር ላይ ሳያትም
ድሎት እየዘሩ ፥ ድል አይመረትም ::
@getem
@getem
@beckyalexander
#በእውቀቱ ስዩም
ይቅርብኝ ፍሪዳው፥
አልጠግብ- ባይ ይብላው
ወይኑም በፅዋ ላይ ፤ እንደ እንኮይ የቀላው
ግዴለም ይለፈኝ !
ጊዜ ምቾት ነስቶ
ምንጣፉን አንስቶ ፤
ፅናቱን ያውሰኝ
በመጋዝ ጠርዝ ላይ፤
መራመድ ከተማርኩ፤ ማንም አይመልሰኝ::
አውቃለሁ
አሳር አሻራውን፣ ግንባር ላይ ሳያትም
ድሎት እየዘሩ ፥ ድል አይመረትም ::
@getem
@getem
@beckyalexander
😁1