#በእውቀቱ_ስዩም
.
እንደ ጊዜው መክፋት
እንደ ግፉ መስፋት
እንዳገሩ ክስመት
እንዳገሬው ጥመት
እንደሰው ጭካኔ፤ እንደ ልቡ ፍሬ
ታምር ነው መትረፍሽ ፤ ታምር ነው መኖሬ::
የበጎ ሰው ሀሳብ ፤ ሲካድ እለት በለት
ጉድጏድ ተምሶለት
ሰብእና ሲቀበር፤
በዚህ ምድር መኖር ፤ አያስመኝም ነበር::
ምድሩ ሳር ቅጠሉ፤ በስጋት ተሞልቶ
የማለዳው ሰማይ፤ እንዳንቀልባ ቀልቶ
ታረደ
ነደደ
ከዘብጥያ ወጥቶ
ዘብጥያ ወረደ
የሚል ዜና ብቻ አየሩን ሲሞላው
ሰው በገዛ ጥላው
በርግጎ ሲሸበር
በዚህ ምድር መኖር ፤አያስመኝም ነበር::
አዎ
ለጊዜውም ቢሆን፤ ግፍ ያደነዝዛል
በደል ያስተክዛል
ጊዜም ጠብን ሽሮ፤ ወደ ፊት ይጏዛል
በልብ ሰሌዳ ላይ ፤ቂም ይደበዝዛል
በነገ ያመነ
ልጁን ቀብሮ መጥቶ፤ ሚስቱን ያስረግዛል::
ይቅርታና ምህረት
ፍቅርና ህብረት
ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው ፤ ቢሆን የሞት ሽረት
ዳገት ይወጣሉ ፤ በንጥፍጣፊ አቅም
የመኖር ፍላጎት
ዘመም ይላል እንጂ ፤ ተገርስሶ አይወድቅም::
@getem
@getem
@getem
.
እንደ ጊዜው መክፋት
እንደ ግፉ መስፋት
እንዳገሩ ክስመት
እንዳገሬው ጥመት
እንደሰው ጭካኔ፤ እንደ ልቡ ፍሬ
ታምር ነው መትረፍሽ ፤ ታምር ነው መኖሬ::
የበጎ ሰው ሀሳብ ፤ ሲካድ እለት በለት
ጉድጏድ ተምሶለት
ሰብእና ሲቀበር፤
በዚህ ምድር መኖር ፤ አያስመኝም ነበር::
ምድሩ ሳር ቅጠሉ፤ በስጋት ተሞልቶ
የማለዳው ሰማይ፤ እንዳንቀልባ ቀልቶ
ታረደ
ነደደ
ከዘብጥያ ወጥቶ
ዘብጥያ ወረደ
የሚል ዜና ብቻ አየሩን ሲሞላው
ሰው በገዛ ጥላው
በርግጎ ሲሸበር
በዚህ ምድር መኖር ፤አያስመኝም ነበር::
አዎ
ለጊዜውም ቢሆን፤ ግፍ ያደነዝዛል
በደል ያስተክዛል
ጊዜም ጠብን ሽሮ፤ ወደ ፊት ይጏዛል
በልብ ሰሌዳ ላይ ፤ቂም ይደበዝዛል
በነገ ያመነ
ልጁን ቀብሮ መጥቶ፤ ሚስቱን ያስረግዛል::
ይቅርታና ምህረት
ፍቅርና ህብረት
ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው ፤ ቢሆን የሞት ሽረት
ዳገት ይወጣሉ ፤ በንጥፍጣፊ አቅም
የመኖር ፍላጎት
ዘመም ይላል እንጂ ፤ ተገርስሶ አይወድቅም::
@getem
@getem
@getem
❤1👍1
ድሎት እየዘሩ
#በእውቀቱ ስዩም
ይቅርብኝ ፍሪዳው፥
አልጠግብ- ባይ ይብላው
ወይኑም በፅዋ ላይ ፤ እንደ እንኮይ የቀላው
ግዴለም ይለፈኝ !
ጊዜ ምቾት ነስቶ
ምንጣፉን አንስቶ ፤
ፅናቱን ያውሰኝ
በመጋዝ ጠርዝ ላይ፤
መራመድ ከተማርኩ፤ ማንም አይመልሰኝ::
አውቃለሁ
አሳር አሻራውን፣ ግንባር ላይ ሳያትም
ድሎት እየዘሩ ፥ ድል አይመረትም ::
@getem
@getem
@beckyalexander
#በእውቀቱ ስዩም
ይቅርብኝ ፍሪዳው፥
አልጠግብ- ባይ ይብላው
ወይኑም በፅዋ ላይ ፤ እንደ እንኮይ የቀላው
ግዴለም ይለፈኝ !
ጊዜ ምቾት ነስቶ
ምንጣፉን አንስቶ ፤
ፅናቱን ያውሰኝ
በመጋዝ ጠርዝ ላይ፤
መራመድ ከተማርኩ፤ ማንም አይመልሰኝ::
አውቃለሁ
አሳር አሻራውን፣ ግንባር ላይ ሳያትም
ድሎት እየዘሩ ፥ ድል አይመረትም ::
@getem
@getem
@beckyalexander
😁1