የጨረቃ ምች
"""''"""""""""""""
ተዘንግቶኝ ኖሮ
የጨረቃ ብርሃን ከፀሀይ መበደር፤
ቅቤውን አንጥሬ
ያላንዳች ከለላ ብገኝ ከቤቴ በር።
ክፉኛ ተጎዳሁ
ህመሙ ፀናብኝ አለማወቄ እንጂ፤
መች ያስተኛኝ ነበር
ሊገለኝ ከጅሎ የጨረቃ ምቺ!!
አብርሃም
@Run_Viva_Run
@getem
@getem
"""''"""""""""""""
ተዘንግቶኝ ኖሮ
የጨረቃ ብርሃን ከፀሀይ መበደር፤
ቅቤውን አንጥሬ
ያላንዳች ከለላ ብገኝ ከቤቴ በር።
ክፉኛ ተጎዳሁ
ህመሙ ፀናብኝ አለማወቄ እንጂ፤
መች ያስተኛኝ ነበር
ሊገለኝ ከጅሎ የጨረቃ ምቺ!!
አብርሃም
@Run_Viva_Run
@getem
@getem
መርሳት ያማረው ሰው
ተፃፈ (በአኑ)
እኔ አንቺን ለመርሳት
የሄድነውን መንገድ ዳግም አልሄደውም
አብረን ያየነውን
የፍቅር ፊልሞችን ብቻዬን አላየውም
ልልሽ አስብና
ሀገሬው በሙላ
ያንቺን ትዝታ ይዞ ስለሚከተለኝ
ልረሳሽ አልቻልኩም
ትዝታሽ ጥላዬ ሆኖ እየወረረኝ።
ትዝታሽ ጥበብ ነው
ልክ እንደ ሰለሞን ጥበብ የበዛበት
ትዝታሽ ሀያል ነው
እንደ ዳዊት ጠጠር
ያ ግዙፍ ጎልያድ እንደወደቀበት
ትዝታሽ ልዩ ነው
ትዝታሽ ልዩ ነው ብሎ የሚያፅፈኝ
ትዝታሽ ብቻ ነው
ያለፈውን ሁሉ የሚያስቀባጥረኝ።
እርግጥ አንድ ሰሞን
እኔ አንቺን አፍቅሬ ከእኔነቴ ጠፋሁ
ያፈቀርሽኝ እለት
ባንቺ ማንነት ውስጥ ራሴን አገኘሁ
አንቺነት ውስጥ አለሽ
እኔነት ውስጥ አለው አምሬ ተውበሽ
ጨለማው ልቤ ላይ
የብርሀንን ኩራዝ በፍቅር ለኩሰሽ
ብዙ አመት ኖረናል
ልብሽን ወርሼ ኦና ልቤን ወረሰሽ።
ይህ ሁሉ አለፈና
የፍቅር ልባችን ጥላቻ ነግሶበት
ያበራሹ ልቤ
ጥለሽው ስትወጪ ጨለማ ሰፍኖበት
ማየት የተሳነው
ጨለማ ልብ ይዤ አላስታውስሽም
ረስቼሻለሁ
ረስቼሻለሁ ማለቴ በራሱ ቢያስታውስሽም ።
ለሀሳብ አስተያየት @anu_yesua
@getem
@getem
@getem
ተፃፈ (በአኑ)
እኔ አንቺን ለመርሳት
የሄድነውን መንገድ ዳግም አልሄደውም
አብረን ያየነውን
የፍቅር ፊልሞችን ብቻዬን አላየውም
ልልሽ አስብና
ሀገሬው በሙላ
ያንቺን ትዝታ ይዞ ስለሚከተለኝ
ልረሳሽ አልቻልኩም
ትዝታሽ ጥላዬ ሆኖ እየወረረኝ።
ትዝታሽ ጥበብ ነው
ልክ እንደ ሰለሞን ጥበብ የበዛበት
ትዝታሽ ሀያል ነው
እንደ ዳዊት ጠጠር
ያ ግዙፍ ጎልያድ እንደወደቀበት
ትዝታሽ ልዩ ነው
ትዝታሽ ልዩ ነው ብሎ የሚያፅፈኝ
ትዝታሽ ብቻ ነው
ያለፈውን ሁሉ የሚያስቀባጥረኝ።
እርግጥ አንድ ሰሞን
እኔ አንቺን አፍቅሬ ከእኔነቴ ጠፋሁ
ያፈቀርሽኝ እለት
ባንቺ ማንነት ውስጥ ራሴን አገኘሁ
አንቺነት ውስጥ አለሽ
እኔነት ውስጥ አለው አምሬ ተውበሽ
ጨለማው ልቤ ላይ
የብርሀንን ኩራዝ በፍቅር ለኩሰሽ
ብዙ አመት ኖረናል
ልብሽን ወርሼ ኦና ልቤን ወረሰሽ።
ይህ ሁሉ አለፈና
የፍቅር ልባችን ጥላቻ ነግሶበት
ያበራሹ ልቤ
ጥለሽው ስትወጪ ጨለማ ሰፍኖበት
ማየት የተሳነው
ጨለማ ልብ ይዤ አላስታውስሽም
ረስቼሻለሁ
ረስቼሻለሁ ማለቴ በራሱ ቢያስታውስሽም ።
ለሀሳብ አስተያየት @anu_yesua
@getem
@getem
@getem
ቀንዲል የጥበብ ምሽታችን አዳዲስ የጥበብ ፊቶችን ይዞ ለእሮብ #ጥቅምት_12 ... ጉርድ ሾላ በሚገኘው #ቶፕ_10 ሆቴል ይደረጋል ።
በዚህ ምሽታችን
ወገኛው አሳዬ ደርቤ
ገጣሚ ሰለሞን ሳህለ
ገጣሚ ያዴል ትዛዙ
ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ
ገጣሚ እዮብ ዘ ማርያም
ገጣሚ ፍቃዱ ጌታቸው
ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ
ገጣሚ ዲበኩሉ ጌታ
ገጣሚ እሱባለው የኔ ነህ
ባለ ቅኔ በቃሉ ሙሉ
ገጣሚ ልዑል ሀይሌ እና ገጣሚ ሚካኤል አስጨናቂ ስራዎቻቸውን ይዘው የሚቀርቡ ይሆናል ።
አዲስ እና በእለቱ የሚቀርብም ክብር እንግዳ ይኖረናል ።
ምሽታችንን ለማድመቅ ለምትፈልጉ ሁሉ ትኬቱ ከጃፋር መፅሀፍት መደብር ...ይገኛል ....በተጨማሪም ልዑል ሀይሌ (0910630305) ...ሚካኤል አስጨናቂ (0920059005) ላይ በመደወል ማግኘት ትችላላችሁ ።
#ሼር ማድረግ እናንተን አይጎዳም እኛን ይጠቅማልና ሼር አድርጉልን
በዚህ ምሽታችን
ወገኛው አሳዬ ደርቤ
ገጣሚ ሰለሞን ሳህለ
ገጣሚ ያዴል ትዛዙ
ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ
ገጣሚ እዮብ ዘ ማርያም
ገጣሚ ፍቃዱ ጌታቸው
ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ
ገጣሚ ዲበኩሉ ጌታ
ገጣሚ እሱባለው የኔ ነህ
ባለ ቅኔ በቃሉ ሙሉ
ገጣሚ ልዑል ሀይሌ እና ገጣሚ ሚካኤል አስጨናቂ ስራዎቻቸውን ይዘው የሚቀርቡ ይሆናል ።
አዲስ እና በእለቱ የሚቀርብም ክብር እንግዳ ይኖረናል ።
ምሽታችንን ለማድመቅ ለምትፈልጉ ሁሉ ትኬቱ ከጃፋር መፅሀፍት መደብር ...ይገኛል ....በተጨማሪም ልዑል ሀይሌ (0910630305) ...ሚካኤል አስጨናቂ (0920059005) ላይ በመደወል ማግኘት ትችላላችሁ ።
#ሼር ማድረግ እናንተን አይጎዳም እኛን ይጠቅማልና ሼር አድርጉልን
#የወፈፌው ቃላት!!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።
ደግሞ ተነሳብኝ!
የአምና ካቻምናው ፥ የፊቱ እብደቴ
አንቺን ባየው ቁጥር.. .
ወፈፈ ሚያስብለኝ ፥ ህመም ምልክቴ።
ይኸው ፌስታል ሸረብሁ !
ቡልኮዬን ቀደድሁ
ገረባዬን ሸከፍሁ
ካላፊ ካግዳሚው ...
ቅጥሬን ለይቼ ፥ በፅኑ ተኳረፍሁ።
ብልሀት በራቀው ፥ መላ በሌለበት
ህመምን የሚያብስ...
ከንፈር መጣጭ ሀኪም ፥ ደጁን በሞላበት
ከተማ ሸሽቼ ...
ብቻዬን ወጥቼ...
ለሚሰግር ፍቅር ፥ መንገድ ላበጅለት
አበድሁ ስላንቺ ...
ያለ አንዳች ከልካይ ፥ ተመላለሺበት ።
ይኸው እንኪ ሰበዙን
የልምዱ እብደቴን...
በወስፌ ለይተሽ ፥ መሶቡን አበጂ
ተቀበይ ህመሜን!
አንጀትሽ እንዲርስ...
ከዳሩ ላይ ጨልፈሽ ፥ ወይንሽን ቅጂ ።
እንኪ ንሽማሽን!
ዘርጊው መዳፍሽን ...
ጠያቂው በተርታ ፥ በሰልፍ ተሰድሮ
ምን ክፉ አጊንቶህ
ከጤናህ ተሽረህ ፥ ሆንህ እንደ ድሮ ?
ብለው ሳይጠይቁኝ ....
#እኔም በተራዬ
"አዎን እንደዚህ ነው !
ሰው ፍቅርን ሊያነግስ ፥
ልቡን ተሸክሞ ፥ ሲወርድ ከገበያ
አቅልን የመሳት ፥ የእብደት መጀመርያ
ደግሞም የእውነት ህመም ...
መላወሻ አልባው ፥ ሀቀኛው በሽታ
ሰው ልቡን አቅርቦ ፥ ዘርግቶ በፎጣ
ሸማች ሲርቀው ነው ፥ የሚገዛው ሲያጣ "
ብዬ ሳልመልስ ፥ ሳይገለጥ ምክንያቴ
ፈጥነሽ ድረሽልኝ ፥ ተሿሚ ልዕልቴ ።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።
ደግሞ ተነሳብኝ!
የአምና ካቻምናው ፥ የፊቱ እብደቴ
አንቺን ባየው ቁጥር.. .
ወፈፈ ሚያስብለኝ ፥ ህመም ምልክቴ።
ይኸው ፌስታል ሸረብሁ !
ቡልኮዬን ቀደድሁ
ገረባዬን ሸከፍሁ
ካላፊ ካግዳሚው ...
ቅጥሬን ለይቼ ፥ በፅኑ ተኳረፍሁ።
ብልሀት በራቀው ፥ መላ በሌለበት
ህመምን የሚያብስ...
ከንፈር መጣጭ ሀኪም ፥ ደጁን በሞላበት
ከተማ ሸሽቼ ...
ብቻዬን ወጥቼ...
ለሚሰግር ፍቅር ፥ መንገድ ላበጅለት
አበድሁ ስላንቺ ...
ያለ አንዳች ከልካይ ፥ ተመላለሺበት ።
ይኸው እንኪ ሰበዙን
የልምዱ እብደቴን...
በወስፌ ለይተሽ ፥ መሶቡን አበጂ
ተቀበይ ህመሜን!
አንጀትሽ እንዲርስ...
ከዳሩ ላይ ጨልፈሽ ፥ ወይንሽን ቅጂ ።
እንኪ ንሽማሽን!
ዘርጊው መዳፍሽን ...
ጠያቂው በተርታ ፥ በሰልፍ ተሰድሮ
ምን ክፉ አጊንቶህ
ከጤናህ ተሽረህ ፥ ሆንህ እንደ ድሮ ?
ብለው ሳይጠይቁኝ ....
#እኔም በተራዬ
"አዎን እንደዚህ ነው !
ሰው ፍቅርን ሊያነግስ ፥
ልቡን ተሸክሞ ፥ ሲወርድ ከገበያ
አቅልን የመሳት ፥ የእብደት መጀመርያ
ደግሞም የእውነት ህመም ...
መላወሻ አልባው ፥ ሀቀኛው በሽታ
ሰው ልቡን አቅርቦ ፥ ዘርግቶ በፎጣ
ሸማች ሲርቀው ነው ፥ የሚገዛው ሲያጣ "
ብዬ ሳልመልስ ፥ ሳይገለጥ ምክንያቴ
ፈጥነሽ ድረሽልኝ ፥ ተሿሚ ልዕልቴ ።
@getem
@getem
@getem
👍1
እያዩ እስታይል
፩
ተው!
ከንፁሑ ልቤ አታኑር አንካካ
ኪስህን ልታደልብ አስራቴን አትንካ።
እረፍ!
ላታስታግስልኝ
ቁስሌን አታራግበው
ከዝንቦቹ ብሰህ ፥ ልታንገበግበው
አድብ
በንባዬ ጠብታ ኩሬህን አትገድብ።
፪
ይቅርብሽ
ከኔ ለማትረጊ ህይወቴን አትረብሽ።
ተኚ በትራስሽ
እንኳንስ ልተርፊኝ አትበቂም ለራስሽ።
አትምጪ
ከኔ ጩኸት ርቀሽ የራስሽን አድምጪ።
አንቀላፊ ባልጋሽ
በራስሽ ህልም ነው የሚተመን ዋጋሽ
አይደለም ባጃቢሽ ስምሽ የሚጻፈው
በየራስ እግር ነው ፥ ዳና ሚነደፈው።
ደግሞም አትኩራሪ
ድህረ ጠላነት ነውና ቅራሪ
እኔና አንቺንማ፥
መጨረሻችን ነው ፥ የሚዳኘን እኩል
መቃብር ስንገባ ፥ በሞት በር በኩል።
፫
እረፉ!
ንፁሕ ነን ለማለት ሰፈር አታከርፉ!
አትንኩን
ልክ ሳይኖራችሁ ፥ እኛን አትለኩን።
ኧረ ትርፍ የለውም፥ነገር አትፈልፍሉ
አዋቂ ለመባል ፥ እውቅና አትቀፍሉ!!
አድምጡን!
አትራፊ ለመባል ፥ በጫረታ አትሽጡን።
ለጋራችን ማጀት ፥ ምሰሶና ማገር
ስላገር ካነሳን፥
ምነው ብቻችሁን¡ ፥ እኛም እንናገር¡¡
ተዉ እረፉ!
እቤት ልታንጹ ሀገር አትዝረፉ።
ተው ግን አይበጅም ፥
ዲስኩር ለመኳኳል ፥ አትንገሩን ውሸት
ሀገርን ያፈርሳል ፥ ታሪክ ማበላሸት
ውርስም አታውርሱን፥ ያለንን አትቀሙን
በመወደድ ናፍቆት ፥ሙታን አታሰሙን።
ዛሬ በቁማችሁ ፥ ደግደጉን ስሩ
ክፋት ስትነግዱ ፥ለነገ እንዳትከስሩ።
#Dagim Hiwet
@getem
@getem
@getem
፩
ተው!
ከንፁሑ ልቤ አታኑር አንካካ
ኪስህን ልታደልብ አስራቴን አትንካ።
እረፍ!
ላታስታግስልኝ
ቁስሌን አታራግበው
ከዝንቦቹ ብሰህ ፥ ልታንገበግበው
አድብ
በንባዬ ጠብታ ኩሬህን አትገድብ።
፪
ይቅርብሽ
ከኔ ለማትረጊ ህይወቴን አትረብሽ።
ተኚ በትራስሽ
እንኳንስ ልተርፊኝ አትበቂም ለራስሽ።
አትምጪ
ከኔ ጩኸት ርቀሽ የራስሽን አድምጪ።
አንቀላፊ ባልጋሽ
በራስሽ ህልም ነው የሚተመን ዋጋሽ
አይደለም ባጃቢሽ ስምሽ የሚጻፈው
በየራስ እግር ነው ፥ ዳና ሚነደፈው።
ደግሞም አትኩራሪ
ድህረ ጠላነት ነውና ቅራሪ
እኔና አንቺንማ፥
መጨረሻችን ነው ፥ የሚዳኘን እኩል
መቃብር ስንገባ ፥ በሞት በር በኩል።
፫
እረፉ!
ንፁሕ ነን ለማለት ሰፈር አታከርፉ!
አትንኩን
ልክ ሳይኖራችሁ ፥ እኛን አትለኩን።
ኧረ ትርፍ የለውም፥ነገር አትፈልፍሉ
አዋቂ ለመባል ፥ እውቅና አትቀፍሉ!!
አድምጡን!
አትራፊ ለመባል ፥ በጫረታ አትሽጡን።
ለጋራችን ማጀት ፥ ምሰሶና ማገር
ስላገር ካነሳን፥
ምነው ብቻችሁን¡ ፥ እኛም እንናገር¡¡
ተዉ እረፉ!
እቤት ልታንጹ ሀገር አትዝረፉ።
ተው ግን አይበጅም ፥
ዲስኩር ለመኳኳል ፥ አትንገሩን ውሸት
ሀገርን ያፈርሳል ፥ ታሪክ ማበላሸት
ውርስም አታውርሱን፥ ያለንን አትቀሙን
በመወደድ ናፍቆት ፥ሙታን አታሰሙን።
ዛሬ በቁማችሁ ፥ ደግደጉን ስሩ
ክፋት ስትነግዱ ፥ለነገ እንዳትከስሩ።
#Dagim Hiwet
@getem
@getem
@getem
ጮክ ብለን አብረን ጮክ እንበል!
(ልዑል ኃይሌ)
.
ጮክ ብለን አብረን ጮክ እንበል!
ከሠው መሐል እንግባ
አቀርቅረን መኖር ይብቃን፤
በዝምታ ፈጅተነው ነው
ጊዜ ንቆን ለዚህ ያበቃን፤
እንጮሃለን ላንታፈን፤
ይበቃናል
ዝምታችን ለዘመናት የገረፈን፤
.
ጮክ ብለን አብረን ጮክ እንበል!
እንደተዋደድን እንደተላመድን፤
ተጋባን ተዳርን አንድ ልጅ ወለድን፤
አርባ መዓልት ሲሆን
በጥምቀቱ አምነን ክርስትና አነሳን፤
ስም ማውጣቱ ላይ ግን
መስማማት አቃተን ለፍቺ ተነሳን፤
ልጃችን አደገ መጥሪያ ስም ሳይኖረው፤
ባሻነው ሰይመን ባሻነው ጠራነው፤
ሁሉም እየጠራው
ሁሉንም አቤት ሲል ልጃችን ስም ረሳ፤
ግራ እንደተጋባ
ከተቀመጠበት በቁጭት ተነሣ፤
.
ጮክ ብለን አብረን ጮክ እንበል!
በስም ጥል ተኳርፈን
ትዳራችንንም ልጃችንም አጣን፤
በጋብቻችን ላይ የተማማልንበት
መፅሐፍ ቅዱስ ጥለን ሌላ ህግ አወጣን፤
ፍቺ በሚል ድንበር ቤትና አልጋ ለየን፤
መስታወቱን ሰበርን እንዳያተያየን፤
እንዳልተዋደድን
በቅፅበት ጥላቻ በስም ተረሣሣን፤
ልንጋደልበት ጠብ-መንጃ አነሣን፤
ልጃችንም መጣ
ሳንጠራው "ወይ!" ብሎ፤
በኛ ስም ወጥቶለት
በተኮስነው ጥይት ስሙን ተቀብሎ፤
.
ጮክ ብለን አብረን ጮክ እንበል!
በጥይቶቹ ድምፅ ልጃችን አገኘን፤
ሁሌም አቤት እንዲል
ተኩሳችን እንዳይቆም መጋደል ተመኘን፤
ልጃችንም "ወይ!" ሲል
አጋማሹን ዕድሜ በከንቱ ጨረሠው፤
ቢወጣም ባይወጣም
ስም የሌለው ፍቅር ስያሜ አፈረሰው፤
.
ጮክ ብለን አብረን ጮክ እንበል!
ለምን እንታፈን
የምን መቆዘም ነው ለምን ነው ዝምታ፤
"መሐረነ!.." እንበለው
"እግዚኦ!" በሚለው ቃል አፋችን ይፈታ፤
"እግዚኦ!" ለልጃችን
"እግዚኦ!" ለተኩሳችን ለጥላችን ማረን፤
የሠውን ሕግ ጥሠህ
ያንተን ሕግ አስተምረን፤
.
"እግዚኦ! መሐረነ!..."
በጠብ-መንጃው ፈንታ መስቀልህ ያስታርቀን፤
በጥበብህ ዋጅተህ በፍቅር አጥምቀን፤
ልጃችንም ይዳን ካ'ፍህ ስም እናውጣ፤
"ፍቅር!!..." እንበለው
ፍቅራችን ፍፁም ነው ካንተ ዘንድ ከመጣ፤
.
"እግዚኦ!..መሐረነ!.."
አለመደማመጥ ትዕቢት ገደለነ፤
ከጉርሻችን ነጥቀን ጠመንጃ አጎረስነ፤
ፋኖሳችን ሰብረን እሳቱን ለኮስነ፤
ከምንም ተነስተን ከምንም ደረስነ፤
"እግዚኦ መሐረነ!.."
..
አትቁጠር ሐጢያቱን
አትቁጠር ቂም በቀል፤
ስራችንን ትተህ
የሚያኳርፈንን ዘመን ሠይጣን ንቀል፤
በጠብ-መንጃው ፈንታ መስቀልህ ያስታርቀን፤
በጥበብህ ዋጅተህ በፍቅር አጥምቀን፤
ልጃችንም ይዳን ካ'ፍህ ስም እናውጣ፤
"ፍቅር!!..." እንበለው
ፍቅራችን ፍፁም ነው ካንተ ዘንድ ከመጣ፤
@getem
@getem
@getem
(ልዑል ኃይሌ)
.
ጮክ ብለን አብረን ጮክ እንበል!
ከሠው መሐል እንግባ
አቀርቅረን መኖር ይብቃን፤
በዝምታ ፈጅተነው ነው
ጊዜ ንቆን ለዚህ ያበቃን፤
እንጮሃለን ላንታፈን፤
ይበቃናል
ዝምታችን ለዘመናት የገረፈን፤
.
ጮክ ብለን አብረን ጮክ እንበል!
እንደተዋደድን እንደተላመድን፤
ተጋባን ተዳርን አንድ ልጅ ወለድን፤
አርባ መዓልት ሲሆን
በጥምቀቱ አምነን ክርስትና አነሳን፤
ስም ማውጣቱ ላይ ግን
መስማማት አቃተን ለፍቺ ተነሳን፤
ልጃችን አደገ መጥሪያ ስም ሳይኖረው፤
ባሻነው ሰይመን ባሻነው ጠራነው፤
ሁሉም እየጠራው
ሁሉንም አቤት ሲል ልጃችን ስም ረሳ፤
ግራ እንደተጋባ
ከተቀመጠበት በቁጭት ተነሣ፤
.
ጮክ ብለን አብረን ጮክ እንበል!
በስም ጥል ተኳርፈን
ትዳራችንንም ልጃችንም አጣን፤
በጋብቻችን ላይ የተማማልንበት
መፅሐፍ ቅዱስ ጥለን ሌላ ህግ አወጣን፤
ፍቺ በሚል ድንበር ቤትና አልጋ ለየን፤
መስታወቱን ሰበርን እንዳያተያየን፤
እንዳልተዋደድን
በቅፅበት ጥላቻ በስም ተረሣሣን፤
ልንጋደልበት ጠብ-መንጃ አነሣን፤
ልጃችንም መጣ
ሳንጠራው "ወይ!" ብሎ፤
በኛ ስም ወጥቶለት
በተኮስነው ጥይት ስሙን ተቀብሎ፤
.
ጮክ ብለን አብረን ጮክ እንበል!
በጥይቶቹ ድምፅ ልጃችን አገኘን፤
ሁሌም አቤት እንዲል
ተኩሳችን እንዳይቆም መጋደል ተመኘን፤
ልጃችንም "ወይ!" ሲል
አጋማሹን ዕድሜ በከንቱ ጨረሠው፤
ቢወጣም ባይወጣም
ስም የሌለው ፍቅር ስያሜ አፈረሰው፤
.
ጮክ ብለን አብረን ጮክ እንበል!
ለምን እንታፈን
የምን መቆዘም ነው ለምን ነው ዝምታ፤
"መሐረነ!.." እንበለው
"እግዚኦ!" በሚለው ቃል አፋችን ይፈታ፤
"እግዚኦ!" ለልጃችን
"እግዚኦ!" ለተኩሳችን ለጥላችን ማረን፤
የሠውን ሕግ ጥሠህ
ያንተን ሕግ አስተምረን፤
.
"እግዚኦ! መሐረነ!..."
በጠብ-መንጃው ፈንታ መስቀልህ ያስታርቀን፤
በጥበብህ ዋጅተህ በፍቅር አጥምቀን፤
ልጃችንም ይዳን ካ'ፍህ ስም እናውጣ፤
"ፍቅር!!..." እንበለው
ፍቅራችን ፍፁም ነው ካንተ ዘንድ ከመጣ፤
.
"እግዚኦ!..መሐረነ!.."
አለመደማመጥ ትዕቢት ገደለነ፤
ከጉርሻችን ነጥቀን ጠመንጃ አጎረስነ፤
ፋኖሳችን ሰብረን እሳቱን ለኮስነ፤
ከምንም ተነስተን ከምንም ደረስነ፤
"እግዚኦ መሐረነ!.."
..
አትቁጠር ሐጢያቱን
አትቁጠር ቂም በቀል፤
ስራችንን ትተህ
የሚያኳርፈንን ዘመን ሠይጣን ንቀል፤
በጠብ-መንጃው ፈንታ መስቀልህ ያስታርቀን፤
በጥበብህ ዋጅተህ በፍቅር አጥምቀን፤
ልጃችንም ይዳን ካ'ፍህ ስም እናውጣ፤
"ፍቅር!!..." እንበለው
ፍቅራችን ፍፁም ነው ካንተ ዘንድ ከመጣ፤
@getem
@getem
@getem
#በነፍስ መወራረድ!
(ሚካኤል አስጨናቂ )
።።።።።።።።።።።
የልቦናው እውነት ፥ ሳለ የረቀቀ
ለፈጠረው ፍጥረት.. .
መዳረሻ ግቡ ፥ ቀድሞ ከታወቀ
ኤልሻዳይ ነው ያልነው.. .
የአዳም ልጆች አባት ፥ የዓለሙ ቤዛ
ፍፃሜዋን ሲያውቀው ፥ የሰውን ነፍስያ
ነፃ ፍቃድ በሚል ፥ የነጋዴ ቋንቋ
ለፈተና ድሯት ፥ አወጣት ገበያ ።
#አሁን ይሄ ሸክላ !
አንዳንዴ ሲዘይድ...
ለእሳትና ውሀ ፥ ቀድሞ ተወስኖ
ከሲኦል ለመዳን...
ዱር ጫካ ሲከትም ፥ በስጋው መንኖ
በፅድቁ ጀግኖ ...
#አንዳንዴም ሲያጠፋ
ሕሊናው ሲያደብነው ፥ ገፅታው ሲከፋ
ሲጨነቅ ሲጠበብ ፥ በከንቱ ሲለፋ
እኔ ደግሞ እላለሁ ፥ እግዚሀር አጠፋ !
@getem
@getem
@paappii
(ሚካኤል አስጨናቂ )
።።።።።።።።።።።
የልቦናው እውነት ፥ ሳለ የረቀቀ
ለፈጠረው ፍጥረት.. .
መዳረሻ ግቡ ፥ ቀድሞ ከታወቀ
ኤልሻዳይ ነው ያልነው.. .
የአዳም ልጆች አባት ፥ የዓለሙ ቤዛ
ፍፃሜዋን ሲያውቀው ፥ የሰውን ነፍስያ
ነፃ ፍቃድ በሚል ፥ የነጋዴ ቋንቋ
ለፈተና ድሯት ፥ አወጣት ገበያ ።
#አሁን ይሄ ሸክላ !
አንዳንዴ ሲዘይድ...
ለእሳትና ውሀ ፥ ቀድሞ ተወስኖ
ከሲኦል ለመዳን...
ዱር ጫካ ሲከትም ፥ በስጋው መንኖ
በፅድቁ ጀግኖ ...
#አንዳንዴም ሲያጠፋ
ሕሊናው ሲያደብነው ፥ ገፅታው ሲከፋ
ሲጨነቅ ሲጠበብ ፥ በከንቱ ሲለፋ
እኔ ደግሞ እላለሁ ፥ እግዚሀር አጠፋ !
@getem
@getem
@paappii
አረፍተ ሀገር
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
አበበ ምንለው ፣ በሶ የሚበላ
ጩቤ እንደጨበጠ ፣ ለምናውቀው ጫላ
ጣሳ እያጠበ ፣ ለሚኖር ጨቡዴ
ሀገርሽ ሀገሬ
አረፍተ ነገር ላይ ፣ ትገኛለች ውዴ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ለምሳሌ ያህል ፣ ለውጥ ለከጀሉ
መንግስት አበበ ነው ፣ በሶ ደግሞ ቃሉ
ሳትገባሽ የምትኖር ፣ ስትገባኝ ሀገሬ
"መንግስት ቃል በላ"
የሚል ትርጉም አለው ፣ አረፍተ ነገሬ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ጫላ ባለ ስልጣን ፣ ስልጣን ደሞ ጩቤ
በጨበጡት ሁሉ...
ሲቆስል ይኖራል ፣ ህዝብሽና ህዝቤ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ጨቡዴ ሙስና ፣ ጣሳ ደሞ ህዝቡ
እርቃን የሚያስቀሩት ...
በየ መስሪያ ቤቱ ፣ ኪሱን እያጠቡ፡፡
@getem
@getem
@getem
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
አበበ ምንለው ፣ በሶ የሚበላ
ጩቤ እንደጨበጠ ፣ ለምናውቀው ጫላ
ጣሳ እያጠበ ፣ ለሚኖር ጨቡዴ
ሀገርሽ ሀገሬ
አረፍተ ነገር ላይ ፣ ትገኛለች ውዴ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ለምሳሌ ያህል ፣ ለውጥ ለከጀሉ
መንግስት አበበ ነው ፣ በሶ ደግሞ ቃሉ
ሳትገባሽ የምትኖር ፣ ስትገባኝ ሀገሬ
"መንግስት ቃል በላ"
የሚል ትርጉም አለው ፣ አረፍተ ነገሬ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ጫላ ባለ ስልጣን ፣ ስልጣን ደሞ ጩቤ
በጨበጡት ሁሉ...
ሲቆስል ይኖራል ፣ ህዝብሽና ህዝቤ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ጨቡዴ ሙስና ፣ ጣሳ ደሞ ህዝቡ
እርቃን የሚያስቀሩት ...
በየ መስሪያ ቤቱ ፣ ኪሱን እያጠቡ፡፡
@getem
@getem
@getem
😁1
እንኳን ከኔ ሰራሽ
°°°
አቤት ውበት! አቤት ማማር
እንደ አበባ ልክ እንደ ማር።
ወለላ ነሽ፣ ጥዑም ጣፋጭ
ታየኝ ውበት ተርፎሽ ሲረጭ።
ሺ ዓይና እንጀራ ይቅርብኝ
ያንቺ ዓይን ነው የሚያጠግበኝ
ካይኖችሽ ስር ተሰይሜ
ሲያስተዉሉኝ እያየሁኝ
ኮከብ እንጂ የማለዳ
ዓይኗ አይደለም ብዬ ማልኩኝ።
ከንፈርሽ ላይ ትክ ብዬ፣ አተኩሬ ስመረምር
ግር ይለኛል፣ አበባ ነው ወይስ ከንፈር?
የምን ከንፈር? አበባ ነው።
ንብ ያድርገኝ እንድቀስመው።
የለም የለም ይህ ቅጥፈት ነው።
አምላኳ ሆይ ይቅር በለኝ
ለጌጥም ከበቃት ነው
እንኳን ከንፈሯን ሊመስለኝ።
ካይኖችሽ ስር ተሰይሜ
ቀና እንዳልል ዓይንሽ ገታኝ
ፍቅርሽ ከአድማስ እራቀብኝ።
ከሁለንታ ረቀቀብኝ።
አቅም አጣሁ ለማቀርቀር
አነሁልሎኝ ውብ ማር ከንፍር።
የኔ ልዩ፣ ውብ ስጦታ
ቃላት አጣሁ ምን ልበልሽ?
አትሰልቺኝ ደጋግሜ ውብ ነሽ ስልሽ።
እራሴንም ይሄን ያህል የወደድኩት አይምሰልሽ
ብቻ እግዜሩን እግዜር ይስጠው
አንቺን መርጦ ከኔ ሰራሽ።
ከኔ ሰርቶም ለኔ አረገሽ።
የኔ ልዩ፣ አንቺ ማለት ውብም ቆንጆም ሙሉ ሴት ነሽ
አድማስ አልፎ የሚሻገር የዘላለም ሚዛኔ ነሽ።
©ዘርዓሰብ ሣጌጥ
፫\፪\፪፳፩፪ ዓ.ም
@getem
@getem
@getem
°°°
አቤት ውበት! አቤት ማማር
እንደ አበባ ልክ እንደ ማር።
ወለላ ነሽ፣ ጥዑም ጣፋጭ
ታየኝ ውበት ተርፎሽ ሲረጭ።
ሺ ዓይና እንጀራ ይቅርብኝ
ያንቺ ዓይን ነው የሚያጠግበኝ
ካይኖችሽ ስር ተሰይሜ
ሲያስተዉሉኝ እያየሁኝ
ኮከብ እንጂ የማለዳ
ዓይኗ አይደለም ብዬ ማልኩኝ።
ከንፈርሽ ላይ ትክ ብዬ፣ አተኩሬ ስመረምር
ግር ይለኛል፣ አበባ ነው ወይስ ከንፈር?
የምን ከንፈር? አበባ ነው።
ንብ ያድርገኝ እንድቀስመው።
የለም የለም ይህ ቅጥፈት ነው።
አምላኳ ሆይ ይቅር በለኝ
ለጌጥም ከበቃት ነው
እንኳን ከንፈሯን ሊመስለኝ።
ካይኖችሽ ስር ተሰይሜ
ቀና እንዳልል ዓይንሽ ገታኝ
ፍቅርሽ ከአድማስ እራቀብኝ።
ከሁለንታ ረቀቀብኝ።
አቅም አጣሁ ለማቀርቀር
አነሁልሎኝ ውብ ማር ከንፍር።
የኔ ልዩ፣ ውብ ስጦታ
ቃላት አጣሁ ምን ልበልሽ?
አትሰልቺኝ ደጋግሜ ውብ ነሽ ስልሽ።
እራሴንም ይሄን ያህል የወደድኩት አይምሰልሽ
ብቻ እግዜሩን እግዜር ይስጠው
አንቺን መርጦ ከኔ ሰራሽ።
ከኔ ሰርቶም ለኔ አረገሽ።
የኔ ልዩ፣ አንቺ ማለት ውብም ቆንጆም ሙሉ ሴት ነሽ
አድማስ አልፎ የሚሻገር የዘላለም ሚዛኔ ነሽ።
©ዘርዓሰብ ሣጌጥ
፫\፪\፪፳፩፪ ዓ.ም
@getem
@getem
@getem
👍1