ይህን ያህል ዘመን ፤
በኦና ጎጆው ውስጥ ፤
ምነው በባዶ ቤት ፤
ቆልፎ መቀመጥ ዘግቶ ብቻ ማውራት ፤
አይጨንቀውም ዛሬም በሩን ገርበብ አርጎ አይወጣም አንዳንዴ ፤
ትይኛለሽ አሉ የማለዳዋ ልጅ የከንፈር ወዳጄ፤
የልቤን አዳራሽ፤
በላምባዲና ቁልፍ፤
ቆልፈሽ የሄድሽው አንችው መሆንሽን ዘነጋሽው እንዴ???
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
በኦና ጎጆው ውስጥ ፤
ምነው በባዶ ቤት ፤
ቆልፎ መቀመጥ ዘግቶ ብቻ ማውራት ፤
አይጨንቀውም ዛሬም በሩን ገርበብ አርጎ አይወጣም አንዳንዴ ፤
ትይኛለሽ አሉ የማለዳዋ ልጅ የከንፈር ወዳጄ፤
የልቤን አዳራሽ፤
በላምባዲና ቁልፍ፤
ቆልፈሽ የሄድሽው አንችው መሆንሽን ዘነጋሽው እንዴ???
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
የ 2011 # የአመቱ_የመጨረሻው_ዝክረ_ኸሚስ
☞ ዝክረ ኸሚስ ( 43 )
..
ሰው በመሆን መንገድ
።።።።።።።።።።።።።።።።
ሸጋ ነፍስ ገልጦ ፣
ሰው በማለት ዜማ ፣
ከዱንያ እራስጌ ላይ የሀቁን ውብ ሀድራ እያንጎራጎረው ፣
" ስማኝማ " እያለ እርቀት ላይገረግር መድረስ ላያክረው።
የነፍሴን ባልጃ ፣
የጂስሜን ቢሊኮ ፣
ያፈር ገላ ልብሴን ቁረንጮየን ገፎ ድቤነት አውጥቶኝ ፣
ሲደባኝ ሰማሁት በውደታው መዳፍ እንደ ሀድራው ሽቶኝ ።
.
<< ብቻነት ጥፍጥናው ፣
ከነፍስህ አንጀት ላይ ደስ የሚል ህመሙ ፣
ሰው የሆንክ ለት ነው ጣሙ የሚገባህ የመሄጃ መሙ ።
ሰው ለመሆን ደግሞ ...
መነጠል አለብህ ከሚሸነግልህ ቁስልህን አግሞ ።
ለመነጠል ደግሞ ...
ካብሮነት ሊያጋልል በዳይ ያስፈልጋል ገፍታሪ ደጋግሞ ! >>
.
ይለኛል !
በገምሻራው ሌሊት ፣
ሀድራው ገደምዳሜ ፣
ጋሜው ክምብል ደፋ በኸሚሱ ሞገድ ፣
ዋናው ከኒያው ነው ቼቼ ለመኮልኮል ዝምቻው ላይታገድ ፣
በነፍስያ እንቅፋትገርፍጦ በሚያደርስ ሰው በማለት መንገድ ።
..
እውነቱን ነው !
ሰው የመሆን ጣሙ ...
የነፍስያን ቡጡ የእኔነትን ትግል ፣
ተጋጥመው ረተው እንደመገላገል ፣
የኔነትን አመል ከራስ እንደማግለል ፣
የሚጣፍጥ የለም መቻያ ላደለው ሀቁን ለጠቆመ ፣
ከመገፋት መንገድ በብቻነት ምርኩዝ ሰው ሆኖ ለቆመ ።
..
ሰው ነው የሰው ወንፊት ...
ግርዱ ተለይቶ ሰው የመሆን ፍሬ ለዘር እንዲታደም ፣
አዙሮ ‘ ሚመታ ካለም ግፋት በፊት ሰው ነው የሚቀደም ።
ያኔ ነው ከፍታ ፣
የከጀሉት መኖር ፣
ወና ሌሊት ገፍተው ፣
ብቻ ሲማልዱ ከቀን ወፍ ተቀድቶ ፈጅሩ ሲዘምር ፣
ያኔ ነው ሰው መሆን የወጋገኑ ቀን ንጋቱ ‘ ሚጀምር ።
.
ሰው መሆን አፍታ ነው ...
ማርፈጃ አያስደካም አይገፋም እስኪጠር እስኪመሽ ይርቃል
ደግሞ አፍታ ለመሆን በአቅል ለማስተንተን ብቻነት ይበቃል ።
ያኔ ...
ሰው በመሆን ንጋት ፣
ሰው በመሆምን ቀትር ፣
ሰው በመሆን ጀንበር ፣
በህብሩ ሰንጠረዥ በቀን ስሌት ግብር ፣
ሸጋ ህልም ፈትሎ ሌሊቱን ሲያደግስ ምሽቱ ሲነጠፍ ፣
በሰውነት ንጋት ሸጋ አድማስ ለመኳል ማምሻው ሲዘነጠፍ ፣
( ያኔ ነው ሰው መሆን )
በሚያቆስል ቀን ውስጥ በሚያገረሽ ሌሊት ፣
ባለፈው ሲያክሙት የህመሙን መግል የፊቱን በኋሊት ።
..
ሀየይይይ ... !
..
..
ሸጋ ነፍስ ገልጦ ፣
ሰው በማለት ዜማ ፣
ከዱንያ እራስጌ ላይ የሀቁን ውብ ሀድራ እያንጎራጎረው ፣
ስማኝማ እያለ እርቀት ላይገረግር መድረስ ላያክረው።
የነፍሴን ባልጃ ፣
የጂስሜን ቢሊኮ ፣
ያፈር ገላ ልብሴን ቁረንጮየን ገፎ ድቤነት አውጥቶኝ ፣
ሲደባኝ ሰማሁት በመወዳድ መዳፍ እንደ ሀድራው ሽቶኝ ።
..
እንግዲህ ምን እችል ፣
በምን አቅሜ ልዘልቅ የወዳጄን መዝሙር ፣
በገዛ እኔው ድቤ ሰው በመሆን አግቦ የናልኝን አሽሙር ።
አልጅልም ባልንጀር ፣
አልሶብርም ለይሉን ፣
በኸሚሱ ግላጭ የጠናውን ሃጃ ዘንበን ለማረስረስ ፣
የሙሃባን ፈረስ በሀድራ ለጉሜ በነፍሴ ለመድረስ ።
..
( ወዲህም እዝነት ነው .. )
ቢንድው ተማያልቅ ፣
ከፍቅሩ ቁልል ነገን መሻገሪያ ሊያድል ሲገመድል ፣
የሻለት ብቻ ነው ሰው እንሁን የሚል ወዳጅ የሚታደል ።
..
በልማ ባልንጀር ፣
መጣሁኝ እንግዲህ ፣
ካለመድረስ ወዲህ
ኸሚስ ሽቅርቅሩ ቀሃ ጀባው ደርሷል አወሉን ገምጨ ፣
የመሻገሪያውን የቀለሙን ቀንድል ቀንበጤን ሸምጥጨ ፣
አፍታም አላረፍድ ፣
ሰው በመሆን መንገድ ፣
በተገማሸረው በወዳጃው ጥርጊያ ደግ ልንገናኝ ፣
በኮከብ ምልክት በጠፍ ጨረቃ ሌት እደወጣ መናኝ ፣
በወለላው ሀድራ እንደ ከፋው ሽፍታ እያንጎራጎርኩኝ ።
እዘልቅልሃለሁ ... !!
___
ሙሀመድ ሙፍቲ ( ጀዋድ ) 💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
☞ ዝክረ ኸሚስ ( 43 )
..
ሰው በመሆን መንገድ
።።።።።።።።።።።።።።።።
ሸጋ ነፍስ ገልጦ ፣
ሰው በማለት ዜማ ፣
ከዱንያ እራስጌ ላይ የሀቁን ውብ ሀድራ እያንጎራጎረው ፣
" ስማኝማ " እያለ እርቀት ላይገረግር መድረስ ላያክረው።
የነፍሴን ባልጃ ፣
የጂስሜን ቢሊኮ ፣
ያፈር ገላ ልብሴን ቁረንጮየን ገፎ ድቤነት አውጥቶኝ ፣
ሲደባኝ ሰማሁት በውደታው መዳፍ እንደ ሀድራው ሽቶኝ ።
.
<< ብቻነት ጥፍጥናው ፣
ከነፍስህ አንጀት ላይ ደስ የሚል ህመሙ ፣
ሰው የሆንክ ለት ነው ጣሙ የሚገባህ የመሄጃ መሙ ።
ሰው ለመሆን ደግሞ ...
መነጠል አለብህ ከሚሸነግልህ ቁስልህን አግሞ ።
ለመነጠል ደግሞ ...
ካብሮነት ሊያጋልል በዳይ ያስፈልጋል ገፍታሪ ደጋግሞ ! >>
.
ይለኛል !
በገምሻራው ሌሊት ፣
ሀድራው ገደምዳሜ ፣
ጋሜው ክምብል ደፋ በኸሚሱ ሞገድ ፣
ዋናው ከኒያው ነው ቼቼ ለመኮልኮል ዝምቻው ላይታገድ ፣
በነፍስያ እንቅፋትገርፍጦ በሚያደርስ ሰው በማለት መንገድ ።
..
እውነቱን ነው !
ሰው የመሆን ጣሙ ...
የነፍስያን ቡጡ የእኔነትን ትግል ፣
ተጋጥመው ረተው እንደመገላገል ፣
የኔነትን አመል ከራስ እንደማግለል ፣
የሚጣፍጥ የለም መቻያ ላደለው ሀቁን ለጠቆመ ፣
ከመገፋት መንገድ በብቻነት ምርኩዝ ሰው ሆኖ ለቆመ ።
..
ሰው ነው የሰው ወንፊት ...
ግርዱ ተለይቶ ሰው የመሆን ፍሬ ለዘር እንዲታደም ፣
አዙሮ ‘ ሚመታ ካለም ግፋት በፊት ሰው ነው የሚቀደም ።
ያኔ ነው ከፍታ ፣
የከጀሉት መኖር ፣
ወና ሌሊት ገፍተው ፣
ብቻ ሲማልዱ ከቀን ወፍ ተቀድቶ ፈጅሩ ሲዘምር ፣
ያኔ ነው ሰው መሆን የወጋገኑ ቀን ንጋቱ ‘ ሚጀምር ።
.
ሰው መሆን አፍታ ነው ...
ማርፈጃ አያስደካም አይገፋም እስኪጠር እስኪመሽ ይርቃል
ደግሞ አፍታ ለመሆን በአቅል ለማስተንተን ብቻነት ይበቃል ።
ያኔ ...
ሰው በመሆን ንጋት ፣
ሰው በመሆምን ቀትር ፣
ሰው በመሆን ጀንበር ፣
በህብሩ ሰንጠረዥ በቀን ስሌት ግብር ፣
ሸጋ ህልም ፈትሎ ሌሊቱን ሲያደግስ ምሽቱ ሲነጠፍ ፣
በሰውነት ንጋት ሸጋ አድማስ ለመኳል ማምሻው ሲዘነጠፍ ፣
( ያኔ ነው ሰው መሆን )
በሚያቆስል ቀን ውስጥ በሚያገረሽ ሌሊት ፣
ባለፈው ሲያክሙት የህመሙን መግል የፊቱን በኋሊት ።
..
ሀየይይይ ... !
..
..
ሸጋ ነፍስ ገልጦ ፣
ሰው በማለት ዜማ ፣
ከዱንያ እራስጌ ላይ የሀቁን ውብ ሀድራ እያንጎራጎረው ፣
ስማኝማ እያለ እርቀት ላይገረግር መድረስ ላያክረው።
የነፍሴን ባልጃ ፣
የጂስሜን ቢሊኮ ፣
ያፈር ገላ ልብሴን ቁረንጮየን ገፎ ድቤነት አውጥቶኝ ፣
ሲደባኝ ሰማሁት በመወዳድ መዳፍ እንደ ሀድራው ሽቶኝ ።
..
እንግዲህ ምን እችል ፣
በምን አቅሜ ልዘልቅ የወዳጄን መዝሙር ፣
በገዛ እኔው ድቤ ሰው በመሆን አግቦ የናልኝን አሽሙር ።
አልጅልም ባልንጀር ፣
አልሶብርም ለይሉን ፣
በኸሚሱ ግላጭ የጠናውን ሃጃ ዘንበን ለማረስረስ ፣
የሙሃባን ፈረስ በሀድራ ለጉሜ በነፍሴ ለመድረስ ።
..
( ወዲህም እዝነት ነው .. )
ቢንድው ተማያልቅ ፣
ከፍቅሩ ቁልል ነገን መሻገሪያ ሊያድል ሲገመድል ፣
የሻለት ብቻ ነው ሰው እንሁን የሚል ወዳጅ የሚታደል ።
..
በልማ ባልንጀር ፣
መጣሁኝ እንግዲህ ፣
ካለመድረስ ወዲህ
ኸሚስ ሽቅርቅሩ ቀሃ ጀባው ደርሷል አወሉን ገምጨ ፣
የመሻገሪያውን የቀለሙን ቀንድል ቀንበጤን ሸምጥጨ ፣
አፍታም አላረፍድ ፣
ሰው በመሆን መንገድ ፣
በተገማሸረው በወዳጃው ጥርጊያ ደግ ልንገናኝ ፣
በኮከብ ምልክት በጠፍ ጨረቃ ሌት እደወጣ መናኝ ፣
በወለላው ሀድራ እንደ ከፋው ሽፍታ እያንጎራጎርኩኝ ።
እዘልቅልሃለሁ ... !!
___
ሙሀመድ ሙፍቲ ( ጀዋድ ) 💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
ሀገር ማለትማ...
(ሚካኤል አስጨናቂ )
.
ሀገር ማለት ሰው ነው ብለሽ ያልሽኝ ዕለት
ሀገር ሰው አይደለም እያልኩሽ ስሟገት
ምክንያት ነበረኝ!
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ትዝ ይልሽ እንደሆን እንዲህ እልሽ ነበር ከመስኩ ዳር ሆነን
ተራራውን ወንዙን ሜዳውን እያየን..
.
ዓለሜ!
ሀገር ማለት እኮ ተራራ ማለት ነው
ከምድር ከፍ አርጎ ፈጣሪ ያነፀው
.
ከተራራው አናት ከላይ ተቀምጠሽ
ቁልቁል እንደምታይ መስኩን ዝቅ ብለሽ
ሀገርም ያለሽ ቀን ከፍታው ያንቺ ነው
ከማማው አናት ላይ በኩራት እንደቆምሽ
ዝቅ ብለሽ ማየት ነው!
"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ!
ሀገር ማለትማ....
አዎን ተራራ ነው
ማንም እየካበ ማንም የሚያፈርሰው።
.
በቆመ ተራራ አናት የወጡ ለት
ከበላይ እንዳሉ የበታችን ማየት
አውቃለሁ ያኮራል..
እመኚኝ የኔ ውድ!
ሀገርም ያለሽ ቀን እንደዚህ ያደርጋል።
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
የተናደስ ዕለት?...
የተናደስ ዕለት ተራራው ሲፈርስ?!
ከፍታሽ ያልፍና ይጀመራል ማነስ
ወርዶ መገኘት ነው ቁመት መለካካት
ትከሻን አስታኮ አቀብ መንጠራራት
.
አየሽው ዓለሜ?
አየሽው ዓለሜ? .... ሀገር ተራራ ነው
ማንም እየካበ ማንም የሚያፈርሰው
.
ሀገር ማለትማ ሲክቡት የሚካብ በኩራት የሚያደምቅ
ሲንዱት የሚናድ ተስፋሽን የሚያደቅ
ተራራ ማለት ነው!
እና ታዲያ ፍቅሬ...
ዕውን አንቺ እንዳልሽው ሀገር ማለት ሰው ነው?
.
አይደለም የኔ ውድ!
ሀገር ሰው አይደለም!
ሀገር ማለትማ ሜዳና መስኩ ነው
ፈጣሪ አንጣሎ ዘርግቶ የጣለው።
አዎን!
.
አዎን!
.
አዎን ሀገር ማለት ሳር ያቆጠቆጠ ለጥ ያለ ሜዳ ነው
የቤት ብቻ ሳይሆን የጫካም እንስሳ መቶ የሚግጠው።.
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ
ሀገር ማለትማ ሜዳና መስክ ነው
ከጫካ ውስጥ ወቶ በቤት እንስሳ ላይ አለቃ መሆን ነው።
.
እና ታዲያ ዓለሜ
ሀገር ማለት ሰው ነው?
እኔ ብቻ ልጋጥ የሚሉት አባባል
የሰው ባህሪይ ነው?
.
አይደለም የኔ ውድ
አይደለም ዓለሜ
እንደውም ልንገርሽ.. .
ሀገር ማለትማ
ሀገር ማለትማ ፏፏቴው ወንዙ ነው
አፈር ተሸክሞ የመጓዝን ዕጣ ፈጣሪ የቸረው
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ!
ሀገር ማለትማ..ጉቶ እየነደሉ ግንድ ይዞ መዞር ነው
ማደሪያ ዳስ አጥቶ ህልምን መናፈቅ ነው
.
ሀገር መቆለል ነው
ሀገር መደርመስ ነው
ሀገር በመስክ ላይ
ቦርቆ መዝለል ነው
ግንድና አፈር ይዞ
ሲጓዙ እየዋሉ ሲጓዙ ማደር ነው።
እና አንቺ እንዳልሽ ሀገር ሰው አይደለም
ቀን እየተጓዙ ማታ በማሸለብ ሀገርነት የለም
.
እልሽ ነበር ያኔ ከመስኩ ዳር ሆነን
ተራራውን ወንዙን ሜዳውን እያየን።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ )
.
ሀገር ማለት ሰው ነው ብለሽ ያልሽኝ ዕለት
ሀገር ሰው አይደለም እያልኩሽ ስሟገት
ምክንያት ነበረኝ!
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ትዝ ይልሽ እንደሆን እንዲህ እልሽ ነበር ከመስኩ ዳር ሆነን
ተራራውን ወንዙን ሜዳውን እያየን..
.
ዓለሜ!
ሀገር ማለት እኮ ተራራ ማለት ነው
ከምድር ከፍ አርጎ ፈጣሪ ያነፀው
.
ከተራራው አናት ከላይ ተቀምጠሽ
ቁልቁል እንደምታይ መስኩን ዝቅ ብለሽ
ሀገርም ያለሽ ቀን ከፍታው ያንቺ ነው
ከማማው አናት ላይ በኩራት እንደቆምሽ
ዝቅ ብለሽ ማየት ነው!
"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ!
ሀገር ማለትማ....
አዎን ተራራ ነው
ማንም እየካበ ማንም የሚያፈርሰው።
.
በቆመ ተራራ አናት የወጡ ለት
ከበላይ እንዳሉ የበታችን ማየት
አውቃለሁ ያኮራል..
እመኚኝ የኔ ውድ!
ሀገርም ያለሽ ቀን እንደዚህ ያደርጋል።
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
የተናደስ ዕለት?...
የተናደስ ዕለት ተራራው ሲፈርስ?!
ከፍታሽ ያልፍና ይጀመራል ማነስ
ወርዶ መገኘት ነው ቁመት መለካካት
ትከሻን አስታኮ አቀብ መንጠራራት
.
አየሽው ዓለሜ?
አየሽው ዓለሜ? .... ሀገር ተራራ ነው
ማንም እየካበ ማንም የሚያፈርሰው
.
ሀገር ማለትማ ሲክቡት የሚካብ በኩራት የሚያደምቅ
ሲንዱት የሚናድ ተስፋሽን የሚያደቅ
ተራራ ማለት ነው!
እና ታዲያ ፍቅሬ...
ዕውን አንቺ እንዳልሽው ሀገር ማለት ሰው ነው?
.
አይደለም የኔ ውድ!
ሀገር ሰው አይደለም!
ሀገር ማለትማ ሜዳና መስኩ ነው
ፈጣሪ አንጣሎ ዘርግቶ የጣለው።
አዎን!
.
አዎን!
.
አዎን ሀገር ማለት ሳር ያቆጠቆጠ ለጥ ያለ ሜዳ ነው
የቤት ብቻ ሳይሆን የጫካም እንስሳ መቶ የሚግጠው።.
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ
ሀገር ማለትማ ሜዳና መስክ ነው
ከጫካ ውስጥ ወቶ በቤት እንስሳ ላይ አለቃ መሆን ነው።
.
እና ታዲያ ዓለሜ
ሀገር ማለት ሰው ነው?
እኔ ብቻ ልጋጥ የሚሉት አባባል
የሰው ባህሪይ ነው?
.
አይደለም የኔ ውድ
አይደለም ዓለሜ
እንደውም ልንገርሽ.. .
ሀገር ማለትማ
ሀገር ማለትማ ፏፏቴው ወንዙ ነው
አፈር ተሸክሞ የመጓዝን ዕጣ ፈጣሪ የቸረው
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ!
ሀገር ማለትማ..ጉቶ እየነደሉ ግንድ ይዞ መዞር ነው
ማደሪያ ዳስ አጥቶ ህልምን መናፈቅ ነው
.
ሀገር መቆለል ነው
ሀገር መደርመስ ነው
ሀገር በመስክ ላይ
ቦርቆ መዝለል ነው
ግንድና አፈር ይዞ
ሲጓዙ እየዋሉ ሲጓዙ ማደር ነው።
እና አንቺ እንዳልሽ ሀገር ሰው አይደለም
ቀን እየተጓዙ ማታ በማሸለብ ሀገርነት የለም
.
እልሽ ነበር ያኔ ከመስኩ ዳር ሆነን
ተራራውን ወንዙን ሜዳውን እያየን።
@getem
@getem
@getem
/////------/////
እንደ አባቴ ገዳይ ልክ እንደ ሉሲፈር ሁሌ እጠላሻለው፤
ድንገት ስቅ ሲለኝ እያነሳሺኝ መስሎኝ ፎቶሽን አያለው።
ይህው እስከዛሬ..........
ካንቺ ወይም ከኔ አለኝ ልቤ አልፀና፤
መጥላት እና መውደድ ሆነብኝ ፈተና።
[ በለጠ ተክሉ ]
@getem
@getem
@gebriel_19
እንደ አባቴ ገዳይ ልክ እንደ ሉሲፈር ሁሌ እጠላሻለው፤
ድንገት ስቅ ሲለኝ እያነሳሺኝ መስሎኝ ፎቶሽን አያለው።
ይህው እስከዛሬ..........
ካንቺ ወይም ከኔ አለኝ ልቤ አልፀና፤
መጥላት እና መውደድ ሆነብኝ ፈተና።
[ በለጠ ተክሉ ]
@getem
@getem
@gebriel_19
አርቲስት ተዘራ ለማ
ነብስህን በአፀደ ገነት ያኑርልን!! 🙏🙏
ማንንም ቢሆን ድንገት ማጣት ከባድ ነዉ። በተለይ ደግሞ የምትወደዉ ሰዉ ሲሆን ይከብዳል። ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጆቹና ለሙያ አጋሮቹ መፅናናትን እንመኛለን!!
#RIP😭
ነብስህን በአፀደ ገነት ያኑርልን!! 🙏🙏
ማንንም ቢሆን ድንገት ማጣት ከባድ ነዉ። በተለይ ደግሞ የምትወደዉ ሰዉ ሲሆን ይከብዳል። ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጆቹና ለሙያ አጋሮቹ መፅናናትን እንመኛለን!!
#RIP😭
👍1
((እጣ ፈንታ))
.......
ታቦት ይሰራ ዘንድ ፤ እንጨት ይመረጣል
ወንበር ይሰራ ዘንድ ፤ እንጨት ይፈለጋል
ታቦት ይከብር ዘንድ ፤ ሰው ይሸከመዋል
ወንበር ይዋረድ ዘንድ ፤ ሰው ይሰፍርበታል
ሸክላ ሰሪው ካለ አንድም ለዋንጫ ነው አንድ ለማሰሮ
ሸክላ ሰሪው ካለ አንድም ትከብራለህ አንድም ትወድቃለህ
ጴጥሮስ የወይን ዋንጫ የከበረ ታቦት
ይሁዳ እንስራ የወደቀ እንጨት
ጎን ለጎን ሆነው አብረው የበቀሉ
ተቆርጠው ሲወድቁ ፤ የህይታቸው ዳራ ፤የነፍሳቸው ትርጉም ሁሉም ለየቅሉ
ከአንድ ሸክላ አፈር የተድበለበሉ
አንዳቸው በወይን ሌሎቹ በጠላ እስከ አፍ ይሞላሉ
ታድያ እኔስ
ምን ይሆን እጣዬ
ምን አድርጎኝ ይሆን ያ ሸክላ ሰሪዬ
አድርጎኝ እንደሆን የዛ ጴጥሮስ ዘመድ
ወይስ ታንቄ እሞት በይሁዳ ገመድ
ሸክላነት እጣዬን ለይቼ ባላውቅም
በወይን መደሰቴ በጠላ መስከሬን ፈፅሜ አልተውም።
(((ሞሲሳ ደምሴ)))
@getem
@getem
@getem
.......
ታቦት ይሰራ ዘንድ ፤ እንጨት ይመረጣል
ወንበር ይሰራ ዘንድ ፤ እንጨት ይፈለጋል
ታቦት ይከብር ዘንድ ፤ ሰው ይሸከመዋል
ወንበር ይዋረድ ዘንድ ፤ ሰው ይሰፍርበታል
ሸክላ ሰሪው ካለ አንድም ለዋንጫ ነው አንድ ለማሰሮ
ሸክላ ሰሪው ካለ አንድም ትከብራለህ አንድም ትወድቃለህ
ጴጥሮስ የወይን ዋንጫ የከበረ ታቦት
ይሁዳ እንስራ የወደቀ እንጨት
ጎን ለጎን ሆነው አብረው የበቀሉ
ተቆርጠው ሲወድቁ ፤ የህይታቸው ዳራ ፤የነፍሳቸው ትርጉም ሁሉም ለየቅሉ
ከአንድ ሸክላ አፈር የተድበለበሉ
አንዳቸው በወይን ሌሎቹ በጠላ እስከ አፍ ይሞላሉ
ታድያ እኔስ
ምን ይሆን እጣዬ
ምን አድርጎኝ ይሆን ያ ሸክላ ሰሪዬ
አድርጎኝ እንደሆን የዛ ጴጥሮስ ዘመድ
ወይስ ታንቄ እሞት በይሁዳ ገመድ
ሸክላነት እጣዬን ለይቼ ባላውቅም
በወይን መደሰቴ በጠላ መስከሬን ፈፅሜ አልተውም።
(((ሞሲሳ ደምሴ)))
@getem
@getem
@getem
👍2
አባቶቹን ጠልፎ ፤
በጣላቸው ድንጋይ ፤
ልጅየው ሳይማር ዳግም ተደናቅፎ ወድቆ ከተደፋ፤
ድንጋዩ ልጁ እንጅ ድንጋይ ምን አጠፋ???
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
በጣላቸው ድንጋይ ፤
ልጅየው ሳይማር ዳግም ተደናቅፎ ወድቆ ከተደፋ፤
ድንጋዩ ልጁ እንጅ ድንጋይ ምን አጠፋ???
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
#እየሄዱ ~መግደል
፡
መንገድ የጀመረ
የሸፈተ ልብን
በተማፅኖ ምልጃ ላያስቀሩት ነገር
ህመሙ ቢከብድም
ምን አማራጭ አለ ከመሸኘት በቀር፡፡
፡
ያ'ንቺም ልብ እንዲያ ነው
የሸፈተ ተጓዥ
መንገድ የጀመረ ብኩን ስደተኛ
እኔም እንደዛ ነኝ
ህመሙ ያቃተኝ
አማራጭ አጥቼ
ልብሽን የሸኘው ቀሪ በሽተኛ፡፡
፡
መንገድሽ ህመሜ
መሸፈትሽ ፀፀት የህሊና ቁስል
ህመሜ ድህነትሽ
ስብራቴ ተስፋ ላንቺ መልካም እድል፡፡
፡
በበዛው ፍቅሬ ላይ
በአንድ የታጠረው የምርጫዬ ግድብ
ለነጠፈው ፍቅርሽ
እልፍ አማራጭ ሆኖ የፍላጎትሽ ግብ
ይኸው ባንቺ ቀዬ
የገባዎት ሰማይ
የማጠልቅ ጀንበር ፀሀይን አትሞ
በኔ ቀዬ ላይ ግን
እንደመሸ ቀረ ላይነጋ ጨልሞ፡፡
((ልብ አልባው ገጣሚ))
@getem
@getem
@gebriel_19
፡
መንገድ የጀመረ
የሸፈተ ልብን
በተማፅኖ ምልጃ ላያስቀሩት ነገር
ህመሙ ቢከብድም
ምን አማራጭ አለ ከመሸኘት በቀር፡፡
፡
ያ'ንቺም ልብ እንዲያ ነው
የሸፈተ ተጓዥ
መንገድ የጀመረ ብኩን ስደተኛ
እኔም እንደዛ ነኝ
ህመሙ ያቃተኝ
አማራጭ አጥቼ
ልብሽን የሸኘው ቀሪ በሽተኛ፡፡
፡
መንገድሽ ህመሜ
መሸፈትሽ ፀፀት የህሊና ቁስል
ህመሜ ድህነትሽ
ስብራቴ ተስፋ ላንቺ መልካም እድል፡፡
፡
በበዛው ፍቅሬ ላይ
በአንድ የታጠረው የምርጫዬ ግድብ
ለነጠፈው ፍቅርሽ
እልፍ አማራጭ ሆኖ የፍላጎትሽ ግብ
ይኸው ባንቺ ቀዬ
የገባዎት ሰማይ
የማጠልቅ ጀንበር ፀሀይን አትሞ
በኔ ቀዬ ላይ ግን
እንደመሸ ቀረ ላይነጋ ጨልሞ፡፡
((ልብ አልባው ገጣሚ))
@getem
@getem
@gebriel_19
👍1
*የኔ ትውልድ*
አገር ምድሩ ተራኮተ
አፍ ተወልዶ ጆሮ ሞተ
አዋቂነት ተሟሸሸ
አለማወቅ በረከተ
አፈር ለዘር ተሟገተ
አፈር ለአፈር ጉድጓድ ማሰ
አፈር ለአፈር ተካሰሰ
መበላላት መቀማማት
መጠላለፍ መተማማት
መተራመስ መንጠራወዝ
በነገር ላይ ነገር መምዘዝ
አንገት ለአንገት መገዛገዝ
እዚም እዚያም መወዛወዝ
ሚዛን ማጣት ማቀላቀል
ይሄን ከዚያ ያንን ከዚህ
ማደባለቅ ማመሳቀል
የህይወት ጭንቅ የዕለት ምስ
ደስታን ጥሎ ደስታን ማሰስ
ሰላም ጥሎ ሰላም ማሰስ
ፍቅርን ጥሎ ፍቅርን ማሰስ
እውነት ጥሎ እውነት ማሰስ
ይሄ ሆኗል የዛሬው ቅርስ
ህ¡ የኔ ትውልድ¡
[አቶ እገሌ]
@getem
@getem
@gebriel_19
አገር ምድሩ ተራኮተ
አፍ ተወልዶ ጆሮ ሞተ
አዋቂነት ተሟሸሸ
አለማወቅ በረከተ
አፈር ለዘር ተሟገተ
አፈር ለአፈር ጉድጓድ ማሰ
አፈር ለአፈር ተካሰሰ
መበላላት መቀማማት
መጠላለፍ መተማማት
መተራመስ መንጠራወዝ
በነገር ላይ ነገር መምዘዝ
አንገት ለአንገት መገዛገዝ
እዚም እዚያም መወዛወዝ
ሚዛን ማጣት ማቀላቀል
ይሄን ከዚያ ያንን ከዚህ
ማደባለቅ ማመሳቀል
የህይወት ጭንቅ የዕለት ምስ
ደስታን ጥሎ ደስታን ማሰስ
ሰላም ጥሎ ሰላም ማሰስ
ፍቅርን ጥሎ ፍቅርን ማሰስ
እውነት ጥሎ እውነት ማሰስ
ይሄ ሆኗል የዛሬው ቅርስ
ህ¡ የኔ ትውልድ¡
[አቶ እገሌ]
@getem
@getem
@gebriel_19
አሲማሙየ(አሴሞየ)
(የጳጉሜ የልጅነት ዝማሬያችን..በስነ ቃል አገጣጠም ስልት የተዘየነ)
የዘመን ጉንጉን ሹርቤ ገላዉ፤
የበጋዉ ካሳ የደም አባላዉ፤
የጸደይ ኩርፊያ የመጸዉ ምርጊት፤
የገሳዉ ድፎ ያገር መግላሊት፤
የከሰለ ገል ጠል የናፈቀዉ፤
የሰማይ ምጣድ እሳት የሞቀዉ፤
የሰማይ ግለት የወንዙ እሪታ፤
የጅረት ሀሩር የጥም ስቅታ፤
ሲንጠዉ ከርሞ እንደተኮሰ፤
የበጋዉ ሙሽር ቀልቡ ታመሰ።
በል ርገጥ ርገጥ እንዳሽከር በቅሎ፤
በል ሰበር ሰካ እንደ ሀይ ጃሎ፤
የቆላዉ እፊያ የደጋዉ ገንፎ፤
ሀምሌን ይጦማል በጋዉን ሰንፎ፤
በበጋዉ ሲዞር እግሩን ሲያማታ፤
አታዉቅም ሚስቱ እራቷን በልታ፤
የእጁን ስንፍና እንዳናይበት፤
ፍስለታ ግቢ ይላል በግንቦት፤
ገና በግንቦት ሰኔ ሳይገባ፤
ላርስ ነዉ ብሎ ሆዱ እየባባ፤
አመመኝ ብሎ ጋቲራ ገባ።
ጋቲራ ገብቶ የጠመቁት እለት፤
አርባ መጋኛ በእጁ ወጣለት፤
የመጋኛዉ ስም ቁጥሩ ሲፈታ፤
አባ ስንፍና አባ ቸልታ፤
ከቸልታዉ ላይ ሆዱ መብዛቱ፤
ቤተስኪያን ስማ አታዉቅም ሚስቱ፤
የአባ ሰነፍ ሚስት ተኝቶ አዳሪ፤
ያልበላችዉን ቂጣ ቆጣሪ፤
አፈረች አሉ ባደባባይ፤
መሬት ለመሬት እንደ እንጉዳይ፤
በቁና ጥርብብ ብድር ለመደች፤
ደሞ ለከርሞ እየተሳለች፤
ሀገሩ ሁላ ብድሯን ፈርቶ፤
ወይ አይላትም ጥሪዋን ሰምቶ፤
አዳ ዘንድሮ ቀየዉ ቢምራት፤
በሸንጎ ጠርቶ ምክር መከራት።
የሰነፉ ሚስት የአባ ሸንበቆ፤
በሽታ አይገለዉ ወይ አይሞት ታንቆ፤
ክረምቱ ሳያልፍ እሸት ሳይመጣ፤
ጋቲራ ሂዶ ጠበል ይጠጣ፤
መስከረም ሳይብት በጳጉሜይቱ፤
ባሴሞየ ወግ በእናት ባባቱ፤
የጁ ካሰኘዉ ጋራ ጊወርጊስ፤
መቻሬ ይዉረድ ማልዶ ይገስግስ፤
መስከረም ሳይብት ጣዩ ሳይመጣ፤
እጠቡኝ ብሎ አባ ጋር ይምጣ፤
በግንቦት ሀሩር በሰኔ ላይ፤
ቤትሽ ያልሞቀዉ ባደባባይ፤
የሰነፉ ሚስት ስንቅ የለሽቱ።
በእንተ ለማርያም በይ ባዛኝቱ፤
በእንቁጣጣሽ ቀን በመስከረሙ፤
መች ይጠቅምና ማንጎራጎሩ፤
በጳጉሜ ሰማይ በዉሃዉ ላይ፤
ባልሽን ይዘሽ ከጠበል ዋይ፤
የታጠበለ እለት የአሲማሙየ፤
ያኔ ነዉ አጀብ ባልሽን ላየ፤
ያቄመ ገላ ዝንጉ ሰዉነት፤
ጳጉሜ ያበራል የታጠበ እለት፤
በአሲማሙየ ዉሃ የነካ፤
በጳጉሜ ጠበል ህልሙን የለካ፤
የርዚቁ ድንበር የለዉም ድካ።
አሴማሙየ የልጅነቴ፤
የዉሀሽ ገላ ዉብ ምልክቴ፤
ይዞኛልና የበጋዉ ግርሻ፤
ጠልፎኛልና የዘመን ጥሻ፤
አረም ዉጦታል የፍቅሬን እርሻ፤
ባምስቱ ቀንሽ ልጠበልበት፤
ንጹህ ገላየን ላስመልስበት፤
አሴሞየ ..ሴሞ
አሲማሙየ..ሴሞ..
"እ..ንትን" ያለዉ…ከእንትናየ
ማን በነገረልኝ…
እረ እናንተ ሆየ…
አ..ሲ..ማ..ሙ..የ…አሴሞየ
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!💚
@getem
@getem
@balmbaras
(የጳጉሜ የልጅነት ዝማሬያችን..በስነ ቃል አገጣጠም ስልት የተዘየነ)
የዘመን ጉንጉን ሹርቤ ገላዉ፤
የበጋዉ ካሳ የደም አባላዉ፤
የጸደይ ኩርፊያ የመጸዉ ምርጊት፤
የገሳዉ ድፎ ያገር መግላሊት፤
የከሰለ ገል ጠል የናፈቀዉ፤
የሰማይ ምጣድ እሳት የሞቀዉ፤
የሰማይ ግለት የወንዙ እሪታ፤
የጅረት ሀሩር የጥም ስቅታ፤
ሲንጠዉ ከርሞ እንደተኮሰ፤
የበጋዉ ሙሽር ቀልቡ ታመሰ።
በል ርገጥ ርገጥ እንዳሽከር በቅሎ፤
በል ሰበር ሰካ እንደ ሀይ ጃሎ፤
የቆላዉ እፊያ የደጋዉ ገንፎ፤
ሀምሌን ይጦማል በጋዉን ሰንፎ፤
በበጋዉ ሲዞር እግሩን ሲያማታ፤
አታዉቅም ሚስቱ እራቷን በልታ፤
የእጁን ስንፍና እንዳናይበት፤
ፍስለታ ግቢ ይላል በግንቦት፤
ገና በግንቦት ሰኔ ሳይገባ፤
ላርስ ነዉ ብሎ ሆዱ እየባባ፤
አመመኝ ብሎ ጋቲራ ገባ።
ጋቲራ ገብቶ የጠመቁት እለት፤
አርባ መጋኛ በእጁ ወጣለት፤
የመጋኛዉ ስም ቁጥሩ ሲፈታ፤
አባ ስንፍና አባ ቸልታ፤
ከቸልታዉ ላይ ሆዱ መብዛቱ፤
ቤተስኪያን ስማ አታዉቅም ሚስቱ፤
የአባ ሰነፍ ሚስት ተኝቶ አዳሪ፤
ያልበላችዉን ቂጣ ቆጣሪ፤
አፈረች አሉ ባደባባይ፤
መሬት ለመሬት እንደ እንጉዳይ፤
በቁና ጥርብብ ብድር ለመደች፤
ደሞ ለከርሞ እየተሳለች፤
ሀገሩ ሁላ ብድሯን ፈርቶ፤
ወይ አይላትም ጥሪዋን ሰምቶ፤
አዳ ዘንድሮ ቀየዉ ቢምራት፤
በሸንጎ ጠርቶ ምክር መከራት።
የሰነፉ ሚስት የአባ ሸንበቆ፤
በሽታ አይገለዉ ወይ አይሞት ታንቆ፤
ክረምቱ ሳያልፍ እሸት ሳይመጣ፤
ጋቲራ ሂዶ ጠበል ይጠጣ፤
መስከረም ሳይብት በጳጉሜይቱ፤
ባሴሞየ ወግ በእናት ባባቱ፤
የጁ ካሰኘዉ ጋራ ጊወርጊስ፤
መቻሬ ይዉረድ ማልዶ ይገስግስ፤
መስከረም ሳይብት ጣዩ ሳይመጣ፤
እጠቡኝ ብሎ አባ ጋር ይምጣ፤
በግንቦት ሀሩር በሰኔ ላይ፤
ቤትሽ ያልሞቀዉ ባደባባይ፤
የሰነፉ ሚስት ስንቅ የለሽቱ።
በእንተ ለማርያም በይ ባዛኝቱ፤
በእንቁጣጣሽ ቀን በመስከረሙ፤
መች ይጠቅምና ማንጎራጎሩ፤
በጳጉሜ ሰማይ በዉሃዉ ላይ፤
ባልሽን ይዘሽ ከጠበል ዋይ፤
የታጠበለ እለት የአሲማሙየ፤
ያኔ ነዉ አጀብ ባልሽን ላየ፤
ያቄመ ገላ ዝንጉ ሰዉነት፤
ጳጉሜ ያበራል የታጠበ እለት፤
በአሲማሙየ ዉሃ የነካ፤
በጳጉሜ ጠበል ህልሙን የለካ፤
የርዚቁ ድንበር የለዉም ድካ።
አሴማሙየ የልጅነቴ፤
የዉሀሽ ገላ ዉብ ምልክቴ፤
ይዞኛልና የበጋዉ ግርሻ፤
ጠልፎኛልና የዘመን ጥሻ፤
አረም ዉጦታል የፍቅሬን እርሻ፤
ባምስቱ ቀንሽ ልጠበልበት፤
ንጹህ ገላየን ላስመልስበት፤
አሴሞየ ..ሴሞ
አሲማሙየ..ሴሞ..
"እ..ንትን" ያለዉ…ከእንትናየ
ማን በነገረልኝ…
እረ እናንተ ሆየ…
አ..ሲ..ማ..ሙ..የ…አሴሞየ
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!💚
@getem
@getem
@balmbaras
ልብ አልባው ገጣሚ
#አልደክምም~ስላንቺ
፡
የፊደላት ጥምረት
ቃላት እያነፀ ሀረግ አሰባጥሮ
ከልቤ ድርሳን ላይ
በምናብ ቀለማት ስንኞችን ፈጥሮ
ከነጩ ብራና
በሾተላይ ብዕር እንድፅፍሽ ሲያዘኝ
ለምን እንደው እንጃ
አንዳች ነገር አለ እጄን የሚይዘኝ፡፡
፡
ግን እታገላለሁ
ከሰማይ ማማ ስር ሰንደቅሽን አይቼ
ከፍታሽን ሳስብ
ብርታት እያገኘሁ ለዛሉ ክንዶቼ፡፡
፡
ያኔ ለመሻቴ
ሀሳብ እያማጥኩኝ ነፍሴ ብትገረጣም
እጄ ቢታሰርም
አንቺን ምፅፍበት ብልሀት አላጣም፡፡
፡
ስለዚህ ልፃፍሽ
እያነሱ መብለጥ ባንቺ ቢገለጥም
የካዱሽ ይካዱ
የ'ጆቼ መታሰር ከክብርሽ አይበልጥም፡፡
፡
እመኚኝ እምዬ
ከፍታሽ ክብሬ ነው አልቀርም ወድቄ
ሰላምሽ ይመለስ
ሁሌም በሰማይ ላይ ከፍ ይበል ሰንደቄ
እኔም እፅፋለሁ
መቼም ሳይታክተኝ ስንኞች አርቅቄ፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19
#አልደክምም~ስላንቺ
፡
የፊደላት ጥምረት
ቃላት እያነፀ ሀረግ አሰባጥሮ
ከልቤ ድርሳን ላይ
በምናብ ቀለማት ስንኞችን ፈጥሮ
ከነጩ ብራና
በሾተላይ ብዕር እንድፅፍሽ ሲያዘኝ
ለምን እንደው እንጃ
አንዳች ነገር አለ እጄን የሚይዘኝ፡፡
፡
ግን እታገላለሁ
ከሰማይ ማማ ስር ሰንደቅሽን አይቼ
ከፍታሽን ሳስብ
ብርታት እያገኘሁ ለዛሉ ክንዶቼ፡፡
፡
ያኔ ለመሻቴ
ሀሳብ እያማጥኩኝ ነፍሴ ብትገረጣም
እጄ ቢታሰርም
አንቺን ምፅፍበት ብልሀት አላጣም፡፡
፡
ስለዚህ ልፃፍሽ
እያነሱ መብለጥ ባንቺ ቢገለጥም
የካዱሽ ይካዱ
የ'ጆቼ መታሰር ከክብርሽ አይበልጥም፡፡
፡
እመኚኝ እምዬ
ከፍታሽ ክብሬ ነው አልቀርም ወድቄ
ሰላምሽ ይመለስ
ሁሌም በሰማይ ላይ ከፍ ይበል ሰንደቄ
እኔም እፅፋለሁ
መቼም ሳይታክተኝ ስንኞች አርቅቄ፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19
❤1👍1