*ህመም ፩***
በአንዲት ትንሽ ቅፅበት
በትንሽ መንደር ውሥጥ
ዙሪያየን ሥቃኘው
ይህ ነው የሚታየኝ.....
ሢጠጡ ያደሩ የጀዘቡ ነፍሶች
የተበታተኑ የቢራ ጠርሙሶች
ከበሩ ፊት ለፊት....
ሀገር የገነቡ ድንበር ያሥከበሩ
ጊዜ የጣላቸው ሠው ያላነሣቸው
ንፋሥ ላይ ተቀምጠው የሚራቡ ፊቶች
.....ትንሽ ዝቅ ብሎ...
ሁለት ልጅ ያዘለች
ከጡአት እሥከ ማታ ላፍታ ያላረፈች
የተጎሣቆለች ቆሎ ምትሸጥ እናት
ምንገድ ዳር ላይ ውላ ምንገድ የምታድር
..........................ማረፊያ የሌላት
ከዚህ አለፍ ብሎ...
ሽቶ ተርከፍክፈው ድሀ ተፀይፈው
የሚጉአዙ ጥንዶች..
ከነሡ ከፍ ብሎ
አየር ላይ ሚበሩ ጥንብ አንሣ ጭልፊቶች
..
ዱላ የጨበጠ ጋንጃ መቶ አዳሪ
ከቅርብ እርቀት ላይ..
እንዳላየ የሚያልፍ ሠላም አሥከባሪ
..
የተበታተኑ መፈክር የያዙ በጭሥ የታፈኑ
ሥራ አጥ ወጣቶች...
ከነሡ ፊት ለፊት...
ጥይት የታጠቁ እልፍ ወታደሮች
ከዚህ ሁሉ ጀርባ...
ግርማ የሌላቸው የፈረሡ ግንቦች
/ኅይሌ፩/
@getem
@getem
@getem
በአንዲት ትንሽ ቅፅበት
በትንሽ መንደር ውሥጥ
ዙሪያየን ሥቃኘው
ይህ ነው የሚታየኝ.....
ሢጠጡ ያደሩ የጀዘቡ ነፍሶች
የተበታተኑ የቢራ ጠርሙሶች
ከበሩ ፊት ለፊት....
ሀገር የገነቡ ድንበር ያሥከበሩ
ጊዜ የጣላቸው ሠው ያላነሣቸው
ንፋሥ ላይ ተቀምጠው የሚራቡ ፊቶች
.....ትንሽ ዝቅ ብሎ...
ሁለት ልጅ ያዘለች
ከጡአት እሥከ ማታ ላፍታ ያላረፈች
የተጎሣቆለች ቆሎ ምትሸጥ እናት
ምንገድ ዳር ላይ ውላ ምንገድ የምታድር
..........................ማረፊያ የሌላት
ከዚህ አለፍ ብሎ...
ሽቶ ተርከፍክፈው ድሀ ተፀይፈው
የሚጉአዙ ጥንዶች..
ከነሡ ከፍ ብሎ
አየር ላይ ሚበሩ ጥንብ አንሣ ጭልፊቶች
..
ዱላ የጨበጠ ጋንጃ መቶ አዳሪ
ከቅርብ እርቀት ላይ..
እንዳላየ የሚያልፍ ሠላም አሥከባሪ
..
የተበታተኑ መፈክር የያዙ በጭሥ የታፈኑ
ሥራ አጥ ወጣቶች...
ከነሡ ፊት ለፊት...
ጥይት የታጠቁ እልፍ ወታደሮች
ከዚህ ሁሉ ጀርባ...
ግርማ የሌላቸው የፈረሡ ግንቦች
/ኅይሌ፩/
@getem
@getem
@getem
*አንዴ ባይከፈል*
"""""""""፠""""""'''"''
ደርሶ ዛሬ ጠየኩ የትናቱ 'ያለ
በከፈልኩ ኖሮኝ ጠይቄው ከማለ!
ያለመድኩት ዱቤ ትላንት በሠጠውት
ካቲካላ ፣ አረቄ ቢተወኝ በተውኩት!
@getem
@getem
@getem
@Johny_Debx ✍ገጣሚ
"""""""""፠""""""'''"''
ደርሶ ዛሬ ጠየኩ የትናቱ 'ያለ
በከፈልኩ ኖሮኝ ጠይቄው ከማለ!
ያለመድኩት ዱቤ ትላንት በሠጠውት
ካቲካላ ፣ አረቄ ቢተወኝ በተውኩት!
@getem
@getem
@getem
@Johny_Debx ✍ገጣሚ
#አዬ_ሙሴ_ግሪክ
አንድ ግሪክ ነበር አሉ ከጠላት በፊት
አራት ኪሎ ሰፈር መጠጥ ምግብ ቤት
ከፍቶ የሚነግድ በጣም የታወቀ
መኳንንቱ ሳይቀር እየተሰረቀ
ጓዳው ተለይቶ ጉዱ እንዳይወጣ
እቤቱ የሚውል ሲበላ ሲጠጣ !
ከእለታት አንድ ቀን በሁዳዴ ቀን
ደንበኛው የሆነ አንድ መኮንን
ከለመዱት ጓዳ ተሰርቀው ገቡና
ሲበሉ ሲጠጡ ሲያወሩ ዋሉና
ሊወጡ ሲነሱ እንዲህ አሉት ሙሴን
"ሙሴ ልብ አድርግ በፃም ቀን መግደፌን
ኀላ እንዳትናገር ለማንም ቢሆን !
ትልቅ ሰው ነኝና ክርስቲያን አማራ
አገር ጉድ ይለኛል ስሜን ብትጠራ !"
ግሪኩም መለሰ " ጌታዬ ምን ቆርጦኝ
እርሶ ብቻ አይደሉም አደራ ያሉኝ !
ደጃዝማች ታፈሰ ባላምበራስ ግርማ
ቀኛዝማች አደራ እነራስ ይማማ
መኳንንቱ ሁሉ በጦም የሚበላ
አደራ ብሎኛል ከበላ በኃላ ፤
ስለዚህ ግዴለም አያስቡ ፍጹም
በኔ ይሁንብዎ ማንም አይሰማውም !"
አለና ሲጨርስ ሰውየው ደንግጠው
እንዲህ አሉ ይባላል ሲወጡ ተናደው
"አዬ ሙሴ ግሪክ ወራዳ ገገት
ምስጢር መያዙ ነው አሁን ባንተ ቤት !"
1951 አ.ም
አዲስ አበባ
የመስከረም ጮራ
#አሰፋ_ገ/ማርያም ተሰማ
@getem
@getem
@getem
አንድ ግሪክ ነበር አሉ ከጠላት በፊት
አራት ኪሎ ሰፈር መጠጥ ምግብ ቤት
ከፍቶ የሚነግድ በጣም የታወቀ
መኳንንቱ ሳይቀር እየተሰረቀ
ጓዳው ተለይቶ ጉዱ እንዳይወጣ
እቤቱ የሚውል ሲበላ ሲጠጣ !
ከእለታት አንድ ቀን በሁዳዴ ቀን
ደንበኛው የሆነ አንድ መኮንን
ከለመዱት ጓዳ ተሰርቀው ገቡና
ሲበሉ ሲጠጡ ሲያወሩ ዋሉና
ሊወጡ ሲነሱ እንዲህ አሉት ሙሴን
"ሙሴ ልብ አድርግ በፃም ቀን መግደፌን
ኀላ እንዳትናገር ለማንም ቢሆን !
ትልቅ ሰው ነኝና ክርስቲያን አማራ
አገር ጉድ ይለኛል ስሜን ብትጠራ !"
ግሪኩም መለሰ " ጌታዬ ምን ቆርጦኝ
እርሶ ብቻ አይደሉም አደራ ያሉኝ !
ደጃዝማች ታፈሰ ባላምበራስ ግርማ
ቀኛዝማች አደራ እነራስ ይማማ
መኳንንቱ ሁሉ በጦም የሚበላ
አደራ ብሎኛል ከበላ በኃላ ፤
ስለዚህ ግዴለም አያስቡ ፍጹም
በኔ ይሁንብዎ ማንም አይሰማውም !"
አለና ሲጨርስ ሰውየው ደንግጠው
እንዲህ አሉ ይባላል ሲወጡ ተናደው
"አዬ ሙሴ ግሪክ ወራዳ ገገት
ምስጢር መያዙ ነው አሁን ባንተ ቤት !"
1951 አ.ም
አዲስ አበባ
የመስከረም ጮራ
#አሰፋ_ገ/ማርያም ተሰማ
@getem
@getem
@getem
#ርእስ_አልባ
(ሀሳቡን እንደተረዳችሁት ርእስ ስጡልኝ 🙏 በፍቅር ጋበዝኳቹ)
በልብ ማህደር ባለው ክቡር ዙፋን
ከመለኮት ፀጋ የተቸረ ፍቅርን
መዋደድ 'ሚሰጠንን አፍልሶ ጥላቻን
በልባችን መንበር አንግሰን ካኖርን
ፍቅር #በልብ #ቃል #እስትንፋስ ዘርቶ
ህያው ያደርገናል በበረከት መልቶ
ግና እስትንፋስ የዘራ
በበረከት የተመላ የአፍቃሪ ልቡ
የ'ራስ ስሜት ብቻ ከሆነ ቀለቡ
ከ'ኔነት ጎጆ ወቶ እኛነት ቀዬ ካልገባ
የፍቅር ትርጉሙ ሆኗል የተዛባ......
እናማ ጃል ስማኝ
ከልብህ አድምጠኝ
የኦሪቱን ክዳን የአዲሱም መሰረት
የመለኮት ባህሪ ቃል የተገለጠበት
የተሸመነበት የጦቢያነት ጥለት
ድርና ማግ አድርጎ ዘላለም ሚያኖር
ትርጉሙ ተዛብቶ በታሪክ እንዳይቀር
ዘሩ ተጥሎ ፍሬን እንድናይ
እኔን እንተውና እኛ እንበል በአንድላይ
ከመለኮት ፀጋ እንድንሆን ተካፋይ
እርሱ እንኳን ሲናገር ፈጣሪ ሀያሉ
እንፍጠር ነው እንጂ ልፍጠር
አልነበረም ቃሉ።
✍ #መኳስ
@getem
@getem
@getem
(ሀሳቡን እንደተረዳችሁት ርእስ ስጡልኝ 🙏 በፍቅር ጋበዝኳቹ)
በልብ ማህደር ባለው ክቡር ዙፋን
ከመለኮት ፀጋ የተቸረ ፍቅርን
መዋደድ 'ሚሰጠንን አፍልሶ ጥላቻን
በልባችን መንበር አንግሰን ካኖርን
ፍቅር #በልብ #ቃል #እስትንፋስ ዘርቶ
ህያው ያደርገናል በበረከት መልቶ
ግና እስትንፋስ የዘራ
በበረከት የተመላ የአፍቃሪ ልቡ
የ'ራስ ስሜት ብቻ ከሆነ ቀለቡ
ከ'ኔነት ጎጆ ወቶ እኛነት ቀዬ ካልገባ
የፍቅር ትርጉሙ ሆኗል የተዛባ......
እናማ ጃል ስማኝ
ከልብህ አድምጠኝ
የኦሪቱን ክዳን የአዲሱም መሰረት
የመለኮት ባህሪ ቃል የተገለጠበት
የተሸመነበት የጦቢያነት ጥለት
ድርና ማግ አድርጎ ዘላለም ሚያኖር
ትርጉሙ ተዛብቶ በታሪክ እንዳይቀር
ዘሩ ተጥሎ ፍሬን እንድናይ
እኔን እንተውና እኛ እንበል በአንድላይ
ከመለኮት ፀጋ እንድንሆን ተካፋይ
እርሱ እንኳን ሲናገር ፈጣሪ ሀያሉ
እንፍጠር ነው እንጂ ልፍጠር
አልነበረም ቃሉ።
✍ #መኳስ
@getem
@getem
@getem
ስላልሺኝ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ተወኝ አልሺኝ ተውኩሽ
እንዳደገ ህጻን የእናት ጡት ወተት
በግድ እንዳስተዉት
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እርሳኝ አልሽኝ ረሳሁሽ
ከነመፈጠርሽ ማስታውሰው የለም
ባደጋ እንደመጣ የጭንቅላት ህመም
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ጥላኝ እንኳ ብትይ
ነፍሴን የሚገድል ጠላት እንደመጥላት
ከቃልሽ ላልወጣ ጠላሻለሁ መጥላት
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
የሚወደኝ ቢኖር ትዛዜን ይፈጽም
በፍቅር መጽሐፍ የፍቅር አምላክ እንዲል
ቃልሽ ትዛዜ ነው ያልሺው ይፈፀማል
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ሌላ ፈልግ ብትይ ሌላ ፍቅር ጀመርሁ
አትሆነኝም ላልሺው ምትሆነኝ አገኘሁ
ዞርበል ባልሺኝ ማግስት ሀገር ለቅቄአለሁ
ላይኔ የጠላሁሽ
ስላልሺኝ ነው እንጂ እኔ አፈቅርሻለሁ
ፍቅር ማለት ለኔ የተፈቃሪን ቃል ትዛዙን ማክበር ነው
መጽሐፉ እንደሚለው።
06/02/11
@getem
@getem
@getem
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ተወኝ አልሺኝ ተውኩሽ
እንዳደገ ህጻን የእናት ጡት ወተት
በግድ እንዳስተዉት
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እርሳኝ አልሽኝ ረሳሁሽ
ከነመፈጠርሽ ማስታውሰው የለም
ባደጋ እንደመጣ የጭንቅላት ህመም
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ጥላኝ እንኳ ብትይ
ነፍሴን የሚገድል ጠላት እንደመጥላት
ከቃልሽ ላልወጣ ጠላሻለሁ መጥላት
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
የሚወደኝ ቢኖር ትዛዜን ይፈጽም
በፍቅር መጽሐፍ የፍቅር አምላክ እንዲል
ቃልሽ ትዛዜ ነው ያልሺው ይፈፀማል
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ሌላ ፈልግ ብትይ ሌላ ፍቅር ጀመርሁ
አትሆነኝም ላልሺው ምትሆነኝ አገኘሁ
ዞርበል ባልሺኝ ማግስት ሀገር ለቅቄአለሁ
ላይኔ የጠላሁሽ
ስላልሺኝ ነው እንጂ እኔ አፈቅርሻለሁ
ፍቅር ማለት ለኔ የተፈቃሪን ቃል ትዛዙን ማክበር ነው
መጽሐፉ እንደሚለው።
06/02/11
@getem
@getem
@getem
🔥1
#የደርግ ዘመን
#የኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙር
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ -- ኢትዮጵያ ቅደሚ
በህብረሰባዊነት -- አብቢ ለምልሚ !
ቃል ኪዳን ገብተዋል -- ጀግኖች ልጆችሽ
ወንዞች ተራሮችሽ -- ድንግል መሬትሽ
ለኢትዮጵያ አንድነት -- ለነፃነትሽ
መስዋህት ሊሆኑ -- ለክብር ለዝናሽ !
ተራመጅ ወደፊት -- በጥበብ ጎዳና
ታጠቂ ለስራ -- ላገር ብልፅግና !
የጀግኖች እናት ነሽ -- በልጆችሽ ኩሪ
ጠላቶችሽ ይጥፉ -- ለዘላለም ኑሪ !
መስከረም 1 ቀን 1968 ዓ.ም
አዲስ አበባ
@getem
@getem
@getem
#የኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙር
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ -- ኢትዮጵያ ቅደሚ
በህብረሰባዊነት -- አብቢ ለምልሚ !
ቃል ኪዳን ገብተዋል -- ጀግኖች ልጆችሽ
ወንዞች ተራሮችሽ -- ድንግል መሬትሽ
ለኢትዮጵያ አንድነት -- ለነፃነትሽ
መስዋህት ሊሆኑ -- ለክብር ለዝናሽ !
ተራመጅ ወደፊት -- በጥበብ ጎዳና
ታጠቂ ለስራ -- ላገር ብልፅግና !
የጀግኖች እናት ነሽ -- በልጆችሽ ኩሪ
ጠላቶችሽ ይጥፉ -- ለዘላለም ኑሪ !
መስከረም 1 ቀን 1968 ዓ.ም
አዲስ አበባ
@getem
@getem
@getem
የአፋልጉኝ ማስታወቂያ
ወጣት ማሙሽ ቀጀላ ተክሌ
ይድረስ ልጅህ ማሙሽ ቀጀላ ነኝ ማለትም 1982 ዓ.ም ማጂ ከተማ ሻልት የሚባል ቦታ ስታስተምር ነበርበመቀጠል አሮ ተቀይረህ እኔም እዛው ተወልጄ እያለሁ ወደ አዲስ አበባ ከሄድክ በኃላ አልተመለስክም እናቴም ሰንበቴና እኔ ማሙሽ ቀጀላ ፈልገን የአንተን አድራሻ ለማግኘት አልቻልንም
ውድ ጋደኞቼ የአባት ቀጀላ ተክሌን አድራሻ የምታውቁት ካለችሁ ከታች በተገለፀው ስልክ ቁጥር እድትጠቁሙን በትህትና እንጠይቃለን።
Tel:-0910540871
@getem
@gebriel_19
ወጣት ማሙሽ ቀጀላ ተክሌ
ይድረስ ልጅህ ማሙሽ ቀጀላ ነኝ ማለትም 1982 ዓ.ም ማጂ ከተማ ሻልት የሚባል ቦታ ስታስተምር ነበርበመቀጠል አሮ ተቀይረህ እኔም እዛው ተወልጄ እያለሁ ወደ አዲስ አበባ ከሄድክ በኃላ አልተመለስክም እናቴም ሰንበቴና እኔ ማሙሽ ቀጀላ ፈልገን የአንተን አድራሻ ለማግኘት አልቻልንም
ውድ ጋደኞቼ የአባት ቀጀላ ተክሌን አድራሻ የምታውቁት ካለችሁ ከታች በተገለፀው ስልክ ቁጥር እድትጠቁሙን በትህትና እንጠይቃለን።
Tel:-0910540871
@getem
@gebriel_19
#መሄዴ ነው
ባር ባር አለ ሆዴ ፥ ልቤ መሬት ለቆ
ሊያከንፈኝ እንዳይሆን ፥ አለግብሩ መጥቆ
አለአስተዳደጉ ፥ አለባህሉ ወድቆ፡፡
ሽው እልም ሽው እልም ፥ ልቤ ወፌ-ይላላ
በመስተፋቅር ቀስት ፥ በሮሮ ምህላ
እንደደመና አክናፍ ፥እንደጮራው ጥላ
ሸው እልም ሽው እልም ፥ ሽው እልም ይላላ፡፡
ነሸጠው ፥ ሸፈጠ ፥ ሄደ ሸመጠጠ
በመስተፋቅር ጦር ፥ በሮሮ አመለጠ ፡፡
ብላቴን ጌታ ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
@yeaseratfere
@getem
@getem
@getem
ባር ባር አለ ሆዴ ፥ ልቤ መሬት ለቆ
ሊያከንፈኝ እንዳይሆን ፥ አለግብሩ መጥቆ
አለአስተዳደጉ ፥ አለባህሉ ወድቆ፡፡
ሽው እልም ሽው እልም ፥ ልቤ ወፌ-ይላላ
በመስተፋቅር ቀስት ፥ በሮሮ ምህላ
እንደደመና አክናፍ ፥እንደጮራው ጥላ
ሸው እልም ሽው እልም ፥ ሽው እልም ይላላ፡፡
ነሸጠው ፥ ሸፈጠ ፥ ሄደ ሸመጠጠ
በመስተፋቅር ጦር ፥ በሮሮ አመለጠ ፡፡
ብላቴን ጌታ ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
@yeaseratfere
@getem
@getem
@getem
#የታለ_ሰንደቅሽ?
የብዙ ሺ አመታት... የታሪክ አዝመራ
የጥበብ የፍቅር ...የሰላም ጎተራ
የሃይማኖት ትጋት ፀሎት ከበዛበት
በምግባር ትሩፋት ስብዕና ካ'በበት
ሳባ ወእስራኤል ከሆነ ነገድሽ
የጦቢያ ደምግባት ካለ በፊት ገፅሽ.....
ጥማትሽን ማርኪያ ውሀ 'ምትቀጂው
ፈለገ ጊዮን ከሆነ 'ምትጎነጪው
ገዳማት ሀሰሳ ጣና ኃይቅን ቀዝፈሽ
ማዕበሉን ካልፈሽ በረከትን ሽተሽ
ጥበብን ለማድነቅ በአንድም በሌላ
እግሮችሽ ካቀኑ ወደ ላሊበላ......
ጠዋት በማለዳ እርሱን ለማመስገን
ከገሰገሽ ፈጥነሽ ወደ አክሱም ጽዮን
ወደ ታላቁ ረመዳን
የአበው ደመቻው ዛሬ አንቺን ከሠራ
ኣንግሶ ካኖረሽ በዙፋኑ ስፍራ
የማንነት ኪዳን የጦቢያዊነትሽ
ከዙፋኑ በላይ የታለ ሰንደቅሽ ???
✍መኳስ✍
@getem
@getem
@getem
የብዙ ሺ አመታት... የታሪክ አዝመራ
የጥበብ የፍቅር ...የሰላም ጎተራ
የሃይማኖት ትጋት ፀሎት ከበዛበት
በምግባር ትሩፋት ስብዕና ካ'በበት
ሳባ ወእስራኤል ከሆነ ነገድሽ
የጦቢያ ደምግባት ካለ በፊት ገፅሽ.....
ጥማትሽን ማርኪያ ውሀ 'ምትቀጂው
ፈለገ ጊዮን ከሆነ 'ምትጎነጪው
ገዳማት ሀሰሳ ጣና ኃይቅን ቀዝፈሽ
ማዕበሉን ካልፈሽ በረከትን ሽተሽ
ጥበብን ለማድነቅ በአንድም በሌላ
እግሮችሽ ካቀኑ ወደ ላሊበላ......
ጠዋት በማለዳ እርሱን ለማመስገን
ከገሰገሽ ፈጥነሽ ወደ አክሱም ጽዮን
ወደ ታላቁ ረመዳን
የአበው ደመቻው ዛሬ አንቺን ከሠራ
ኣንግሶ ካኖረሽ በዙፋኑ ስፍራ
የማንነት ኪዳን የጦቢያዊነትሽ
ከዙፋኑ በላይ የታለ ሰንደቅሽ ???
✍መኳስ✍
@getem
@getem
@getem
ባዶህን ያዝ
1 2 3 4 5 6 7 8 9
በቁጥር አሀዝ ውስጥ
ለጥቆ ሚመጠው ስንት ነው ብላቹ
10 እንድትሉ ግልፅ ነው መልሳቹ
ግና ከ 0 አልጀመርክም ብሎ ሚጠይቀኝ
እርግጥ ነው ከመካከላቹ 1ም ሰው አላገኝ
ጥሪው እንኳን ቀርቶ ከትርጉም ማትገባ
ቀድማ ብትገኝም ቀድማ ማትጠራ
የመጀመሪያ መጀመሪያ
ባዶ ናት ምንም ናት 0 ናት
ብትደመር ብትቀነስ ዋጋም የላት
በጅ ላይ ላትታይ ከኪስ ላትወጣ
ምእናብ ብቻ ሆና ማትያዝ ማትመጣ
የመጀመሪያ መጀመሪያ
ባዶ ናት ምንም ናት 0 ናት
ጅማሬን ከባዶ
ማድረግን ማን ወዶ??
ሰራተኛው ጌታ ከባዶ ጀመረ
1 2 እያለ አለምን ፈጠረ
መፍጠር ብቻ ሳይሆን ማኖር ነው ትረጉሙ
ከእርሱ የወጣው የዘላለም ቃሉ
ሁሉን ቻዪ ጌታ ከባዶ ጀመረ
1 2 እያለ አለምን ፈጠረ
አናም አንተም ዛሬም
በመስረቅ ማምታታት በውሸት ድንጋይ ላይ ቁጢጥ ከምትል
አቋራጬን ሄደህ ጌታን ከምትጥል
ባዶህን ያዝና ካምላክህ ጋር ጀምር
ግጥም:ምህረት ሻውል(ምሬ)
@getem
@getem
@getem
1 2 3 4 5 6 7 8 9
በቁጥር አሀዝ ውስጥ
ለጥቆ ሚመጠው ስንት ነው ብላቹ
10 እንድትሉ ግልፅ ነው መልሳቹ
ግና ከ 0 አልጀመርክም ብሎ ሚጠይቀኝ
እርግጥ ነው ከመካከላቹ 1ም ሰው አላገኝ
ጥሪው እንኳን ቀርቶ ከትርጉም ማትገባ
ቀድማ ብትገኝም ቀድማ ማትጠራ
የመጀመሪያ መጀመሪያ
ባዶ ናት ምንም ናት 0 ናት
ብትደመር ብትቀነስ ዋጋም የላት
በጅ ላይ ላትታይ ከኪስ ላትወጣ
ምእናብ ብቻ ሆና ማትያዝ ማትመጣ
የመጀመሪያ መጀመሪያ
ባዶ ናት ምንም ናት 0 ናት
ጅማሬን ከባዶ
ማድረግን ማን ወዶ??
ሰራተኛው ጌታ ከባዶ ጀመረ
1 2 እያለ አለምን ፈጠረ
መፍጠር ብቻ ሳይሆን ማኖር ነው ትረጉሙ
ከእርሱ የወጣው የዘላለም ቃሉ
ሁሉን ቻዪ ጌታ ከባዶ ጀመረ
1 2 እያለ አለምን ፈጠረ
አናም አንተም ዛሬም
በመስረቅ ማምታታት በውሸት ድንጋይ ላይ ቁጢጥ ከምትል
አቋራጬን ሄደህ ጌታን ከምትጥል
ባዶህን ያዝና ካምላክህ ጋር ጀምር
ግጥም:ምህረት ሻውል(ምሬ)
@getem
@getem
@getem