ግጥም ብቻ 📘
67.3K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
ልብሽን ዝሪበት

አንገቴን ሰውተሽ
ሰማዕት ሁኚበት፥
ደሜን አንቆርቁረሽ
ቅኔ ዝረፊበት፥
አጥንቴንም ወስደሽ
ማኅሌት ቁሚበት፥
ንጠቂና ነፍሴን
ከመቃብር ወርደሽ
ሙታን አስነሺበት፥
ልቤን ግን ስትወስጂው
ዘር የለውምና
ልብሽን ዝሪበት።

💝💝 ሜሎስ 💝💝

@getem
@getem
@getem
አልሞትም
(በላይ በቀለ ወያ) በበእውቄ ስታይል
.
.
ስሚ
ፎቶ ባሳጥብም ፣ ልብሴን አቆሽሼ
ግዙፍ ነኝ በሚል ፊት ፣ ብታይም አንሼ
ሀገር እንደ ሀገር ፣
አንድ ሆና እንድትቀጥል ፣ አቅለ ቢስ መስዬ
እልፍ አእላፍ ጎልያድን ፣ በአንዲት ጠጠር ጥዬ
ልኩን ሳላሳውቅ ፣አቅሜን ሳላሳየው
ያልታወቀ ኋይል
የሚሉትን አካል ፣ ኋይሉን ሳላጋየው
ገንጣይ አስገንጣዩን ፣ ከህዝቡ ሳልለየው
ፍቅርሽ ቢገድለኝም፣ አልሞትም እንቢየው!
።።።

@getem
@getem
@gebriel_19
ኖር
(በተስፋ ብዙወርቅ)
በፊት በፊት ድሮ ድሮ፣
ድንጋይ ሁሉ ዳቦ ጠጠር ሁሉ ንፍሮ፣
በነበረበቱ
ኖር………… በጃንሆይ
ኖር ………… በእግዜሩ
ነበር ንግግሩ
በፊት በፊት ድሮ ድሮ
ጭልፊት ሳለች ዶሮ
ክንፍ ሳትሰፋ
ኖር ሲባል
ኖር
ኖራ ……… በግዜራ
ኖራ ……….. ሆራ
ሎን ኩመ ሆራ
የሺዎች አባት ሁን
እልፍ መንጋ አፍራ
በሺህ ሰው ተፈራ
ነበር ንግግሩ

ዛሬ ዛሬ
ተተወ ማክበር ሽበት
ኖር ቀረ ሆነ ተረት
ነበር ተብሎ የሚተረት
ያለውም ሆነ ካንገት
ከበደ ብድግ ከተቀመጡበት
ወገብ ስራ በዝቶበት፡፡

@getem
@getem
የሰምና ወርቅ ምድር !
__________________
እናትን እ_ናት ናት ብለን ቃል ካማጥን
ሀገርን ሀ_ገር ናት ብለን ከመሠከርን
ሰሟን(someone) እንፍጨርጨር ወርቋ ስለራቀን።

ብሩኬ(የወይን ፍሬ)

@getem
@getem
እቴን ለኔ ብቻ

እቴ ስትርቂኝ፣

ምሽቱ ጸጥ ይላል፣
ጀምበር ትሸሻለች፣
አጽናኝ ብርሀኗን፣
ትደብቀኛለች

ወፎች መዘመር፣
ማዜም ያቆማሉ፣
አንቺ እስክትመጪ፣
በድን ይሆናሉ

እቴ ስትርቂኝ

አበቦች አይፈኩም፣
ከዋክብት አያምሩም፣
ተራሮች ኮረብቶች፣
ሁሉም ያስጠሉኛል፣
ነፋስ በሌለበት፣
የፈዘዙት ዛፎች፣
አስጠልተውኛል

እኔ ለኔ ብቻ፣
የሆንኩኝ መሰለኝ፣
ይሄ ሰፊ ምድር፣
እጅጉን ጠበበኝ፣
ሽታ አልባው
ውሃ እንኳን
መራር መስሎ ታየኝ

ምድሩ ባዶ ሆነብኝ
ልቤም ተሸበረ፣
ናፍቆት ሽቅብ ስቦት፣
አንቺን ለመፈለግ፣
ሰማይ ሰማይ እያየ፣
ተለጥፎ ቀረ

ምን ሆኗል እያለ፣
ጎረቤት በሙሉ፣
አብሮ ያንሾካሹካል፣
እኔስ ምኑ ጨንቆኝ፣
እንኳን ለሰው ቀርቶ፣
የሚያስብሽ ልቤ፣
እኔን ጥሎ ከንፏል

እቴ ስትርቂኝ

በእረፍት አልባው
ምሽት
አይኔ ይስለመለማል፣
ሰዎች ይሸሹኛል፣
ግልምጫው ትችቱ፣
ሀሳቡ ጭንቀቱ፣
ጸንቶ ልብ ያደማል፣
የሚመረጥ የለም፣
ሁሉም ነገር ያማል

አድማሱ ጠቋቁሮ፣
ጀንበር ተለይታው፣
ወርቃማ ብርሀኗን፣
ከላዩ ላይ ገፋው፣
አእዋፍ በዙሪያው፣
መንዣበብ አቁመው፣
ሌላ አለም መሰለኝ፣
የናፍቆት ማእበል፣
ጸንቶ ሲያናውጠኝ

ዮሐንስ

@getem
@getem
@getem
((በላይ በቀለ ወያ))

አንቺ ሚያበሳጭሽ ፣ የኔ ፎቶ ማብዛት
እኔ ምጨነቀው
ዘር ላመማት ሀገር ፣ መድሐኒት ለመግዛት።
አንቺን ሚያስጨንቅሽ ፣ የወንዶች ጋጋታ
እኔን ሚያስጨንቀኝ ፣ የመንጋ ጫጫታ
።።።
አንቺ የምትዩኝ ፣ ገብተህ ተኛ መሽቷል
እኔ ግን የምልሽ
ሲሮጥ የታጠቀ ፣ ሲሸሽ ትጥቅ ይፈታል
።።።
አንቺ ምታወሪኝ ፣ ዋይፋይ ስለሞላ
እኔ የማወራሽ
ቴሌ ጅብ አስሬ ፣ ካርድ እየተበደርኩ ፣ ካርዴን ከሚበላ
አንቺ ሚያስጨንቅሽ ፣ ዘር ማንዘር ቆጣሪ
እኔ ሚያስጨንቀኝ ፣
"ያልታወቀ ኋይል ፣ ሚሉት አሸባሪ
የኔ ሀሳብ ሀገር ፣ ያንቺ ሀሳብ መንደር
እኔ ያልኩሽ ሰላም ዋይ ፣ አንች ያልሽኝ ደናደር
።።።
አንቺ ሚያምርሽ ዘፈን ፣ የሚያምረኝ ፉከራ
የኔ ርሃብ ፍቅር ፣ ያንቺ አምሮት እንጀራ
ምስለው ነጭ እርግብ ፣ ሚታይሽ ገጀራ
።።
ታዲያ እኔናአንቺ ፣በምን እንግባባ
ያንቺ ናፍቆት ዜማ ፣ የኔ ናፍቆት እንባ
ወሬያችን አንድነት ፣ ኑሯችን ለየቅል
አንቺ ሚያምርሽ ልቤ ፣ እኔ ሚያምረኝ ቅቅል (አስተናጋጅ መረቅ
ጭማሪ)
የኔ ተስፋ አንድነት ፣ያንቺ ተስፋ አንድ ቀን
ቋንቋ እንዴት ያግባባን ፣ ፍቅር እያራራቀን?

@getem
@getem
@getem
👍1
በጭድ ላይ ጭነት
"""""""''''፠""""""""፠"""""""

ተከምሮ ቁልል ጭድ ታይቶ ለእሳት
ተቃጥሎ ከቀረ አለፉት አመታት
*
ያ ሁሉ ተንዶ... ጭድ 'ና ጭነቱ
ሞልቶ አያቅ "ክምር" ቢለኝ ባለቤቱ
*
እኔም አልኩ ታዲያ~
ከስር ከስሩ መዘህ ፣ ከላይ ተመንምኖ
ጭድ እ'የት ያቅና መክበድ ተመዝኖ?
.

@getem
@getem
@Johny_Debx
የእንትን ግጥም(ልዑል ሀይሌ)
እንትን እንትን ላሉሽ እንትን አትበያቸው፤
እንትን ስለሆነ ነው እንትን እንትናቸው፤
.
እንትናም ነው መቼም የእንትን እንትኑ፤
እንትን አይሉትም እንትን ስላልሆኑ፤
እንትንሽን እንትን በይ እንትን እንዲያደርጉ፤
እንትን እንትን ይላል የእንትን እንትን ወጉ፤
.
እናም እንትናዬ...
እንትና እና እንትና እንትን ሲጠይቁ፤
እንትን አይምሰልሽ
እንትን ስላሉ ነው እንትን እያወቁ፤
.
እንትኔን 'ታቂያለሽ...
ጊዜውን ማያምን
እንደኔ ያለሰው ብዙ ይጠነቀቃል፤
መልዕክቴ ሲደርስሽ
በእንትን ተርጉሚው
እንትን ያልኩሽን ቃል፤
፬-፰-፳፻፲፩ ዓ.ም.

@gebriel_19
@getem
@getem
#ለሸገር#

ቅጠልሽ በፀሃይ ብዛት 'ማይጠወልግ
ዘር'ሽ የሰማንያ ብሄር ሃረግ፤
ፍቅርሽ፥እያደር አዲስ የሚያባባ
የማዕ'ዛሽም ጽጌ ፥እንደ ጥቅምት አባባ።

በስስት መወርወሪያ፥ ዉዴ ደጅሽ ከተዘጋ
ቶጵያዊነቴም ይታ'በይ ፥እንዳይቆጥሩኝ በለዉ ዜጋ
እነሆ
ሃገሬም ያለመዲና
ምድረ-በዳ ናትና።


መሪጌታ
@getem
@getem
ቆሎነት እና ብልሐት
(ልዑል ሀይሌ)

ቆሎ ነው ጥሬ ነው የአንዳንድ ሰው እውነት፤
ቆርጣሚን መማጠን የተዘገኑ ዕለት፤
ዘጋኝ እጅ ከገቡ ምን ምን ሊያ'ረግ መማጠን፤
ፈጣሪ ሆይ ስማን
ከመዘገን በፊት
ከሰፌድ ማምለጫ አንዳች ብልሐት ስጠን፤
፬-፰-፳፻፲፩ ዓ.ም.

@getem
@getem
@gebriel_19
Forwarded from SPACE COMPUTER
Forwarded from SPACE COMPUTER
#ድምፃችን_ሁሉም_ጋር_ይደርስ_
ዘንድ_ሼር_በማድረግ_የበኩላችንን_እንወጣ !!
.
እስቲ በዘረኝነት በጠባብነት በወገንተኝነት የጠበበውን ዓይናችንን እና ጆሯችንን እንክፈትና የሰውን ልጅ ሰቆቃ የሰውን ልጅ ተማፅኖእናዳምጥበት!!...እንይበት!!...ብሩ ህ ተስፋ ትባላለች..ስትወለድ እንደስሟ ብሩህ የሆነ ተስፋን ይዛ ይህቺን ምድር የተቀላቀለች ነገር ግን ባላሰበችውና ባልገመተችው አጋጣሚ የውፍረት ሆርሞን ችግር ገጥሟት በ2 ወራት ውስጥ 90 ኪሎ የጨመረች ሕክምናውም ሐገር ውስጥ እንደማይገኝ እና የውጪ ሕክምና ለማድረግ ደግሞ
700,000 ብር የተጠየቀች እህታችንን ወደ ጤንነቷ ትመለስ ዘንድ የበኩላችንን ጥረት እያደረግን እንገኛለን። አግዙን!!...አግዙን!!
...አግዙን!!...እባካችሁ ሰኞ ሚያዚያ 7 በሚቀርበው የኪነ-ጥበብ ምሽት ላይ በመገኘት "እኔም ብሩህ ተስፋን ላድን የተቻለኝን አደርጋለሁ!!..." የሚል የአጋርነት ድጋፋችሁ አይለየን።

አዘጋጆች:- እንድቅትዮን የኪነ-ጥበብ ቤተሠብ፤አለን የበጎ አድራጎት
ማሕበር፤ኑሃሚን ፕሮዳክሽን፤ከዋቢ ሸበሌ ሆቴል ጋር በመተባበር

@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
Ethiopia: “ለውጥ መጣ ሲሉን ድጋፍ እየወጣን ነፃ አውጪ ነን ሲሉን በሰልፍ እየወጣን ለውጥ ወዴት……
Andafta
"ለውጥ መጣ ሲሉን ድጋፍ እየወጣን ነፃ አውጪ ነን ሲሉን በሰልፍ እየወጣን ለውጥ ወዴት አለ መቼ ነፃ ወጥን!!” በበላይ በቀለ ወያ
👤


🕕 10:02
💾 1.2 mb
ግጥም ብቻ

@getem
@getem
@getem
" ፅኑ እንባ"

አዝማች ያንቺ ገላ ለሙዚቃው ነብሴ
እንዴት ሆኜ ልኑር ልሸሸግ ከራሴ...???
......ፍቅርሽ ዶቃ አመድ ነው ተውቦ እማይጠቅም
እንቡጥ ለነበረው ለልጅ እግር ልቤ ማሸበቻ ቀለም
እንጂ አንቺ ምን ተዳሽ ምን በደልሽ እናቴ
ከጅሽ ስሞትብሽ ልቅበርህ አልሽ እንጂ ከአፈሩ አከላቴ፡፡

✍️.......አብርሀም <ልጅ ኤቢ>

@getem
@getem
@gebriel_19
"ትስብእት"

ጉራጌ ነህ ብሎ ሲነግረኝ አባቴ
አንተ ሲዳማ ነህ አለችኝ አክስቴ
ሴት አያቴ ደግሞ ይሉኛል አማራ
ትግሬ ነህ ይለኛል የኔ ባልንጀራ
የእናቴ ዘመዶች በአንድ ድምፅ ባድማ
አንተ ኦሮሞ ነህ ማንንም አትስማ
ሲሉኝ ስለሰሙ ወንድ አያቴ ፈጥነው
ሀረሪ ነህ አሉኝ አመጣጤን ቆጥረው
የዚኔ ሲጨንቀኝ ስለገባኝ ግራ
ገበሬ ባልሆንም ገባሁ ዘር ቆጠራ
ጉራጌ ነህ ብለው ነግረውኝ የኖሩ
ምንጅላቶቼ ግን አርጎባ ነበሩ
ቅም አያቴ ምዕራብ ነበረ መዠንገር
ቅድመ አያቴ ደግሞ ምስራቅ ነበር ሀረር
አጎቴ ከሰሜን አግብቶ ኩናማ
አክስቴም ለደቡብ ተዳረች ሲዳማ
ሴት አያቶቼማ ስለተዘናጉ
ብዙ ሰው ተላልፏል በራቸው ሳይዘጉ
አባቴ ጉራጌ እናቴ ኦሮሞ
ታዲያ አሁን ምን ልሁን ምንስ ነበርኩ ቀድሞ
ብሔሬን ለማወቅ ያረግኩት ዘመቻ
ሆኜ ያገኘሁት ኢትዮጵያዊ ብቻ !

🇪🇹🇪🇹🇪🇹

@getem
@getem
@getem
ሰውየው ሩሚ ነው ገጣሚ ብቻ ሳይሆን በራሱ ግጥም የሆነ ሰው። በፐርሺያ እና በፐርሺያዊያን ልብ ውስጥ የማይጠፋ ብርሀን። ምንም እንኳን በ1273 በ66 አመቱ ይህቺን ዓለም ቢሰናበታትም ዓለም ግን ጨክና ልትሰናበተው አልቻለችም ምክንያቱም ከዛሬ 700 አመት በፊት የፃፋቸው ግጥሞች ህያው አድርገውታልና፤ እንደ ወይን ጠጅ እያደር የሚጣፍጡ ስንኞቹ ዛሬም ድረስ የማስደመም አቅማቸው የሚናቅ አይደለም።

ጀላለዲን ሙሀመድ ሩሚ የፐርሺያ ቅኔ ልብ።

በረከት በላይነህ የመንፈስ ከፍታ በተሰኘው ስራው የሩሚን ግጥሞች በስፋት አካቷል እዛ ላይ ብዙ የሩሚን ግጥሞች ማግኘት ትችላላችሁ ለዛሬ ግን አንድ የሩሚን ግጥም ተገባብዘን እንሰነባበት

if You want the moon...
do not hide at night.
if you want a rose...
do not run
from the thorns.
if you want love...
do not hide
from yourself.
(ሩሚ አንደፃፈው)
:
:
ጨረቃዋን ካሻህ
ከጭለማ ታረቅ
አበባዋን ካሻህ
ከሾሗ ተዋደቅ
ፍ ቅ ርን ከፈለክ
ከራስህ አትደበቅ።

( ወደ አማርኛ እንደመለስኩት)

©rumi!

#eyoba

@getem
@getem
@getem
#እኛ_ጓደኛሞቹ
አቅራቢ :ትንቢት ዳንኤል
ገጣሚ ፦ትንቢት ዳንኤል

@getem
@getem
ግጥም ብቻ
Belay Bekele Weya
ፍካሬ እውነት የሚለው የክቡር ሰው በእውቀቱ ስዩም ግጥም ወደ ዘመናችን ፖለቲካ ቢቀየርስ?
(በላይ በቀለ ወያ) ፈገግ ብላችሁ እደሩ
.
.
ሰማዩን
የአፄዎቹ ነገስታቶች፥ ሳይወረውሩት አርቀው
ፀሐይ ጨረቃ ሳይመጡበት ፣ በቀን በሌት ተፈራርቀው
ከዋክብቱ ሳይሰፍሩበት ፣ ከገበሬው ቦታ ነጥቀው
የአያቴ ምድር ነበር ፣ ቅድመ አያቴ የሚያርሰው
የአፄው ዘመን በጉልበቱ
ፈጣሪና መላእክቱን ፣ ከኛ ላይ ነው የወረሰው "
ብለሽ የነገርሺኝን ፣ እውነት ነው ተቀብያለሁ
ምክንያቱም አንቺ ታጥቀሻል ፣ ባዶ እጄን እፈራሻለሁ
።።።
“አያቴ
ሶስት ሺህ አመት ታገለ
ገና ሀምሣ አመት እያለ
አንዲት ኢትዮጵያን ለማቆም ፣አንድ አለም በጥፊ ጣለ
አንድ ጥይት ተኩሶ፣ ቢልየን ጠላት ገደለ
እልፍ አእላፍ ጎልያዶችን ፣ በአንዲት ጠጠር ረታ
ለቡሔ ጅራፍ ሲተኩስ
ኒውክለር ታጣቂው ሁሉ ፣ ደንግጦ ትጥቆቹን ፈታ
ብለሽ የነገርሺኝን ፣ እውነት ነው ተቀብያለኹ
ምክንያቱም አንቺ ታጥቀሻል ፣ ባዶ እጄን እፈራሻለሁ
።።
“አባቴ
ትግሉ ከታጋይ ይለያል
አይኑን ጨፍኖ ሲተኩስ ፣ ጠብመንጃው ዐይን አለው ያያል
እሱ ለሠላም ሲታገል ፣ ሰላም ባስ በእሳት ይጋያል
ብለሽ የነገርሺኝን እውነት ነው ተቀብያለኹ
ምክንያቱም አንቺ ታጥቀሻል ፣ ባዶ እጄን እፈራሻለሁ
።።።
ግና ..
ጅል እንዳልመስልሽ ፣አይደለሁም በፍፁም ሞኝ
በእርግጥ እውነት ብዬሻለሁ ፣ በባዶ እጄ መሞት ደክሞኝ
እየሮጠ ያስታጠቀሽ ፣ ሲሮጥ ትጥቅሽ እስኪላላ
እውነት ማለት
ከገዳይ ጋር መሰንበት ነው ፣ ሟቹ ትጥቁን እስኪያሟላ

@getem
@getem
@Bebra48
👍1
እዛ ጋር ዝም በሉ ! 🤫

በፍርሃት ደውል የምትናውዙ
ብልጥ በበዛበት እናንት 'ምትፈዙ

🤫 እዛ ጋር ዝም በሉ !

በሆነው ባልሆነው ሽቅብ 'ምታናፉ
አቅም የሌለው ላይ ከምትደነፉ

🤫 እዛ ጋር ዝም በሉ !

ሁለት ፍቅረኛሞች የተቃቃራቹ የአብርሃም የሳራ ካልመሠለላቹ

🤫 እዛ ጋር ዝም በሉ !

ቆሼ የሚለቅም ፊደል ያለቆጠረ
አወኩ አወኩኝ ባይ ቆሻሻ 'ምትጥሉ

🤫 እዛ ጋር ዝም በሉ !

ለማይጠቅም ነገር በወንድምህ ላይ ተንኮል የምትሰራ
አጅሬን በለጥከው በክፋት በሴራ

ካለምከው ሆነሃል ልብህ የማይራራ
ክፋት ተቆልሎ ሆነልህ ተራራ

ለማይጠቅም ነገር በእህትሽ ላይ ተንኮል የምትሰሪ
ልዕልናሽ ወድቋል ጠንከር አርገሽ ስሪ
በጨለማ ሆነሽ ባትበሪ እንኳን ብሪ

እናንተም እናንተም በልባቹ ጓዳ ሴራ የምትጭሩ
ነቀፋ ትታቹ ጠቃሚውን አውሩ
የሰው ስም ተነስቶ ቅስም ከምትሰብሩ

🤫 እዛ ጋር ዝም በሉ !

ወንዶቹኔ በሙሉ የመሸትሞክሪ
ከዚኛው ከዛኛው እንዳሻሽ 'ምታድሪ

🤫 እዛ ጋር ዝም በይ !
......

ልጁን ከሚደፍር አባት ካልጠበቀን
የሰው ሆደሸ ዘርግፎ ከሚያድር ወመኔ ዐይን ካልሰወረን
እቅፍ ድግፍ አርጎ በዘር ከሚያባላን ነቅቶ ካልከለለን
በምላስ አታሎ ሴቶቹን ለሚፈጅ ከሌለ እንኳን ፈራጅ

🤫 እኔ ዝም ልበል !


(በሀይሉ አርጋው)

@getem
@getem