መምህር ወምስክር
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በረዶው ቀለጠ . . .!
ምድር ሰውነት ላይ
ነፍስ አቀጠቀጠ፤
ጥውልግ ገላ ሁሉ
አምሮ ተገለጠ።
-
አበባን አየሽ ወይ?
ሕይወትን አየሽ ወይ?!
(ያበበ አበባና ሕይወት ምስስሉ፣
ከረገፉ ወዲያ እንደአዲስ መብቀሉ፤
መፍካትና መክሰም፥መክሰምና መፍካት
የፍጥረት አመሉ።)
-
ይሰማሻል ወይ ድምፅ . . .?
ይሰማሻል ወይ ድምፅ?!
ከሩ . . .ቅ የሚመጣ
የወንዝ ዜማ ወረብ፣
ግኡዝ አካል ያልነው
'ዮም ፍሥሓ ኮነ'
(ቀኑ ደስታ ሆነ)እያለ ሲደረብ።
ልብ ብለሽዋል ወይ . . .?
ልብ ብለሻል ወይ?!
ከመፀው ወፍ ዘሮች
ወርዶ ሲ-ን-ቆ-ረ-ቆ-ር
የቀን ደስታ ልሳን፣
ጥዩፍ ትላንትናን . . .
ባዲስ ቀን ቀይሮ
ነበርን ሲያስረሳን።
ልብ ብለሽዋል ወይ??
-
አስተውይ እንግዲህ . . .
አጣጥሚ በደንብ
የዘመንን ድግስ፥የወቅቶችን ዝክር፣
ከሰው ልጆች ይልቅ
መምህር ይሆናል . . .!
የተፈጥሮ ምክር፥ለፍቅርም ምስክር።
@getem
@getem
@paappii
በቃሉ ሙሉ ይማነው
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በረዶው ቀለጠ . . .!
ምድር ሰውነት ላይ
ነፍስ አቀጠቀጠ፤
ጥውልግ ገላ ሁሉ
አምሮ ተገለጠ።
-
አበባን አየሽ ወይ?
ሕይወትን አየሽ ወይ?!
(ያበበ አበባና ሕይወት ምስስሉ፣
ከረገፉ ወዲያ እንደአዲስ መብቀሉ፤
መፍካትና መክሰም፥መክሰምና መፍካት
የፍጥረት አመሉ።)
-
ይሰማሻል ወይ ድምፅ . . .?
ይሰማሻል ወይ ድምፅ?!
ከሩ . . .ቅ የሚመጣ
የወንዝ ዜማ ወረብ፣
ግኡዝ አካል ያልነው
'ዮም ፍሥሓ ኮነ'
(ቀኑ ደስታ ሆነ)እያለ ሲደረብ።
ልብ ብለሽዋል ወይ . . .?
ልብ ብለሻል ወይ?!
ከመፀው ወፍ ዘሮች
ወርዶ ሲ-ን-ቆ-ረ-ቆ-ር
የቀን ደስታ ልሳን፣
ጥዩፍ ትላንትናን . . .
ባዲስ ቀን ቀይሮ
ነበርን ሲያስረሳን።
ልብ ብለሽዋል ወይ??
-
አስተውይ እንግዲህ . . .
አጣጥሚ በደንብ
የዘመንን ድግስ፥የወቅቶችን ዝክር፣
ከሰው ልጆች ይልቅ
መምህር ይሆናል . . .!
የተፈጥሮ ምክር፥ለፍቅርም ምስክር።
@getem
@getem
@paappii
በቃሉ ሙሉ ይማነው
//አንዳንዴ //
ሲከፋኝ:~
ድንገት አስቀይሟት ወይም እሷ አጥፍታ
የሞቀውን ፍቅር የሳቁን ቤት ትታ
አሳየኝ አንድዬ ከባሏ ተፋታ
እያልኩኝ ልፀልይ ድንገት አስብና
ሀዘን ያጠላበት መልክሽን አይና
ተወው በቃ አምላኬ ምልጃዬን መልሰው
የኔን ልብ ትተህ የሷን እንባ አብሰው
እያለኩ ፀሎቴን ቀለብሰዋለው
ምክንያቱም ያኔ
አብረን በሰፋነው በለበስነው ሸማ
አፍሽ ከአፌ ላይ ጨዋታ እየቀማ
ያሳለፍነው ጊዜ ቀጭኑ ትውስታ
ካንቺ ባይነጥለኝ ሆኖብኝ ትዝታ
ያለጊዜ ወድጄ በጊዜ ባጣሽም
ክፉ አርገሻል ብዬ
አንቺን አልወቅስሽም
ይሄ ሁሉ ሀተታ ይሄ ሁሉ ወሬ
አንድ እውነት ልነግርሽ አስቤ ነው ዛሬ
የእስካሁኑ ይብቃ የያበጠው ይፈንዳ
አንቺንም አላሳቅ እኔም አልጎዳ
በሰፊው አደባባይ ብዙ ህዝብ ካለው
እንዲህ ይነበባል ምስጢሬን ብሰቅለው
ለሺህ የስሜቴ ጎርፍ ገላጭ ቃሉ አንድ ነው
"ባልነግርሽ ነው እንጂ ዛሬም ወድሻለው"
((ምንያህል ጥላሁን))
አዶኒስ
@getem
@getem
@gebriel_19
ሲከፋኝ:~
ድንገት አስቀይሟት ወይም እሷ አጥፍታ
የሞቀውን ፍቅር የሳቁን ቤት ትታ
አሳየኝ አንድዬ ከባሏ ተፋታ
እያልኩኝ ልፀልይ ድንገት አስብና
ሀዘን ያጠላበት መልክሽን አይና
ተወው በቃ አምላኬ ምልጃዬን መልሰው
የኔን ልብ ትተህ የሷን እንባ አብሰው
እያለኩ ፀሎቴን ቀለብሰዋለው
ምክንያቱም ያኔ
አብረን በሰፋነው በለበስነው ሸማ
አፍሽ ከአፌ ላይ ጨዋታ እየቀማ
ያሳለፍነው ጊዜ ቀጭኑ ትውስታ
ካንቺ ባይነጥለኝ ሆኖብኝ ትዝታ
ያለጊዜ ወድጄ በጊዜ ባጣሽም
ክፉ አርገሻል ብዬ
አንቺን አልወቅስሽም
ይሄ ሁሉ ሀተታ ይሄ ሁሉ ወሬ
አንድ እውነት ልነግርሽ አስቤ ነው ዛሬ
የእስካሁኑ ይብቃ የያበጠው ይፈንዳ
አንቺንም አላሳቅ እኔም አልጎዳ
በሰፊው አደባባይ ብዙ ህዝብ ካለው
እንዲህ ይነበባል ምስጢሬን ብሰቅለው
ለሺህ የስሜቴ ጎርፍ ገላጭ ቃሉ አንድ ነው
"ባልነግርሽ ነው እንጂ ዛሬም ወድሻለው"
((ምንያህል ጥላሁን))
አዶኒስ
@getem
@getem
@gebriel_19
ታምር አያልቅበት
ከጠላት ከደመኛዬ
በገጠመኝ ቢገጥም - የጉዟችን አቅጣጫ
የጎሪጥ እየተያየን
ያይጥ ና የድመት - የሌባ ፖሊስ ፍጥጫ
ኃላ ና ፊት ተፈራርተን - በጎንዮሽ ግርመማ
ጉዟችንን ሳንጨርስ
ብርሃን ተለወጠብን - ተደፋብን ጨለማ ::
በፍርሃት ተውጠን - ስንርድ ስንደናቀፍ
ተጣጥለን ለማለፍ - ለትግል ብንተቃቀፍ
የሚተናኮል አውሬ - ግብግባችንን ዓይቶ
ለሆዱ ቢፈልገንም - አለፈን ሳይበላን ፈርቶ
ምንም ቢፈጠር በሕይወት - በጎነው ማለት ለበጎ
እግዜር ታምር ይሰራል - እንዳንጠፋ ፈልጎ ፡፡
የአስራትፍሬ ይበልጣል ( ሮሪሳ )
ታህሳስ 26 / 2011 ዓ ም መቂ
@getem
@getem
@gebriel_19
ከጠላት ከደመኛዬ
በገጠመኝ ቢገጥም - የጉዟችን አቅጣጫ
የጎሪጥ እየተያየን
ያይጥ ና የድመት - የሌባ ፖሊስ ፍጥጫ
ኃላ ና ፊት ተፈራርተን - በጎንዮሽ ግርመማ
ጉዟችንን ሳንጨርስ
ብርሃን ተለወጠብን - ተደፋብን ጨለማ ::
በፍርሃት ተውጠን - ስንርድ ስንደናቀፍ
ተጣጥለን ለማለፍ - ለትግል ብንተቃቀፍ
የሚተናኮል አውሬ - ግብግባችንን ዓይቶ
ለሆዱ ቢፈልገንም - አለፈን ሳይበላን ፈርቶ
ምንም ቢፈጠር በሕይወት - በጎነው ማለት ለበጎ
እግዜር ታምር ይሰራል - እንዳንጠፋ ፈልጎ ፡፡
የአስራትፍሬ ይበልጣል ( ሮሪሳ )
ታህሳስ 26 / 2011 ዓ ም መቂ
@getem
@getem
@gebriel_19
# ሩብ_ጉዳይ
በሰለሞን ሳህሌ
ነብሴን ከነብስሽ አጣምረሽ ዓለም ጥግ ላይ ያኖርሽው
ሩብ ጉዳይ የሳምሽኝ ልጅ ጥበቡን ከየት ተማርሽው?
እውነት እውነት
ከንፈርሽ እጅግ ልዩ ነው የሜንት ጠረን ታድሏል
ሰሞኑን የሳምሽው ጉንጬ አየር ማስገባት ጀምሯል።
በሩብሽ እንዲህ የሆነው የጉንጬ ከንፈር ጥጉ
በሙሉ ቢሆን ኖሮማ ልቤና ነፍሴ ተማክረው እኔን ጥለውኝ ባረጉ።
እውነት እውነት
ለካንስ የመሳም ጥበብ እጅጉን እጅግ ተራቋል
በሜንት ጠረን ታጅቦ በሩብ ጉዳይ ልብ ይሰልባል
እኔ ምልሽ?
ይሄ የምሄድበት ጎዳና ጠረኑን በሜንት የናኘው
ንፋሱንም ልክ እንደኔ ሩብ ጉዳይ ስመሽው ነው?
እውነት እውነት
የምጠጣው የእግዜር ውሃ ጣዕም መልኩ ተቀይሯል
ግድ የለሽም አትደብቂኝ ውሃውንም ስመሽዋል?
ከሳሙስ አይቀር እንዲህ ነው ለስለስ አርጎ ሸረፍ አርጎ
መዓዛ ጠረን ደባልቆ በከንፈር አብሾ ልኮ
እንዲህ ነችኔ ሩብ ጉዳይ ወፈፍ አረገኝ እኮ
እናልሽ ከሳምሽኝ በኋላ ለሩብ ጉዳይ እጅ ሰጠው
ሠዓቱ ሙሉ ሆኖ እንኳን ሩብ ጉዳይ ነው እላለው
እውነት እውነት
ከመስታወቱ ፊት ቆሜ ከውስጡ እኔን እያየው
መተት አርጋብኝ ይሆን እያልኩ እጠይቃለው
የጉንጬን የከንፈሬን ጥግ በእጆቼ ዳብሳለው
የዳበስኩትን እጄን ሩብ ጉዳይ ስመዋለው
ወይ ጣጣዬ ወይ መከራ
ግድ የለሽም ልለምንሽ ግድ የለሽም ተለመኚኝ
አንድ ያጣላል ወዳጄ ሆይ ሩብ ጉዳይ አንዴ ሳሚኝ።
#መልስ ከጥያቄ ለሰለሞን ሳህለ #ከኤሽታ
እንኳን ንዑስ ሆነ
ከግማሽ ዝቅ አለ
እሰይ እሩብ ሆነ ከንኡስ ከፍ ያለ፤
የከንፈርን ሾርኔ የሽሙጥ የቻለ።
ጥበበ ስሞሽን ከልብ እየሳለ
አይነኬ ዝልፈት በምናብ ካኖረ
# ፀጋዬን አውጥቼ የውስጥ ፍኖቴን ቅኔ ካናገረ
እንኳን እሩብ ሆነ ከግማሽ ያነሰ
ንዑስ ላይሆን ወርዶ ቁልቁል ያልተማሰ
አልቦ ላይሆን ሞልቶ ከልብ ያልደረሰ፤
እንዲሞላ ተስፋ እንዳይጎልም ስጋት
የጨረፍታ ስሞሽ የእሩብ ጉዳይ ጥለት
አይገቡ ልኬትን በግጥም ያሰረ
እሩብ ጉዳይ ብሎ ቅኔ ካዘረፈ፤
ከንፈሯ ምን ይሁን በኪሎ ያረፈ?
@getem
@getem
@gebriel_19
በሰለሞን ሳህሌ
ነብሴን ከነብስሽ አጣምረሽ ዓለም ጥግ ላይ ያኖርሽው
ሩብ ጉዳይ የሳምሽኝ ልጅ ጥበቡን ከየት ተማርሽው?
እውነት እውነት
ከንፈርሽ እጅግ ልዩ ነው የሜንት ጠረን ታድሏል
ሰሞኑን የሳምሽው ጉንጬ አየር ማስገባት ጀምሯል።
በሩብሽ እንዲህ የሆነው የጉንጬ ከንፈር ጥጉ
በሙሉ ቢሆን ኖሮማ ልቤና ነፍሴ ተማክረው እኔን ጥለውኝ ባረጉ።
እውነት እውነት
ለካንስ የመሳም ጥበብ እጅጉን እጅግ ተራቋል
በሜንት ጠረን ታጅቦ በሩብ ጉዳይ ልብ ይሰልባል
እኔ ምልሽ?
ይሄ የምሄድበት ጎዳና ጠረኑን በሜንት የናኘው
ንፋሱንም ልክ እንደኔ ሩብ ጉዳይ ስመሽው ነው?
እውነት እውነት
የምጠጣው የእግዜር ውሃ ጣዕም መልኩ ተቀይሯል
ግድ የለሽም አትደብቂኝ ውሃውንም ስመሽዋል?
ከሳሙስ አይቀር እንዲህ ነው ለስለስ አርጎ ሸረፍ አርጎ
መዓዛ ጠረን ደባልቆ በከንፈር አብሾ ልኮ
እንዲህ ነችኔ ሩብ ጉዳይ ወፈፍ አረገኝ እኮ
እናልሽ ከሳምሽኝ በኋላ ለሩብ ጉዳይ እጅ ሰጠው
ሠዓቱ ሙሉ ሆኖ እንኳን ሩብ ጉዳይ ነው እላለው
እውነት እውነት
ከመስታወቱ ፊት ቆሜ ከውስጡ እኔን እያየው
መተት አርጋብኝ ይሆን እያልኩ እጠይቃለው
የጉንጬን የከንፈሬን ጥግ በእጆቼ ዳብሳለው
የዳበስኩትን እጄን ሩብ ጉዳይ ስመዋለው
ወይ ጣጣዬ ወይ መከራ
ግድ የለሽም ልለምንሽ ግድ የለሽም ተለመኚኝ
አንድ ያጣላል ወዳጄ ሆይ ሩብ ጉዳይ አንዴ ሳሚኝ።
#መልስ ከጥያቄ ለሰለሞን ሳህለ #ከኤሽታ
እንኳን ንዑስ ሆነ
ከግማሽ ዝቅ አለ
እሰይ እሩብ ሆነ ከንኡስ ከፍ ያለ፤
የከንፈርን ሾርኔ የሽሙጥ የቻለ።
ጥበበ ስሞሽን ከልብ እየሳለ
አይነኬ ዝልፈት በምናብ ካኖረ
# ፀጋዬን አውጥቼ የውስጥ ፍኖቴን ቅኔ ካናገረ
እንኳን እሩብ ሆነ ከግማሽ ያነሰ
ንዑስ ላይሆን ወርዶ ቁልቁል ያልተማሰ
አልቦ ላይሆን ሞልቶ ከልብ ያልደረሰ፤
እንዲሞላ ተስፋ እንዳይጎልም ስጋት
የጨረፍታ ስሞሽ የእሩብ ጉዳይ ጥለት
አይገቡ ልኬትን በግጥም ያሰረ
እሩብ ጉዳይ ብሎ ቅኔ ካዘረፈ፤
ከንፈሯ ምን ይሁን በኪሎ ያረፈ?
@getem
@getem
@gebriel_19
👍3
የሰማውን ይዞ ፤
ያየውን ጠምዝዞ ፤
ሁሉም በየጎራው ፤
ፊደል እየሻረ ፉከራ እያበዛ ፤
ጃሂል ልታይ አለ ፣
ተሸከሙኝ አለ ፤
ልክ እንደ ወሳንሳ ፤ ልክ እንደጂናዛ ።
ጃሂል ከምሸከም ፤
ድንጋይ ከምሸከም ፤ ትክሻየ አውጥቼ ፤
ኪታቤ ጋር ልዋል ፥
ዛሬም በስተርጅና፤ አንገቴን ደፍቼ ፤
የከተበ ሲሽር ፤
ይኸው ስንት ዘመን ፤ አይተዋል አይኖቼ ።
በዚህች በኛ ቀየ ፤
ጃሂል በየሜዳው ፤
ልርገጣችሁ ብሎ ፤ ስለሚደነፋ ፤
ይማረን እያለ ፤
ቀለሜው በሙሉ ፤ ቀለም ላይ ተደፋ! !!!!
@getem
@getem
@paappii
Mengistu zegeye
ያየውን ጠምዝዞ ፤
ሁሉም በየጎራው ፤
ፊደል እየሻረ ፉከራ እያበዛ ፤
ጃሂል ልታይ አለ ፣
ተሸከሙኝ አለ ፤
ልክ እንደ ወሳንሳ ፤ ልክ እንደጂናዛ ።
ጃሂል ከምሸከም ፤
ድንጋይ ከምሸከም ፤ ትክሻየ አውጥቼ ፤
ኪታቤ ጋር ልዋል ፥
ዛሬም በስተርጅና፤ አንገቴን ደፍቼ ፤
የከተበ ሲሽር ፤
ይኸው ስንት ዘመን ፤ አይተዋል አይኖቼ ።
በዚህች በኛ ቀየ ፤
ጃሂል በየሜዳው ፤
ልርገጣችሁ ብሎ ፤ ስለሚደነፋ ፤
ይማረን እያለ ፤
ቀለሜው በሙሉ ፤ ቀለም ላይ ተደፋ! !!!!
@getem
@getem
@paappii
Mengistu zegeye
👍1
# ሃገረ_ኢትዮጵ
°
በታላቁ መፅሃፍ ፥ ታሪኩ የሰፈረ
እዮብ ሰው አይደለም ፥ በምድር የኖረ።
°
"እዮብ" የተባለች
ምስኪን ሀገሬ ነች፤
ልጆች ሞተውባት
ገላዋ ተልቶባት
አመድ ላይ የተኛች።
°
በእምነት ተንበርክካ ፥ እጆቿን ዘርግታ
ምህረት የምትለምን ፥ ከሠራዊት ጌታ።
ወዳጅ ዘመዶቿ ፥ ሰድበሽው ሙች ሲሏት
"ሰጠ! -- ነሳ!" ብላ ፥ የምትኖር በፅናት።
~~~~~~~~~//~~~~~~~~~
( በርናባስ ከበደ )
@getem
@getem
@gebriel_19
°
በታላቁ መፅሃፍ ፥ ታሪኩ የሰፈረ
እዮብ ሰው አይደለም ፥ በምድር የኖረ።
°
"እዮብ" የተባለች
ምስኪን ሀገሬ ነች፤
ልጆች ሞተውባት
ገላዋ ተልቶባት
አመድ ላይ የተኛች።
°
በእምነት ተንበርክካ ፥ እጆቿን ዘርግታ
ምህረት የምትለምን ፥ ከሠራዊት ጌታ።
ወዳጅ ዘመዶቿ ፥ ሰድበሽው ሙች ሲሏት
"ሰጠ! -- ነሳ!" ብላ ፥ የምትኖር በፅናት።
~~~~~~~~~//~~~~~~~~~
( በርናባስ ከበደ )
@getem
@getem
@gebriel_19
ዘፈንና ሙሾ ተዳቅለው ነው አሉ
አንቺን የፈጠሩ፥
ላ'ቤት የቸኮሉ
አንዳቸው ሲጠሩ፤
እስኪ ቆይ ይግረመኝ
እነሱ ተዳቅለው
አንቺን ካበቀሉ፥
በ'ኔ ትብስ ፍጭት
እኛን ሲበቀሉ፤
መካሪ እንዳቶኚ
ተቆጭ አስታራቂ፥
ልቅሶሽ ወዴት ጠፋ
እዝጎን አሟሟቂ?
*
ሳቂ ግዴለኝም
ዘፈንሽ አይንጠፍ፥
ከውብ ጥርሶችሽ ላይ
ዘንዶ ከሚለጠፍ፤
*
ሳቂ ግድ የለሽም!
ካንቺ ወዲያ ላንቺ
ስላንቺ ሊያውቅ የሻ
ሥርሽን አጠና፥
ከህልቀትሽ ቀድሞ
ዘርሽ ላይ አቀና፤
አባትሽ ሙሾ ነው አፈር የዘገነ፥
እናትሽም ዘፈን
እዚህ እዛ ፈሶ የተበታተነ፤
ከዘፈን ተወልደሽ በሙሾ እንድታልቂ፥
ተጽፎ ነው መሰል
በዘመናት መሀል በስተት ማትስቂ!
*
አንቺዬ!?
ሳቂ ግዴለሽም የጥርሶችሽ ስድር
ሰርክ ይተራመሱ፥
አልቅሽ እባክሽን ዘለላ እምባወችሽ
አፈሩን ሲያርሱ፤
አዲስ ታሪክ በቅሎ
ቡቃያ ከወጣ
ፍሬ አናጣም እኛ፥
አይጨክንምና
ከላይ ያለ ዳኛ።
*
ሳቂ ግድ-የለሽም
ደግሞ አልቅሽ ነፍርቂ፥
ሞላ ብለሽ ዘለሽ ከደጁ እንዳ'ርቂ።
ለምን ካልሽ?
*
ሳቅሽ ምሥጋና ነው
ልቅሶሽ የልመና፥
ከእግዜር ስትጣዪ አንች የለሽምና::
@getem
@getem
@paappii
Mitu yimer
አንቺን የፈጠሩ፥
ላ'ቤት የቸኮሉ
አንዳቸው ሲጠሩ፤
እስኪ ቆይ ይግረመኝ
እነሱ ተዳቅለው
አንቺን ካበቀሉ፥
በ'ኔ ትብስ ፍጭት
እኛን ሲበቀሉ፤
መካሪ እንዳቶኚ
ተቆጭ አስታራቂ፥
ልቅሶሽ ወዴት ጠፋ
እዝጎን አሟሟቂ?
*
ሳቂ ግዴለኝም
ዘፈንሽ አይንጠፍ፥
ከውብ ጥርሶችሽ ላይ
ዘንዶ ከሚለጠፍ፤
*
ሳቂ ግድ የለሽም!
ካንቺ ወዲያ ላንቺ
ስላንቺ ሊያውቅ የሻ
ሥርሽን አጠና፥
ከህልቀትሽ ቀድሞ
ዘርሽ ላይ አቀና፤
አባትሽ ሙሾ ነው አፈር የዘገነ፥
እናትሽም ዘፈን
እዚህ እዛ ፈሶ የተበታተነ፤
ከዘፈን ተወልደሽ በሙሾ እንድታልቂ፥
ተጽፎ ነው መሰል
በዘመናት መሀል በስተት ማትስቂ!
*
አንቺዬ!?
ሳቂ ግዴለሽም የጥርሶችሽ ስድር
ሰርክ ይተራመሱ፥
አልቅሽ እባክሽን ዘለላ እምባወችሽ
አፈሩን ሲያርሱ፤
አዲስ ታሪክ በቅሎ
ቡቃያ ከወጣ
ፍሬ አናጣም እኛ፥
አይጨክንምና
ከላይ ያለ ዳኛ።
*
ሳቂ ግድ-የለሽም
ደግሞ አልቅሽ ነፍርቂ፥
ሞላ ብለሽ ዘለሽ ከደጁ እንዳ'ርቂ።
ለምን ካልሽ?
*
ሳቅሽ ምሥጋና ነው
ልቅሶሽ የልመና፥
ከእግዜር ስትጣዪ አንች የለሽምና::
@getem
@getem
@paappii
Mitu yimer
ለሷ ብቻ
*
እንቅልፌን ውሰደው ~ሞቴን አቅርብልኝ
ሰላሜን ቀንሰህ ~ ሰላሟን ስጥልኝ
*
*
ለኔ ያሰብከዉን ~ለሷ ብቻ አድርገው
እንቅፋቷን ሁሉ ~በገደል አስርገው
*
እያልኩ ዘወትር ~ ከደጅህ መቆሜ
በሷ ታስሬ ነው~ አይደለም ታምሜ
***** ******
(✍️እሱባለው @esubalewbuze )
@getem
@getem
@getem
*
እንቅልፌን ውሰደው ~ሞቴን አቅርብልኝ
ሰላሜን ቀንሰህ ~ ሰላሟን ስጥልኝ
*
*
ለኔ ያሰብከዉን ~ለሷ ብቻ አድርገው
እንቅፋቷን ሁሉ ~በገደል አስርገው
*
እያልኩ ዘወትር ~ ከደጅህ መቆሜ
በሷ ታስሬ ነው~ አይደለም ታምሜ
***** ******
(✍️እሱባለው @esubalewbuze )
@getem
@getem
@getem
ኢትዪጲያ 💚💛❤️
እፎይ ብላ እንድታርፍ ፀሎቷ ተሰምቶ
ምላሽ እንድታገኝ እጇ ተዘርግቶ
ጥላቻ እይብቀል ጥላቻ ተዘርቶ!!!!
(ሀና ሀይሉ)
Join here
@hanahailu
@hanahailu
እፎይ ብላ እንድታርፍ ፀሎቷ ተሰምቶ
ምላሽ እንድታገኝ እጇ ተዘርግቶ
ጥላቻ እይብቀል ጥላቻ ተዘርቶ!!!!
(ሀና ሀይሉ)
Join here
@hanahailu
@hanahailu
<ጠልቼሽ አላውቅም>
…✍እሱባለው ኢ.
እኔ ላንቺ ማለት
ከሬሳዎች መሀል~ ወድቆ የተገኘ፣
በጣም የረከሰ ~ሞቱን የተመኘ፣
ሁሉም የጠየፈው~ ህሊናውን ሽጦ፣
ባዶውን የቀረ ~መንፈሱ ተሟጦ፣
ተተጠሪ የሌለው ~ትብያ የወደቀ፣
ወኔው እንደከዳው ~ጉልበቱ የደቀቀ፣
ሳይወለድ ሞቶ ~ሳይጀምር ያለቀ፣
በጣም ተራ ሰው ነኝ፡
ምንም የማልረባ፣
ላንቺ የማልመጥን ~ከቁብ የማልገባ፣
...በኔ መጠየቅሽ ~አካልሽ ተሳቆ፣
ዕርኩስ እንደነካው~ ውስጥሽ ተሸማቆ፣
እኔን ላለማየት ~ህይወትሽ ቢርቅም፣
....ጠልቼሽ አላውቅም።
*** ✍️እሱባለው ኢ
.( @esubalewbuze)
@getem
@getem
@getem
…✍እሱባለው ኢ.
እኔ ላንቺ ማለት
ከሬሳዎች መሀል~ ወድቆ የተገኘ፣
በጣም የረከሰ ~ሞቱን የተመኘ፣
ሁሉም የጠየፈው~ ህሊናውን ሽጦ፣
ባዶውን የቀረ ~መንፈሱ ተሟጦ፣
ተተጠሪ የሌለው ~ትብያ የወደቀ፣
ወኔው እንደከዳው ~ጉልበቱ የደቀቀ፣
ሳይወለድ ሞቶ ~ሳይጀምር ያለቀ፣
በጣም ተራ ሰው ነኝ፡
ምንም የማልረባ፣
ላንቺ የማልመጥን ~ከቁብ የማልገባ፣
...በኔ መጠየቅሽ ~አካልሽ ተሳቆ፣
ዕርኩስ እንደነካው~ ውስጥሽ ተሸማቆ፣
እኔን ላለማየት ~ህይወትሽ ቢርቅም፣
....ጠልቼሽ አላውቅም።
*** ✍️እሱባለው ኢ
.( @esubalewbuze)
@getem
@getem
@getem
* ባዶነት*
.
.
አምቄ በውሥጤ
ሺ ሀሜት
ሺ ቅናት
ሆኖብኝ መንገዴ
የ ርኩሠት
የ ዝሙት
ሥጨነቅ እየዋልኩ
ለሥጋ ለሆዴ
ሣልፆም አርብ እና እሮብ
ገና እና ሁዳዴ
ቄሥ ባገኘሁ ቁጥር
ይባርኩኝ እላለሁ
ብሩክ ሣይታሠብ
መባረክ የት አየሁ??
©marry
@getem
@getem
@gebriel_19
.
.
አምቄ በውሥጤ
ሺ ሀሜት
ሺ ቅናት
ሆኖብኝ መንገዴ
የ ርኩሠት
የ ዝሙት
ሥጨነቅ እየዋልኩ
ለሥጋ ለሆዴ
ሣልፆም አርብ እና እሮብ
ገና እና ሁዳዴ
ቄሥ ባገኘሁ ቁጥር
ይባርኩኝ እላለሁ
ብሩክ ሣይታሠብ
መባረክ የት አየሁ??
©marry
@getem
@getem
@gebriel_19
👍1
ሠፊ ንፁህ ሰማይ
ከላይ ተዘርግቶ
ለምለም አደይ መሬት
እፊቴ ተሰጥቶ።
ማስተዋያ ልቤ
ብሌኔ አንቺ ሆነሽ
"ውብ ነው" ያሉት ግዛት.....
"ውብ ነው" ያሉት መሬት......
አሁን እንዴት ይፍካ አንቺ የሌለሽበት.....?....።
ዳግማዊ 2007 ዓ.ም
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ከላይ ተዘርግቶ
ለምለም አደይ መሬት
እፊቴ ተሰጥቶ።
ማስተዋያ ልቤ
ብሌኔ አንቺ ሆነሽ
"ውብ ነው" ያሉት ግዛት.....
"ውብ ነው" ያሉት መሬት......
አሁን እንዴት ይፍካ አንቺ የሌለሽበት.....?....።
ዳግማዊ 2007 ዓ.ም
@getem
@getem
@lula_al_greeko
አውቃለው አትበይኝ
*እሱባለው
*
*
ያወቀ መች በቅሎ~ ፍሬውን የታየን
ካምፓስ ውስጥ ያለነው~እውቀት መች ገበየን
ያልገባውን ተይው
ሆስፒታል የገባው ~ስንት ሰው ተለየን
*
አውቃለው አትበይኝ
ያወቀ መች ያውቃል~ አውቆስ ምን አመጣ
ምሁራንን ይዘን ~በረሃብ ስንቀጣ
ለምለም መሬት ይዘን ~ልመና ስንወጣ።
*
አውቃለው አትበይኝ
ማወቅሽ~ ምን በጀኝ
አብሬሽ እየኖርኩ ~ፍቅርሽ እየፈጀኝ።
*
*
*
*
እሽ በቃ ታውቂያለሽ
*
(✍️ Esubalew, @esubalewbuze )
@getem
@getem
@getem
*እሱባለው
*
*
ያወቀ መች በቅሎ~ ፍሬውን የታየን
ካምፓስ ውስጥ ያለነው~እውቀት መች ገበየን
ያልገባውን ተይው
ሆስፒታል የገባው ~ስንት ሰው ተለየን
*
አውቃለው አትበይኝ
ያወቀ መች ያውቃል~ አውቆስ ምን አመጣ
ምሁራንን ይዘን ~በረሃብ ስንቀጣ
ለምለም መሬት ይዘን ~ልመና ስንወጣ።
*
አውቃለው አትበይኝ
ማወቅሽ~ ምን በጀኝ
አብሬሽ እየኖርኩ ~ፍቅርሽ እየፈጀኝ።
*
*
*
*
እሽ በቃ ታውቂያለሽ
*
(✍️ Esubalew, @esubalewbuze )
@getem
@getem
@getem
*** ከተራራው ግርጌ ***
በረሃብ አለንጋ በጭቆና ጅራፍ የተጎሳቆሉ
የችግራችን ምንጭ ምንድን ነው እንዳይሉ
በቁና መሉ ክክ በድጎማ ስንዴ እየተደለሉ
ከተራራው ግርጌ ተገፍተው ተጣሉ
የአገዛዙን ቀንበር ሰብረው እንዳይወጡ
ባለማወቅ ገመድ ታስረው ተቀመጡ
ወጣቱ እንዳይጠይቅ እንዳይሆን መርማሪ
ቤተመፅሐፍት የለ የህዝብ ላይበራሪ
በየጥጋጥጉ ነፍ ጭፈራ ቤት ነፍ ግሮሰሪ
በየመንገዱ ዳር የዝሙት ማህበር
ታች አንበሳ-መደብ ከላይ ሸራ ሰፈር
ደፍሬ እንዳልልሽ ሰዶም ወገሞራ
ከደጅ ይዘረፋል የወንጌሉ አዝመራ
ፍቅርሽ ተደግሶ ፍቅር ይዘከራል
እምወድህ ስትይ ልቤ ይሸብራል
ወይ ንስሐ አትገቢ ልክ እንደ ነነዌ
ሁልጊዜ ቃጠሎ ጥዋት ማታ ደዌ
አልቮ ልምላሜ ጉም ጥርት ያለ ሰማይ
እንደ እሣት ምትፋጅ አሳቃቂ ፀሐይ
ኤድስ አቫላዘር ወስፋት ወቁርባ
ሲፈራረቁብሽ ልብሽ የማይባባ
በፈርጣማ ክንዱ ችግር ያደባዬሽ
ለብዙ ዘመናት መቅሰፍት ያልተለዬሽ
በማን እና በምን እመስልሻለሁ
አስተዋይ ልቡናን እመኝልሻለሁ
እሳት ነበልባሉን ፍሙን የሚገታ
ዳግማዊ ዮናስ ይላክልሽ ጌታ
© ዶ/ር ጌታነህ ካሴ 12/07/2011 ዓ.ም
@getem
@getem
@gebriel_19
በረሃብ አለንጋ በጭቆና ጅራፍ የተጎሳቆሉ
የችግራችን ምንጭ ምንድን ነው እንዳይሉ
በቁና መሉ ክክ በድጎማ ስንዴ እየተደለሉ
ከተራራው ግርጌ ተገፍተው ተጣሉ
የአገዛዙን ቀንበር ሰብረው እንዳይወጡ
ባለማወቅ ገመድ ታስረው ተቀመጡ
ወጣቱ እንዳይጠይቅ እንዳይሆን መርማሪ
ቤተመፅሐፍት የለ የህዝብ ላይበራሪ
በየጥጋጥጉ ነፍ ጭፈራ ቤት ነፍ ግሮሰሪ
በየመንገዱ ዳር የዝሙት ማህበር
ታች አንበሳ-መደብ ከላይ ሸራ ሰፈር
ደፍሬ እንዳልልሽ ሰዶም ወገሞራ
ከደጅ ይዘረፋል የወንጌሉ አዝመራ
ፍቅርሽ ተደግሶ ፍቅር ይዘከራል
እምወድህ ስትይ ልቤ ይሸብራል
ወይ ንስሐ አትገቢ ልክ እንደ ነነዌ
ሁልጊዜ ቃጠሎ ጥዋት ማታ ደዌ
አልቮ ልምላሜ ጉም ጥርት ያለ ሰማይ
እንደ እሣት ምትፋጅ አሳቃቂ ፀሐይ
ኤድስ አቫላዘር ወስፋት ወቁርባ
ሲፈራረቁብሽ ልብሽ የማይባባ
በፈርጣማ ክንዱ ችግር ያደባዬሽ
ለብዙ ዘመናት መቅሰፍት ያልተለዬሽ
በማን እና በምን እመስልሻለሁ
አስተዋይ ልቡናን እመኝልሻለሁ
እሳት ነበልባሉን ፍሙን የሚገታ
ዳግማዊ ዮናስ ይላክልሽ ጌታ
© ዶ/ር ጌታነህ ካሴ 12/07/2011 ዓ.ም
@getem
@getem
@gebriel_19
👍1
ፈራጅ ሚዛን ጥሎ?
በጦዘ ዘመን ላይ - አብረው የሚጦዙ፥
የዘመን ዐለቆች - መንበርን ሲይዙ፥
“እኔ ብቻ ልታይ”፥
የሚልን ተከታይ፥
ደርሶ የሚያሰክን - ይጠፋል ካ’ገሩ፥
የሚሰማም አይኖር - እንዳይነጋገሩ።
“እስቲ ያውሩም” ቢባል - በየትኛው ዳኛ፥
ኹሉም ለ’ህል ፈራጅ - እስከዳር ቀማኛ።
ጥያቄውም ከንቱ - ባለመልሱም ከንቱ፥
ያ’ገር እንቆቅልሽ - በዘር የሚፈቱ።
ይነሳል ጥያቄ - መልስ ያልኾነ ምሱ፥
ለሕዝብ ያጮኹታል - የሚያተራምሱ፤
ይቀበላል መንጋ - መጯጯህ የራበው፥
ጠያቂም፥ መላሽም - ይጠቅሳሉ “ካ’በው”።
“ጭቁኖች ነን” ባዮች - ዘውትር የሚከሱን፥
ልዩነቱን እንጂ - አይፈልጉም መልሱን፤
ጥያቄን አይሰማም - ጆሮውን የያዘ - “መላሽ ነኝ” ባይ ደሞ፥
ይባስ የገዘፈ - ጥያቄን ይሸጣል - ትንሿ ላይ ቆሞ።
ተረግሟል ሀገሩ፥
ተጠልቷል መንደሩ፥
የጥያቄ አምላክ - ይቅር አትቆጣ፥
መልስ፥ መልሱ ይቆይ - ጥያቄውን አምጣ፤
መልስ ፈላጊዎች - ከጥያቄ መንደር - ጠፉ እየሸሹ፥
በጩኸት የሚያምኑ - ጥያቄዎች ሲያጡ - መልሶችን የሚሹ!
@getem
@getem
@paappii
ንጉሱ አበረ አያሌው
በጦዘ ዘመን ላይ - አብረው የሚጦዙ፥
የዘመን ዐለቆች - መንበርን ሲይዙ፥
“እኔ ብቻ ልታይ”፥
የሚልን ተከታይ፥
ደርሶ የሚያሰክን - ይጠፋል ካ’ገሩ፥
የሚሰማም አይኖር - እንዳይነጋገሩ።
“እስቲ ያውሩም” ቢባል - በየትኛው ዳኛ፥
ኹሉም ለ’ህል ፈራጅ - እስከዳር ቀማኛ።
ጥያቄውም ከንቱ - ባለመልሱም ከንቱ፥
ያ’ገር እንቆቅልሽ - በዘር የሚፈቱ።
ይነሳል ጥያቄ - መልስ ያልኾነ ምሱ፥
ለሕዝብ ያጮኹታል - የሚያተራምሱ፤
ይቀበላል መንጋ - መጯጯህ የራበው፥
ጠያቂም፥ መላሽም - ይጠቅሳሉ “ካ’በው”።
“ጭቁኖች ነን” ባዮች - ዘውትር የሚከሱን፥
ልዩነቱን እንጂ - አይፈልጉም መልሱን፤
ጥያቄን አይሰማም - ጆሮውን የያዘ - “መላሽ ነኝ” ባይ ደሞ፥
ይባስ የገዘፈ - ጥያቄን ይሸጣል - ትንሿ ላይ ቆሞ።
ተረግሟል ሀገሩ፥
ተጠልቷል መንደሩ፥
የጥያቄ አምላክ - ይቅር አትቆጣ፥
መልስ፥ መልሱ ይቆይ - ጥያቄውን አምጣ፤
መልስ ፈላጊዎች - ከጥያቄ መንደር - ጠፉ እየሸሹ፥
በጩኸት የሚያምኑ - ጥያቄዎች ሲያጡ - መልሶችን የሚሹ!
@getem
@getem
@paappii
ንጉሱ አበረ አያሌው