++ ለክርስቶስ ልደት መንገድ የጠረገ ልደት ++
እንኳን አደረሳችሁ!!
☞ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ ጥንተ አብሶ ካመጣው ፍዳና መርገም ጠብቋታል:: የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ዓለም በጥንተ አብሶ በነበረበት ዘመን በክርስቶስ ማዳን ዋዜማ ሲያበሥራት፤ ቅድስት ኤልሳቤትም በፅንሰቷ ጊዜ ስታመሰግናት ደጋግመው "ጸጋን የሞላብሽ ሆይ" "አንቺ ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ።" እያሉ ይህን እውነት መስክረዋል። (ሉቃ፩:፳፮-፵)
☞ በጥንተ አብሶና ውጤቱ (origional sin and its effects) ምክንያት ሰዎች "የእግዚአብሔር ክብር ጎድሏቸዋል በተባሉበት ዘመን ጸጋን የተመላች ብቸኛ ልዩ እርሷ ነበረች::" (ሮሜ ፫:፳፫) እግዚአብሔር እርሷ የዓለም መድኃኒት ክርስቶስን ለመውለድ ፈቃደኛ እንደምትሆን ስለሚያውቅ አስቀድሞ በአካል የሚመስለው በባሕርይ ከእርሱ ጋር አንድ የሆነ አንድያ ልጁን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና እንድትወልድ ቅድመ ዓለም መርጧታልና የእመቤታችን ልደት (ልደታ ለማርያም) የዓለም መዳን የማይቀር መሆኑ ለታወቀበት ለጌታችን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መንገድ የጠረገ ልደት ነው እንላለን። (The nativity of the blessed virgin Mary prepares the way for the birth of Jesus Christ) እንዳለ ሊቁ። (The book of the nativity of Virgin Mary)
☞ የጌታችን ሰው መሆን "ከዘላለምና (ቅድመ ዓለም) ከትውልዶች ጀምሮ (ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ) ተሰውሮ የነበረ ምሥጢር ነው።" መባሉም የአምላክ ሰው መሆን እንዲሁም የእርሷ እርሱን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና መውለድ ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ሕሊና የሚታወቅ መሆኑን ያስረዳናል። (ቆላ፩:፳፮፣ኢሳ ፯:፲፬ ፱:፮)
☞ እርሱ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የነገሥታት ንጉሥ፣ የጌቶች ጌታ፣ የአማልክት አምላክ ነው። (መዝ ፻፴፭:፩ ራእ፲፱:፲፮)
☞ እርሱ ፍጥረትን ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ ፈጣሪ ነው:: "ሁሉ በእርሱ ሆነ ከሆነውም አንዳች ያለ እርሱ አልሆነም።" (ዮሐ ፩:፫)፤ "መልካሙን ነገር ለማድረግ በክርስቶስ ተፈጠርን።"፤ "የሚታዩትና የማይታዩትም ዙፋናት ቢሁኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና።" እንደተባለ:: (ቆላ ፩:፲፭-፲፮፣ ኤፌ ፪:፲)
☞ እርሱ ለቅዱሳን የጸጋ አምላክነትን ክብር የሰጠ ሁሉን ፈጥሮ የሚገዛ የባሕርይ አምላክ ነው:: (ዘጸ ፯:፩፣ መዝ ፹፩:፩፣ ዮሐ፲÷፴፬፣ ሮሜ ፱:፭፣ ፩ተሰ ፫:፲፩፣ ቲቶ ፪:፲፩፣ ፩ዮሐ ፭:፳)
☞ እርሱ ቸር ከሆነ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በአገዛዝ በሥልጣን በሕልውና በመለኮት አንድ ነው:: (ዮሐ ፲:፴፣ ፲፯:፲፣ ማቴ ፲፩:፳፯-፳፱፣ ዮሐ ፲፬:፮-፰)
☞ እርሱ ፀሐይ እናቱ ምሥራቅ ናት:: (ሕዝ ፵፬:፩፣ ዮሐ ፰:፲፪፣ ሚል ፬:፪) ምሥራቅ እናቱን ዘወትር መሻታችን የፀሐይ ክርስቶስን በረከት ፍቅርና ቸርነት ለማግኘት ነው:: እንኳንስ እናቱን ነቢዩ ዳዊት ስለ ወዳጆቹ "ምስክሮችህ ድንቆች ናቸው ስለዚህም ነፍሴ ፈለገቻቸው።" ብሎ ዘምሯል:: (መዝ ፻፲፰:፻፳፭)
☞ እርሱ የባሕርይ አምላክ እርሷ ደግሞ ወላዲተ አምላክ ( Theotokos) ናት:: ዓለም ከመፈጠሩ በፊት ከተፈጠረም በኋላ መቸም መች አምላክን "ልጄ ወዳጄ" ማለት ከቶ ለማን ተችሏል? እርሱ ፈጣሪ እርሷ ደግሞ ወላዲተ ፈጣሪ ኩሉ ዓለም ናት::
☞ እርሱ እውነተኛ ደስታ እርሷ የደስታ መፍሰሻ ናት። (መዝ ፵፭:፭)
☞ እርሱ ሕይወት እርሷ ነቅዐ ሕይወት (የሕይወት ምንጭ) ናት። ይህች ብርሃን ሙዳየ መድኃኒት ቤዛዊተ ኩሉ ብርሃንን ትሰጠን ሕይወት ክርስቶስን ትወልድልን ዘንድ ከተቀደሱ ተራሮች ከአብርሃም ከዳዊት ቤት ተወለደች። (መዝ ፹፰(፹፱):፩)
+++ የልደቷ ቀን +++
አንተ የራስህን እንዲሁም የምትወዳቸውን ሰዎች ልደት ሻማ አብርተህ፣ ኬክ አስጋግረህ፣ ወዳጅ ዘመዶችህን ጠርተህ፣ በዳንስ በጭፈራና እስክስታ በመውረግረግ ታከብራለህ የአምላክ እናት ድንግል ማርያም የተወለደችበትን ቀን በማሰብ በዓለ ልደቷን የሚያከብሩ ሰዎችን ግን ለምን ያከብራሉ? ብለህ ትተቻለህ::
የእናቱን ልደት እርሱን እያመሰገንን፣ እያወደስን እናቱ "ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑኛል።" (ሉቃ ፩:፵፱) እንዳለችም እርሷንም እያመሰገንን "ብርቱ የሆን እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጓልና።" ብላ እንደመሠከረችም በእርሷ ለሰው ዘር የተደረገውን ታላቅ ሥራ እያሰብን ብናከብር የሚያዝንብን ይመስላሃልን? ከማዳኑስ በላይ ምን ታላቅ ሥራ አለ? ዓለም:- የኤድስ ቀን፣ የጉበት ቀን፣ የኩላሊት ቀን፣ የላብ አደር ቀን፣ የውሃ ቀን፣ የአፈር ቀን፣ የእናቶች ቀን፣ የአባቶች ቀን እያለ በልዩ ልዩ መንገድ ሲያከብር ቅር አይለውም የእናቱ የእመቤታችንን ልደት ለማክበር ግን ያመዋል::
ልደታ ለማርያምን ስናከብር
☞ ቤተ ክርስቲያንን በሚያስነቅፍ አብዝቶ በመብላትና በመጠጣት በዳንኪራና በአስረሽ ምስናከብር
ሆን በመንፈሳዊ ሥርዓት እናክብረው ያኔ የልጇ በረከት እጥፍ ድርብ ይሆንልናል። (ምሳ ፲:፯፣ ፩ጴጥ ፪:፲፪)
☞ የቤተክርስቲያን ባልሆነ የልደቷን ነገር በማይገልጥ በማይወክል መንገድ በአምልኮ ባዕድ፣ በየዛፉ ዙርያ አረቄና ቡና በማፍሰስ የሚያከብሩትን ሰዎች በማስተማርና ትክክለኛውንና የክርስትናውን መንገድ በተከተለ መንገድ እንዲያከብሩት በማድረግ ድርሻችንን በመወጣት እናክብር ::
☞ ልደቷ "በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።" ከተባለለት ከዮሐንስ ልደት የሚልቅ መሆኑን እንወቅ። እርሷ የዮሐንስ ፈጣሪ የክርስቶስ እናቱ ናትና። ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም " ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው እርሱም እናቱን ፈጠረ።" እንዳለ:: እርሱ ክርስቶስ "ሁሉን በስሜ አድርጉት" እንዳለን እርሷን በእርሱ ስም ወላዲተ አምላክ እመ ብርሃን ብለን ተቀብለን ልደቷን እንደምናከብር እንረዳ:: (ሉቃ ፩:፲፬)
+++ አድባር +++
አድባር የሚለው ቃል የግእዝ ሲሆን ትርጉሙም ተራሮች ማለት ነው:: እመቤታችን በሊባኖስ ተራሮች መሐል ተወልዳለችና የልደቷን ወቅት አድባር እንላለን። (መኃ ፬:፰)
🚹የእናቱን በዓለ ልደት ማክበር ማኅበራዊ ፋይዳ 🚹
በዚህ ቀን የአንድ ቀዬ ሰዎች በአንድነት ተሰብስበው ጸሎት በማድረግ እግዚአብሔርን በማመስገን እናቱንም በማወደስ ማክበራቸው ከሃይማኖታዊው ፋይዳ ባለፈ በልዩ ልዩ ምክንያት እየደበዘዘና እንደ ዳይኖሰርና ዶዶ ድራሹ እየጠፋ የመጣውን አብሮነት ማኅበራዊ ትስስር የሚያጠነክር መልካም ባሕላችንም ጭምር ነውና አጥብቀን ልንይዘው ይገባናል:: የድንግል ልጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ የልደት ቀን በረከት ያሳትፈን!!!
ቢትወደድ ወርቁ
ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፲፯ ዓ ም
እንኳን አደረሳችሁ!!
☞ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ ጥንተ አብሶ ካመጣው ፍዳና መርገም ጠብቋታል:: የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ዓለም በጥንተ አብሶ በነበረበት ዘመን በክርስቶስ ማዳን ዋዜማ ሲያበሥራት፤ ቅድስት ኤልሳቤትም በፅንሰቷ ጊዜ ስታመሰግናት ደጋግመው "ጸጋን የሞላብሽ ሆይ" "አንቺ ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ።" እያሉ ይህን እውነት መስክረዋል። (ሉቃ፩:፳፮-፵)
☞ በጥንተ አብሶና ውጤቱ (origional sin and its effects) ምክንያት ሰዎች "የእግዚአብሔር ክብር ጎድሏቸዋል በተባሉበት ዘመን ጸጋን የተመላች ብቸኛ ልዩ እርሷ ነበረች::" (ሮሜ ፫:፳፫) እግዚአብሔር እርሷ የዓለም መድኃኒት ክርስቶስን ለመውለድ ፈቃደኛ እንደምትሆን ስለሚያውቅ አስቀድሞ በአካል የሚመስለው በባሕርይ ከእርሱ ጋር አንድ የሆነ አንድያ ልጁን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና እንድትወልድ ቅድመ ዓለም መርጧታልና የእመቤታችን ልደት (ልደታ ለማርያም) የዓለም መዳን የማይቀር መሆኑ ለታወቀበት ለጌታችን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መንገድ የጠረገ ልደት ነው እንላለን። (The nativity of the blessed virgin Mary prepares the way for the birth of Jesus Christ) እንዳለ ሊቁ። (The book of the nativity of Virgin Mary)
☞ የጌታችን ሰው መሆን "ከዘላለምና (ቅድመ ዓለም) ከትውልዶች ጀምሮ (ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ) ተሰውሮ የነበረ ምሥጢር ነው።" መባሉም የአምላክ ሰው መሆን እንዲሁም የእርሷ እርሱን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና መውለድ ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ሕሊና የሚታወቅ መሆኑን ያስረዳናል። (ቆላ፩:፳፮፣ኢሳ ፯:፲፬ ፱:፮)
☞ እርሱ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የነገሥታት ንጉሥ፣ የጌቶች ጌታ፣ የአማልክት አምላክ ነው። (መዝ ፻፴፭:፩ ራእ፲፱:፲፮)
☞ እርሱ ፍጥረትን ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ ፈጣሪ ነው:: "ሁሉ በእርሱ ሆነ ከሆነውም አንዳች ያለ እርሱ አልሆነም።" (ዮሐ ፩:፫)፤ "መልካሙን ነገር ለማድረግ በክርስቶስ ተፈጠርን።"፤ "የሚታዩትና የማይታዩትም ዙፋናት ቢሁኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና።" እንደተባለ:: (ቆላ ፩:፲፭-፲፮፣ ኤፌ ፪:፲)
☞ እርሱ ለቅዱሳን የጸጋ አምላክነትን ክብር የሰጠ ሁሉን ፈጥሮ የሚገዛ የባሕርይ አምላክ ነው:: (ዘጸ ፯:፩፣ መዝ ፹፩:፩፣ ዮሐ፲÷፴፬፣ ሮሜ ፱:፭፣ ፩ተሰ ፫:፲፩፣ ቲቶ ፪:፲፩፣ ፩ዮሐ ፭:፳)
☞ እርሱ ቸር ከሆነ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በአገዛዝ በሥልጣን በሕልውና በመለኮት አንድ ነው:: (ዮሐ ፲:፴፣ ፲፯:፲፣ ማቴ ፲፩:፳፯-፳፱፣ ዮሐ ፲፬:፮-፰)
☞ እርሱ ፀሐይ እናቱ ምሥራቅ ናት:: (ሕዝ ፵፬:፩፣ ዮሐ ፰:፲፪፣ ሚል ፬:፪) ምሥራቅ እናቱን ዘወትር መሻታችን የፀሐይ ክርስቶስን በረከት ፍቅርና ቸርነት ለማግኘት ነው:: እንኳንስ እናቱን ነቢዩ ዳዊት ስለ ወዳጆቹ "ምስክሮችህ ድንቆች ናቸው ስለዚህም ነፍሴ ፈለገቻቸው።" ብሎ ዘምሯል:: (መዝ ፻፲፰:፻፳፭)
☞ እርሱ የባሕርይ አምላክ እርሷ ደግሞ ወላዲተ አምላክ ( Theotokos) ናት:: ዓለም ከመፈጠሩ በፊት ከተፈጠረም በኋላ መቸም መች አምላክን "ልጄ ወዳጄ" ማለት ከቶ ለማን ተችሏል? እርሱ ፈጣሪ እርሷ ደግሞ ወላዲተ ፈጣሪ ኩሉ ዓለም ናት::
☞ እርሱ እውነተኛ ደስታ እርሷ የደስታ መፍሰሻ ናት። (መዝ ፵፭:፭)
☞ እርሱ ሕይወት እርሷ ነቅዐ ሕይወት (የሕይወት ምንጭ) ናት። ይህች ብርሃን ሙዳየ መድኃኒት ቤዛዊተ ኩሉ ብርሃንን ትሰጠን ሕይወት ክርስቶስን ትወልድልን ዘንድ ከተቀደሱ ተራሮች ከአብርሃም ከዳዊት ቤት ተወለደች። (መዝ ፹፰(፹፱):፩)
+++ የልደቷ ቀን +++
አንተ የራስህን እንዲሁም የምትወዳቸውን ሰዎች ልደት ሻማ አብርተህ፣ ኬክ አስጋግረህ፣ ወዳጅ ዘመዶችህን ጠርተህ፣ በዳንስ በጭፈራና እስክስታ በመውረግረግ ታከብራለህ የአምላክ እናት ድንግል ማርያም የተወለደችበትን ቀን በማሰብ በዓለ ልደቷን የሚያከብሩ ሰዎችን ግን ለምን ያከብራሉ? ብለህ ትተቻለህ::
የእናቱን ልደት እርሱን እያመሰገንን፣ እያወደስን እናቱ "ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑኛል።" (ሉቃ ፩:፵፱) እንዳለችም እርሷንም እያመሰገንን "ብርቱ የሆን እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጓልና።" ብላ እንደመሠከረችም በእርሷ ለሰው ዘር የተደረገውን ታላቅ ሥራ እያሰብን ብናከብር የሚያዝንብን ይመስላሃልን? ከማዳኑስ በላይ ምን ታላቅ ሥራ አለ? ዓለም:- የኤድስ ቀን፣ የጉበት ቀን፣ የኩላሊት ቀን፣ የላብ አደር ቀን፣ የውሃ ቀን፣ የአፈር ቀን፣ የእናቶች ቀን፣ የአባቶች ቀን እያለ በልዩ ልዩ መንገድ ሲያከብር ቅር አይለውም የእናቱ የእመቤታችንን ልደት ለማክበር ግን ያመዋል::
ልደታ ለማርያምን ስናከብር
☞ ቤተ ክርስቲያንን በሚያስነቅፍ አብዝቶ በመብላትና በመጠጣት በዳንኪራና በአስረሽ ምስናከብር
ሆን በመንፈሳዊ ሥርዓት እናክብረው ያኔ የልጇ በረከት እጥፍ ድርብ ይሆንልናል። (ምሳ ፲:፯፣ ፩ጴጥ ፪:፲፪)
☞ የቤተክርስቲያን ባልሆነ የልደቷን ነገር በማይገልጥ በማይወክል መንገድ በአምልኮ ባዕድ፣ በየዛፉ ዙርያ አረቄና ቡና በማፍሰስ የሚያከብሩትን ሰዎች በማስተማርና ትክክለኛውንና የክርስትናውን መንገድ በተከተለ መንገድ እንዲያከብሩት በማድረግ ድርሻችንን በመወጣት እናክብር ::
☞ ልደቷ "በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።" ከተባለለት ከዮሐንስ ልደት የሚልቅ መሆኑን እንወቅ። እርሷ የዮሐንስ ፈጣሪ የክርስቶስ እናቱ ናትና። ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም " ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው እርሱም እናቱን ፈጠረ።" እንዳለ:: እርሱ ክርስቶስ "ሁሉን በስሜ አድርጉት" እንዳለን እርሷን በእርሱ ስም ወላዲተ አምላክ እመ ብርሃን ብለን ተቀብለን ልደቷን እንደምናከብር እንረዳ:: (ሉቃ ፩:፲፬)
+++ አድባር +++
አድባር የሚለው ቃል የግእዝ ሲሆን ትርጉሙም ተራሮች ማለት ነው:: እመቤታችን በሊባኖስ ተራሮች መሐል ተወልዳለችና የልደቷን ወቅት አድባር እንላለን። (መኃ ፬:፰)
🚹የእናቱን በዓለ ልደት ማክበር ማኅበራዊ ፋይዳ 🚹
በዚህ ቀን የአንድ ቀዬ ሰዎች በአንድነት ተሰብስበው ጸሎት በማድረግ እግዚአብሔርን በማመስገን እናቱንም በማወደስ ማክበራቸው ከሃይማኖታዊው ፋይዳ ባለፈ በልዩ ልዩ ምክንያት እየደበዘዘና እንደ ዳይኖሰርና ዶዶ ድራሹ እየጠፋ የመጣውን አብሮነት ማኅበራዊ ትስስር የሚያጠነክር መልካም ባሕላችንም ጭምር ነውና አጥብቀን ልንይዘው ይገባናል:: የድንግል ልጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ የልደት ቀን በረከት ያሳትፈን!!!
ቢትወደድ ወርቁ
ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፲፯ ዓ ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
#አዲስመዝሙር "ቅድስት ኄራኒ ኄራኒ ኮከብ " በዘማሪት ኦብሴ አበበ #መዝሙር #ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #ቅዱሳትአንስት #2025Mezmure
ቅድስት ኄራኒ - ኄራኒ ኮከብ
ቃልኪዳንሽ - ዘውትር የሚያብብ
ትህትናሽ - ምዑዝ ነው ሽቶ
የጠራሽ - ማን ያፍራል ከቶ (2)
አዝ............................
በልደትሽ ቀን ኄራኒ ቅድስት
በመጀመሪያው '' ''
በእመ አምላክ ክንዶች '' ''
ነው የታቀፍሽው '' ''
የመርቆርዮስ በረከት ደርሶሽ
በምግባር በእምነት በፍቅር አደግሽ…
ቃልኪዳንሽ - ዘውትር የሚያብብ
ትህትናሽ - ምዑዝ ነው ሽቶ
የጠራሽ - ማን ያፍራል ከቶ (2)
አዝ............................
በልደትሽ ቀን ኄራኒ ቅድስት
በመጀመሪያው '' ''
በእመ አምላክ ክንዶች '' ''
ነው የታቀፍሽው '' ''
የመርቆርዮስ በረከት ደርሶሽ
በምግባር በእምነት በፍቅር አደግሽ…
#አባቴ_ነውና_አዎን አውቀዋለሁ !
______
#ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት
#ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ።
ሰይፍ አርእድ በተባለ በነዋየ ክርስቶስ መንግሥት ደግሞ ከንጉሥ ሠራዊት አንዱ ወደ ዋሊ ገዳም ሄደ ።ሁለት መነኮሳት አግኝቶ እጅ ነሳቸው ፤ ከወዴት ነህ? አሉት? ከሸዋ ክፍለ ሀገር ከዚያው ግራርያ ከምትባል አውራጃ ነኝ አላቸው። ተክለ ሃይማኖት የሚሉትን ታውቀዋለህ ? አሉት። #አባቴ_ነውና_አዎን_አውቀዋለሁ አላቸው።
#ወደ_መቃብሩ_ደርስሃል ? አሉት። አዎን ደርሻለሁ አላቸው። እነዚያም መነኮሳት ተነስሀው ሰገዱለት የእግሮቹንም ትቢያ ይልሱ እጆቹንም ይስሙ ጀመሩ። ጭፍራውም ጌቶቼ ይህንን ስለምን አደረጋችሁ?? አላቸው ። እኛ እናውቃለን አሉት። ዳግመኛም በተክለ ሃይማኖት የመቃብር ቦታ ሥጋ ወደሙን ተቀበልክን? አሉት። አልተቀበልኩም አላቸው። ከቅዱሱ መቃብር ዘንድ ቁርባን ያልተቀበልክ #እቡዘ_ልብ_ለምን_ሆንክ ? የተክለ ሃይማኖት አጽም ካረፈበት ቦታ ቁርባንን የተቀበለ ሁሉ ሲዖልን ዐያይም ሲል ከጌታ አንደበት በእውነት ሰማን ብለን በእውነት እንነግርሃለን አሉት።
#በውስጧም የሚቀበር ለዘለዓለም እንዳይጎዳም እኛም መንፈስ ቅዱስ በየሰዓቱ ይልቁንም በቁርባን ጊዜ እየወረደ በውስጧም መሥዋት ለሚያቀርቡ መዐዛ ያለውን ሽቱ ሲቀባቸው ዘወትር እናያለን ፤እንደ ብርሃን ደመና በላይዋ የረበበ ነው እንጂ ለሊትና ቀን ከእርሷ መንፈስ ቅዱስ አይርቅም።
እንዲሁ ዘወትር ይኖራል።በእርሷም የተቀመጠ የቆመ በውስጧም የተቀበረ በረድኤቷም የተጠጋ የተመሰገነ ነው። #ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት_ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ። አሉት
ሌላም የተሰወረ ምሥጢር ነገሩትሌላውን ግን ልንጽፈው አንችልም መጽሐፍ የምንገልጠውም የምንሰውረውም ነገር አለ እንዳለ ይንንም ብለውት ከእርሱ ተሰወሩ።
" #አዎን_ለምንፍገመገም_ለኛ_ለኢትዮጵያውያን ያላንተ ረዳት የለንምና #ምልጃህ አትለየን " #አሜን!
#ገድለ_ተክለ_ሃይማኖት ምዕራፍ 50/60
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥንተ ጽሕፈቱ #ግንቦት 11/2014ዓ.ም
______
#ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት
#ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ።
ሰይፍ አርእድ በተባለ በነዋየ ክርስቶስ መንግሥት ደግሞ ከንጉሥ ሠራዊት አንዱ ወደ ዋሊ ገዳም ሄደ ።ሁለት መነኮሳት አግኝቶ እጅ ነሳቸው ፤ ከወዴት ነህ? አሉት? ከሸዋ ክፍለ ሀገር ከዚያው ግራርያ ከምትባል አውራጃ ነኝ አላቸው። ተክለ ሃይማኖት የሚሉትን ታውቀዋለህ ? አሉት። #አባቴ_ነውና_አዎን_አውቀዋለሁ አላቸው።
#ወደ_መቃብሩ_ደርስሃል ? አሉት። አዎን ደርሻለሁ አላቸው። እነዚያም መነኮሳት ተነስሀው ሰገዱለት የእግሮቹንም ትቢያ ይልሱ እጆቹንም ይስሙ ጀመሩ። ጭፍራውም ጌቶቼ ይህንን ስለምን አደረጋችሁ?? አላቸው ። እኛ እናውቃለን አሉት። ዳግመኛም በተክለ ሃይማኖት የመቃብር ቦታ ሥጋ ወደሙን ተቀበልክን? አሉት። አልተቀበልኩም አላቸው። ከቅዱሱ መቃብር ዘንድ ቁርባን ያልተቀበልክ #እቡዘ_ልብ_ለምን_ሆንክ ? የተክለ ሃይማኖት አጽም ካረፈበት ቦታ ቁርባንን የተቀበለ ሁሉ ሲዖልን ዐያይም ሲል ከጌታ አንደበት በእውነት ሰማን ብለን በእውነት እንነግርሃለን አሉት።
#በውስጧም የሚቀበር ለዘለዓለም እንዳይጎዳም እኛም መንፈስ ቅዱስ በየሰዓቱ ይልቁንም በቁርባን ጊዜ እየወረደ በውስጧም መሥዋት ለሚያቀርቡ መዐዛ ያለውን ሽቱ ሲቀባቸው ዘወትር እናያለን ፤እንደ ብርሃን ደመና በላይዋ የረበበ ነው እንጂ ለሊትና ቀን ከእርሷ መንፈስ ቅዱስ አይርቅም።
እንዲሁ ዘወትር ይኖራል።በእርሷም የተቀመጠ የቆመ በውስጧም የተቀበረ በረድኤቷም የተጠጋ የተመሰገነ ነው። #ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት_ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ። አሉት
ሌላም የተሰወረ ምሥጢር ነገሩትሌላውን ግን ልንጽፈው አንችልም መጽሐፍ የምንገልጠውም የምንሰውረውም ነገር አለ እንዳለ ይንንም ብለውት ከእርሱ ተሰወሩ።
" #አዎን_ለምንፍገመገም_ለኛ_ለኢትዮጵያውያን ያላንተ ረዳት የለንምና #ምልጃህ አትለየን " #አሜን!
#ገድለ_ተክለ_ሃይማኖት ምዕራፍ 50/60
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥንተ ጽሕፈቱ #ግንቦት 11/2014ዓ.ም
Forwarded from Sami 🦴
🔴ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ🌹እንኳን አደረሳችሁ🌹በዘማሪት ሲስተር ማኀደር ለታሪክ 🌹አዲስ ዝማሬ💐/New mezmur/
https://youtube.com/watch?v=tM3jdFxXdSs&si=lCt7XXjVGsSBHPiC
https://youtube.com/watch?v=tM3jdFxXdSs&si=lCt7XXjVGsSBHPiC
#ቤተ_ክርስቲያን አሙስ ላይ ናት !
_________
የአሙስ ማታ የጌታችን የአምላካችን የድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ንግግር
___________
" #በዚች ሌሊት ሁላችሁ በእኔ ትሰናከላላችሁ፤ #እረኛውን እመታለሁ የመንጋውም በጎች ይበተናሉ የሚል ተጽፎአልና፤”
#ማቴዎ 26፥31
#ከፊት ይልቅ አሁን ላይ #ለቤተ_ክርስቲያን ትጉላት ! #አሙስ ላይ ናትና
_________
የአሙስ ማታ የጌታችን የአምላካችን የድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ንግግር
___________
" #በዚች ሌሊት ሁላችሁ በእኔ ትሰናከላላችሁ፤ #እረኛውን እመታለሁ የመንጋውም በጎች ይበተናሉ የሚል ተጽፎአልና፤”
#ማቴዎ 26፥31
#ከፊት ይልቅ አሁን ላይ #ለቤተ_ክርስቲያን ትጉላት ! #አሙስ ላይ ናትና
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
ይነበብ 🙏🙏🙏🙏
መንፈሳዊ መርሐግብር ጥሪ !!!!
ላልሰሙ እንድታሰሙ በእመቤታችን ስም እንጠይቃለን !🙏🙏🙏
የታኅሳስዳር ደብረ ጽዮን ማርያም ልጆች ማኅበር
መንፈሳዊ መርሐግብር ጥሪ !!!!
ለኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምዕመናን በሙሉ በቅድሚያ የታኃሳስዳር ደብረ ጽዮን ህንፃ ቤተክርስቲያን ለማሰራት እያደረጋችሁልን ስላለው ሁለንተናዊ ድጋፍ ከልብ እያመሰገንን ፤ ይህንን ስራ አጠናክረን ለማስቀጠል እና ለህንፃ ማሠሪያው ከዚህ የተሻለ እርዳታ ለማድረግ ያስችለን ዘንድ በአይነቱ የተለየ መርሐ ግብር በማዘጋጀት ለተለያዩ ሰዎች ጥሪ በማድረግ ላይ እንገናኛለን ። በመሆኑም ግንቦት 24/9/2017 ዓ.ም ከ 5:30 ጀምሮ በሚኖረን ልዩ መርሐ ግብር ለመሳተፍ 5 ኪሎ በሚገኘው መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም እንድትገኙልን ስንል በእመቤታችን ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።።
ላልሰሙ እንድታሰሙ በእመቤታችን ስም እንጠይቃለን !🙏🙏🙏
የታኅሳስዳር ደብረ ጽዮን ማርያም ልጆች ማኅበር
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
"ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት" የዘወትር ጸሎታችን ነው።አስቀድሞ በማኅፀነ #ድንግል ሥጋችንን ቃል ስለተዋሐደው በባሕርይ አምላክነት (በፈጣሪነት) ዐርጓል (ከፍ ከፍ ብሏል)።ሆኖም ግን እስከ ትንሣኤ ድረስ የትሕትናን ሥራ ከልዕልና ጋር ሲሠራ ቆይቷል።ከትንሣኤ በኋላ እስከ ዐርባ ቀን ድረስ ምሥጢረ መንግሥተ ሰማያትን ለቅዱሳን #ሐዋርያት ሲያስተምር ቆይቶ በአርባኛው ቀን በግርማና በስብሐት ወደ ሰማይ ዐረገ፤በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ።
አካላዊ ቃል ከድንግል #ማርያም ነሥቶ የተዋሐደው ሥጋ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነው ማለትም ምልዐትን፣ ስፋትን ፣ርቀትን የአብ ልጅነትን ገንዘብ ያደረገው ቃል ሥጋን በተዋሐደበት (ጌታ በተፀነሰበት) ቅጽበት ነው።ዳግመኛ በትሕትና ሥራ ላይገለጥ ከብሮ የታየበት በዓሉ ደግሞ ዕርገት ነው።
"ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ባለ ክብር ሰውነታችንን ያከብር ዘንድ በእውነት እኛ ምንድነን?ዛሬ የእኛ ሰውነት በቅዱሳን በመላእክት ታጅቦ ወደ ሰማይ ወጣ።ድል ነሥቶ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።
"በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ" ስንል ክርስቶስ ከአባቱ ቀኝ ተለይቶ ኖሮ ኋላ
ወደ አባቱ ቀኝ የሄደ አይደለም።ሰው የሆነበትን ዓላማ ፈጽሞ ሰይጣንን አሥሮ ሰውን ነፃ አውጥቶ በድል ነሺነት በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ ማለታችን ነው።
#ዕርገትን ስናስብ
#የእግዚአብሔርን ውለታ እናስባለን (እኛን ያከበረበትን ክብር)
#ያዘጋጀልንን መንግሥተ ሰማያት እናስባለን።ተስፋችን ይለመልማል።
“ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።”(ዮሐ 14፥3) "ሄጄም" ሲል ዕርገቱን ተናገረ።
#የዳግም ምጽአትን ፍርድን በማሰብ ራሳችንን እናዘጋጃለን።
“የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው #ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።”(ሐዋ 1፥11)
#በመንግሥተ ሰማያት የሚኖረንን ዕርገታዊ ሕይወት እናስባለን።
በክብር ላይ ክብር፣በጸጋ ላይ ጸጋ፣በጣዕም ላይ ጣዕም፣በመዓዛ ላይ መዓዛ በማያቋርጥ ከፍ ማለት መኖራችንን ተስፋ እናደርጋለን።
"የሙታንን መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን" "የሚመጣው ሕይወት" ምንድንነው?ከትንሣኤ በኋላ የሚኖረን የማያቋርጥ ሱታፌ #አምላክ (#እግዚአብሔርን መምሰል) ነው እንጂ!!!
ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን!!
#ኢዮብ ክንፈ
ግንቦት 21/2017 ዓ.ም
አካላዊ ቃል ከድንግል #ማርያም ነሥቶ የተዋሐደው ሥጋ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነው ማለትም ምልዐትን፣ ስፋትን ፣ርቀትን የአብ ልጅነትን ገንዘብ ያደረገው ቃል ሥጋን በተዋሐደበት (ጌታ በተፀነሰበት) ቅጽበት ነው።ዳግመኛ በትሕትና ሥራ ላይገለጥ ከብሮ የታየበት በዓሉ ደግሞ ዕርገት ነው።
"ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ባለ ክብር ሰውነታችንን ያከብር ዘንድ በእውነት እኛ ምንድነን?ዛሬ የእኛ ሰውነት በቅዱሳን በመላእክት ታጅቦ ወደ ሰማይ ወጣ።ድል ነሥቶ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።
"በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ" ስንል ክርስቶስ ከአባቱ ቀኝ ተለይቶ ኖሮ ኋላ
ወደ አባቱ ቀኝ የሄደ አይደለም።ሰው የሆነበትን ዓላማ ፈጽሞ ሰይጣንን አሥሮ ሰውን ነፃ አውጥቶ በድል ነሺነት በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ ማለታችን ነው።
#ዕርገትን ስናስብ
#የእግዚአብሔርን ውለታ እናስባለን (እኛን ያከበረበትን ክብር)
#ያዘጋጀልንን መንግሥተ ሰማያት እናስባለን።ተስፋችን ይለመልማል።
“ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።”(ዮሐ 14፥3) "ሄጄም" ሲል ዕርገቱን ተናገረ።
#የዳግም ምጽአትን ፍርድን በማሰብ ራሳችንን እናዘጋጃለን።
“የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው #ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።”(ሐዋ 1፥11)
#በመንግሥተ ሰማያት የሚኖረንን ዕርገታዊ ሕይወት እናስባለን።
በክብር ላይ ክብር፣በጸጋ ላይ ጸጋ፣በጣዕም ላይ ጣዕም፣በመዓዛ ላይ መዓዛ በማያቋርጥ ከፍ ማለት መኖራችንን ተስፋ እናደርጋለን።
"የሙታንን መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን" "የሚመጣው ሕይወት" ምንድንነው?ከትንሣኤ በኋላ የሚኖረን የማያቋርጥ ሱታፌ #አምላክ (#እግዚአብሔርን መምሰል) ነው እንጂ!!!
ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን!!
#ኢዮብ ክንፈ
ግንቦት 21/2017 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
"ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት" የዘወትር ጸሎታችን ነው።አስቀድሞ በማኅፀነ #ድንግል ሥጋችንን ቃል ስለተዋሐደው በባሕርይ አምላክነት (በፈጣሪነት) ዐርጓል (ከፍ ከፍ ብሏል)።ሆኖም ግን እስከ ትንሣኤ ድረስ የትሕትናን ሥራ ከልዕልና ጋር ሲሠራ ቆይቷል።ከትንሣኤ በኋላ እስከ ዐርባ ቀን ድረስ ምሥጢረ መንግሥተ ሰማያትን ለቅዱሳን #ሐዋርያት ሲያስተምር ቆይቶ በአርባኛው ቀን በግርማና በስብሐት ወደ ሰማይ ዐረገ፤በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ።
አካላዊ ቃል ከድንግል #ማርያም ነሥቶ የተዋሐደው ሥጋ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነው ማለትም ምልዐትን፣ ስፋትን ፣ርቀትን የአብ ልጅነትን ገንዘብ ያደረገው ቃል ሥጋን በተዋሐደበት (ጌታ በተፀነሰበት) ቅጽበት ነው።ዳግመኛ በትሕትና ሥራ ላይገለጥ ከብሮ የታየበት በዓሉ ደግሞ ዕርገት ነው።
"ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ባለ ክብር ሰውነታችንን ያከብር ዘንድ በእውነት እኛ ምንድነን?ዛሬ የእኛ ሰውነት በቅዱሳን በመላእክት ታጅቦ ወደ ሰማይ ወጣ።ድል ነሥቶ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።
"በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ" ስንል ክርስቶስ ከአባቱ ቀኝ ተለይቶ ኖሮ ኋላ
ወደ አባቱ ቀኝ የሄደ አይደለም።ሰው የሆነበትን ዓላማ ፈጽሞ ሰይጣንን አሥሮ ሰውን ነፃ አውጥቶ በድል ነሺነት በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ ማለታችን ነው።
#ዕርገትን ስናስብ
#የእግዚአብሔርን ውለታ እናስባለን (እኛን ያከበረበትን ክብር)
#ያዘጋጀልንን መንግሥተ ሰማያት እናስባለን።ተስፋችን ይለመልማል።
“ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።”(ዮሐ 14፥3) "ሄጄም" ሲል ዕርገቱን ተናገረ።
#የዳግም ምጽአትን ፍርድን በማሰብ ራሳችንን እናዘጋጃለን።
“የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው #ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።”(ሐዋ 1፥11)
#በመንግሥተ ሰማያት የሚኖረንን ዕርገታዊ ሕይወት እናስባለን።
በክብር ላይ ክብር፣በጸጋ ላይ ጸጋ፣በጣዕም ላይ ጣዕም፣በመዓዛ ላይ መዓዛ በማያቋርጥ ከፍ ማለት መኖራችንን ተስፋ እናደርጋለን።
"የሙታንን መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን" "የሚመጣው ሕይወት" ምንድንነው?ከትንሣኤ በኋላ የሚኖረን የማያቋርጥ ሱታፌ #አምላክ (#እግዚአብሔርን መምሰል) ነው እንጂ!!!
ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን!!
#ኢዮብ ክንፈ
ግንቦት 21/2017 ዓ.ም
አካላዊ ቃል ከድንግል #ማርያም ነሥቶ የተዋሐደው ሥጋ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነው ማለትም ምልዐትን፣ ስፋትን ፣ርቀትን የአብ ልጅነትን ገንዘብ ያደረገው ቃል ሥጋን በተዋሐደበት (ጌታ በተፀነሰበት) ቅጽበት ነው።ዳግመኛ በትሕትና ሥራ ላይገለጥ ከብሮ የታየበት በዓሉ ደግሞ ዕርገት ነው።
"ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ባለ ክብር ሰውነታችንን ያከብር ዘንድ በእውነት እኛ ምንድነን?ዛሬ የእኛ ሰውነት በቅዱሳን በመላእክት ታጅቦ ወደ ሰማይ ወጣ።ድል ነሥቶ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።
"በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ" ስንል ክርስቶስ ከአባቱ ቀኝ ተለይቶ ኖሮ ኋላ
ወደ አባቱ ቀኝ የሄደ አይደለም።ሰው የሆነበትን ዓላማ ፈጽሞ ሰይጣንን አሥሮ ሰውን ነፃ አውጥቶ በድል ነሺነት በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ ማለታችን ነው።
#ዕርገትን ስናስብ
#የእግዚአብሔርን ውለታ እናስባለን (እኛን ያከበረበትን ክብር)
#ያዘጋጀልንን መንግሥተ ሰማያት እናስባለን።ተስፋችን ይለመልማል።
“ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።”(ዮሐ 14፥3) "ሄጄም" ሲል ዕርገቱን ተናገረ።
#የዳግም ምጽአትን ፍርድን በማሰብ ራሳችንን እናዘጋጃለን።
“የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው #ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።”(ሐዋ 1፥11)
#በመንግሥተ ሰማያት የሚኖረንን ዕርገታዊ ሕይወት እናስባለን።
በክብር ላይ ክብር፣በጸጋ ላይ ጸጋ፣በጣዕም ላይ ጣዕም፣በመዓዛ ላይ መዓዛ በማያቋርጥ ከፍ ማለት መኖራችንን ተስፋ እናደርጋለን።
"የሙታንን መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን" "የሚመጣው ሕይወት" ምንድንነው?ከትንሣኤ በኋላ የሚኖረን የማያቋርጥ ሱታፌ #አምላክ (#እግዚአብሔርን መምሰል) ነው እንጂ!!!
ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን!!
#ኢዮብ ክንፈ
ግንቦት 21/2017 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
🔴 NEW 🔴 አዲስ የአማኑኤል ዝማሬ "ስምህ ሞገሳችን" ዘማሪ ተዋቸው ዘሪሁን Zemari Tewachew Zerihun New orthodox Mezmur @ገብርኤል
@ተልሚድቲዩብ-TelmidTube ቲዩብ-Telmid Tube ኦርቶዶክሳዊ የቪድዮ ትምህርቶች፣ መዝሙራት፣ ምክረ አበው፣ ብሒለ አበው፣ ወቅታዊ የቤተክርስቲያን መረጃዎች፣ ሃይማኖታዊ ጥቅሶችና አባባሎች እንዲሁም ትምህርታዊ የቀጥታ ሥርጭቶች የሚቀርቡበት መድረክ ነው። ማንኛውንም ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን የተመለከተ ቁም ነገር ሲፈልጉ የመጀመሪያ መድረሻዎን ተልሚድ ቲዩብ-Telmid Tube ቢያደርጉ ። የቤተ ክርስቲያናችንን…
የአፎምያ ጥያቄ የባሕራን መልስ
#ቅዱስ_ሚካኤል
እርግብ የምታገባው አንድ ብቻ ነው። ቢሞት እንኳን ሌላ መጥቶ እንዳይተናኮላት ምላሷን ትሰነጥቃለች። ድንገት ቢመጣባት በደንብ መጮህ እንድትችል እና ሌሎች መጥተው ደርሰውላት እንዲያባርሩላት ነው። ቅድስት አፎምያን እንደ እርግ የምትኖር ደገኛ ሴት ነበረች።
የኬልቅያ መስፍን የነበረው የምትወደው ባሏ አስተራኒቆስ በሞት ከተለያት በኋላ በዕውቅ አስሎ የሰጣትን የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ይዛ በጾም በጸሎት ተስና ስትኖር ጸላዬ ሰናያት የመልካም ነገሮች ሁሉ ጠላት የሆነ ሰይጣን ዲያቢሎስ ደግ መነኩሴ መስሎ መቶ ጾም ጸሎት እንድትተው ሌላ ባል አግብታ ተድላ ደስታ እንድታደርግ መከራት እርሷ ግን አባ አለባበሶት ደግ ነበር ንግግሮት ግን የከፋ ነው። ጾም ፣ጸሎት ና ምጽዋት ደገኛ ሥርዓት አይደሉምን? ስለምንስ ዳግመኛ እንዳገባ ይመክሩኛል በሉ ከኔ ወግዱልኝ ብላ አሳፍረችው። ይህን ግዜ የደበቀውን ሰይጣናዊ ግብር ገልጦ ቆቡን ጥሎ ከቁራ ሰባት ጅ ጠቆረ ሰኔ አሥራሁለት ቀን ተመልሼ እመጣለሁ አጠፋሻለሁም ብሎ ዝቶባት እንደ ጢስ ተኞ እንደ ትብያ ተኖ ጠፍቶ ሄደ ።
ሰይጣን ዲያቢሎስ እንዳለሁም ግብሩን ለውጦ በሰኔ አሥራ ሁለት ቀንም የመላእከት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን መስሎ ባማረና በተዋበ ልብስ ወደ ቤቷ መጥቶ ተገለጠላት “ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።” ተብሎ እንደተጻፈ 2ኛ ቆሮ 11፥14
ቤቴን በብርሃንህ የሞላህ አንተ ማነህ ? አለችሁ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነኝ ይህ ከብርሃኔ ተረጂ አላት ቆየኝ መጣው ብላ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጂ የነበረው ባሏ አስተራኒቆስ አስሎ ነሰጣትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕለ አድህኖ ይዛ መጣች ። እያመሳሰለችሽ ንጉሥ ለጭፍሮቹ መታወቂያ ማኅተቡን አትሞ አስይዞ ይልካቸዋል የእግዚአብሔር መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ከሆንክ ማዕተመ መስቀልህ የንጉሥህ መታወቂያ በትረ መስቀልህ የታለ ?አለችሁ። እርሱም ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና እኛ በእግዚአብሔር ፊት የምንቆም መላእክት መስቀል መያዝ ለምናችን ጨርሶ አያስፈልገንም አላት ይህን ጊዜ አንተማ መላእኩ ቅዱስ ሚካኤል አይደለህም አላምንህም አለችሁ ያን ጊዜ እንዳ ወቀችበት ሲረዳ ግብሩ ቀይሮ በብርሃን የመላው ቤቷን በጽልመት መላው ቀንዱ በቀለ ፣ጥፍሩ እረዘረዘ፣ ዐይኑ ፈጠጠ ፣ጥርሱ ገጠጠ አንቺንስ ካላጠፋሁ ሠላሜን አላገኝም ብሎ ተወርውሮም አንቆ ያዛት ቅድስት እናት አፎምያም እውነተኛው ታላቁ መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እርዳኝ ብላ በጣር ውስጥ ሆና ተጣራች እውነተኛው የእግዚአብሔር መላእክም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጣና ዲያቢሎስን ረግጦ ያስጨንቀው ገባ ሰይጣንም ሚካኤል ሆይ ጊዜዬ ሳይደርስ እንዳታጠፋኝ በፈጣሪህ እለምንሃለው እያለ ጮኸ ቅዱስ ሚካኤልም ለቀቀው በኖ ተኖ ጠፋ ቅድስት እናት አፎምያንንም ያረጋጋት ጀመር ። “ #የእግዚአብሔር_መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” እዳለ መጻሕፍ #መዝ (33) 34፥7
*አንባቢ ሆይ አንተስ በክርስቶስ ክርስቲያን ነኝ ትላለህንን እንግዲያውስ መስቀልህ የታል?
*አንባቢት ሆይ የንጉሥሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ትያለሽን? መልካም ትያለሽ ግን የንጉሡ ደመ ማዕተብ በትረ መስቀልሽ ከወዴት አለ? የአፎምያ ጥያቄ ይህ ነበር መስቀልህ የታለህ? ለአፎምያ ትክለኛ ጥያቄ መልስ የሆናት እውነተኛው ቅዱስ ሚካዬል በትረ መስቀሉን ጨብጦ ይዞ በመታየት ነው።ወዳጄ የድልህ ዐርማ የሆነውም " ሁልጊዜ በልብህ አኑረው፥ በአንገትህም እሰረው። ስትሄድም ይመራሃል፤ ስትተኛ ይጠብቅሃል፤ ስትነሣ ያነጋግርሃል። " #ምሳ 6÷21-22 የደሃ አደጊቱ ልጅ ባሕራንም የሞት ደብዳቤውን ተቀብሎ የደስታ የፍስሐ የሰርግ ደብዳቤ አድርጎ የመለሰለት የደስታ ሁሉ መልስ ቅዱስ ሚካኤል በዚህች ዕለት በነገዱ ሁሉ ላይ የተሾመበት የሹመቱ በዓል ነው!
መንፈስ ቅዱስ ያወቀውን ሰይጣን የሸመቀውን ከጠላት የተንኮል እንቆቅልሽ ሁሉ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የደስታ መልስ ይሁንልን!
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
ሰኔ ፲ ፪ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#ቅዱስ_ሚካኤል
እርግብ የምታገባው አንድ ብቻ ነው። ቢሞት እንኳን ሌላ መጥቶ እንዳይተናኮላት ምላሷን ትሰነጥቃለች። ድንገት ቢመጣባት በደንብ መጮህ እንድትችል እና ሌሎች መጥተው ደርሰውላት እንዲያባርሩላት ነው። ቅድስት አፎምያን እንደ እርግ የምትኖር ደገኛ ሴት ነበረች።
የኬልቅያ መስፍን የነበረው የምትወደው ባሏ አስተራኒቆስ በሞት ከተለያት በኋላ በዕውቅ አስሎ የሰጣትን የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ይዛ በጾም በጸሎት ተስና ስትኖር ጸላዬ ሰናያት የመልካም ነገሮች ሁሉ ጠላት የሆነ ሰይጣን ዲያቢሎስ ደግ መነኩሴ መስሎ መቶ ጾም ጸሎት እንድትተው ሌላ ባል አግብታ ተድላ ደስታ እንድታደርግ መከራት እርሷ ግን አባ አለባበሶት ደግ ነበር ንግግሮት ግን የከፋ ነው። ጾም ፣ጸሎት ና ምጽዋት ደገኛ ሥርዓት አይደሉምን? ስለምንስ ዳግመኛ እንዳገባ ይመክሩኛል በሉ ከኔ ወግዱልኝ ብላ አሳፍረችው። ይህን ግዜ የደበቀውን ሰይጣናዊ ግብር ገልጦ ቆቡን ጥሎ ከቁራ ሰባት ጅ ጠቆረ ሰኔ አሥራሁለት ቀን ተመልሼ እመጣለሁ አጠፋሻለሁም ብሎ ዝቶባት እንደ ጢስ ተኞ እንደ ትብያ ተኖ ጠፍቶ ሄደ ።
ሰይጣን ዲያቢሎስ እንዳለሁም ግብሩን ለውጦ በሰኔ አሥራ ሁለት ቀንም የመላእከት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን መስሎ ባማረና በተዋበ ልብስ ወደ ቤቷ መጥቶ ተገለጠላት “ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።” ተብሎ እንደተጻፈ 2ኛ ቆሮ 11፥14
ቤቴን በብርሃንህ የሞላህ አንተ ማነህ ? አለችሁ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነኝ ይህ ከብርሃኔ ተረጂ አላት ቆየኝ መጣው ብላ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጂ የነበረው ባሏ አስተራኒቆስ አስሎ ነሰጣትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕለ አድህኖ ይዛ መጣች ። እያመሳሰለችሽ ንጉሥ ለጭፍሮቹ መታወቂያ ማኅተቡን አትሞ አስይዞ ይልካቸዋል የእግዚአብሔር መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ከሆንክ ማዕተመ መስቀልህ የንጉሥህ መታወቂያ በትረ መስቀልህ የታለ ?አለችሁ። እርሱም ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና እኛ በእግዚአብሔር ፊት የምንቆም መላእክት መስቀል መያዝ ለምናችን ጨርሶ አያስፈልገንም አላት ይህን ጊዜ አንተማ መላእኩ ቅዱስ ሚካኤል አይደለህም አላምንህም አለችሁ ያን ጊዜ እንዳ ወቀችበት ሲረዳ ግብሩ ቀይሮ በብርሃን የመላው ቤቷን በጽልመት መላው ቀንዱ በቀለ ፣ጥፍሩ እረዘረዘ፣ ዐይኑ ፈጠጠ ፣ጥርሱ ገጠጠ አንቺንስ ካላጠፋሁ ሠላሜን አላገኝም ብሎ ተወርውሮም አንቆ ያዛት ቅድስት እናት አፎምያም እውነተኛው ታላቁ መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እርዳኝ ብላ በጣር ውስጥ ሆና ተጣራች እውነተኛው የእግዚአብሔር መላእክም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጣና ዲያቢሎስን ረግጦ ያስጨንቀው ገባ ሰይጣንም ሚካኤል ሆይ ጊዜዬ ሳይደርስ እንዳታጠፋኝ በፈጣሪህ እለምንሃለው እያለ ጮኸ ቅዱስ ሚካኤልም ለቀቀው በኖ ተኖ ጠፋ ቅድስት እናት አፎምያንንም ያረጋጋት ጀመር ። “ #የእግዚአብሔር_መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” እዳለ መጻሕፍ #መዝ (33) 34፥7
*አንባቢ ሆይ አንተስ በክርስቶስ ክርስቲያን ነኝ ትላለህንን እንግዲያውስ መስቀልህ የታል?
*አንባቢት ሆይ የንጉሥሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ትያለሽን? መልካም ትያለሽ ግን የንጉሡ ደመ ማዕተብ በትረ መስቀልሽ ከወዴት አለ? የአፎምያ ጥያቄ ይህ ነበር መስቀልህ የታለህ? ለአፎምያ ትክለኛ ጥያቄ መልስ የሆናት እውነተኛው ቅዱስ ሚካዬል በትረ መስቀሉን ጨብጦ ይዞ በመታየት ነው።ወዳጄ የድልህ ዐርማ የሆነውም " ሁልጊዜ በልብህ አኑረው፥ በአንገትህም እሰረው። ስትሄድም ይመራሃል፤ ስትተኛ ይጠብቅሃል፤ ስትነሣ ያነጋግርሃል። " #ምሳ 6÷21-22 የደሃ አደጊቱ ልጅ ባሕራንም የሞት ደብዳቤውን ተቀብሎ የደስታ የፍስሐ የሰርግ ደብዳቤ አድርጎ የመለሰለት የደስታ ሁሉ መልስ ቅዱስ ሚካኤል በዚህች ዕለት በነገዱ ሁሉ ላይ የተሾመበት የሹመቱ በዓል ነው!
መንፈስ ቅዱስ ያወቀውን ሰይጣን የሸመቀውን ከጠላት የተንኮል እንቆቅልሽ ሁሉ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የደስታ መልስ ይሁንልን!
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
ሰኔ ፲ ፪ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም