እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሰን።
ነገረ ጥምቀት
ወአሜሃ መጽአ እግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ እም ገሊላ ውስተ ዮርዳኖስ ከመ ይጠመቅ እም ዮሐንስ ... ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።
ለጌታ ሠላሳ ሲሞላው ለዮሐንስ መንፈቅ ሲተርፈው (ሠላሳ ዓመት ከስድስት ወር በኃላ) ያን ጊዜ ጌታ በዮሐንስ እጅ ይጠመቅ ዘንድ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።
እስቲ እንጠይቅ?
ማን ወደ ማን ነበር መሔድ የነበረበት? ዮሐንስ ወደ ጌታ ወይስ ጌታ ወደ ዮሐንስ? እርግጥ ፈጣሪ ወደ ፍጡሩ መሔዱ የመጣው ለትዕትና እንጂ ለልዕልና አለመሆኑን ሲያጠይቅ ነው። እንዴት ያለ ትዕትና ነው!
አንድም ስርዓትን ሲሰራ ነው። እንዴት ያለ ስርዓት ቢሉ ማንም ተጠማቂ ወደ ካህናት መሔድ እንዳለበት ሲያጠይቅ ወደ ዮሐንስ ሄዶ ተጠመቀ።
ለምን በዮርዳኖስ ተጠመቀ ቢሉ?
1. ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ
• ❝ባሕር አየች ሸሸችም፥ ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ።❞ መዝሙር 114: 3
• ❝አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ፥ምን ሆናችኋል?❞ መዝሙር 114: 5
2. ምሳሌነቱ ይፈጸም ዘንድ
• ዮርዳኖስ ነቁ አንድ ነው በኃላም በደሴቱ ይከፈላል መልሶ ከታች መልሶ ይገናኛል ።
ምሳሌነቱ ፡- ከላይ ነቁ (መነሻው) አንድ መሆኑ የሰው ዘር ሁሉ በአዳም አንድ መሆኑን ሲሆን በኃላም በደሴት መለያየቱ አንድ የነበረው የሰው ልጅ ደሴት በተባለ ኃጥያት መከፋፈሉ አንድም ህዝበ እስራኤል እና አህዛብ ተብሎ መለያየቱ ፣ ወርዶ አንድ መሆኑ በጥምቀተ ክርስቶስ ህዝብ እና አህዛብ አንድ መሆናቸውን ያሳየናል።
ዮሐንስ ግን፦ እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ ይከለክለው ነበር።
እናቱ ኤልሳቤጥ ድንግል ወደ እርሷ በመጣች ጊዜ የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል ያለው በማዕጸን እያለ ሰምቶ ነበር እና እርሱም አምላኩን ወደ እርሱ መምጣቱ ተመልክቶ ይህ ነገር እንዴት ይሆንልኛል ብሎ የጌታውን አምላክነት መሰከረ !
ኢየሱስም መልሶ፦ አሁንስ ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው። ያን ጊዜ ፈቀደለት። ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤ እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።
ማቴ 3 ፡ 13-17
ጌታ ለምን ተጠመቀ?
1. በጥምቀቱ ድኅነተ ሰጋ ድኅነተ ነብስን ሊሰጠን
• ማርቆስ 16: 16 ❝ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።❞
2. ዳግም ልደትን ለእኛ ሊሰጠን
• ዮሐንስ 3: 3 ❝ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው።❞
• ቲቶ 3፡4 ❞ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ፥ እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም❞
3. ለኃጥያታችን የስርየት መንገድ ሲሰራልን
• ሐዋርያት ስራ 22: 16 ❝አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።❞
በጥምቀት ከክርስቶስ ጋር አንድ እንደሆንን እንዲሁ መለያየታችንን ክርስቶስ በፍቅር አንድ ያድርገን ።
መምህር ዲ/ን ኢ/ር እስጢፋኖስ ደሳለኝ
👇👇👇👇
👉@Yotor24
@Yotor24
ጥር 11 2013 ዓ.ም
አ.አ / ኢትዮጲያ
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ነገረ ጥምቀት
ወአሜሃ መጽአ እግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ እም ገሊላ ውስተ ዮርዳኖስ ከመ ይጠመቅ እም ዮሐንስ ... ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።
ለጌታ ሠላሳ ሲሞላው ለዮሐንስ መንፈቅ ሲተርፈው (ሠላሳ ዓመት ከስድስት ወር በኃላ) ያን ጊዜ ጌታ በዮሐንስ እጅ ይጠመቅ ዘንድ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።
እስቲ እንጠይቅ?
ማን ወደ ማን ነበር መሔድ የነበረበት? ዮሐንስ ወደ ጌታ ወይስ ጌታ ወደ ዮሐንስ? እርግጥ ፈጣሪ ወደ ፍጡሩ መሔዱ የመጣው ለትዕትና እንጂ ለልዕልና አለመሆኑን ሲያጠይቅ ነው። እንዴት ያለ ትዕትና ነው!
አንድም ስርዓትን ሲሰራ ነው። እንዴት ያለ ስርዓት ቢሉ ማንም ተጠማቂ ወደ ካህናት መሔድ እንዳለበት ሲያጠይቅ ወደ ዮሐንስ ሄዶ ተጠመቀ።
ለምን በዮርዳኖስ ተጠመቀ ቢሉ?
1. ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ
• ❝ባሕር አየች ሸሸችም፥ ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ።❞ መዝሙር 114: 3
• ❝አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ፥ምን ሆናችኋል?❞ መዝሙር 114: 5
2. ምሳሌነቱ ይፈጸም ዘንድ
• ዮርዳኖስ ነቁ አንድ ነው በኃላም በደሴቱ ይከፈላል መልሶ ከታች መልሶ ይገናኛል ።
ምሳሌነቱ ፡- ከላይ ነቁ (መነሻው) አንድ መሆኑ የሰው ዘር ሁሉ በአዳም አንድ መሆኑን ሲሆን በኃላም በደሴት መለያየቱ አንድ የነበረው የሰው ልጅ ደሴት በተባለ ኃጥያት መከፋፈሉ አንድም ህዝበ እስራኤል እና አህዛብ ተብሎ መለያየቱ ፣ ወርዶ አንድ መሆኑ በጥምቀተ ክርስቶስ ህዝብ እና አህዛብ አንድ መሆናቸውን ያሳየናል።
ዮሐንስ ግን፦ እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ ይከለክለው ነበር።
እናቱ ኤልሳቤጥ ድንግል ወደ እርሷ በመጣች ጊዜ የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል ያለው በማዕጸን እያለ ሰምቶ ነበር እና እርሱም አምላኩን ወደ እርሱ መምጣቱ ተመልክቶ ይህ ነገር እንዴት ይሆንልኛል ብሎ የጌታውን አምላክነት መሰከረ !
ኢየሱስም መልሶ፦ አሁንስ ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው። ያን ጊዜ ፈቀደለት። ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤ እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።
ማቴ 3 ፡ 13-17
ጌታ ለምን ተጠመቀ?
1. በጥምቀቱ ድኅነተ ሰጋ ድኅነተ ነብስን ሊሰጠን
• ማርቆስ 16: 16 ❝ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።❞
2. ዳግም ልደትን ለእኛ ሊሰጠን
• ዮሐንስ 3: 3 ❝ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው።❞
• ቲቶ 3፡4 ❞ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ፥ እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም❞
3. ለኃጥያታችን የስርየት መንገድ ሲሰራልን
• ሐዋርያት ስራ 22: 16 ❝አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።❞
በጥምቀት ከክርስቶስ ጋር አንድ እንደሆንን እንዲሁ መለያየታችንን ክርስቶስ በፍቅር አንድ ያድርገን ።
መምህር ዲ/ን ኢ/ር እስጢፋኖስ ደሳለኝ
👇👇👇👇
👉@Yotor24
@Yotor24
ጥር 11 2013 ዓ.ም
አ.አ / ኢትዮጲያ
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
✞ቻይ ሆይ ታገስ✞
ስትታገስ የምታተርፈው እንጂ የምታጣው አንዳችም ነገር አይኖርም ለጊዜው በጽኑ ብትፈተንም በለሷን በመታገስ ጠብቀሃታልና ፍሬዋን ትበላለህ ይህች ፍሬ ግን እንደዘበት አትገኝም ታለፋለች ታደክማለች ካወቅባት ለምትሄደው መንገድ ርስት ብሎም ስንቅ ትሆንሃለች ካሰብክበት ካለምክበት ቦታ ታደርስሃለች ቻይ ሆይ ታገስ ! በምትሰማው ነገር በምታየው ድርጊት እንዳትሸበር ትዕግስትክ እየተሸረሸረ ተመናምኖ ይቀራልና ክርስቶስ ይህችን ግራ ይምታጋባ ዓለም በምን ያሸነፋት ይመስልሃል? በትዕግስት እኮ ነው! ሀሜቱን፣ ስድቡን፣ ዱላውን ፣መከራውን፣ረሃብ ጥሙን ታግሶ አልፎ " በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ፤ ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ" ብሎ ዓለም ለምታቀርብልን ፈተና ዝግጁ እንድንሆን እርሱን ይዘን እንደምናሸንፋት ተስፋ ሰጥቶ ልበ ሙሉ እንድንሆን በር የከፈተልን። አድምጠኝማ ወዳጄ ክርስትያን በዓላማው የሚጸና ጽኑ ታጋሽ አስተውሎ ነገሮችን መርምሮ የሚናገር ሁሌም አዛኝቷ ድንግል ማርያምን ከመንገዱ አስቀድሞ የሚጓዝ ተስፈኛ .. ኸረ ምኑን ጠቅሼ ልጨርስልህ! በቃ ጠቅለል ሳደርግልሀህ አምላኩን መድኅን ዓለም ክርስቶስን በቃልም በህይወቱም የመሰለ ማለት ነው ። ስለዚህ ወዳጄ ቶሎ እንደ ጀበና የምትገነፍል ከሆነ ልምድ በልምድ ይሻራልና ትዕግስትን ተለማመዳት ከዛ ሳታውቀው እንደ ቀሚስ ከአካልህ አጥልቀሃት እንደ መቀነት ትታጠቃታለህ ያኔ ትሁት ትሆናለህ ክርስቶስን ትመስላለህ በእምነት ጠንክረው እንደጸኑት አባቶች ትመስላለህ ይህን ታደርግ ዘንድ ቸሩ መድኃኔዓለም ከእናቱ ከቸሪቱ ከአማላጂቱ ከድንግል ማርያም ጋር አብሮህ ይሁን።!!!አሜን!!!
ቡሩክ መልሳቸው
ጥር 13 2013 ዓ.ም
አ.አ/ኢትዮጵያ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ስትታገስ የምታተርፈው እንጂ የምታጣው አንዳችም ነገር አይኖርም ለጊዜው በጽኑ ብትፈተንም በለሷን በመታገስ ጠብቀሃታልና ፍሬዋን ትበላለህ ይህች ፍሬ ግን እንደዘበት አትገኝም ታለፋለች ታደክማለች ካወቅባት ለምትሄደው መንገድ ርስት ብሎም ስንቅ ትሆንሃለች ካሰብክበት ካለምክበት ቦታ ታደርስሃለች ቻይ ሆይ ታገስ ! በምትሰማው ነገር በምታየው ድርጊት እንዳትሸበር ትዕግስትክ እየተሸረሸረ ተመናምኖ ይቀራልና ክርስቶስ ይህችን ግራ ይምታጋባ ዓለም በምን ያሸነፋት ይመስልሃል? በትዕግስት እኮ ነው! ሀሜቱን፣ ስድቡን፣ ዱላውን ፣መከራውን፣ረሃብ ጥሙን ታግሶ አልፎ " በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ፤ ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ" ብሎ ዓለም ለምታቀርብልን ፈተና ዝግጁ እንድንሆን እርሱን ይዘን እንደምናሸንፋት ተስፋ ሰጥቶ ልበ ሙሉ እንድንሆን በር የከፈተልን። አድምጠኝማ ወዳጄ ክርስትያን በዓላማው የሚጸና ጽኑ ታጋሽ አስተውሎ ነገሮችን መርምሮ የሚናገር ሁሌም አዛኝቷ ድንግል ማርያምን ከመንገዱ አስቀድሞ የሚጓዝ ተስፈኛ .. ኸረ ምኑን ጠቅሼ ልጨርስልህ! በቃ ጠቅለል ሳደርግልሀህ አምላኩን መድኅን ዓለም ክርስቶስን በቃልም በህይወቱም የመሰለ ማለት ነው ። ስለዚህ ወዳጄ ቶሎ እንደ ጀበና የምትገነፍል ከሆነ ልምድ በልምድ ይሻራልና ትዕግስትን ተለማመዳት ከዛ ሳታውቀው እንደ ቀሚስ ከአካልህ አጥልቀሃት እንደ መቀነት ትታጠቃታለህ ያኔ ትሁት ትሆናለህ ክርስቶስን ትመስላለህ በእምነት ጠንክረው እንደጸኑት አባቶች ትመስላለህ ይህን ታደርግ ዘንድ ቸሩ መድኃኔዓለም ከእናቱ ከቸሪቱ ከአማላጂቱ ከድንግል ማርያም ጋር አብሮህ ይሁን።!!!አሜን!!!
ቡሩክ መልሳቸው
ጥር 13 2013 ዓ.ም
አ.አ/ኢትዮጵያ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
@AwediMeherit
"፤አንደበትህን ከክፉ ከልክል፥ ከንፈሮችህም ሽንገላን እንዳይናገሩ። "
አንደበት እሳት ነው። አንደበትህን ካልተቆጣጠርህ አንድ የክብሪት እንጨት ትልቁን ግንድ እንደምታነደው ሁሉ ያንተ ምላስ ብዙኃንን ታስከፋለች ስሜት ትጎዳለች ቅዱሱ ያዕቆብ በመልዕክቱ ስለ አንደበት ሲናገር "(የያዕቆብ መልእክት ምዕራፍ 3 ) እንዲሁም አንደበት ደግሞ ትንሽ ብልት ሆኖ በታላላቅ ነገር ይመካል። እነሆ፥ ትንሽ እሳት እንዴት ያለ ትልቅ ጫካ ያቃጥላል ፤ አንደበትም እሳት ነው። አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአል፤ ሥጋን ሁሉ ያሳድፋልና፥ የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፥ በገሃነምም ይቃጠላል።" ብሎ ገልጦታል።
* ታዲያ አንደበታችንን ክፋውን ነገር ከመናገር እንዲቆጠብ ምን እናድርግ? ቀላል ነው! በማስተዋል ማውራት ይህም ማለት ሕሊናችንን( አዕምሮ ) ከአንደበታችንን (ምላስ) ጋር በማስተባበር በመጽሐፍ ቅዱስ እንደምናነበው አንድ ሰው ለጌታችን (የማርቆስ ወንጌል 9 ) "መምህር ሆይ፥ ዲዳ መንፈስ ያደረበትን ልጄን ወደ አንተ አምጥቼአለሁ፤በያዘውም ስፍራ ሁሉ ይጥለዋል፤ አረፋም ይደፍቃል፥ ጥርሱንም ያፋጫል ይደርቃልም፤ እንዲያወጡለትም ለደቀ መዛሙርትህ ነገርኋቸው፥ አልቻሉምም አለው"። እርሱም መልሶ። የማታምን ትውልድ ሆይ፥ እስከመቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ወደ እኔ አምጡት አላቸው።ወደ እርሱም አመጡት። እርሱንም ባየ ጊዜ ያ መንፈስ ወዲያው አንፈራገጠው፤ ወደ ምድርም ወድቆ አረፋ እየደፈቀ ተንፈራፈረ። ብዙ ጊዜም ሊያጠፋው ወደ እሳትም ወደ ውኃም ጣለው፤ ቢቻልህ ግን እዘንልን እርዳንም አለው። ኢየሱስም። ቢቻልህ ትላለህ፤ ለሚያምን ሁሉ ይቻላል አለው። ወዲያውም የብላቴናው አባት ጮኾ። አምናለሁ፤ አለማመኔን እርዳው አለ። ይህ ሰው በችኮላ መድኃኒት የሆነውን ክርስቶስን " ቢቻልህ እዘንልን" ብሎ በአንደበቱ ችኩልነት የፍጥረትን ጌታ ባለማስተዋሉ ተሳሳተ። አንተ ሰው አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ እንደው ሠማይና ምድርን የፈጠረ ጌታን ይህን ፈውሰ አያደርግም ብለህ እንዴት አሰብክ? ኋላ ግን ማመንህ በጀህ ጥፋትህን አምነህ አለማመኔን እርዳው ብለህ ታረምህ ። እንዲሁም ጌታችንን አንዲት ከነናዊት ሴት ልጄን ማርልኝ ብላ ብትጠይቀው (የማቴዎስ ወንጌል 15 ) እርሱ ግን መልሶ። የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም አለ።እርስዋም አዎን ጌታ ሆይ፤ ''ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ'' አለች። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ አንቺ ሴት እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ዳነች። ይህ አይነት አንደበት ሲኖረን ጥበብ ከእውቀት ጋር ከእኛ ትሆናለች ሐስት ቦታ አጥታ ከእኛ ትሸሻለች ለሐሰት ሞተን ለእውነት መኖር እንጀምራለን " የእውነት ከንፈር ለዘላለም ትቆማለች ፤ ውሸተኛ ከንፈር ግን ለቅጽበት ነው " እንደተባለ ከዚያም ንግግራችን በጨው እንደተቀመመ በጸጋ ይሆናል ትህትናን ገንዘብ እናደርጋለን "፤ ሞትና ሕይወት በምላስ እጅ ናቸው፤ የሚወድዱአትም ፍሬዋን ይበላሉ። " እንደተባለ መልካሙን የሕይወት ፍሬ ለመብላት እንበቃለን ማለት ነው ..... ይህን እንፈጽም ዘንድ እመብርሃን ድንግል ማርያም ትርዳን...አሜን!!!
* ማውራት ከመጀመርህ በፊት ሁለቱን ማገናኘት አትርሳ *
.....ቡሩክ መልሣቸው ...
.....ጥር 14/ 2013....
.....አ.አ ኢትዮጵያ
@BarokZamin
አንደበት እሳት ነው። አንደበትህን ካልተቆጣጠርህ አንድ የክብሪት እንጨት ትልቁን ግንድ እንደምታነደው ሁሉ ያንተ ምላስ ብዙኃንን ታስከፋለች ስሜት ትጎዳለች ቅዱሱ ያዕቆብ በመልዕክቱ ስለ አንደበት ሲናገር "(የያዕቆብ መልእክት ምዕራፍ 3 ) እንዲሁም አንደበት ደግሞ ትንሽ ብልት ሆኖ በታላላቅ ነገር ይመካል። እነሆ፥ ትንሽ እሳት እንዴት ያለ ትልቅ ጫካ ያቃጥላል ፤ አንደበትም እሳት ነው። አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአል፤ ሥጋን ሁሉ ያሳድፋልና፥ የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፥ በገሃነምም ይቃጠላል።" ብሎ ገልጦታል።
* ታዲያ አንደበታችንን ክፋውን ነገር ከመናገር እንዲቆጠብ ምን እናድርግ? ቀላል ነው! በማስተዋል ማውራት ይህም ማለት ሕሊናችንን( አዕምሮ ) ከአንደበታችንን (ምላስ) ጋር በማስተባበር በመጽሐፍ ቅዱስ እንደምናነበው አንድ ሰው ለጌታችን (የማርቆስ ወንጌል 9 ) "መምህር ሆይ፥ ዲዳ መንፈስ ያደረበትን ልጄን ወደ አንተ አምጥቼአለሁ፤በያዘውም ስፍራ ሁሉ ይጥለዋል፤ አረፋም ይደፍቃል፥ ጥርሱንም ያፋጫል ይደርቃልም፤ እንዲያወጡለትም ለደቀ መዛሙርትህ ነገርኋቸው፥ አልቻሉምም አለው"። እርሱም መልሶ። የማታምን ትውልድ ሆይ፥ እስከመቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ወደ እኔ አምጡት አላቸው።ወደ እርሱም አመጡት። እርሱንም ባየ ጊዜ ያ መንፈስ ወዲያው አንፈራገጠው፤ ወደ ምድርም ወድቆ አረፋ እየደፈቀ ተንፈራፈረ። ብዙ ጊዜም ሊያጠፋው ወደ እሳትም ወደ ውኃም ጣለው፤ ቢቻልህ ግን እዘንልን እርዳንም አለው። ኢየሱስም። ቢቻልህ ትላለህ፤ ለሚያምን ሁሉ ይቻላል አለው። ወዲያውም የብላቴናው አባት ጮኾ። አምናለሁ፤ አለማመኔን እርዳው አለ። ይህ ሰው በችኮላ መድኃኒት የሆነውን ክርስቶስን " ቢቻልህ እዘንልን" ብሎ በአንደበቱ ችኩልነት የፍጥረትን ጌታ ባለማስተዋሉ ተሳሳተ። አንተ ሰው አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ እንደው ሠማይና ምድርን የፈጠረ ጌታን ይህን ፈውሰ አያደርግም ብለህ እንዴት አሰብክ? ኋላ ግን ማመንህ በጀህ ጥፋትህን አምነህ አለማመኔን እርዳው ብለህ ታረምህ ። እንዲሁም ጌታችንን አንዲት ከነናዊት ሴት ልጄን ማርልኝ ብላ ብትጠይቀው (የማቴዎስ ወንጌል 15 ) እርሱ ግን መልሶ። የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም አለ።እርስዋም አዎን ጌታ ሆይ፤ ''ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ'' አለች። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ አንቺ ሴት እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ዳነች። ይህ አይነት አንደበት ሲኖረን ጥበብ ከእውቀት ጋር ከእኛ ትሆናለች ሐስት ቦታ አጥታ ከእኛ ትሸሻለች ለሐሰት ሞተን ለእውነት መኖር እንጀምራለን " የእውነት ከንፈር ለዘላለም ትቆማለች ፤ ውሸተኛ ከንፈር ግን ለቅጽበት ነው " እንደተባለ ከዚያም ንግግራችን በጨው እንደተቀመመ በጸጋ ይሆናል ትህትናን ገንዘብ እናደርጋለን "፤ ሞትና ሕይወት በምላስ እጅ ናቸው፤ የሚወድዱአትም ፍሬዋን ይበላሉ። " እንደተባለ መልካሙን የሕይወት ፍሬ ለመብላት እንበቃለን ማለት ነው ..... ይህን እንፈጽም ዘንድ እመብርሃን ድንግል ማርያም ትርዳን...አሜን!!!
* ማውራት ከመጀመርህ በፊት ሁለቱን ማገናኘት አትርሳ *
.....ቡሩክ መልሣቸው ...
.....ጥር 14/ 2013....
.....አ.አ ኢትዮጵያ
@BarokZamin
❤ውድ ታዳሚዎቻችን እንደምን ዋላችሁ (አደራችሁ) ...አሜን ስለ ቸርነቱ እግዚአብሔር አምላክ የተመሰገነ ይሁን አትለይምና እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ #ቅድስት_ድንግል_ማርያምም እንደተሰጣት ከፍ ያለ ጸጋ የተመሠገነች ትሁንልን አሜን..!::
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
✞ኀዘናችንን ወደ ደስታ ለውጦታል✞
ዛሬ ወደ አስቴር ህይወት እናቅና መጽሐፍ ቅዱሱ " የተዋበች መልከመልካም ነበረች" ብሎ ስለ አካላዊ ውበቷ ተናግሮ አድንቆ ይጀምራል። የገጽዋ ውበት እንዲ ከተገለጸ ውሳጣዊ ውበቷን ማወቅ ምን ያክል እንደሚያጓጓ መገመት አያቅትም። ንጉሱ አርጤክስ ቀዳማዊ ሚስቱ አስጢን በድላው ፊቱን አዙሮባት ነበርና የእርሱ አገልጋዮች ሁለተኛ ድንግል ልጃገረድ እንደሚያስፈልገው ያወጉት። መቼስ ንጉስ አልጋ ወራሽ ያስፈልገው ብቻውንም ይሆን ዘንድ አይገባምና ሀሳባቸውን ተቀብሎ ከድንግልናዋ ውጪ የእርሱን መስፈርት ልታሟላ የምትችል ሴት መጥታ ፈተናውን መፈተን እንደምትችል አዋጅ ያስነገረው።ያን ጊዜ ነበር መልከ መልካሟ አመለ ሸጋዋ አስቴር በንጉሱ ቅጽር የተገኘችው። የፈተናው ጊዜ ተጀመረ! ሁሉም ንግስት የመሆን ፍላጓታቸውን አንግበው በተስፋ ወደ ንጉሱ እልፍኝ ገቡ ፈተናቸውን አጠናቀው እየወጡ የአስቴር ተራ ደርሶ ወደ ፈተናው አዳራሽ ያለፍርሃት እግዚአብሔርን ይዛ ገባች። ወዲያውኑ ንጉሱ ፊት ክብርና ሞገስ አግኝታ ንጉሱም በእርሷ ተማርኳ ድል ተነሳ። ያኔ በዚያ የተሰበሰቡ በንጉሱ ዘንድ ተቀባይነት ያጡ ሴቶች ምነኛ አዘኑ ይሆን? የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደተጻፈ አስቴር በእግዚአብሔር ተመክታ እርሱን ይዛ የንጉሱን ልብ ተቆጣጠረች ውጫዊ ብቻ ሳይሆን የውስጧ ውበት ልዩ ነበር ። ነገር ግን የውስጥ ውበት ምንድር ነው ? በአጭሩ ስንገልጸው ትሁትነት ነው። ትሁት ልብ ቅን ነው ደግነትን ያበዛል፤ ትሁት ልብ የዋህ ነው ይራራል፤ ትሁት ልብ እውነተኛ ፍቅር አለው ሁሉንም በእኩል ያያል አይጨክንም ምክንያቱም ፍቅር ይታገሣል፥ ቸርነትንም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር አይመካም፥ አይታበይም፤ የማይገባውን አያደርግም፥ የራሱንም አይፈልግም፥ አይበሳጭም፥ በደልን አይቆጥርም። ይህን ያሟላ በምድራውያን ሰዎች በሰማያውያን መላእክት ብሎም በእግዚአብሔር ዘንድ ክብርን ይጎናጸፋል።
ወደ አስቴር ስንመለስ በንግስናዋ ወራት ክፋውን እና ደጉንም በእግዚአብሔር አጋዥነት ለንጉሱ እየገለጠች ተአማኒነትን ፍቅርን በንጉሱም በሐዝቡ ዘንድ አተረፈች። ክፋውንም ድግስ ሲያሰናዳ የነበረውን በአሳዳጊዋ በመርዶክዮስ እና በሕዝቦቿ ላይ ሲያሴር የነበረውን የሐማን ግብር በልዩ ጥበብ አጋለጠች። የሐማ ዘውድ የሐማ ቀለበት የሐማ ክብር እና ሥልጣን ለመርዶክዮስ ተሠጠ።ሐማ ለመርዶክዮስ ባዘጋጀው መስቀል ላይ እራሱ ተሰቀለ ፤ አዳም ከእስራቱ ተፈቶ ነፃ ወጥቶ የሐሰት አባት ዲያቢሎስ በንፋስ አውታር በእሳት ዣንዥርታ እንደታሰረ ሁሉ፤ የአስቴር ሕዝብ አይሁዶች በአስቴር ድንቅ ስራ ነፃ ወጡ ከሞት ዳኑ የአዳም ልጆች እኛም በክርስቶስ የማዳን ስራ በደሙ ቤዛነት ከሞት አመለጥን ከውርደት ድነን ክብርን አገኘን።
በዚያችም ቀን ለአይሁድም ብርሃንና ደስታ ተድላና ክብርም ሆነ። ኀዘናቸው ወደ ደስታ ተለውጧልና ፤ እኛም ከጨለማ ወደ ብርሃን ገብተናልና ከዲያቢሎስ ቁራኝነት ነጻ ወጥተናልና እንደ አስቴር ከርስቶስን ይዘናልና እርሱ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ኀዘናችንን ወደ ደስታ ለውጦልናል ለማይከፈል ውለታው ለመድኃኒታችን ክብር እና ምስጋና አምልኮ እና ውዳሴ ለእርሱ ይሁን አሜን!!!።
........ቡሩክ መልሳቸው......
......ጥር 15/2013......
.......አ.አ ኢትዮጵያ .......
@BarokZamin
ዛሬ ወደ አስቴር ህይወት እናቅና መጽሐፍ ቅዱሱ " የተዋበች መልከመልካም ነበረች" ብሎ ስለ አካላዊ ውበቷ ተናግሮ አድንቆ ይጀምራል። የገጽዋ ውበት እንዲ ከተገለጸ ውሳጣዊ ውበቷን ማወቅ ምን ያክል እንደሚያጓጓ መገመት አያቅትም። ንጉሱ አርጤክስ ቀዳማዊ ሚስቱ አስጢን በድላው ፊቱን አዙሮባት ነበርና የእርሱ አገልጋዮች ሁለተኛ ድንግል ልጃገረድ እንደሚያስፈልገው ያወጉት። መቼስ ንጉስ አልጋ ወራሽ ያስፈልገው ብቻውንም ይሆን ዘንድ አይገባምና ሀሳባቸውን ተቀብሎ ከድንግልናዋ ውጪ የእርሱን መስፈርት ልታሟላ የምትችል ሴት መጥታ ፈተናውን መፈተን እንደምትችል አዋጅ ያስነገረው።ያን ጊዜ ነበር መልከ መልካሟ አመለ ሸጋዋ አስቴር በንጉሱ ቅጽር የተገኘችው። የፈተናው ጊዜ ተጀመረ! ሁሉም ንግስት የመሆን ፍላጓታቸውን አንግበው በተስፋ ወደ ንጉሱ እልፍኝ ገቡ ፈተናቸውን አጠናቀው እየወጡ የአስቴር ተራ ደርሶ ወደ ፈተናው አዳራሽ ያለፍርሃት እግዚአብሔርን ይዛ ገባች። ወዲያውኑ ንጉሱ ፊት ክብርና ሞገስ አግኝታ ንጉሱም በእርሷ ተማርኳ ድል ተነሳ። ያኔ በዚያ የተሰበሰቡ በንጉሱ ዘንድ ተቀባይነት ያጡ ሴቶች ምነኛ አዘኑ ይሆን? የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደተጻፈ አስቴር በእግዚአብሔር ተመክታ እርሱን ይዛ የንጉሱን ልብ ተቆጣጠረች ውጫዊ ብቻ ሳይሆን የውስጧ ውበት ልዩ ነበር ። ነገር ግን የውስጥ ውበት ምንድር ነው ? በአጭሩ ስንገልጸው ትሁትነት ነው። ትሁት ልብ ቅን ነው ደግነትን ያበዛል፤ ትሁት ልብ የዋህ ነው ይራራል፤ ትሁት ልብ እውነተኛ ፍቅር አለው ሁሉንም በእኩል ያያል አይጨክንም ምክንያቱም ፍቅር ይታገሣል፥ ቸርነትንም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር አይመካም፥ አይታበይም፤ የማይገባውን አያደርግም፥ የራሱንም አይፈልግም፥ አይበሳጭም፥ በደልን አይቆጥርም። ይህን ያሟላ በምድራውያን ሰዎች በሰማያውያን መላእክት ብሎም በእግዚአብሔር ዘንድ ክብርን ይጎናጸፋል።
ወደ አስቴር ስንመለስ በንግስናዋ ወራት ክፋውን እና ደጉንም በእግዚአብሔር አጋዥነት ለንጉሱ እየገለጠች ተአማኒነትን ፍቅርን በንጉሱም በሐዝቡ ዘንድ አተረፈች። ክፋውንም ድግስ ሲያሰናዳ የነበረውን በአሳዳጊዋ በመርዶክዮስ እና በሕዝቦቿ ላይ ሲያሴር የነበረውን የሐማን ግብር በልዩ ጥበብ አጋለጠች። የሐማ ዘውድ የሐማ ቀለበት የሐማ ክብር እና ሥልጣን ለመርዶክዮስ ተሠጠ።ሐማ ለመርዶክዮስ ባዘጋጀው መስቀል ላይ እራሱ ተሰቀለ ፤ አዳም ከእስራቱ ተፈቶ ነፃ ወጥቶ የሐሰት አባት ዲያቢሎስ በንፋስ አውታር በእሳት ዣንዥርታ እንደታሰረ ሁሉ፤ የአስቴር ሕዝብ አይሁዶች በአስቴር ድንቅ ስራ ነፃ ወጡ ከሞት ዳኑ የአዳም ልጆች እኛም በክርስቶስ የማዳን ስራ በደሙ ቤዛነት ከሞት አመለጥን ከውርደት ድነን ክብርን አገኘን።
በዚያችም ቀን ለአይሁድም ብርሃንና ደስታ ተድላና ክብርም ሆነ። ኀዘናቸው ወደ ደስታ ተለውጧልና ፤ እኛም ከጨለማ ወደ ብርሃን ገብተናልና ከዲያቢሎስ ቁራኝነት ነጻ ወጥተናልና እንደ አስቴር ከርስቶስን ይዘናልና እርሱ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ኀዘናችንን ወደ ደስታ ለውጦልናል ለማይከፈል ውለታው ለመድኃኒታችን ክብር እና ምስጋና አምልኮ እና ውዳሴ ለእርሱ ይሁን አሜን!!!።
........ቡሩክ መልሳቸው......
......ጥር 15/2013......
.......አ.አ ኢትዮጵያ .......
@BarokZamin
+ #እመ_ዕረፍት +
ዛሬ እመ ዕረፍት ዐረፈች፤እመ ሕይወት ዛሬ ሞትን ቀመሰች፤ዛሬ አማናዊት ዕፀ ሕይወት
ከዕፀ ሕይወት ሥር ዐረፈች።ዲያቢሎስ በክፋት ግብሩ ጥል ፣ሞት እየተባለ እንደሚጠራ
(ኤፌ 2፥16፤1ኛ ቆሮ 15፥26) እንዲሁ እግዚአብሔርም በጽድቁ ንጹህ ብቻ ሳይሆን
ንጽሕና ሕያው ብቻ ሳይሆን ሕይወት እየተባለ ይጠራል።ዛሬ "የአሸናፊ እግዚአብሔር እናቱ"
ድንግል ማርያም ዐረፈች።አራቱ ባሕርያተ ሥጋን አምስተኛ ባሕርየ ነፍስን አዋሕዶ የፈጠረ
(ዘፍ 2፥7) የጌታችን እናቱ ዛሬ ቅድስት ነፍሷ ከክቡር ሥጋዋ ተለየ።"እንደ እመቤታችን
እንደ ማርያም የአብ ማረፊያ የሆነ ማን ነው?እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የወልድ
ማደሪያ የሆነ ማን ነው?እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የመንፈስቅዱስ ንጹሕ አዳራሽ
የሆነ ማን ነው?"(ተአምረ ማርያም)።እኛም በአንክሮ በተደሞ "እንደ እመቤታችን እንደ
ማርያም ሞት እንግዳ ነገር ምንድን ነው?" ስንል እንጠይቃለን።"ሞት የኃጢአት ደሞዝ
ነዋ"(ዘፍ 2፥17፤ሮሜ6፥23)።በክብር ሁሉ ጌጥ ያጌጠ እርሱ ያደረባት ንጽሕት የሰርግ ቤት
ታዲያ ለምን ታርፋለች?ይህስ መርምረን የማንዘልቀው ድንቅ የመለኮት ሥራ ነው።አዳምና
ሔዋን የእግዚአብሔርን ቃል አቃልለው ምክረ ሰይጣንን ሰምተው ሞትን ወደ ዓለም
አገቡ።ድንግል ማርያም ግን በመልአከ ብሥራት በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ቃለ
እግዚአብሔርን ሰምታ ሕይወትን ለዓለም ሰጠች።(ሮሜ 5፥12-17)።ታዲያ እመቤታችን
እንዴት ዐረፈች?ይህንን ነገር ፈጽመን መናገር አይቻለንምና ዝም እንበል።
ሰንበተ ክርሰቲያን ድንግል ማርያም በሰንበተ ክርስቲያን እሑድ ዐረፈች።ዕለተ እሑድ
የድንግል ማርያም ምሳሌ ነው።በዕለተ እሑድ የፍጥረታት መሠረት የሆኑ አራቱ ባሕርያተ
ሥጋ(አሥራወ ፍጥረታት) ተገኝተዋል።ከድንግል ማርያምም የፍጥረታት ሁሉ አስገኚ ጌታ
ተገኝቷል።ዕለተ እሑድ የፍጥረታት መጀመሪያ ነው ድንግል ማርያም ግን ለጠፋው ፍጥረት
ሁሉ "የደኅንነት መጀመሪያ" ናት።በዕለተ እሑድ ገነት ተፈጠረልን "ስለ ሔዋን የተዘጋብን
የገነት ደጅ" "በምትናገር ገነት" በድንግል ማርያም "ዳግመኛ ተከፈተልን"
በዕለተ እሑድ መንግሥተ ሰማያት ተፈጠርልን በድንግል ማርያም ግን ዕለት ተዕለት
"መንግሥትህ ትምጣ" "መንግሥት የአንተ ናትና" እያልን የምንማጸነው መንግሥቱን
የሚያወርሰን አምላካችን አማኑኤል ተገኘልን።በዕለተ እሑድ እግዚአብሔር አምላክ ውኃን
ፈጠረ በፈጠረው ውኃም ላይ መንፈሱን አሰፈረ።መንፈስ ቅዱስ የጠበቃት ኃይለ ልዑል
የጋረዳት ድንግል ማርያም ግን "ማንም የተጠማ" ከእርሱ የሚጠጣ ጠጥተውት ዳግመኛ
የማያስጠማ ማየ ሕይወት ክርስቶስን ወለደችልን።በዕለተ እሑድ መላእክት ተፈጠሩ
በአማናዊት እሑድ በድንግል ማርያም ግን"ኪሩቤል በፍርሃት የሚሰግዱለት ሱራፌልም
የሚያመሰግኑት" "የመላእክት ደስታቸው"መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገኘ።በዕለተ
እሑድ "እግዚአብሔር ብርሃን ይሁን አለ ብርሃንም ሆነ።"(ዘፍ 1፥3)በድንግል ማርያም ግን
"በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ" ለምንኖር ለእኛ "ታላቅ ብርሃን ወጣልን።"በዕለተ እሑድ
መንግሥተ ሰማያት ለጻድቃን ትሰጣለች ጌታችን ከድንግል ማርያም የነሣውን ሥጋ ግን
ወርሰውት ለዘላለም ይኖራሉ።እመቤታችን ሆይ በማንና በምን እንመስልሻለን?ሰንበት
ድንግል ማርያም ሆይ ሰንበት ከሚባል የሰንበታት ጌታ ከሆነ ልጅሽ ጸጋውን ክብሩን
እንዳይነሣን ለምኚልን።
እመቤታችን ካረፈች በኋላ ለምቀኝነት የማያርፉ አይሁድ በፊት ልጇ ከሞተ በኋላ ተነሥቷል
ዐርጓል እያሉ አወኩን።አሁን ደግሞ እሷን ተነሣች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን?
ይህ ከመሆኑ አስቀድሞ ሥጋዋን እናቃለጥለው ተባባሉ።ምቀኝነት ትርፉ ይህ
ነው።መታወክ።"ዓለም እንደሚሰጠው ሰላም ያይደለ እውነተኛ ሰላም የሚሰጠን የሰላም
አለቃ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ" ግን ዕረፍተ ኅሊናን እናገኝ ዘንድ "ጠላቶቻችሁን
ውደዱ" ብሎ አስተማረን።ማኅደረ ሰይጣን የሆነ ታዖፋንያ የሚባል ከእነርሱ አንዱ ክቡር
ሥጋዋን አቃጥላለሁ ብሎ የአልጋዋን አጎበር ቢይዝ መልአከ እግዚአብሔር እጆቹን በሰይፍ
ቆርጧቸዋል።አላወቃትማ "ቢያውቃትስ ኖሮ የክብርን እናት ሥጋ ለማቃጠል ባልደፈረ
ነበር።" በመስቀል ላይ"አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያዉቁምና ይቅር በላቸው"ብሎ የለመነ
የፍቅር እናቱ የምትሆን ድንግል ማርያም ግን በከበረ ምልጃዋ እጆቹን አሰጠችው።እሱ
ቅዱስ ሥጋዋን ለማቃጠል እጆቹን ዘረጋ እመቤታችን ግን በሥጋዉም ሆነ በነፍሱ ታድነው
ዘንድ የምህረት እጆቿን ዘረጋችለት።ወንጌልን ያስተማርሽን ንጽሕት ፊደላችን ሆይ
እናመሰግንሻለን።የድንግል ማርያም ትንሣኤ ያውካልን?አዎን፤ በእኛ በክርስቲያኖች ዘንድ
"ከኪሩቤልና ከሱራፌል የሚበልጥ የመወደድ ግርማ" ያላት ድንግል ማርያም
በአጋጋንት፣በአይሁድና በመናፍቃን ዘንድ ግን "ከቅዱስ ሚካኤልና ከቅዱስ ገብርኤል
የሚበልጥ የማስፈራት" ግርማ አላት።
ከከበረ ዮሐንስ ጋር ወደ ዕፀ ሕይወት ተነጠቀች።"ዓለም አልተገባቸውምና።"(ዕብ
11፥38)ጌታን ከሁሉ አብልጦ ለወደደ ዮሐንስ ከሁሉ አብልጦ የሚወዳት ድንግል
ማርያምን በዕለተ ዓርብ ሰጠው።ከወንድሞቹ ሐዋርያት ተለይቶ ከእመቤታችን ጋር ከእግረ
መስቀሉ ሥር የተገኘ ዮሐንስ አሁን ደግሞ ከእነርሱ ተለይቶ ከእመቤታችን ጋር ከዕፀ
ሕይወት ሥር ተገኘ።ቅዱስ ዮሐንስ ከሕይወት ከክርስቶስ ደረት እየተጠጋ ጌታውን ያነጋግር
እንደነበረም ቅዱስ ወንጌል ነግሮናል።የቅዱስ ዮሐንስ እናት ማርያም ጌታ ሆይ በዙፋንህ
በተቀመጥህ ጊዜ አንዱ ልጄን በቀኝህ አንዱን በግራ አስቀምጥልኝ ብላ ለምናው
ነበር።በዙፋኑ "በአባቱ ቀኝ"የተቀመጠውም ቅዱስ "በቀኙ በምትቆመው" በአማናዊቱ ዙፋን
በድንግል ማርያም አጠገብ ከዕፀ ሕይወት ሥር አኖረው።ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን
በዕለተ ዓርብ ከጌታችን ከተቀበለ በኋላ "ወደ ቤቱ ወሰዳት"(ዮሐ19፥27) እሷ ደግሞ አሁን
በዕለተ እሑድ "ወደ ቤቷ ወሰደችው"። የዓርብ መከራ ተካፋይ ቅዱስ ዮሐንስ የእሑድ ደስታ
ተካፋይም ነበር።ዕፀ ሕይወት አዳምን ከእርጅናው(ከኃጢአቱ) ልታድሰው አልቻለችም።ዕፀ
ሕይወት ድንግል ማርያም ግን "በአዲስ ተፈጥሮ" ዳግመኛ የሚፈጥረዉን ሕይወቱ
ክርስቶስን ወለደችለት።ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ይላል "ከዕፀ ሕይወት እንበላ ዘንድ አደለን
ይኸውም... የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙ ነው።"
ሞቷ እንደ ልጇ ሞት ነው።እሱ መላ ዘመኑን አዝኖ "ነፍሱ እስከሞት ድረስ ያዘነች" ሆና
ሞተ።(ማቴ 26፥38)
እሷም ከእሱ ጋር ተንከራታ "በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል"እንዳላት ቅዱስ ስምዖን አረጋዊ(ሉቃ
2፥34-35) እንደ ሰይፍ ነፍስን ከሥጋ ሊለይ የሚችል ጽኑ ኀዘንና መከራ ገጥሟት
ሞተች።የጌታችን ሞት ቅዱሳን መላእክትንና ሰዎችን አንድ አደረገ።የእመቤታችንም ሞት
እንዲሁ ነው።
ትንሣኤዋም እንደ ልጇ ትንሣኤ ነው። እንደ ልጇ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር
ቆይታ ተነሥታለችና።"ከመ ትንሣኤ ወልዳ" "እንደ ልጇ ትንሣኤ" ያሰኘውም ይህ
ነው።"ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር የተባበረች ድንግል ማርያም ትንሣኤውን
ዛሬ እመ ዕረፍት ዐረፈች፤እመ ሕይወት ዛሬ ሞትን ቀመሰች፤ዛሬ አማናዊት ዕፀ ሕይወት
ከዕፀ ሕይወት ሥር ዐረፈች።ዲያቢሎስ በክፋት ግብሩ ጥል ፣ሞት እየተባለ እንደሚጠራ
(ኤፌ 2፥16፤1ኛ ቆሮ 15፥26) እንዲሁ እግዚአብሔርም በጽድቁ ንጹህ ብቻ ሳይሆን
ንጽሕና ሕያው ብቻ ሳይሆን ሕይወት እየተባለ ይጠራል።ዛሬ "የአሸናፊ እግዚአብሔር እናቱ"
ድንግል ማርያም ዐረፈች።አራቱ ባሕርያተ ሥጋን አምስተኛ ባሕርየ ነፍስን አዋሕዶ የፈጠረ
(ዘፍ 2፥7) የጌታችን እናቱ ዛሬ ቅድስት ነፍሷ ከክቡር ሥጋዋ ተለየ።"እንደ እመቤታችን
እንደ ማርያም የአብ ማረፊያ የሆነ ማን ነው?እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የወልድ
ማደሪያ የሆነ ማን ነው?እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የመንፈስቅዱስ ንጹሕ አዳራሽ
የሆነ ማን ነው?"(ተአምረ ማርያም)።እኛም በአንክሮ በተደሞ "እንደ እመቤታችን እንደ
ማርያም ሞት እንግዳ ነገር ምንድን ነው?" ስንል እንጠይቃለን።"ሞት የኃጢአት ደሞዝ
ነዋ"(ዘፍ 2፥17፤ሮሜ6፥23)።በክብር ሁሉ ጌጥ ያጌጠ እርሱ ያደረባት ንጽሕት የሰርግ ቤት
ታዲያ ለምን ታርፋለች?ይህስ መርምረን የማንዘልቀው ድንቅ የመለኮት ሥራ ነው።አዳምና
ሔዋን የእግዚአብሔርን ቃል አቃልለው ምክረ ሰይጣንን ሰምተው ሞትን ወደ ዓለም
አገቡ።ድንግል ማርያም ግን በመልአከ ብሥራት በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ቃለ
እግዚአብሔርን ሰምታ ሕይወትን ለዓለም ሰጠች።(ሮሜ 5፥12-17)።ታዲያ እመቤታችን
እንዴት ዐረፈች?ይህንን ነገር ፈጽመን መናገር አይቻለንምና ዝም እንበል።
ሰንበተ ክርሰቲያን ድንግል ማርያም በሰንበተ ክርስቲያን እሑድ ዐረፈች።ዕለተ እሑድ
የድንግል ማርያም ምሳሌ ነው።በዕለተ እሑድ የፍጥረታት መሠረት የሆኑ አራቱ ባሕርያተ
ሥጋ(አሥራወ ፍጥረታት) ተገኝተዋል።ከድንግል ማርያምም የፍጥረታት ሁሉ አስገኚ ጌታ
ተገኝቷል።ዕለተ እሑድ የፍጥረታት መጀመሪያ ነው ድንግል ማርያም ግን ለጠፋው ፍጥረት
ሁሉ "የደኅንነት መጀመሪያ" ናት።በዕለተ እሑድ ገነት ተፈጠረልን "ስለ ሔዋን የተዘጋብን
የገነት ደጅ" "በምትናገር ገነት" በድንግል ማርያም "ዳግመኛ ተከፈተልን"
በዕለተ እሑድ መንግሥተ ሰማያት ተፈጠርልን በድንግል ማርያም ግን ዕለት ተዕለት
"መንግሥትህ ትምጣ" "መንግሥት የአንተ ናትና" እያልን የምንማጸነው መንግሥቱን
የሚያወርሰን አምላካችን አማኑኤል ተገኘልን።በዕለተ እሑድ እግዚአብሔር አምላክ ውኃን
ፈጠረ በፈጠረው ውኃም ላይ መንፈሱን አሰፈረ።መንፈስ ቅዱስ የጠበቃት ኃይለ ልዑል
የጋረዳት ድንግል ማርያም ግን "ማንም የተጠማ" ከእርሱ የሚጠጣ ጠጥተውት ዳግመኛ
የማያስጠማ ማየ ሕይወት ክርስቶስን ወለደችልን።በዕለተ እሑድ መላእክት ተፈጠሩ
በአማናዊት እሑድ በድንግል ማርያም ግን"ኪሩቤል በፍርሃት የሚሰግዱለት ሱራፌልም
የሚያመሰግኑት" "የመላእክት ደስታቸው"መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገኘ።በዕለተ
እሑድ "እግዚአብሔር ብርሃን ይሁን አለ ብርሃንም ሆነ።"(ዘፍ 1፥3)በድንግል ማርያም ግን
"በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ" ለምንኖር ለእኛ "ታላቅ ብርሃን ወጣልን።"በዕለተ እሑድ
መንግሥተ ሰማያት ለጻድቃን ትሰጣለች ጌታችን ከድንግል ማርያም የነሣውን ሥጋ ግን
ወርሰውት ለዘላለም ይኖራሉ።እመቤታችን ሆይ በማንና በምን እንመስልሻለን?ሰንበት
ድንግል ማርያም ሆይ ሰንበት ከሚባል የሰንበታት ጌታ ከሆነ ልጅሽ ጸጋውን ክብሩን
እንዳይነሣን ለምኚልን።
እመቤታችን ካረፈች በኋላ ለምቀኝነት የማያርፉ አይሁድ በፊት ልጇ ከሞተ በኋላ ተነሥቷል
ዐርጓል እያሉ አወኩን።አሁን ደግሞ እሷን ተነሣች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን?
ይህ ከመሆኑ አስቀድሞ ሥጋዋን እናቃለጥለው ተባባሉ።ምቀኝነት ትርፉ ይህ
ነው።መታወክ።"ዓለም እንደሚሰጠው ሰላም ያይደለ እውነተኛ ሰላም የሚሰጠን የሰላም
አለቃ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ" ግን ዕረፍተ ኅሊናን እናገኝ ዘንድ "ጠላቶቻችሁን
ውደዱ" ብሎ አስተማረን።ማኅደረ ሰይጣን የሆነ ታዖፋንያ የሚባል ከእነርሱ አንዱ ክቡር
ሥጋዋን አቃጥላለሁ ብሎ የአልጋዋን አጎበር ቢይዝ መልአከ እግዚአብሔር እጆቹን በሰይፍ
ቆርጧቸዋል።አላወቃትማ "ቢያውቃትስ ኖሮ የክብርን እናት ሥጋ ለማቃጠል ባልደፈረ
ነበር።" በመስቀል ላይ"አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያዉቁምና ይቅር በላቸው"ብሎ የለመነ
የፍቅር እናቱ የምትሆን ድንግል ማርያም ግን በከበረ ምልጃዋ እጆቹን አሰጠችው።እሱ
ቅዱስ ሥጋዋን ለማቃጠል እጆቹን ዘረጋ እመቤታችን ግን በሥጋዉም ሆነ በነፍሱ ታድነው
ዘንድ የምህረት እጆቿን ዘረጋችለት።ወንጌልን ያስተማርሽን ንጽሕት ፊደላችን ሆይ
እናመሰግንሻለን።የድንግል ማርያም ትንሣኤ ያውካልን?አዎን፤ በእኛ በክርስቲያኖች ዘንድ
"ከኪሩቤልና ከሱራፌል የሚበልጥ የመወደድ ግርማ" ያላት ድንግል ማርያም
በአጋጋንት፣በአይሁድና በመናፍቃን ዘንድ ግን "ከቅዱስ ሚካኤልና ከቅዱስ ገብርኤል
የሚበልጥ የማስፈራት" ግርማ አላት።
ከከበረ ዮሐንስ ጋር ወደ ዕፀ ሕይወት ተነጠቀች።"ዓለም አልተገባቸውምና።"(ዕብ
11፥38)ጌታን ከሁሉ አብልጦ ለወደደ ዮሐንስ ከሁሉ አብልጦ የሚወዳት ድንግል
ማርያምን በዕለተ ዓርብ ሰጠው።ከወንድሞቹ ሐዋርያት ተለይቶ ከእመቤታችን ጋር ከእግረ
መስቀሉ ሥር የተገኘ ዮሐንስ አሁን ደግሞ ከእነርሱ ተለይቶ ከእመቤታችን ጋር ከዕፀ
ሕይወት ሥር ተገኘ።ቅዱስ ዮሐንስ ከሕይወት ከክርስቶስ ደረት እየተጠጋ ጌታውን ያነጋግር
እንደነበረም ቅዱስ ወንጌል ነግሮናል።የቅዱስ ዮሐንስ እናት ማርያም ጌታ ሆይ በዙፋንህ
በተቀመጥህ ጊዜ አንዱ ልጄን በቀኝህ አንዱን በግራ አስቀምጥልኝ ብላ ለምናው
ነበር።በዙፋኑ "በአባቱ ቀኝ"የተቀመጠውም ቅዱስ "በቀኙ በምትቆመው" በአማናዊቱ ዙፋን
በድንግል ማርያም አጠገብ ከዕፀ ሕይወት ሥር አኖረው።ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን
በዕለተ ዓርብ ከጌታችን ከተቀበለ በኋላ "ወደ ቤቱ ወሰዳት"(ዮሐ19፥27) እሷ ደግሞ አሁን
በዕለተ እሑድ "ወደ ቤቷ ወሰደችው"። የዓርብ መከራ ተካፋይ ቅዱስ ዮሐንስ የእሑድ ደስታ
ተካፋይም ነበር።ዕፀ ሕይወት አዳምን ከእርጅናው(ከኃጢአቱ) ልታድሰው አልቻለችም።ዕፀ
ሕይወት ድንግል ማርያም ግን "በአዲስ ተፈጥሮ" ዳግመኛ የሚፈጥረዉን ሕይወቱ
ክርስቶስን ወለደችለት።ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ይላል "ከዕፀ ሕይወት እንበላ ዘንድ አደለን
ይኸውም... የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙ ነው።"
ሞቷ እንደ ልጇ ሞት ነው።እሱ መላ ዘመኑን አዝኖ "ነፍሱ እስከሞት ድረስ ያዘነች" ሆና
ሞተ።(ማቴ 26፥38)
እሷም ከእሱ ጋር ተንከራታ "በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል"እንዳላት ቅዱስ ስምዖን አረጋዊ(ሉቃ
2፥34-35) እንደ ሰይፍ ነፍስን ከሥጋ ሊለይ የሚችል ጽኑ ኀዘንና መከራ ገጥሟት
ሞተች።የጌታችን ሞት ቅዱሳን መላእክትንና ሰዎችን አንድ አደረገ።የእመቤታችንም ሞት
እንዲሁ ነው።
ትንሣኤዋም እንደ ልጇ ትንሣኤ ነው። እንደ ልጇ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር
ቆይታ ተነሥታለችና።"ከመ ትንሣኤ ወልዳ" "እንደ ልጇ ትንሣኤ" ያሰኘውም ይህ
ነው።"ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር የተባበረች ድንግል ማርያም ትንሣኤውን
በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከልጇ ጋር ተባበረች።"(ሮሜ 6፥5)
ዕርገቷም እንደ ልጇ ዕርገት ነው።ልጇ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስፍራ ሊያዘጋጅልን ወደ
ሰማይ ዐረገ።(ዮሐ 14፥2-3)እርሷም በቃልኪዳኗ መንግሥተ ሰማያትን ልታዘጋጅልን ወደ
ሰማይ ዐረገች።ጌታችን ሲያርግ "ምርኮን ማረከ"።(መዝ 67፥18)እመቤታችንም በዕርገቷ
ብዙ ነፍሳትን ማረከች።ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ አለ "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል
ሆንሽ።"እንዲህ ነው እግዚአብሔርን መምሰል ማለት።
"ነገረ ማርያምን ማወቅ ነገረ ክርስቶስን ማወቅ ነው።"
"ቅድስት ሆይ ለምኚልን"
#አዘጋጅ መ/ር ኢዮብ ክንፈ
ጥር 2012 ዓ.ም
ዕርገቷም እንደ ልጇ ዕርገት ነው።ልጇ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስፍራ ሊያዘጋጅልን ወደ
ሰማይ ዐረገ።(ዮሐ 14፥2-3)እርሷም በቃልኪዳኗ መንግሥተ ሰማያትን ልታዘጋጅልን ወደ
ሰማይ ዐረገች።ጌታችን ሲያርግ "ምርኮን ማረከ"።(መዝ 67፥18)እመቤታችንም በዕርገቷ
ብዙ ነፍሳትን ማረከች።ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ አለ "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል
ሆንሽ።"እንዲህ ነው እግዚአብሔርን መምሰል ማለት።
"ነገረ ማርያምን ማወቅ ነገረ ክርስቶስን ማወቅ ነው።"
"ቅድስት ሆይ ለምኚልን"
#አዘጋጅ መ/ር ኢዮብ ክንፈ
ጥር 2012 ዓ.ም
ጎልያድን የገደለ #ሐዲስ ዳዊት #ሊቀ_ሰማዕቱ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ
#በተኵላና_በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ።
#በእኔ_ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ።
#ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤አድነዋለሁ አከብረውማለሁ። " #መዝ 90(91)÷13-15
ይህ #የእግዚአብሔር_ቃል ነው ፤ እንግዲህ #እግዚአብሔር_ያከበረውን ማን ያቀልዋል ? #ማንም!
#በተኵላና_በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ።
#በእኔ_ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ።
#ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤አድነዋለሁ አከብረውማለሁ። " #መዝ 90(91)÷13-15
ይህ #የእግዚአብሔር_ቃል ነው ፤ እንግዲህ #እግዚአብሔር_ያከበረውን ማን ያቀልዋል ? #ማንም!
#ኢትዮጵያዊው_ኤልሳዕ
በአጽሙ ሙት ያስነሳ
፪ኛ ነገሥት ፲ ፫÷፳ -፳ ፩
ገ/ተ ሃይማኖት ም/፶ ፫
አጥንት በመጻሕፍ ቅዱስ ውስጥ በምሳሌነት ሲጠቀስ ሦስት ነገሮችን ያመለክታል።
፩ የሰው ኃይልን ያመላክታል መዝ፶ ፫፥፭ ኢሳ፴፰፥፲፫
፪ የቅርብ ዝምድና መግለጫ ዘፍ ፳፱÷፲፬ ሳሙ ፱÷፪
፫ የሞተ ሰውን ክብር ያስረዳል ዘፍ ፶÷፳፭ ዕብ ፲፩÷፳፪
#ይበልጡኑ_የቅዱሳን_ሰዎች ሞት /አጥንት (አጽም)/ እጅግ የከበረ ነው ። መዝ ፻፲፭ (፻፲፮) ÷፲፭ ለአብነትም ተቀብሮ የነበረው የኤልሳዕ አጥንት /አጽም/ ሌላ የሞተ ሰው ከሞት እንዳስነሳ መመልከት በቂ ነው። ከሞዓብም አደጋ ጣዮች በየዓመቱ ወደ አገሩ ይገቡ ነበር።ሰዎችም አንድ ሰው ሲቀብሩ አደጋ ጣዮችን አዩ፥ ሬሳውንም በኤልሳዕ መቃብር ጣሉት፤ የኤልሳዕንም አጥንት በነካ ጊዜ ሰውዮው ድኖ በእግሩ ቆመ። ፪ኛ ነገሥት ፲፫÷፳ -፳፩
በተመሳሳይ ኢትዮጵያዊው ኤልሳዕ ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖትም የሥጋ ድካም ከትጋቱ እንዳያስታጉለው በስምንት ሰለታም ጦር እራሱን ከቦ ከደብረ አስቦ ዋሻ ከቆመ ሳይቀመጥ ከዘረጋ ሳያጥፍ ፳፪ ዓመት ሲጋደል ሳለ ከመቆም ብዛት አንዲቷ የእግሯ አገዳ ተሰበረችና ከሰውነቱ ተለይታ ወደቀች።
#ደቀ_መዛሙርቱም እንደ ማንም መስሏቸው ስባረ እግሩን ከመቃብር ሥፍራ ወረወሯት የኤልሳዕን አጽም ሲነካው ከሞት ድኖ እንደተነሳው ሰው የአባታችን የእግራቸው አጥንት የነካው በመቃብሩ ሥፍራ ተቀብሮ የነበረ አንድ ሰው አፈፍ ብሎ ድኖ በእግሩ ቆመ ። ገ/ተ ሃይማኖት ፶ ፫
የአባታችንንም ስባረ አጽም (ስባረ እግር) እያመሰገነ ሰላምታ ሰጠ " ይህን ያዮ ደቀ መዛሙርቶቻቸውም የጻድቁ ስባረ አጽም ገባሬ ተአምራት መሆኗን አውቀው ከመንበሩ እግር በታች አክብረው በሰበን ጠቅልለው ቀብረዋታል::
" #የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፥ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል። እግዚአብሔር አጥንቶቻቸውን ሁሉ ይጠብቃል፥ ከእነርሱም አንድ አይሰበርም። " መዝ ፴፫{፴፬}÷፲፱-፳ ይህ የቅዱሳን አጥንት (አጽም) እግዚአብሔር የማይለየውና ሌት ተቀን የሚጠብቀው ነውና ቅዱሳን ጻድቃን ካረፉበት ሄዶ መሳለም በረከትን ያሰጣል ከሥጋም ከነፍስም ህመም አድኖ በጤና ያቆማልና የአጽማቸውን በዓል ማክበር እጅግ የሚገባ ነው ::
ቅዱስ ጳውሎስ በልብሱ ጨርቅ " (ሐዋ፲፱÷፲፩-፲፪) ቅዱስ ጴጥሮስ በሰውነቱ ጥላ ድውያንን ሁሉ ይፈውሳቸው ነበር ። ( ሐዋ ፭÷፲፭ ) ቅዱሳን የነፍሳቸው ቅድስና ለሥጋቸው፣ የሥጋቸው ቅድስና ለለበሱት ልብስና ለአካላቸው ጥላ ተርፎ ድንቅ ተአምራትን የሚሰራ ከሆነ እግዚአብሔር የሚጠብቀው አጽማቸውማ እንዴት አብልጦ ድንቆችን አይሳ?!::
#አጥንት_ለሰዉ ልጅ ተክለ ሰውነት ወሳኝ ድርሻ አለው። ከሚሰጣቸው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች መካከል የተወሰኑት ብንዳስስ፤ ለሰዉነታችን ቅርፅ ለመስጠት፣ የሰዉነት የውስጥ አካላት (Organs) ከአደጋ ለመከላከል #ለምሳሌ ደረት የሚያርፍበት ክፍለ አጥንት ለሳንባና ለልብ ከለላ(covering) ይሰጣል፤ የራስ ቅል አጥንት አንጎል ምንም አይነት ጉዳት እንዳይገጥመው ጠንካራ ልባስ ሆኖ ይከላከላል ፣ ሥጋና ጡነቻዎቻችንን አጣብቆ ለመያዝና የካልስየም ንጥረ ነገርን ለማጠራቀም ይረዳል፡፡
ክቡር የሆነ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖትም ለቀናች ሃይማኖቱ አጥንት ነው። አጥንት የሌለው አካል ጤፍ እንደሌለው ማዳበሪያ መቆም አይቻለሁም:: ሀገሪቱና ቤተክርስቲያኒቱ ዶግማ ቀኖናና ትውፊቷን ይዛ ቅርጻን ሳትለቅ ቀጥ ብላ እንድትቆም አድርጓታልና።
#ምዕመኗ ልዮ ልዮ በሆነ በእግዳ ትምህርት ከበረትቷ እንዳይኮበልሉ ኖላዊ ትጉሁ ሆኖ በጻም በጸሎቱ የሀገር ዋልታ ጥላ ከለለ በመሆንም አካል የምትባል ቤተክርስቲያንን እንደ አጥንት ጋሻ፣ መከታ፣ ጥላ ፣ከለላ ሆነላት።
የሃይማኖት ማነስ የምግባር ጉድለት እንዳያጋጥማትም እንደ አጥንት እያለ በቃሉ ትምህር በእጁ ተአምራት በበረከቱና ሞላት በረድኤቱ ጋረዳት የሃይማኖት መፍሰሻ ነቅ የወንጌል መፍለቂያ ምንጭም አደረጋት።
#ዞሮ_ማስተማሩ ሳይሰለቸው ፳፪ዓመት በጾም፣ በጸሎት መቆሙ ሳይታየው ፤የእግሩም መሰበር ግድ ሳይሰጠው በአንዲት እግሩ ሰባት ዓመት በትእግስት ቆሞ በትግኃ ጸሎት ጽሙድ ሆኖ ፳፱ ዓመት አስቆጠረ። “እነሆ፥ በትዕግሥት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደ ታገሠ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደ ፈጸመለት አይታችኋል፤ ” የሚለውም ቃል በዳግማዊ ኢዮብ በጻድቁ ተክለ ሃይማኖት ደግሞ ተገለጠ ስለዚህ ብጹህ ይባል ዘንድ የተገባው ነው #ያዕቆብ ፭÷፲፩
"በጻድቅ ሰው ጸሎት ሀገር ትለማለች እንጂ አትጠፋም" እዳለው ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የመቆም ምክንያት እርሱ ብጹዊው አባታችን የጀርባ አጥንቷ ነው ። “የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።” ያዕ ፭ ፥፲፮
#በአጽሙ_ሙት ያስነሳ የኢትዮጵያዊው ኤልሳዕ የዳግማዊው ኢዮብ #የብጹዕ_አባታችን_የቅዱስ_ተክለ_ሃይማኖት በረከት በሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ላይ ጸንታ ትኑር!
.......ይቆየን.........
ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
ጥር ፳ ፬\፳ ፻ ፲ ፫ዓ.ም
👇👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
#ዓውደ_ምሕረት_የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
@AwediMeherit
በአጽሙ ሙት ያስነሳ
፪ኛ ነገሥት ፲ ፫÷፳ -፳ ፩
ገ/ተ ሃይማኖት ም/፶ ፫
አጥንት በመጻሕፍ ቅዱስ ውስጥ በምሳሌነት ሲጠቀስ ሦስት ነገሮችን ያመለክታል።
፩ የሰው ኃይልን ያመላክታል መዝ፶ ፫፥፭ ኢሳ፴፰፥፲፫
፪ የቅርብ ዝምድና መግለጫ ዘፍ ፳፱÷፲፬ ሳሙ ፱÷፪
፫ የሞተ ሰውን ክብር ያስረዳል ዘፍ ፶÷፳፭ ዕብ ፲፩÷፳፪
#ይበልጡኑ_የቅዱሳን_ሰዎች ሞት /አጥንት (አጽም)/ እጅግ የከበረ ነው ። መዝ ፻፲፭ (፻፲፮) ÷፲፭ ለአብነትም ተቀብሮ የነበረው የኤልሳዕ አጥንት /አጽም/ ሌላ የሞተ ሰው ከሞት እንዳስነሳ መመልከት በቂ ነው። ከሞዓብም አደጋ ጣዮች በየዓመቱ ወደ አገሩ ይገቡ ነበር።ሰዎችም አንድ ሰው ሲቀብሩ አደጋ ጣዮችን አዩ፥ ሬሳውንም በኤልሳዕ መቃብር ጣሉት፤ የኤልሳዕንም አጥንት በነካ ጊዜ ሰውዮው ድኖ በእግሩ ቆመ። ፪ኛ ነገሥት ፲፫÷፳ -፳፩
በተመሳሳይ ኢትዮጵያዊው ኤልሳዕ ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖትም የሥጋ ድካም ከትጋቱ እንዳያስታጉለው በስምንት ሰለታም ጦር እራሱን ከቦ ከደብረ አስቦ ዋሻ ከቆመ ሳይቀመጥ ከዘረጋ ሳያጥፍ ፳፪ ዓመት ሲጋደል ሳለ ከመቆም ብዛት አንዲቷ የእግሯ አገዳ ተሰበረችና ከሰውነቱ ተለይታ ወደቀች።
#ደቀ_መዛሙርቱም እንደ ማንም መስሏቸው ስባረ እግሩን ከመቃብር ሥፍራ ወረወሯት የኤልሳዕን አጽም ሲነካው ከሞት ድኖ እንደተነሳው ሰው የአባታችን የእግራቸው አጥንት የነካው በመቃብሩ ሥፍራ ተቀብሮ የነበረ አንድ ሰው አፈፍ ብሎ ድኖ በእግሩ ቆመ ። ገ/ተ ሃይማኖት ፶ ፫
የአባታችንንም ስባረ አጽም (ስባረ እግር) እያመሰገነ ሰላምታ ሰጠ " ይህን ያዮ ደቀ መዛሙርቶቻቸውም የጻድቁ ስባረ አጽም ገባሬ ተአምራት መሆኗን አውቀው ከመንበሩ እግር በታች አክብረው በሰበን ጠቅልለው ቀብረዋታል::
" #የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፥ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል። እግዚአብሔር አጥንቶቻቸውን ሁሉ ይጠብቃል፥ ከእነርሱም አንድ አይሰበርም። " መዝ ፴፫{፴፬}÷፲፱-፳ ይህ የቅዱሳን አጥንት (አጽም) እግዚአብሔር የማይለየውና ሌት ተቀን የሚጠብቀው ነውና ቅዱሳን ጻድቃን ካረፉበት ሄዶ መሳለም በረከትን ያሰጣል ከሥጋም ከነፍስም ህመም አድኖ በጤና ያቆማልና የአጽማቸውን በዓል ማክበር እጅግ የሚገባ ነው ::
ቅዱስ ጳውሎስ በልብሱ ጨርቅ " (ሐዋ፲፱÷፲፩-፲፪) ቅዱስ ጴጥሮስ በሰውነቱ ጥላ ድውያንን ሁሉ ይፈውሳቸው ነበር ። ( ሐዋ ፭÷፲፭ ) ቅዱሳን የነፍሳቸው ቅድስና ለሥጋቸው፣ የሥጋቸው ቅድስና ለለበሱት ልብስና ለአካላቸው ጥላ ተርፎ ድንቅ ተአምራትን የሚሰራ ከሆነ እግዚአብሔር የሚጠብቀው አጽማቸውማ እንዴት አብልጦ ድንቆችን አይሳ?!::
#አጥንት_ለሰዉ ልጅ ተክለ ሰውነት ወሳኝ ድርሻ አለው። ከሚሰጣቸው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች መካከል የተወሰኑት ብንዳስስ፤ ለሰዉነታችን ቅርፅ ለመስጠት፣ የሰዉነት የውስጥ አካላት (Organs) ከአደጋ ለመከላከል #ለምሳሌ ደረት የሚያርፍበት ክፍለ አጥንት ለሳንባና ለልብ ከለላ(covering) ይሰጣል፤ የራስ ቅል አጥንት አንጎል ምንም አይነት ጉዳት እንዳይገጥመው ጠንካራ ልባስ ሆኖ ይከላከላል ፣ ሥጋና ጡነቻዎቻችንን አጣብቆ ለመያዝና የካልስየም ንጥረ ነገርን ለማጠራቀም ይረዳል፡፡
ክቡር የሆነ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖትም ለቀናች ሃይማኖቱ አጥንት ነው። አጥንት የሌለው አካል ጤፍ እንደሌለው ማዳበሪያ መቆም አይቻለሁም:: ሀገሪቱና ቤተክርስቲያኒቱ ዶግማ ቀኖናና ትውፊቷን ይዛ ቅርጻን ሳትለቅ ቀጥ ብላ እንድትቆም አድርጓታልና።
#ምዕመኗ ልዮ ልዮ በሆነ በእግዳ ትምህርት ከበረትቷ እንዳይኮበልሉ ኖላዊ ትጉሁ ሆኖ በጻም በጸሎቱ የሀገር ዋልታ ጥላ ከለለ በመሆንም አካል የምትባል ቤተክርስቲያንን እንደ አጥንት ጋሻ፣ መከታ፣ ጥላ ፣ከለላ ሆነላት።
የሃይማኖት ማነስ የምግባር ጉድለት እንዳያጋጥማትም እንደ አጥንት እያለ በቃሉ ትምህር በእጁ ተአምራት በበረከቱና ሞላት በረድኤቱ ጋረዳት የሃይማኖት መፍሰሻ ነቅ የወንጌል መፍለቂያ ምንጭም አደረጋት።
#ዞሮ_ማስተማሩ ሳይሰለቸው ፳፪ዓመት በጾም፣ በጸሎት መቆሙ ሳይታየው ፤የእግሩም መሰበር ግድ ሳይሰጠው በአንዲት እግሩ ሰባት ዓመት በትእግስት ቆሞ በትግኃ ጸሎት ጽሙድ ሆኖ ፳፱ ዓመት አስቆጠረ። “እነሆ፥ በትዕግሥት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደ ታገሠ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደ ፈጸመለት አይታችኋል፤ ” የሚለውም ቃል በዳግማዊ ኢዮብ በጻድቁ ተክለ ሃይማኖት ደግሞ ተገለጠ ስለዚህ ብጹህ ይባል ዘንድ የተገባው ነው #ያዕቆብ ፭÷፲፩
"በጻድቅ ሰው ጸሎት ሀገር ትለማለች እንጂ አትጠፋም" እዳለው ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የመቆም ምክንያት እርሱ ብጹዊው አባታችን የጀርባ አጥንቷ ነው ። “የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።” ያዕ ፭ ፥፲፮
#በአጽሙ_ሙት ያስነሳ የኢትዮጵያዊው ኤልሳዕ የዳግማዊው ኢዮብ #የብጹዕ_አባታችን_የቅዱስ_ተክለ_ሃይማኖት በረከት በሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ላይ ጸንታ ትኑር!
.......ይቆየን.........
ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
ጥር ፳ ፬\፳ ፻ ፲ ፫ዓ.ም
👇👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
#ዓውደ_ምሕረት_የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
@AwediMeherit