ዐውደ ምሕረት
3.67K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
195 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
+ #እመ_ዕረፍት +
ዛሬ እመ ዕረፍት ዐረፈች፤እመ ሕይወት ዛሬ ሞትን ቀመሰች፤ዛሬ አማናዊት ዕፀ ሕይወት
ከዕፀ ሕይወት ሥር ዐረፈች።ዲያቢሎስ በክፋት ግብሩ ጥል ፣ሞት እየተባለ እንደሚጠራ
(ኤፌ 2፥16፤1ኛ ቆሮ 15፥26) እንዲሁ እግዚአብሔርም በጽድቁ ንጹህ ብቻ ሳይሆን
ንጽሕና ሕያው ብቻ ሳይሆን ሕይወት እየተባለ ይጠራል።ዛሬ "የአሸናፊ እግዚአብሔር እናቱ"
ድንግል ማርያም ዐረፈች።አራቱ ባሕርያተ ሥጋን አምስተኛ ባሕርየ ነፍስን አዋሕዶ የፈጠረ
(ዘፍ 2፥7) የጌታችን እናቱ ዛሬ ቅድስት ነፍሷ ከክቡር ሥጋዋ ተለየ።"እንደ እመቤታችን
እንደ ማርያም የአብ ማረፊያ የሆነ ማን ነው?እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የወልድ
ማደሪያ የሆነ ማን ነው?እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የመንፈስቅዱስ ንጹሕ አዳራሽ
የሆነ ማን ነው?"(ተአምረ ማርያም)።እኛም በአንክሮ በተደሞ "እንደ እመቤታችን እንደ
ማርያም ሞት እንግዳ ነገር ምንድን ነው?" ስንል እንጠይቃለን።"ሞት የኃጢአት ደሞዝ
ነዋ"(ዘፍ 2፥17፤ሮሜ6፥23)።በክብር ሁሉ ጌጥ ያጌጠ እርሱ ያደረባት ንጽሕት የሰርግ ቤት
ታዲያ ለምን ታርፋለች?ይህስ መርምረን የማንዘልቀው ድንቅ የመለኮት ሥራ ነው።አዳምና
ሔዋን የእግዚአብሔርን ቃል አቃልለው ምክረ ሰይጣንን ሰምተው ሞትን ወደ ዓለም
አገቡ።ድንግል ማርያም ግን በመልአከ ብሥራት በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ቃለ
እግዚአብሔርን ሰምታ ሕይወትን ለዓለም ሰጠች።(ሮሜ 5፥12-17)።ታዲያ እመቤታችን
እንዴት ዐረፈች?ይህንን ነገር ፈጽመን መናገር አይቻለንምና ዝም እንበል።
ሰንበተ ክርሰቲያን ድንግል ማርያም በሰንበተ ክርስቲያን እሑድ ዐረፈች።ዕለተ እሑድ
የድንግል ማርያም ምሳሌ ነው።በዕለተ እሑድ የፍጥረታት መሠረት የሆኑ አራቱ ባሕርያተ
ሥጋ(አሥራወ ፍጥረታት) ተገኝተዋል።ከድንግል ማርያምም የፍጥረታት ሁሉ አስገኚ ጌታ
ተገኝቷል።ዕለተ እሑድ የፍጥረታት መጀመሪያ ነው ድንግል ማርያም ግን ለጠፋው ፍጥረት
ሁሉ "የደኅንነት መጀመሪያ" ናት።በዕለተ እሑድ ገነት ተፈጠረልን "ስለ ሔዋን የተዘጋብን
የገነት ደጅ" "በምትናገር ገነት" በድንግል ማርያም "ዳግመኛ ተከፈተልን"
በዕለተ እሑድ መንግሥተ ሰማያት ተፈጠርልን በድንግል ማርያም ግን ዕለት ተዕለት
"መንግሥትህ ትምጣ" "መንግሥት የአንተ ናትና" እያልን የምንማጸነው መንግሥቱን
የሚያወርሰን አምላካችን አማኑኤል ተገኘልን።በዕለተ እሑድ እግዚአብሔር አምላክ ውኃን
ፈጠረ በፈጠረው ውኃም ላይ መንፈሱን አሰፈረ።መንፈስ ቅዱስ የጠበቃት ኃይለ ልዑል
የጋረዳት ድንግል ማርያም ግን "ማንም የተጠማ" ከእርሱ የሚጠጣ ጠጥተውት ዳግመኛ
የማያስጠማ ማየ ሕይወት ክርስቶስን ወለደችልን።በዕለተ እሑድ መላእክት ተፈጠሩ
በአማናዊት እሑድ በድንግል ማርያም ግን"ኪሩቤል በፍርሃት የሚሰግዱለት ሱራፌልም
የሚያመሰግኑት" "የመላእክት ደስታቸው"መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገኘ።በዕለተ
እሑድ "እግዚአብሔር ብርሃን ይሁን አለ ብርሃንም ሆነ።"(ዘፍ 1፥3)በድንግል ማርያም ግን
"በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ" ለምንኖር ለእኛ "ታላቅ ብርሃን ወጣልን።"በዕለተ እሑድ
መንግሥተ ሰማያት ለጻድቃን ትሰጣለች ጌታችን ከድንግል ማርያም የነሣውን ሥጋ ግን
ወርሰውት ለዘላለም ይኖራሉ።እመቤታችን ሆይ በማንና በምን እንመስልሻለን?ሰንበት
ድንግል ማርያም ሆይ ሰንበት ከሚባል የሰንበታት ጌታ ከሆነ ልጅሽ ጸጋውን ክብሩን
እንዳይነሣን ለምኚልን።
እመቤታችን ካረፈች በኋላ ለምቀኝነት የማያርፉ አይሁድ በፊት ልጇ ከሞተ በኋላ ተነሥቷል
ዐርጓል እያሉ አወኩን።አሁን ደግሞ እሷን ተነሣች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን?
ይህ ከመሆኑ አስቀድሞ ሥጋዋን እናቃለጥለው ተባባሉ።ምቀኝነት ትርፉ ይህ
ነው።መታወክ።"ዓለም እንደሚሰጠው ሰላም ያይደለ እውነተኛ ሰላም የሚሰጠን የሰላም
አለቃ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ" ግን ዕረፍተ ኅሊናን እናገኝ ዘንድ "ጠላቶቻችሁን
ውደዱ" ብሎ አስተማረን።ማኅደረ ሰይጣን የሆነ ታዖፋንያ የሚባል ከእነርሱ አንዱ ክቡር
ሥጋዋን አቃጥላለሁ ብሎ የአልጋዋን አጎበር ቢይዝ መልአከ እግዚአብሔር እጆቹን በሰይፍ
ቆርጧቸዋል።አላወቃትማ "ቢያውቃትስ ኖሮ የክብርን እናት ሥጋ ለማቃጠል ባልደፈረ
ነበር።" በመስቀል ላይ"አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያዉቁምና ይቅር በላቸው"ብሎ የለመነ
የፍቅር እናቱ የምትሆን ድንግል ማርያም ግን በከበረ ምልጃዋ እጆቹን አሰጠችው።እሱ
ቅዱስ ሥጋዋን ለማቃጠል እጆቹን ዘረጋ እመቤታችን ግን በሥጋዉም ሆነ በነፍሱ ታድነው
ዘንድ የምህረት እጆቿን ዘረጋችለት።ወንጌልን ያስተማርሽን ንጽሕት ፊደላችን ሆይ
እናመሰግንሻለን።የድንግል ማርያም ትንሣኤ ያውካልን?አዎን፤ በእኛ በክርስቲያኖች ዘንድ
"ከኪሩቤልና ከሱራፌል የሚበልጥ የመወደድ ግርማ" ያላት ድንግል ማርያም
በአጋጋንት፣በአይሁድና በመናፍቃን ዘንድ ግን "ከቅዱስ ሚካኤልና ከቅዱስ ገብርኤል
የሚበልጥ የማስፈራት" ግርማ አላት።
ከከበረ ዮሐንስ ጋር ወደ ዕፀ ሕይወት ተነጠቀች።"ዓለም አልተገባቸውምና።"(ዕብ
11፥38)ጌታን ከሁሉ አብልጦ ለወደደ ዮሐንስ ከሁሉ አብልጦ የሚወዳት ድንግል
ማርያምን በዕለተ ዓርብ ሰጠው።ከወንድሞቹ ሐዋርያት ተለይቶ ከእመቤታችን ጋር ከእግረ
መስቀሉ ሥር የተገኘ ዮሐንስ አሁን ደግሞ ከእነርሱ ተለይቶ ከእመቤታችን ጋር ከዕፀ
ሕይወት ሥር ተገኘ።ቅዱስ ዮሐንስ ከሕይወት ከክርስቶስ ደረት እየተጠጋ ጌታውን ያነጋግር
እንደነበረም ቅዱስ ወንጌል ነግሮናል።የቅዱስ ዮሐንስ እናት ማርያም ጌታ ሆይ በዙፋንህ
በተቀመጥህ ጊዜ አንዱ ልጄን በቀኝህ አንዱን በግራ አስቀምጥልኝ ብላ ለምናው
ነበር።በዙፋኑ "በአባቱ ቀኝ"የተቀመጠውም ቅዱስ "በቀኙ በምትቆመው" በአማናዊቱ ዙፋን
በድንግል ማርያም አጠገብ ከዕፀ ሕይወት ሥር አኖረው።ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን
በዕለተ ዓርብ ከጌታችን ከተቀበለ በኋላ "ወደ ቤቱ ወሰዳት"(ዮሐ19፥27) እሷ ደግሞ አሁን
በዕለተ እሑድ "ወደ ቤቷ ወሰደችው"። የዓርብ መከራ ተካፋይ ቅዱስ ዮሐንስ የእሑድ ደስታ
ተካፋይም ነበር።ዕፀ ሕይወት አዳምን ከእርጅናው(ከኃጢአቱ) ልታድሰው አልቻለችም።ዕፀ
ሕይወት ድንግል ማርያም ግን "በአዲስ ተፈጥሮ" ዳግመኛ የሚፈጥረዉን ሕይወቱ
ክርስቶስን ወለደችለት።ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ይላል "ከዕፀ ሕይወት እንበላ ዘንድ አደለን
ይኸውም... የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙ ነው።"
ሞቷ እንደ ልጇ ሞት ነው።እሱ መላ ዘመኑን አዝኖ "ነፍሱ እስከሞት ድረስ ያዘነች" ሆና
ሞተ።(ማቴ 26፥38)
እሷም ከእሱ ጋር ተንከራታ "በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል"እንዳላት ቅዱስ ስምዖን አረጋዊ(ሉቃ
2፥34-35) እንደ ሰይፍ ነፍስን ከሥጋ ሊለይ የሚችል ጽኑ ኀዘንና መከራ ገጥሟት
ሞተች።የጌታችን ሞት ቅዱሳን መላእክትንና ሰዎችን አንድ አደረገ።የእመቤታችንም ሞት
እንዲሁ ነው።
ትንሣኤዋም እንደ ልጇ ትንሣኤ ነው። እንደ ልጇ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር
ቆይታ ተነሥታለችና።"ከመ ትንሣኤ ወልዳ" "እንደ ልጇ ትንሣኤ" ያሰኘውም ይህ
ነው።"ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር የተባበረች ድንግል ማርያም ትንሣኤውን