Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
ከላይኛው የቀጠለ ......
ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እንደመሠከረው የደጋግ ሰዎች ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የከበረ ነው ፡፡ ክብራቸውንም በቃላት ተናግረን በብዕር (ብርዕ) ጽፈን ልንፈጽመው እንደማንችል መረዳት ይኖርብናል ፡፡ ዓለም የራሱ የሆነውን ሰዎች ዕረፍት ቀን በደመቀ ሥነ ሥርዓት ያከብራል ፡፡ እግዚአብሔርም በሕይወታቸው ሁሉ እርሱን እያመለኩ ለእርሱ እየተገዙ ፈቃዱን እየፈጸሙና የዚህ ዓለም ተጋድሏቸውም በሞተ ሥጋ የተቋጨ ወዳጆቹን ዕረፍት በማያልፍና ቃላት በማይገልጡት ክብር ያከብራል፡፡
የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው
ለምን ተባለ?
☞ የሥጋ ሞቱ ሕያው መሆኑ የሚገለጥበት በመሆኑ
በክርስትና ሃይማኖት መሠረታዊ አስተምህሮ መሠረት ሞት የሰው ልጅ የጉዞ ፍጻሜ አይደለም ፡፡ ከሞት በኋላ ዘላለማዊ ሕይወት ከመቃብር በኋላም ትንሣኤ አለና ፡፡ ሰው ከሞት በኋላ ለሚገጥመው ሕይወትና ለሚያገኘው ጸጋ ለሚወርሰው የማያልፍ ርስት የሚፈተነው በዚህ ዓለም በሚኖረው ቆይታ ነው ፡፡ ጌታችን በወንጌል "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።" ሲል ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ "ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ ልንገባ ያስፈልገናል።" ማለቱ ይህ ዓለም ለደጋግ ሰዎች የመከራና የኋዘን ምክንያት መሆኑን ያሳየናል፡፡ (ዮሐ 16፥33፣ የሐዋ 14 ፥22)
ቅዱስ ጴጥሮስም የእምነታችንን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችንን መዳን (መንግሥተ ሰማያትን መውረስ) የምናገኘው በዚህ ዓለም የሚገጥመንን ፈተና፣ መከራና ኃዘን በድል ከተወጣን በኋላ መሆኑን ደጋግሞ መስክሯል። (1ጴጥ 4፥14 2ጴጥ 1፥5-9)
ይህ ዓለም የተጋድሎ ዓለም መሆኑን የተረዳ ሰው ደጋግ ሰዎች ነፍሳቸው ከሥጋቸው የሚለይበት በሥጋ ሞት ከዚህ ዓለም የሚወሰዱበት ቀን ሕያዋን መሆናችው የሚታወቅበት ቀን መሆኑን ለመረዳት አይቸገርም ፡፡ በዚህ ዓለም ስንኖር የነፍስ ከእግዚአብሔር ለመለየት መንሥኤ በሆነ ኃጢአት የመያዛችን ዕድል ሰፊ ነው ፡፡ ስለሆነም በአምልኮተ እግዚአብሔር ጸንቶ በምግባር ቀንቶ ለኖረ ሰው ዕለተ ሞቱ ወደ ኃጢአት ከሚያንደረድሩ ክፉ ምኞቶች ጋር የሚያደርገው ትግል የሚያበቃበትና ጽድቅ በተባለች የእግዚአብሔር መንግሥት በሕይወት ለዘላለም እንደሚኖር የሚታወቅበት ቀን ነው፡፡ ጌታችን በወንጌል "ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ነው።" ብሎ መናገሩ ይህን የሚያጸናልን ነው፡፡ (ዮሐ 11፥25) "ቢሞት እንኳን" ሲል በሥጋ ሞት ቢወሰድ እንኳ ማለቱ ግልጽ ነውና፡፡
ጌታችን በዚህ ስፍራ ብቻ ሳይሆን ደጋግሞ እርሱን አምነውና ትእዛዛቱን በመፈጸም አስደስተውት በበጎ ምግባርም ተሸልመው በሥጋ ሞት ያለፉ እንደነ አብርሃም ያሉ ደጋጎች ዳግም ሞትን እንደማያዩና ሕያዋን እንደሆኑ መስክሯል ፡፡ "እውነት እውነት እላችኋለሁ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም" እንዲል። (ዮሐ 8፥51)
☞ የዚህ ዓለም ተጋድሎው የሚያበቃበት በመሆኑ
ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚመሠክሩት እውነተኛ ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ከሰይጣን ክፉ ከሆነ የዓለም ምኞት ከሥጋ ፈቃድና እና ከክፉ ሀሳቦች ጋር የማያቋርጥ ተጋድሎ አለባቸው፡፡ ሐዋርያው "መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና ነገር ግን በዚህ ዓለም ካሉ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።" ብሎ እንደተናገረ፡፡ (ኤፌ 6፥12-16) ተጋድሎ አንዱ እውነተኛ የክርስትና ሕይወት መገለጫ ነው ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለደቀ መዝሙሩ ለጢሞቴዎስ "መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል።" በማለት የመከረውም ምክር ይህንኑ ያስገነዝበናል ፡፡ (1ጢሞ 6፥12) ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ከርኩሳን መናፍስትና ከሠለጠኑባቸው ሰዎች ጋር ስለ ክርስቶስ የሚያደርጉት ተጋድሎ የክብር አክሊል የሚያገኙበት ጉዞ ነው ፡፡ በተጋድሎ ጸንቶ መኖር እንደሚገባ ሐዋርያው ሲያስተምር "ወዳጆች ሆይ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኳችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።" ይላል (ይሁዳ 1፥3) የክርስትና ሃይማኖት የተጋድሎ ሕይወት የሞላበት መንገድ ነው የሚባለውም ለዚሁ ነው ፡፡ ክርስቲያናዊ ሕይወትን ያለ ተጋድሎ ማሰብ ጉዞውን ሳይጀምሩ ከመንገድ መቅረትን በመሐል መደነቃቀፍንና ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን ወደ ማማረር ያደርሳል። (ያዕ 5፥9) ሐዋርያት በመልእክቶቻቸው "ይሁን እንጂ መጥቼ ባያችሁ ወይም ብርቅ በአንድ ልብ ስለወንጌል ሃይማኖት አብራችሁ እየተጋደላችሁ በአ ንድ መንፈስ እንድትቆሙ ስለ ኑሯችሁ እሰማ ዘንድ ለክርስቶስ ወንጌል እንደሚገባ ኑሩ ...በእኔ ያያችሁት አሁንም በእኔ እንዳለ የምትሰሙት ያው መጋደል ደርሶባችኋልና። " በማለት ያስተማሩን ትምህርት የክርስትናን መንገድ የሚከተል ሰው መከራ መንገዱ፤ መስቀል ምርኩዙ፤ እግዚአብሔር መሪው፤ ወንጌል መመሪያው፤ መንግሥተ ሰማያት ዓላማው መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡ (ፊልጵ 1፥27-30)
ቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችን የዕረፍታቸው ቀን በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው "ከተወለዱበትም ቀን የሚሞቱበት ቀን ይሻላል" የተባለውም ከሥጋ ሞታቸውም በኋላ ዳግመኛ ወደማያለቅሱበት፣ ወደማይራቡበት፣ ወደማይጠሙበት፣ ዕንባቸውም ሁሉ ወደሚታበስበት ዓለም ስለሚጓዙ ነው፡፡ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራእዩ የተመለከታቸው አንድስ እንኳ ሊቆጥራቸው አይችልም የተባለላቸው ነጫጭ ልብስ ለብሰው የተገለጡት እነዚያ ቅዱሳን እነማን እንደሆኑ "እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው ልብሳቸውንም አጥበው (ንስሐ ገብተው) በበጉ ደም አነጹ (በሥጋ ወደሙ ታተሙ) ስለዚህ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት አሉ ሌሊትና ቀንም በመቅደሱ ያመልኩታል ከእንግዲህ ወዲህ አይራቡም አይጠሙም ፀሐይም ትኩሳትም ሁሉ ከቶ አይወርድባቸውም በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናልና ወደ ሕይወትም ውኃ ምንጭ ይመራቸዋልና እግዚአብሔር ዕንባዎችን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል።" ተብሎ ተነግሮታል። (ራዕይ 7፥14-17)
☞ የድል አክሊል የሚቀዳጁበት ቀን በመሆኑ
ጌታችን "እስከሞት ድረስ የታመንክ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለው ።" ብሎ የተናገረው ቃል የሕይወት አክሊል የተባለች መንግሥተ ሰማያት የምትሰጠው ከሥጋ ሞት በኋላ መሆኑን ይመሠክርልናል፡፡ (ራእይ 2፥9)
"የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው " መባሉም የጻድቅ ሰው ዕለተ ሞት የክብር አክሊል የመቀዳጀቱ ማብሠሪያ ቀን በመሆኑ ነው ፡፡ ጌታችንም "እስከ መጨረሻው (እስከ ዕለተ ሞቱ) የሚጸና እርሱ ይድናል (መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳል)።" ማለቱ ይህን ያጠነክርልናል፡፡ (ማቴ 24፥12)
ቅዱሳን የዚህን ዓለም ተጋድሎ ፈጽመው ፈተናውን አሸንፈው መከራውን አልፈው በሞተ ሥጋ ሲወሰዱ በፍጡር ሚዛን የማይለካ በፍጡር አንደበት ተዘርዝሮ የማያልቅ ከፍጡር ሕሊና በላይ የሆነ ክብርን ይቀዳጃሉ ፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን "ጻድቃን ድል ባደረጉ ጊዜ ብዙ ክብር አለ።" ብሎ እንደተናገረ፡፡ (ምሳ 28፥12) ጠቢቡ ቅዱሳን ከሥጋ ሞታቸው በኋላ የሚጠብቃቸውን የክብር መጠን በቁጥር ሳይገድብ "ብዙ ክብር" ማለቱን ልብ ማለት ይገባል፡፡
ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እንደመሠከረው የደጋግ ሰዎች ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የከበረ ነው ፡፡ ክብራቸውንም በቃላት ተናግረን በብዕር (ብርዕ) ጽፈን ልንፈጽመው እንደማንችል መረዳት ይኖርብናል ፡፡ ዓለም የራሱ የሆነውን ሰዎች ዕረፍት ቀን በደመቀ ሥነ ሥርዓት ያከብራል ፡፡ እግዚአብሔርም በሕይወታቸው ሁሉ እርሱን እያመለኩ ለእርሱ እየተገዙ ፈቃዱን እየፈጸሙና የዚህ ዓለም ተጋድሏቸውም በሞተ ሥጋ የተቋጨ ወዳጆቹን ዕረፍት በማያልፍና ቃላት በማይገልጡት ክብር ያከብራል፡፡
የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው
ለምን ተባለ?
☞ የሥጋ ሞቱ ሕያው መሆኑ የሚገለጥበት በመሆኑ
በክርስትና ሃይማኖት መሠረታዊ አስተምህሮ መሠረት ሞት የሰው ልጅ የጉዞ ፍጻሜ አይደለም ፡፡ ከሞት በኋላ ዘላለማዊ ሕይወት ከመቃብር በኋላም ትንሣኤ አለና ፡፡ ሰው ከሞት በኋላ ለሚገጥመው ሕይወትና ለሚያገኘው ጸጋ ለሚወርሰው የማያልፍ ርስት የሚፈተነው በዚህ ዓለም በሚኖረው ቆይታ ነው ፡፡ ጌታችን በወንጌል "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።" ሲል ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ "ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ ልንገባ ያስፈልገናል።" ማለቱ ይህ ዓለም ለደጋግ ሰዎች የመከራና የኋዘን ምክንያት መሆኑን ያሳየናል፡፡ (ዮሐ 16፥33፣ የሐዋ 14 ፥22)
ቅዱስ ጴጥሮስም የእምነታችንን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችንን መዳን (መንግሥተ ሰማያትን መውረስ) የምናገኘው በዚህ ዓለም የሚገጥመንን ፈተና፣ መከራና ኃዘን በድል ከተወጣን በኋላ መሆኑን ደጋግሞ መስክሯል። (1ጴጥ 4፥14 2ጴጥ 1፥5-9)
ይህ ዓለም የተጋድሎ ዓለም መሆኑን የተረዳ ሰው ደጋግ ሰዎች ነፍሳቸው ከሥጋቸው የሚለይበት በሥጋ ሞት ከዚህ ዓለም የሚወሰዱበት ቀን ሕያዋን መሆናችው የሚታወቅበት ቀን መሆኑን ለመረዳት አይቸገርም ፡፡ በዚህ ዓለም ስንኖር የነፍስ ከእግዚአብሔር ለመለየት መንሥኤ በሆነ ኃጢአት የመያዛችን ዕድል ሰፊ ነው ፡፡ ስለሆነም በአምልኮተ እግዚአብሔር ጸንቶ በምግባር ቀንቶ ለኖረ ሰው ዕለተ ሞቱ ወደ ኃጢአት ከሚያንደረድሩ ክፉ ምኞቶች ጋር የሚያደርገው ትግል የሚያበቃበትና ጽድቅ በተባለች የእግዚአብሔር መንግሥት በሕይወት ለዘላለም እንደሚኖር የሚታወቅበት ቀን ነው፡፡ ጌታችን በወንጌል "ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ነው።" ብሎ መናገሩ ይህን የሚያጸናልን ነው፡፡ (ዮሐ 11፥25) "ቢሞት እንኳን" ሲል በሥጋ ሞት ቢወሰድ እንኳ ማለቱ ግልጽ ነውና፡፡
ጌታችን በዚህ ስፍራ ብቻ ሳይሆን ደጋግሞ እርሱን አምነውና ትእዛዛቱን በመፈጸም አስደስተውት በበጎ ምግባርም ተሸልመው በሥጋ ሞት ያለፉ እንደነ አብርሃም ያሉ ደጋጎች ዳግም ሞትን እንደማያዩና ሕያዋን እንደሆኑ መስክሯል ፡፡ "እውነት እውነት እላችኋለሁ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም" እንዲል። (ዮሐ 8፥51)
☞ የዚህ ዓለም ተጋድሎው የሚያበቃበት በመሆኑ
ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚመሠክሩት እውነተኛ ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ከሰይጣን ክፉ ከሆነ የዓለም ምኞት ከሥጋ ፈቃድና እና ከክፉ ሀሳቦች ጋር የማያቋርጥ ተጋድሎ አለባቸው፡፡ ሐዋርያው "መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና ነገር ግን በዚህ ዓለም ካሉ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።" ብሎ እንደተናገረ፡፡ (ኤፌ 6፥12-16) ተጋድሎ አንዱ እውነተኛ የክርስትና ሕይወት መገለጫ ነው ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለደቀ መዝሙሩ ለጢሞቴዎስ "መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል።" በማለት የመከረውም ምክር ይህንኑ ያስገነዝበናል ፡፡ (1ጢሞ 6፥12) ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ከርኩሳን መናፍስትና ከሠለጠኑባቸው ሰዎች ጋር ስለ ክርስቶስ የሚያደርጉት ተጋድሎ የክብር አክሊል የሚያገኙበት ጉዞ ነው ፡፡ በተጋድሎ ጸንቶ መኖር እንደሚገባ ሐዋርያው ሲያስተምር "ወዳጆች ሆይ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኳችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።" ይላል (ይሁዳ 1፥3) የክርስትና ሃይማኖት የተጋድሎ ሕይወት የሞላበት መንገድ ነው የሚባለውም ለዚሁ ነው ፡፡ ክርስቲያናዊ ሕይወትን ያለ ተጋድሎ ማሰብ ጉዞውን ሳይጀምሩ ከመንገድ መቅረትን በመሐል መደነቃቀፍንና ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን ወደ ማማረር ያደርሳል። (ያዕ 5፥9) ሐዋርያት በመልእክቶቻቸው "ይሁን እንጂ መጥቼ ባያችሁ ወይም ብርቅ በአንድ ልብ ስለወንጌል ሃይማኖት አብራችሁ እየተጋደላችሁ በአ ንድ መንፈስ እንድትቆሙ ስለ ኑሯችሁ እሰማ ዘንድ ለክርስቶስ ወንጌል እንደሚገባ ኑሩ ...በእኔ ያያችሁት አሁንም በእኔ እንዳለ የምትሰሙት ያው መጋደል ደርሶባችኋልና። " በማለት ያስተማሩን ትምህርት የክርስትናን መንገድ የሚከተል ሰው መከራ መንገዱ፤ መስቀል ምርኩዙ፤ እግዚአብሔር መሪው፤ ወንጌል መመሪያው፤ መንግሥተ ሰማያት ዓላማው መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡ (ፊልጵ 1፥27-30)
ቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችን የዕረፍታቸው ቀን በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው "ከተወለዱበትም ቀን የሚሞቱበት ቀን ይሻላል" የተባለውም ከሥጋ ሞታቸውም በኋላ ዳግመኛ ወደማያለቅሱበት፣ ወደማይራቡበት፣ ወደማይጠሙበት፣ ዕንባቸውም ሁሉ ወደሚታበስበት ዓለም ስለሚጓዙ ነው፡፡ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራእዩ የተመለከታቸው አንድስ እንኳ ሊቆጥራቸው አይችልም የተባለላቸው ነጫጭ ልብስ ለብሰው የተገለጡት እነዚያ ቅዱሳን እነማን እንደሆኑ "እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው ልብሳቸውንም አጥበው (ንስሐ ገብተው) በበጉ ደም አነጹ (በሥጋ ወደሙ ታተሙ) ስለዚህ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት አሉ ሌሊትና ቀንም በመቅደሱ ያመልኩታል ከእንግዲህ ወዲህ አይራቡም አይጠሙም ፀሐይም ትኩሳትም ሁሉ ከቶ አይወርድባቸውም በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናልና ወደ ሕይወትም ውኃ ምንጭ ይመራቸዋልና እግዚአብሔር ዕንባዎችን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል።" ተብሎ ተነግሮታል። (ራዕይ 7፥14-17)
☞ የድል አክሊል የሚቀዳጁበት ቀን በመሆኑ
ጌታችን "እስከሞት ድረስ የታመንክ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለው ።" ብሎ የተናገረው ቃል የሕይወት አክሊል የተባለች መንግሥተ ሰማያት የምትሰጠው ከሥጋ ሞት በኋላ መሆኑን ይመሠክርልናል፡፡ (ራእይ 2፥9)
"የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው " መባሉም የጻድቅ ሰው ዕለተ ሞት የክብር አክሊል የመቀዳጀቱ ማብሠሪያ ቀን በመሆኑ ነው ፡፡ ጌታችንም "እስከ መጨረሻው (እስከ ዕለተ ሞቱ) የሚጸና እርሱ ይድናል (መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳል)።" ማለቱ ይህን ያጠነክርልናል፡፡ (ማቴ 24፥12)
ቅዱሳን የዚህን ዓለም ተጋድሎ ፈጽመው ፈተናውን አሸንፈው መከራውን አልፈው በሞተ ሥጋ ሲወሰዱ በፍጡር ሚዛን የማይለካ በፍጡር አንደበት ተዘርዝሮ የማያልቅ ከፍጡር ሕሊና በላይ የሆነ ክብርን ይቀዳጃሉ ፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን "ጻድቃን ድል ባደረጉ ጊዜ ብዙ ክብር አለ።" ብሎ እንደተናገረ፡፡ (ምሳ 28፥12) ጠቢቡ ቅዱሳን ከሥጋ ሞታቸው በኋላ የሚጠብቃቸውን የክብር መጠን በቁጥር ሳይገድብ "ብዙ ክብር" ማለቱን ልብ ማለት ይገባል፡፡
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
"ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር"
"የጻድቅ ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።"
መዝ 115:6
- የዛሬው በዓል ደግሞ ልዩ ነው።የጻድቁ አባት የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ፀሐይ የአቡነ ተክለሃይማኖት በዓለ ዕረፍት ነውና!!!
- ለጻድቁ ክብርም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ክብርት ቅድስት ድንግል ማርያምን፣ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልን፣15ቱ ነቢያትን፣12ቱ ሐዋርያትን ብዙዎች የሰማይ ሠራዊትን ይዞ አቡነ ተክለሃይማኖት ወደሚገኙበት የደብረ አስቦ ዋሻ ወርዶ ብዙ ቃልኪዳንን ሰጥቷቸዋል።
- የጻድቁስ ሐሳብ በሰማዕትነት አደባባይ ለክርስቶስ ፍቅር ደማቸውን አፍስሰው፣ሥጋቸው ተቆራርጦ፣አጥንታቸው ተከስክሶ ለማረፍ ነበር።በጣም የሚገርመው ይህንን ሐሳባቸውን ለጌታ የነገሩት የቀራቸው ምንም ዓይነት ተጋድሎ ሳይኖር ነበር።ነገር ግን ጌታ ጻድቁ ለእርሱ ያላቸውን ጽኑ ፍቅር ያውቃልና ምንም የቀራቸው እንደሌለና በከፍተኛ የሆድ ሕመም እንደሚያርፉ፤ይህንንም እንደ ስቅለቱና እንደ ሰማዕታት ደም እንደሚቆጥርላቸው ነግሯቸው በዚያ በክብር ዐርፈዋል።
- ዋሻዪቱን ሊነገርና ሊሰማ የማይችል ብርሃንና በዚህ ዓለም የሌለ የልዩ ልዩ የሽቱና የዕጣን መዓዛ ሞልቶባት፤ምድሪቱም እየተንቀጠቀጠች፤የሰማይ ሠራዊት ቅዱስ ዳዊት"ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ምስጋና መኖሪያ ስፍራ እገባለሁና፤ በዓል የሚያደርጉ ሰዎች የደስታና ምስጋና ቃል አሰሙ።"ሲል እንደተናገረ (መዝ 41፥4) በክቡር ዳዊት ምስጋና“እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።”በማለት እያመሰኑ የጻድቁ ነፍስ ከሥጋቸው ተለየች።(መዝ 117፥24)
- ጌታችን የጻድቁን ነፍስ በክብር ተቀብሎ አቅፎ ሳማት።"የጸራሽ ንጽሕት ነፍስ ሆይ" ሲልም አመሰገናት።አባታችንን በሕይወተ ሥጋ ሳለ እንደነገራቸው በ15ቱ የገነትና በ5ቱ የመንግሥተ ሰማያት አህጉር ላይ ሾመው።አስቀድሞ በቅዱስ ወንጌል
“በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤” ያለ አምላክ ለጻድቁ የመንፈስ ልጆች ይሆኑ ዘንድ በእነዚህ ሁሉ ላይ ሾመው።(ዮሐ 14፥2)
- በጻድቁ ስም ለተራበ ያበላ፤ለተጠማ ያጠጣ፤የየታረዘውን ያለበሰ፤ገድላቸውን የጻፈ ያጻፈ የሰማ፤ለቤተ ክርስቲያናቸው ዕጣን፣ዘቢብ፣ወይን፣ ሜሮን፣ንጹሕ ስንዴ ልዩ ልዩ መባዕ ያገባ፤ለበዓላቸው ለሚዘጋጀው ዝክር ውኃ በመቅዳት፣እንጨት በመፍለጥ፣ቅጠል በመቁረጥ የተራዳ፤በዓላቸውን ደስ ብሎት ያከበረ፤ከእነዚህ ሁሉ ባይቻለው በበዓላቸው ቀን የታመመ የጠየቀ ወይም ያዘነውን ያጽናና፤ በበዓላቸው ቀን ከ ቅዱስ ሥጋው ከክቡር ደሙ የተቀበለውን፤ይህንንም ባይችል ለበዓላቸው ከተዘጋጀው ዝክር የቀምሰ፤ከእነዚህ ሁሉ የተቻለውን አንዱን ቢፈጽም እንደሚምርላቸው ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል።
- ለቅዱሳኑ የሚሰጠውን ቃልኪዳን በተመለከተ ራሱ ጌታችን እንዲህ ሲል ተናግሯል"እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ዋጋው አይጠፋበትም።"(ማቴ 10:40-42)
- የእግዚአብሔር የምሕረቱ ብዛት እንዴት ብዙና ጥልቅ ነው።ጻድቁን የሰጠን አምላካችን እግዚአብሔር ስሙ ይክበር ይመስገን!!!
ጻድቁም በጸሎታቸው በበረከታቸው ይጎብኙን፤በፍጹም ሰማያዊ መስቀላቸውም ይባርኩን፤በፍጹም ሰማያዊ ሥልጣነ ክህነታቸውም ከኃጢአት ማሠሪያ የተፈታን ንጹሐን ለመንግሥተ ሰማያትም የተዘጋጀን ድልዋን ያድርጉን!!! አሜን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
ነሐሴ ተክለሃይማኖት/2016 ዓ.ም
"የጻድቅ ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።"
መዝ 115:6
- የዛሬው በዓል ደግሞ ልዩ ነው።የጻድቁ አባት የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ፀሐይ የአቡነ ተክለሃይማኖት በዓለ ዕረፍት ነውና!!!
- ለጻድቁ ክብርም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ክብርት ቅድስት ድንግል ማርያምን፣ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልን፣15ቱ ነቢያትን፣12ቱ ሐዋርያትን ብዙዎች የሰማይ ሠራዊትን ይዞ አቡነ ተክለሃይማኖት ወደሚገኙበት የደብረ አስቦ ዋሻ ወርዶ ብዙ ቃልኪዳንን ሰጥቷቸዋል።
- የጻድቁስ ሐሳብ በሰማዕትነት አደባባይ ለክርስቶስ ፍቅር ደማቸውን አፍስሰው፣ሥጋቸው ተቆራርጦ፣አጥንታቸው ተከስክሶ ለማረፍ ነበር።በጣም የሚገርመው ይህንን ሐሳባቸውን ለጌታ የነገሩት የቀራቸው ምንም ዓይነት ተጋድሎ ሳይኖር ነበር።ነገር ግን ጌታ ጻድቁ ለእርሱ ያላቸውን ጽኑ ፍቅር ያውቃልና ምንም የቀራቸው እንደሌለና በከፍተኛ የሆድ ሕመም እንደሚያርፉ፤ይህንንም እንደ ስቅለቱና እንደ ሰማዕታት ደም እንደሚቆጥርላቸው ነግሯቸው በዚያ በክብር ዐርፈዋል።
- ዋሻዪቱን ሊነገርና ሊሰማ የማይችል ብርሃንና በዚህ ዓለም የሌለ የልዩ ልዩ የሽቱና የዕጣን መዓዛ ሞልቶባት፤ምድሪቱም እየተንቀጠቀጠች፤የሰማይ ሠራዊት ቅዱስ ዳዊት"ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ምስጋና መኖሪያ ስፍራ እገባለሁና፤ በዓል የሚያደርጉ ሰዎች የደስታና ምስጋና ቃል አሰሙ።"ሲል እንደተናገረ (መዝ 41፥4) በክቡር ዳዊት ምስጋና“እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።”በማለት እያመሰኑ የጻድቁ ነፍስ ከሥጋቸው ተለየች።(መዝ 117፥24)
- ጌታችን የጻድቁን ነፍስ በክብር ተቀብሎ አቅፎ ሳማት።"የጸራሽ ንጽሕት ነፍስ ሆይ" ሲልም አመሰገናት።አባታችንን በሕይወተ ሥጋ ሳለ እንደነገራቸው በ15ቱ የገነትና በ5ቱ የመንግሥተ ሰማያት አህጉር ላይ ሾመው።አስቀድሞ በቅዱስ ወንጌል
“በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤” ያለ አምላክ ለጻድቁ የመንፈስ ልጆች ይሆኑ ዘንድ በእነዚህ ሁሉ ላይ ሾመው።(ዮሐ 14፥2)
- በጻድቁ ስም ለተራበ ያበላ፤ለተጠማ ያጠጣ፤የየታረዘውን ያለበሰ፤ገድላቸውን የጻፈ ያጻፈ የሰማ፤ለቤተ ክርስቲያናቸው ዕጣን፣ዘቢብ፣ወይን፣ ሜሮን፣ንጹሕ ስንዴ ልዩ ልዩ መባዕ ያገባ፤ለበዓላቸው ለሚዘጋጀው ዝክር ውኃ በመቅዳት፣እንጨት በመፍለጥ፣ቅጠል በመቁረጥ የተራዳ፤በዓላቸውን ደስ ብሎት ያከበረ፤ከእነዚህ ሁሉ ባይቻለው በበዓላቸው ቀን የታመመ የጠየቀ ወይም ያዘነውን ያጽናና፤ በበዓላቸው ቀን ከ ቅዱስ ሥጋው ከክቡር ደሙ የተቀበለውን፤ይህንንም ባይችል ለበዓላቸው ከተዘጋጀው ዝክር የቀምሰ፤ከእነዚህ ሁሉ የተቻለውን አንዱን ቢፈጽም እንደሚምርላቸው ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል።
- ለቅዱሳኑ የሚሰጠውን ቃልኪዳን በተመለከተ ራሱ ጌታችን እንዲህ ሲል ተናግሯል"እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ዋጋው አይጠፋበትም።"(ማቴ 10:40-42)
- የእግዚአብሔር የምሕረቱ ብዛት እንዴት ብዙና ጥልቅ ነው።ጻድቁን የሰጠን አምላካችን እግዚአብሔር ስሙ ይክበር ይመስገን!!!
ጻድቁም በጸሎታቸው በበረከታቸው ይጎብኙን፤በፍጹም ሰማያዊ መስቀላቸውም ይባርኩን፤በፍጹም ሰማያዊ ሥልጣነ ክህነታቸውም ከኃጢአት ማሠሪያ የተፈታን ንጹሐን ለመንግሥተ ሰማያትም የተዘጋጀን ድልዋን ያድርጉን!!! አሜን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
ነሐሴ ተክለሃይማኖት/2016 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
"መንገድ"
በደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የም/ደ/ማ/ወ/መ/ማ (ሰንበት ትምህርት ቤት) "መንገድ" የተሰኘ ልዩ መንፈሳዊ ቴአትር አዘጋጅቶላችኋል።እርስዎም በዕለተ እሑድ መስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት በመገኘት ይህን መንፈሳዊ ቴአትር እንዲመለከቱ በክብር ተጋብዘዋል።
ቦታ:- በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ
የመግቢያ ዋጋ:- 100 ብር
የመግቢያ ትኬቱን በ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ነዋየ ቅዱሳን መሸጫ ያገኙታል።
"መንገድ"
በደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የም/ደ/ማ/ወ/መ/ማ (ሰንበት ትምህርት ቤት) "መንገድ" የተሰኘ ልዩ መንፈሳዊ ቴአትር አዘጋጅቶላችኋል።እርስዎም በዕለተ እሑድ መስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት በመገኘት ይህን መንፈሳዊ ቴአትር እንዲመለከቱ በክብር ተጋብዘዋል።
ቦታ:- በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ
የመግቢያ ዋጋ:- 100 ብር
የመግቢያ ትኬቱን በ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ነዋየ ቅዱሳን መሸጫ ያገኙታል።
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
#ምትረተ ርእሱ ለቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ#
#“እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል”(ማቴ 3፥11)ብሎ ስለ ክርስቶስ ትንቢት የተናገረ ታላቅ ነቢይ፤
#“በነቢዩ በኢሳይያስ፦ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ የተባለለት።”(ማቴ3፥3) ጸያሔ ፍኖት (የክርስቶስ መንገድ ጠራጊ)፤
#“ራሱም ዮሐንስ የግመል ጠጉር ልብስ ነበረው፥ በወገቡም ጠፍር ይታጠቅ ነበር፤ ምግቡም አንበጣና የበረሀ ማር ነበረ።”(ማቴ3፥4) የተባለለት ታላቅ መናኝ ባሕታዊ፤
#ለንስሐ የሚሆን ጥምቀትን ያጠመቀ ሰባኬ ጥምቀት፤(ሉቃ 3፥6)
#“አንድ ሰው ከእኔ በኋላ ይመጣል፥ ከእኔም በፊት ነበርና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል ብዬ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነው።”(ዮሐንስ 1፥30) ሲል ስለ ጌታ የመሰከረ ስምዐ ጽድቅ (የእውነት ምስክር)፤
#ጌታችን “እርሱ የሚነድና የሚያበራ መብራት ነበረ፥ እናንተም ጥቂት ዘመን በብርሃኑ ደስ ሊላችሁ ወደዳችሁ።”(ዮሐ 5፥35) ብሎ የመሰከረለት ድንቅ የጸጋ ብርሃን፤
#“እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም።” ማቴ(11፥11) ተብሎ በጌታ የተነገረለት ታላቅ የሃይማኖት ኮከብ፤
#አምላክን በሥጋ ያጠመቀ መጥምቀ መለኮት፤(ማቴ 3:15-16፤ማር 1:9፤ሉቃ 3:21)
#“እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም።”(ማቴዎስ 14፥4 )
ሲል ሄሮድስን በወንድሙ በፊልጶስ ሚስት በሄሮዳድያ ምክንያት ያስተማረና የገሠፀ ሐዋርያ፤
#ሄሮድስ ስለ ክብሩ ተጨንቆ በገዛ መሐላው ተታሎ አንገቱን ያስቆረጠው ሰማዕት፤“ልኮም የዮሐንስን ራስ በወህኒ አስቆረጠው።”(ማቴ14፥10)
እንዲል፤
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዛሬ ክብርት አንገቱ በግፍ የተቆረጠችበት ዕለት ነው።ሄሮድስ ለሄሮድያዳ ልጅ በወጭት የቅዱስ ዮሐንስን አንገት እንዲሰጧት አዘዘ።እግዚአብሔር ባወቀ በርኩስ እጇ የቅዱሱን አንገት እንዳትነካ ነው።
አባታችን ዛሬም እኛ ልጆችህን “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ።”ማቴ3፥1-2 እያልህ ወደ ንስሐ ምራን።ልባችን የደነደነ እኛን "እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ከሚመጣው ቍጣ እንድትሸሹ ማን አመለከታችሁ?እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ"(ማቴ 3፥7-8) እያልህ ዝለፈን!!!
የቅዱስ ዮሐንስ በረከቱ ይደርብን!!!
#መምህር_ኢዮብ_ክንፈ
ወርኃ መስከረም 2/2017 ዓ.ም
#“እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል”(ማቴ 3፥11)ብሎ ስለ ክርስቶስ ትንቢት የተናገረ ታላቅ ነቢይ፤
#“በነቢዩ በኢሳይያስ፦ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ የተባለለት።”(ማቴ3፥3) ጸያሔ ፍኖት (የክርስቶስ መንገድ ጠራጊ)፤
#“ራሱም ዮሐንስ የግመል ጠጉር ልብስ ነበረው፥ በወገቡም ጠፍር ይታጠቅ ነበር፤ ምግቡም አንበጣና የበረሀ ማር ነበረ።”(ማቴ3፥4) የተባለለት ታላቅ መናኝ ባሕታዊ፤
#ለንስሐ የሚሆን ጥምቀትን ያጠመቀ ሰባኬ ጥምቀት፤(ሉቃ 3፥6)
#“አንድ ሰው ከእኔ በኋላ ይመጣል፥ ከእኔም በፊት ነበርና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል ብዬ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነው።”(ዮሐንስ 1፥30) ሲል ስለ ጌታ የመሰከረ ስምዐ ጽድቅ (የእውነት ምስክር)፤
#ጌታችን “እርሱ የሚነድና የሚያበራ መብራት ነበረ፥ እናንተም ጥቂት ዘመን በብርሃኑ ደስ ሊላችሁ ወደዳችሁ።”(ዮሐ 5፥35) ብሎ የመሰከረለት ድንቅ የጸጋ ብርሃን፤
#“እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም።” ማቴ(11፥11) ተብሎ በጌታ የተነገረለት ታላቅ የሃይማኖት ኮከብ፤
#አምላክን በሥጋ ያጠመቀ መጥምቀ መለኮት፤(ማቴ 3:15-16፤ማር 1:9፤ሉቃ 3:21)
#“እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም።”(ማቴዎስ 14፥4 )
ሲል ሄሮድስን በወንድሙ በፊልጶስ ሚስት በሄሮዳድያ ምክንያት ያስተማረና የገሠፀ ሐዋርያ፤
#ሄሮድስ ስለ ክብሩ ተጨንቆ በገዛ መሐላው ተታሎ አንገቱን ያስቆረጠው ሰማዕት፤“ልኮም የዮሐንስን ራስ በወህኒ አስቆረጠው።”(ማቴ14፥10)
እንዲል፤
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዛሬ ክብርት አንገቱ በግፍ የተቆረጠችበት ዕለት ነው።ሄሮድስ ለሄሮድያዳ ልጅ በወጭት የቅዱስ ዮሐንስን አንገት እንዲሰጧት አዘዘ።እግዚአብሔር ባወቀ በርኩስ እጇ የቅዱሱን አንገት እንዳትነካ ነው።
አባታችን ዛሬም እኛ ልጆችህን “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ።”ማቴ3፥1-2 እያልህ ወደ ንስሐ ምራን።ልባችን የደነደነ እኛን "እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ከሚመጣው ቍጣ እንድትሸሹ ማን አመለከታችሁ?እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ"(ማቴ 3፥7-8) እያልህ ዝለፈን!!!
የቅዱስ ዮሐንስ በረከቱ ይደርብን!!!
#መምህር_ኢዮብ_ክንፈ
ወርኃ መስከረም 2/2017 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
+++ እርሷ መድኃኒታችሁ ናትና!!" +++
ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናት ዓመታዊ በዓል (ብዙኃን ማርያም) እንኳን አደረሰን!!
(በትዕግሥት ሆነው ያንብቡት፣ ለሌላውም በማጋራት ሃይማኖታዊ ግዴታዎን ይወጡ)
ላለመማርና ላለማወቅ አእምሯቸውን አሳልፈው የሰጡ ኦርቶዶክሳዊነትንና ኦርቶዶክሳውያንን አምርረው የጠሉ ሰዎች "ድንግል ማርያም ምክንያተ ድኂን እንጂ መድኃኒት አትባልም" ሲሉ ለይቶላቸው የወጡቱ ደግሞ ጥቅሶችን ከዓውድና ከተነገሩበት ዓላማ ውጭ በመጥቀስ "ማርያምን መድኃኒት ቤዛ አድኝን" አትበሏት ብለው በአፍም በመጽሐፍም ይናገራሉ:: ኦርቶዶክሳውያን ድንግል ማርያምን "መድኃኒት፣ ቤዛ" ብለን ስንጠራት በውስጥም በአፋ ያሉ ብዙዎች ባልተረዱት ባላወቁት ባልመረመሩት ነገር እርሷን ከልጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያተካከልናት በእርሱ የማዳን ዙፋን ያስቀመጥናት አድርገው ያስባሉ ይናገራሉም:: ከዚያም አልፈው በክርስቶስ የማዳን ሥራ ላይ የተንሸዋረረ እውቀትና እምነት እንዳለን አድርገው በሌሎች ዘንድ ያጠለሹናል:: ኦርቶዶክሳውያን ያዳነን ማን እንደሆነ ከምን እንዳዳነን ለምን እንዳዳነንና በማዳኑም ሥራ ውስጥ ማዳኑ የተፈጸመለት የሰው ልጅ ሱታፌና ድርሻ ምን መሆን እንደሚገባው ቤተክርስቲያን ታስተምረናለች:: ድንግል ማርያምና ቅዱሳኑን በመንቀፍና በመጥላት ስለ እነርሱም ላለመናገር ዳተኛ በመሆን ለክርስቶስ ያለኝን "ፍቅር" እገልጻለሁ ብሎ መድከም ምንኛ አለመታደል ነው? ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች የ"ፓስተሮቻቸውን የ"መጋቤዎቻቸውን" የ"ነቢያቶቻቸውን" የ"ያድናሉ" መልእክት በፖስተር በብሮሸርና በትላልቅ "ባነሮች" እየለጠፋ ወደ የመስብሰቢያ አዳራሾቻቸው ሰዎችን ይጋብዛሉ : በየጉባኤዎቻቸውም የሚያምኑበትን የራሳቸውን ትምህርት ከማስተማር ይልቅ ኦርቶዶክሳዊነትን እያጨለሙና እያጠለሹ የሌለ ስም እየሰጡ ይሰብካሉ:: ኢየሱስ ክርስቶስ ከምንና ለምን አዳነን? እርሱ ካዳነን ከእኛ ምን ይጠበቃል? የሚሉትን ሀሳቦች ማየቱ እጅግ ሰፊ በመሆኑ ለጊዜው አቆይተነው ወደ ነጥባችን እንመለስ :-
+++ ድንግል ማርያም መድኃኒት አትባልምን ? +++
መልሱ ግልጽ ነው::መድኃኒት ትባላለች:: እርሷ መድኃኒት ማለታችን ግን ከክርስቶስ ጋር አስተካከልናት ማለት አይደለም ሊሆንም አይችልም::በመጽሐፍ ቅዱስ ክርስቶስ ብርሃን ተብሏል ቅዱሳንም ብርሃን ተብለዋል:: (ማቴ 5:14 ዮሐ 5:38፣ 8:12) እናስተውል እርሱን ብርሃን ስንለውና እነርሱን ብርሃናት ስንላቸው አንድ አይደለም:: እርሱን ብርሃን ስንለው ቃሉ እንደ አምላክነቱ ይረቃል ይመጥቃል ይረቃልም:: እነርሱን ብርሃናት ስንላቸውም እንደ ማዕረጋቸው እንደ ቅድስና ደረጃቸው ነው። (ማቴ 13: 8 1ቆሮ 15:41) ያ ባይሆን ቅዱስ መጽሐፍ ክርስቶስንም ብርሃን አገልጋዮቹንም ብርሃን በማለቱ እርሱንና ቅዱሳኑን አፎካከረ ያሰኝ ነበር:: ወዳጆቹን ብርሃናት ማለት የእርሱን ብርሃንነት መካድ አይደለም:: እርሱ እንደውም የብርሃናት (የቅዱሳን) አባት ተብሏል:: (ያዕ 1:17) ይህን እንደ መነሻ ካልን እርሷ መድኃኒት መባል እንደሚገባት መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርገን በንጽጽር እንመልከት::
+++ ቤዛ እስራኤል ቤዛዊተ ዓለም +++
በብሉይ ኪዳን እስራኤል ዘሥጋን ከግብጽ ባርነት ነጻ ያወጣ በጸናች እጅ በተዘረጋችም ክንድ ለሕዝቡ ቤዛ የሆነ ጠላቶቻቸውን የጣለ እርሱ እግዚአብሔር ነው::እግዚአብሔር ሕዝቡን ከባርነት ነፃ ሲያወጣ ነፃ ካወጣቸውም በኋላ የነፃነት ጉዞ ሲያደርጉ መላእክት ቀን በደመና ሌሊት በብርሃን እንደሚመራቸው ተነግሯቸው ነበር:: (ዘጸ 14:19 ዘጸ 23:20) በዚህ ነጻ የመውጣት ጉዞ ውስጥ ታላቅ ሚናና ድርሻ የነበረው ሰው መስፍኑ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ነበር :: ሕዝቡን ይመራና ያስተዳድር ስለእነርሱም ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ነበር:: (ዘጸ 32:32) በዚህም ምክንያት የእግዚአብሔር የሆኑት እስራኤላውያን "የሙሴ ሕዝብ" ሲባሉ ሙሴም በፈጣሪው "የሕዝቡ ነፃ አውጪ" ተብሏል:: (ዘጸ 32:7-8) እስራኤል እግዚአብሔርን ባሳዘኑት ጊዜ ሙሴ ስለ እነርሱ በእግዚአብሔር ፊት ባይቆም ኖሮ ያጠፋቸው ነበር:: (መዝ 105:23) ከዚህ ሁሉ የተነሳ እግዚአብሔር ሙሴን ምክንያት አድርጎ ሕዝቡን ከባርነት ነጻ ስላወጣቸው ሙሴ "የእስራኤል ነፃ አውጪና ቤዛ" ተብሏል:: (ዘጸ 32:7-8፣ የሐዋ 7:35) ይህንም መጽሐፍ ሲመሠክር " ይህ ሰው (ሙሴ) በግብጽ ምድርና በኤርትራ ባሕር በምድረ በዳም አርባ ዓመት ድንቅና ምልክት እያደረገ አወጣቸው" ብሏል :: (የሐዋ 7:36)
እስቲ ጥያቄ እናንሣ እስራኤልን ነፃ ያወጣ ማነው? ሙሴ እንዴት ነፃ አውጪ ተባለ? የእስራኤል ቤዛ ማነው? ሙሴ እንዴት የእስራኤል ቤዛ ተባለ? እስራኤል የማን ሕዝብ ናቸው? የእግዚአብሔር የሆኑት ሕዝቡ እንዴት የሙሴ ሕዝብ ተባሉ? ሙሴ በሕዝቡ መካከል ድንቅና ምልክት ካደረገ "ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ድንቅና ምልክቶችን አድርጋለች።" ተብሎ ሲነገር "ይህማ አይሆንም!" ብሎ ሽንጥ ገትሮ መከራከርን ምን አመጣው? (ማር 16:17 ዮሐ 14:15 ::) በሐዲስ ኪዳን ግብጽ የሲኦል እስራኤላውያን የምእመናነ ሐዲስ ጉዟቸው የጉዟችን የገጠሟቸው ፈተናዎች የፈተናዎቻችን ምሳሌዎች እንደሆኑ ተነግሮናል:: (1ቆሮ 10:1-5) በሙሴ ምስፍና እግዚአብሔር ሕዝቡን ከግብጽ ባርነት ነፃ እንዳወጣ ከእርሷ ከድንግል ማርያም በነሳው (በተዋሐደው) ሥጋ እኛን ከሰይጣን አገዛዝ ከሲኦል ባርነት ነፃ አውጥቶናል:: (ዕብ 2:14-16 1ጴጥ 3:19 ዮሐ 1:14-15) በሙሴ ተልእኮ እስራኤል ከግብጽ ወጡ ከድንግል በነሳው ሥጋ ዓለም ከሲኦል ነፃ ወጣ:: በሙሴ ተልእኮ ፈርኦን ተሸነፈ ከድንግል በተዋሐደው ሥጋ በፈጸመው የማዳን ሥራ ዲያብሎስ አፈረ በመስቀሉም ተጠረቀ:: (ቆላ 2:14-16) እስራኤል ከሥጋ ባርነት ከፈርኦን አገዛዝ ነፃ ከወጡበት መንገድ ዓለም ከነፍስ ባርነት ከሰይጣን አገዛዝ የዳነበት መንገድ ይበልጣል :: በእርሱ ምክንያት በተፈጸመው እስራኤልን ነጻ የማውጣት ጉዞ ሙሴ ቤዛ ነጻ አውጪ ከተባለ በድንግል ማርያም በተፈጸመው የማዳን ሥራ ቤዛዊተ ዓለም ብትባል ምን ያንስባታል? እራሷ " ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ ( ማዳኑን ) አድርጓልና።" እንዳለች (ሉቃ 1:49-50)
+++ እርሷ መድኃኒታችሁ ናት +++
በተአምረ ማርያም መቅድም ከሠፈሩ እመቤታችንን እንድንወዳት ከሚያስገነዝቡን ኃይለ ቃላት አንዱ "ውደዷት እርሷ መድኃኒታችሁ ናት" ይላል:: እንግዲህ ይህን አንብበው ነው ሰዎቹ ለምን እንዲህ ትላላችሁ ብለው እንደ ጥህሎ ሊውጡን እንደ እንቀት ሊጠጡን የሚነሥሡብን ሳይመረምሩና ሳይገነዘቡም የሚተቹን :: እነዚህ ክፍሎች እርሷን እንዴት መድኃኒት ትሏታላችሁ? ብለውም ጉንጭ አልፋ መከራከርያ ያነሣሉ:: እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ መድኃኒት አዳኝ ነው:: ማዳን የባሕርይው የሆነ እርሱ የወደዳቸውን በፍጹም ልባቸው ያመለኩት ወዳጆቹን ምክንያት አድርጎ በልዩ ልዩ መንገድ ማዳኑን ስለገለጠባቸው መድኃኒት አዳኝ እንዲባሉ ፈቀደ ያድኑም ዘንድ የማዳኑን ጥበብ ገለጠላቸው ኃይሉንም አስታጠቃቸው መንገዳቸውንም አቃና:: እስቲ የሚከተሉትን ለግንዛቤ እንመልከት
👇-ይቀጥላል-👇
ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናት ዓመታዊ በዓል (ብዙኃን ማርያም) እንኳን አደረሰን!!
(በትዕግሥት ሆነው ያንብቡት፣ ለሌላውም በማጋራት ሃይማኖታዊ ግዴታዎን ይወጡ)
ላለመማርና ላለማወቅ አእምሯቸውን አሳልፈው የሰጡ ኦርቶዶክሳዊነትንና ኦርቶዶክሳውያንን አምርረው የጠሉ ሰዎች "ድንግል ማርያም ምክንያተ ድኂን እንጂ መድኃኒት አትባልም" ሲሉ ለይቶላቸው የወጡቱ ደግሞ ጥቅሶችን ከዓውድና ከተነገሩበት ዓላማ ውጭ በመጥቀስ "ማርያምን መድኃኒት ቤዛ አድኝን" አትበሏት ብለው በአፍም በመጽሐፍም ይናገራሉ:: ኦርቶዶክሳውያን ድንግል ማርያምን "መድኃኒት፣ ቤዛ" ብለን ስንጠራት በውስጥም በአፋ ያሉ ብዙዎች ባልተረዱት ባላወቁት ባልመረመሩት ነገር እርሷን ከልጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያተካከልናት በእርሱ የማዳን ዙፋን ያስቀመጥናት አድርገው ያስባሉ ይናገራሉም:: ከዚያም አልፈው በክርስቶስ የማዳን ሥራ ላይ የተንሸዋረረ እውቀትና እምነት እንዳለን አድርገው በሌሎች ዘንድ ያጠለሹናል:: ኦርቶዶክሳውያን ያዳነን ማን እንደሆነ ከምን እንዳዳነን ለምን እንዳዳነንና በማዳኑም ሥራ ውስጥ ማዳኑ የተፈጸመለት የሰው ልጅ ሱታፌና ድርሻ ምን መሆን እንደሚገባው ቤተክርስቲያን ታስተምረናለች:: ድንግል ማርያምና ቅዱሳኑን በመንቀፍና በመጥላት ስለ እነርሱም ላለመናገር ዳተኛ በመሆን ለክርስቶስ ያለኝን "ፍቅር" እገልጻለሁ ብሎ መድከም ምንኛ አለመታደል ነው? ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች የ"ፓስተሮቻቸውን የ"መጋቤዎቻቸውን" የ"ነቢያቶቻቸውን" የ"ያድናሉ" መልእክት በፖስተር በብሮሸርና በትላልቅ "ባነሮች" እየለጠፋ ወደ የመስብሰቢያ አዳራሾቻቸው ሰዎችን ይጋብዛሉ : በየጉባኤዎቻቸውም የሚያምኑበትን የራሳቸውን ትምህርት ከማስተማር ይልቅ ኦርቶዶክሳዊነትን እያጨለሙና እያጠለሹ የሌለ ስም እየሰጡ ይሰብካሉ:: ኢየሱስ ክርስቶስ ከምንና ለምን አዳነን? እርሱ ካዳነን ከእኛ ምን ይጠበቃል? የሚሉትን ሀሳቦች ማየቱ እጅግ ሰፊ በመሆኑ ለጊዜው አቆይተነው ወደ ነጥባችን እንመለስ :-
+++ ድንግል ማርያም መድኃኒት አትባልምን ? +++
መልሱ ግልጽ ነው::መድኃኒት ትባላለች:: እርሷ መድኃኒት ማለታችን ግን ከክርስቶስ ጋር አስተካከልናት ማለት አይደለም ሊሆንም አይችልም::በመጽሐፍ ቅዱስ ክርስቶስ ብርሃን ተብሏል ቅዱሳንም ብርሃን ተብለዋል:: (ማቴ 5:14 ዮሐ 5:38፣ 8:12) እናስተውል እርሱን ብርሃን ስንለውና እነርሱን ብርሃናት ስንላቸው አንድ አይደለም:: እርሱን ብርሃን ስንለው ቃሉ እንደ አምላክነቱ ይረቃል ይመጥቃል ይረቃልም:: እነርሱን ብርሃናት ስንላቸውም እንደ ማዕረጋቸው እንደ ቅድስና ደረጃቸው ነው። (ማቴ 13: 8 1ቆሮ 15:41) ያ ባይሆን ቅዱስ መጽሐፍ ክርስቶስንም ብርሃን አገልጋዮቹንም ብርሃን በማለቱ እርሱንና ቅዱሳኑን አፎካከረ ያሰኝ ነበር:: ወዳጆቹን ብርሃናት ማለት የእርሱን ብርሃንነት መካድ አይደለም:: እርሱ እንደውም የብርሃናት (የቅዱሳን) አባት ተብሏል:: (ያዕ 1:17) ይህን እንደ መነሻ ካልን እርሷ መድኃኒት መባል እንደሚገባት መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርገን በንጽጽር እንመልከት::
+++ ቤዛ እስራኤል ቤዛዊተ ዓለም +++
በብሉይ ኪዳን እስራኤል ዘሥጋን ከግብጽ ባርነት ነጻ ያወጣ በጸናች እጅ በተዘረጋችም ክንድ ለሕዝቡ ቤዛ የሆነ ጠላቶቻቸውን የጣለ እርሱ እግዚአብሔር ነው::እግዚአብሔር ሕዝቡን ከባርነት ነፃ ሲያወጣ ነፃ ካወጣቸውም በኋላ የነፃነት ጉዞ ሲያደርጉ መላእክት ቀን በደመና ሌሊት በብርሃን እንደሚመራቸው ተነግሯቸው ነበር:: (ዘጸ 14:19 ዘጸ 23:20) በዚህ ነጻ የመውጣት ጉዞ ውስጥ ታላቅ ሚናና ድርሻ የነበረው ሰው መስፍኑ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ነበር :: ሕዝቡን ይመራና ያስተዳድር ስለእነርሱም ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ነበር:: (ዘጸ 32:32) በዚህም ምክንያት የእግዚአብሔር የሆኑት እስራኤላውያን "የሙሴ ሕዝብ" ሲባሉ ሙሴም በፈጣሪው "የሕዝቡ ነፃ አውጪ" ተብሏል:: (ዘጸ 32:7-8) እስራኤል እግዚአብሔርን ባሳዘኑት ጊዜ ሙሴ ስለ እነርሱ በእግዚአብሔር ፊት ባይቆም ኖሮ ያጠፋቸው ነበር:: (መዝ 105:23) ከዚህ ሁሉ የተነሳ እግዚአብሔር ሙሴን ምክንያት አድርጎ ሕዝቡን ከባርነት ነጻ ስላወጣቸው ሙሴ "የእስራኤል ነፃ አውጪና ቤዛ" ተብሏል:: (ዘጸ 32:7-8፣ የሐዋ 7:35) ይህንም መጽሐፍ ሲመሠክር " ይህ ሰው (ሙሴ) በግብጽ ምድርና በኤርትራ ባሕር በምድረ በዳም አርባ ዓመት ድንቅና ምልክት እያደረገ አወጣቸው" ብሏል :: (የሐዋ 7:36)
እስቲ ጥያቄ እናንሣ እስራኤልን ነፃ ያወጣ ማነው? ሙሴ እንዴት ነፃ አውጪ ተባለ? የእስራኤል ቤዛ ማነው? ሙሴ እንዴት የእስራኤል ቤዛ ተባለ? እስራኤል የማን ሕዝብ ናቸው? የእግዚአብሔር የሆኑት ሕዝቡ እንዴት የሙሴ ሕዝብ ተባሉ? ሙሴ በሕዝቡ መካከል ድንቅና ምልክት ካደረገ "ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ድንቅና ምልክቶችን አድርጋለች።" ተብሎ ሲነገር "ይህማ አይሆንም!" ብሎ ሽንጥ ገትሮ መከራከርን ምን አመጣው? (ማር 16:17 ዮሐ 14:15 ::) በሐዲስ ኪዳን ግብጽ የሲኦል እስራኤላውያን የምእመናነ ሐዲስ ጉዟቸው የጉዟችን የገጠሟቸው ፈተናዎች የፈተናዎቻችን ምሳሌዎች እንደሆኑ ተነግሮናል:: (1ቆሮ 10:1-5) በሙሴ ምስፍና እግዚአብሔር ሕዝቡን ከግብጽ ባርነት ነፃ እንዳወጣ ከእርሷ ከድንግል ማርያም በነሳው (በተዋሐደው) ሥጋ እኛን ከሰይጣን አገዛዝ ከሲኦል ባርነት ነፃ አውጥቶናል:: (ዕብ 2:14-16 1ጴጥ 3:19 ዮሐ 1:14-15) በሙሴ ተልእኮ እስራኤል ከግብጽ ወጡ ከድንግል በነሳው ሥጋ ዓለም ከሲኦል ነፃ ወጣ:: በሙሴ ተልእኮ ፈርኦን ተሸነፈ ከድንግል በተዋሐደው ሥጋ በፈጸመው የማዳን ሥራ ዲያብሎስ አፈረ በመስቀሉም ተጠረቀ:: (ቆላ 2:14-16) እስራኤል ከሥጋ ባርነት ከፈርኦን አገዛዝ ነፃ ከወጡበት መንገድ ዓለም ከነፍስ ባርነት ከሰይጣን አገዛዝ የዳነበት መንገድ ይበልጣል :: በእርሱ ምክንያት በተፈጸመው እስራኤልን ነጻ የማውጣት ጉዞ ሙሴ ቤዛ ነጻ አውጪ ከተባለ በድንግል ማርያም በተፈጸመው የማዳን ሥራ ቤዛዊተ ዓለም ብትባል ምን ያንስባታል? እራሷ " ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ ( ማዳኑን ) አድርጓልና።" እንዳለች (ሉቃ 1:49-50)
+++ እርሷ መድኃኒታችሁ ናት +++
በተአምረ ማርያም መቅድም ከሠፈሩ እመቤታችንን እንድንወዳት ከሚያስገነዝቡን ኃይለ ቃላት አንዱ "ውደዷት እርሷ መድኃኒታችሁ ናት" ይላል:: እንግዲህ ይህን አንብበው ነው ሰዎቹ ለምን እንዲህ ትላላችሁ ብለው እንደ ጥህሎ ሊውጡን እንደ እንቀት ሊጠጡን የሚነሥሡብን ሳይመረምሩና ሳይገነዘቡም የሚተቹን :: እነዚህ ክፍሎች እርሷን እንዴት መድኃኒት ትሏታላችሁ? ብለውም ጉንጭ አልፋ መከራከርያ ያነሣሉ:: እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ መድኃኒት አዳኝ ነው:: ማዳን የባሕርይው የሆነ እርሱ የወደዳቸውን በፍጹም ልባቸው ያመለኩት ወዳጆቹን ምክንያት አድርጎ በልዩ ልዩ መንገድ ማዳኑን ስለገለጠባቸው መድኃኒት አዳኝ እንዲባሉ ፈቀደ ያድኑም ዘንድ የማዳኑን ጥበብ ገለጠላቸው ኃይሉንም አስታጠቃቸው መንገዳቸውንም አቃና:: እስቲ የሚከተሉትን ለግንዛቤ እንመልከት
👇-ይቀጥላል-👇
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
ሐሜተኛ ሰው የእግዚአብሔር ጠላቱ ነው። በጠላትህ ውድቀትና ሞት ደስ አይበልህ፤ ባዘኑት ላይ አትሣለቅ፤ ለዕውሩ መሰናክል አታኑርበት። ስትጸልይ ለመቀመጥ አትቸኩል፤ ለጸሎት ጽሙድ ኾነህ በቆምክበት ቦታ ኹሉ አትነቃነቅ፤ በመካነ ጸሎትህ ላይ አዘውትረህ ቆመህ ተገኝ። ለለመነህ ኹሉ ስጥ፤ ከሌለህ ደግሞ እግዚአብሔር ይስጥህ ካለው ያድርስህ ብለህ በለዘበ ቃል ተናገር። የምትሠራውን ሥራ ኹሉ ፊት አይተህ አድልተህ አትሥራ። የደረሰብህን ኹሉ እግዚአብሔርን አመስግነህ ተቀበል። ይህንን ያደረግህ እንደ ኾነ በእግዚአብሔር ትእዛዛትና ሕግጋት አንተ በእውነት ፍጹም ነህ። እኔስ በእውነት የእግዚአብሔርን ጥበብ አደንቃለሁ።
❝በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።❞
—1ኛ ቆሮንቶስ 15: 19
©️ መምህር ዲ/ን እስጢፋኖስ ደሳለኝ
❝በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።❞
—1ኛ ቆሮንቶስ 15: 19
©️ መምህር ዲ/ን እስጢፋኖስ ደሳለኝ
Forwarded from Zemari Samuel Tekle Official || ዘማሪ ሳሙኤል ተክሌ (𝑠𝑎𝑚𝑢𝑒𝑙 🅃)
YouTube
🔴 አዲስ ዝማሬ በተሰጠው ጸጋ | Betesetew Tsega | mezmur orthodox ethiopian | new orthodox mezmur 2024 | Mezmur
አዲስ ዝማሬ:- በዘማሪ ሳሙኤል ከበደ
በዘማሪት ዝናቧ ደምሴ
በዘማሪት ማህሌት አንዳርጌ
ስብስክራይብ ላይክ ሼር በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ
This video prepared for educational & spiritual meditation purpose
#sibket
#habesha #ethiopiannews
#amharicnews
Sibket Ethiopian…
በዘማሪት ዝናቧ ደምሴ
በዘማሪት ማህሌት አንዳርጌ
ስብስክራይብ ላይክ ሼር በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ
This video prepared for educational & spiritual meditation purpose
#sibket
#habesha #ethiopiannews
#amharicnews
Sibket Ethiopian…
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
እኔ ለተክለሃይማኖት 24 ቻሌንጅን ተቀላቅያለሁ
ለሕንፃ ቤ/ክ ግዥ የቀረውን ለማሟላት ሁላችንም የ24€ ቻሌንጅን ከታች ባለው በሚመቻችሁ አካውንት በማስገባት እንቀላቀል
በተጨማሪም ለዚሁ ዓለማ ኖቬምበር 10/2024(ሕዳር 1/2017ዓም ) በኢትዮጵያ ከምሽቱ 3:00ሰዓት በአውሮፓ ከምሽቱ 19:00 ሰዓት በሰሜን አሜሪካ እኩለ ቀን 12:00pm @yednehabesha ቲክቶክ አድራሻ ላይቭ እንገናኝ።!
ለሕንፃ ቤ/ክ ግዥ የቀረውን ለማሟላት ሁላችንም የ24€ ቻሌንጅን ከታች ባለው በሚመቻችሁ አካውንት በማስገባት እንቀላቀል
በተጨማሪም ለዚሁ ዓለማ ኖቬምበር 10/2024(ሕዳር 1/2017ዓም ) በኢትዮጵያ ከምሽቱ 3:00ሰዓት በአውሮፓ ከምሽቱ 19:00 ሰዓት በሰሜን አሜሪካ እኩለ ቀን 12:00pm @yednehabesha ቲክቶክ አድራሻ ላይቭ እንገናኝ።!
Forwarded from Abeto Production አቤቶ ፕሮዳክሽን
Make ur day wiz us!
Abeto production
Contact us 0953856891
Abeto production
Contact us 0953856891