Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
#ምትረተ ርእሱ ለቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ#
#“እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል”(ማቴ 3፥11)ብሎ ስለ ክርስቶስ ትንቢት የተናገረ ታላቅ ነቢይ፤
#“በነቢዩ በኢሳይያስ፦ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ የተባለለት።”(ማቴ3፥3) ጸያሔ ፍኖት (የክርስቶስ መንገድ ጠራጊ)፤
#“ራሱም ዮሐንስ የግመል ጠጉር ልብስ ነበረው፥ በወገቡም ጠፍር ይታጠቅ ነበር፤ ምግቡም አንበጣና የበረሀ ማር ነበረ።”(ማቴ3፥4) የተባለለት ታላቅ መናኝ ባሕታዊ፤
#ለንስሐ የሚሆን ጥምቀትን ያጠመቀ ሰባኬ ጥምቀት፤(ሉቃ 3፥6)
#“አንድ ሰው ከእኔ በኋላ ይመጣል፥ ከእኔም በፊት ነበርና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል ብዬ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነው።”(ዮሐንስ 1፥30) ሲል ስለ ጌታ የመሰከረ ስምዐ ጽድቅ (የእውነት ምስክር)፤
#ጌታችን “እርሱ የሚነድና የሚያበራ መብራት ነበረ፥ እናንተም ጥቂት ዘመን በብርሃኑ ደስ ሊላችሁ ወደዳችሁ።”(ዮሐ 5፥35) ብሎ የመሰከረለት ድንቅ የጸጋ ብርሃን፤
#“እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም።” ማቴ(11፥11) ተብሎ በጌታ የተነገረለት ታላቅ የሃይማኖት ኮከብ፤
#አምላክን በሥጋ ያጠመቀ መጥምቀ መለኮት፤(ማቴ 3:15-16፤ማር 1:9፤ሉቃ 3:21)
#“እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም።”(ማቴዎስ 14፥4 )
ሲል ሄሮድስን በወንድሙ በፊልጶስ ሚስት በሄሮዳድያ ምክንያት ያስተማረና የገሠፀ ሐዋርያ፤
#ሄሮድስ ስለ ክብሩ ተጨንቆ በገዛ መሐላው ተታሎ አንገቱን ያስቆረጠው ሰማዕት፤“ልኮም የዮሐንስን ራስ በወህኒ አስቆረጠው።”(ማቴ14፥10)
እንዲል፤
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዛሬ ክብርት አንገቱ በግፍ የተቆረጠችበት ዕለት ነው።ሄሮድስ ለሄሮድያዳ ልጅ በወጭት የቅዱስ ዮሐንስን አንገት እንዲሰጧት አዘዘ።እግዚአብሔር ባወቀ በርኩስ እጇ የቅዱሱን አንገት እንዳትነካ ነው።
አባታችን ዛሬም እኛ ልጆችህን “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ።”ማቴ3፥1-2 እያልህ ወደ ንስሐ ምራን።ልባችን የደነደነ እኛን "እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ከሚመጣው ቍጣ እንድትሸሹ ማን አመለከታችሁ?እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ"(ማቴ 3፥7-8) እያልህ ዝለፈን!!!
የቅዱስ ዮሐንስ በረከቱ ይደርብን!!!
#መምህር_ኢዮብ_ክንፈ
ወርኃ መስከረም 2/2017 ዓ.ም
#“እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል”(ማቴ 3፥11)ብሎ ስለ ክርስቶስ ትንቢት የተናገረ ታላቅ ነቢይ፤
#“በነቢዩ በኢሳይያስ፦ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ የተባለለት።”(ማቴ3፥3) ጸያሔ ፍኖት (የክርስቶስ መንገድ ጠራጊ)፤
#“ራሱም ዮሐንስ የግመል ጠጉር ልብስ ነበረው፥ በወገቡም ጠፍር ይታጠቅ ነበር፤ ምግቡም አንበጣና የበረሀ ማር ነበረ።”(ማቴ3፥4) የተባለለት ታላቅ መናኝ ባሕታዊ፤
#ለንስሐ የሚሆን ጥምቀትን ያጠመቀ ሰባኬ ጥምቀት፤(ሉቃ 3፥6)
#“አንድ ሰው ከእኔ በኋላ ይመጣል፥ ከእኔም በፊት ነበርና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል ብዬ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነው።”(ዮሐንስ 1፥30) ሲል ስለ ጌታ የመሰከረ ስምዐ ጽድቅ (የእውነት ምስክር)፤
#ጌታችን “እርሱ የሚነድና የሚያበራ መብራት ነበረ፥ እናንተም ጥቂት ዘመን በብርሃኑ ደስ ሊላችሁ ወደዳችሁ።”(ዮሐ 5፥35) ብሎ የመሰከረለት ድንቅ የጸጋ ብርሃን፤
#“እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም።” ማቴ(11፥11) ተብሎ በጌታ የተነገረለት ታላቅ የሃይማኖት ኮከብ፤
#አምላክን በሥጋ ያጠመቀ መጥምቀ መለኮት፤(ማቴ 3:15-16፤ማር 1:9፤ሉቃ 3:21)
#“እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም።”(ማቴዎስ 14፥4 )
ሲል ሄሮድስን በወንድሙ በፊልጶስ ሚስት በሄሮዳድያ ምክንያት ያስተማረና የገሠፀ ሐዋርያ፤
#ሄሮድስ ስለ ክብሩ ተጨንቆ በገዛ መሐላው ተታሎ አንገቱን ያስቆረጠው ሰማዕት፤“ልኮም የዮሐንስን ራስ በወህኒ አስቆረጠው።”(ማቴ14፥10)
እንዲል፤
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዛሬ ክብርት አንገቱ በግፍ የተቆረጠችበት ዕለት ነው።ሄሮድስ ለሄሮድያዳ ልጅ በወጭት የቅዱስ ዮሐንስን አንገት እንዲሰጧት አዘዘ።እግዚአብሔር ባወቀ በርኩስ እጇ የቅዱሱን አንገት እንዳትነካ ነው።
አባታችን ዛሬም እኛ ልጆችህን “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ።”ማቴ3፥1-2 እያልህ ወደ ንስሐ ምራን።ልባችን የደነደነ እኛን "እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ከሚመጣው ቍጣ እንድትሸሹ ማን አመለከታችሁ?እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ"(ማቴ 3፥7-8) እያልህ ዝለፈን!!!
የቅዱስ ዮሐንስ በረከቱ ይደርብን!!!
#መምህር_ኢዮብ_ክንፈ
ወርኃ መስከረም 2/2017 ዓ.ም