Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
አዲሱ ወይን
ይህ ቃል ለብዙዎቻችን አዲስ አይደለም።በቅዱስ ወንጌል ንባብ፣በሠርግ ዝማሬዎችና በመንፈሳዊ ስብከቶች ውስጥ ደጋግመን ሰምተነዋል።ምንም እንኳን "ቃና ዘገሊላ" የሚለው ቃል ለጆሮአችን አዲስ ባይሆንም አዲስ ምሥጢር የተፈጸመበት ቦታ ነው።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠምቆ፤በገዳመ ቆሮንጦስ ሦስቱን አርእስተ ኃጣውእ በሦስቱ አርእስተ ምግባራት ድል ነሥቶ፤ከገዳም በወጣ :
"በሦስተኛው ቀን በቃና ዘገሊላ ሠርግ ሆነ።የጌታችን የኢየሱስ እናትም በዚያ ነበረች።" ብሎ ፍቁረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስ ጻፈልን።ይህቺን "ቃና" የተባለች ስፍራ "ዘገሊላ" ወይም በገሊላ አውራጃ የምትገኝ በማለት ከሌሎች ቃናዎች ለይቶልናል።
ይህቺ መንደር(ቃና ዘገሊላ)ድሆችና አሕዛብ የሚበዙባት መንደር ናት።ጌታችን ጥንቱንም ሰው የሆነው ድሆችን ባለጠጎች አሕዛብንም ሕዝብ ሊያደርግ ነውና።
"የጌታችን የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች" ሲል ወንጌላዊው ትረካውን ይቀጥላል።"ሙሽራዋ ንጹሕ የሆነ ንጽሕት የሠርግ ቤት" በሠርግ ቤት ተገኘች።ከሠርጉ በኋላ የተጠቀሰችው የመጀመሪያዋ አካል እመቤታችን ናት።እንግዲህ ቅዱስ ዮሐንስ ነባቤ መለኮት ነውና እርሷን ያስቀደመበት ምክንያት አለው።
ከእርሷ ለሚገኘው ፀሐይ ሰማይ፤ከእርሷ ለሚወለደው ፍሬ አበባ፤ከእርሷ ለሚፈስስልን ወንዝ ምንጭ ናትና መሠረቲቱን አስቀድሞ ሕይወትን ሊያስከትል ነው።እሷ መሠረተ ሕይወት ናትና።የምትሠራውም ግሩም ሥራ አለና እሷን አስቀደመ።የሠርግ ቤቷ ስንዱ ከሆነች ዘንድ ሙሽራውንና ሙሽሪትን፣መብልና መጠጥን፣ከበሮንና መዝሙርን፤የሙሽራውንና የሙሽሪትን ዘመዶች አንድ መሆን እንጠብቃለን።
"ጌታችን ኢየሱስም ደግሞ ደቀመዛሙርቱም ወደ ሠርጉ ታደሙ።" እናት ካለች ልጅ መምህርም ካለ ደቀመዛሙርት አሉና፤ሠርገኞቹ እናትን ከልጇ መምህሩንም ከተማሪዎቹ ጋር ጠሯቸው።ጉባኤ ሐዋርያት ቅድስት ቤተክርስቲያንም በሠርጉ ተገኘች።
"የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የጌታችን የኢየሱስ እናት የወይን ጠጅኮ የላቸውም አለችው።" ምልዕተ ጸጋ ናትና ማንም ሳይነግራት ዐውቃ፤ርኅርኂተ ኅሊና ናትና ለሙሽሮቹና ለቤተ ዘመዶቻቸው ራርታ፤ትምክህተ ዘመድነ ድንግል ማርያም ልጇን ለመነች።መስጠት ስትችል ልጇ እንዲሰጣቸው አሳሰበች።የራሷ ክብር ከሚገለጥ የልጇ ክብር ቢገለጥ ትወዳለችና።
"መስጠትማ አትችልም" የሚል ማንም ቢኖር ግን ለስም አጠራሯ ክብር ስግደት ይግባትና እንኳን የወይን ጠጅ አማናዊውን (እውነተኛውን) ወይን በሥጋ ወልዳ ሰጥታን የለም ወይ እንለዋለን።ልጇ በማይታበል ቃሉ "እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ" ብሎ ነግሮናልና።"የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም" ባለችው አንዲት የልመና ቃል ብቻ ይህ ዓለም እስከሚያልፍ ድረስ እንደ ልጇ ፈቃድ ለሚጋቡ ሙሽሮች ሁሉ የፍቅር ወይንን ስታሰጥ ትኖራለች።
"ጌታችን ኢየሱስም አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት።" የጠይቅሽኝን እንዳላደርግልሽ ከአንቺ ምን ጸብ አለኝ? ማለቱ ነው።ሴት ማለት ምትክ ማለት ነው፤እርሷም የቀዳሚት ሔዋን ምትክ ናትና ሴት አላት።ሴት ማለት "ሥጋሽ ከሥጋዬ አጥንትሽ ከአጥንቴ ነው" ማለት ነውና ይህን ሥጋ የነሣሁት ከአንቺ ነው ለማለት ሴት አላት።
"በአንተና በሴቲቱ በዘርህና በዘሯ መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ።እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል አንተም ሰኮናውን ትነክሳለህ።"(ዘፍ 3:15) የሚለው ትንቢተ እግዚአብሔር የተፈጸመባት፤ ዘሯ(ልጇ) ኢየሱስ ክርስቶስም የዘንዶውን ራስ የቀጠቀጠ(መዝ 73:14)
የሴቶች ሁሉ ራስ ናትና "አንቺ ሴት" አላት።
"ጊዜዬ ገና አልደረሰም" ወይኑ ፈጽሞ አላለቀምና፤ተአምሩን(ክብሩን) የሚገልጥበት ሰዓት አልደረሰምና፤እግዚአብሔር ሥራ የሚሠራበት ጊዜ አለውና፤እውነተኛ ወይን የሆነ ወርቀ ደሙን የሚያፈስስበት ጊዜ አልደረሰምና እንዲህ አለ።ዓለም ሳይፈጠር የወይን ጠጁን ማለቅ የሚያወቅ አምላክ የርኅርኂት እናቱን ምልጃ ጠበቀ።
"እናቱም ለአገልጋዮቹ የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው"።"መርዓቱ ለአብ"(የአብ ሙሽሪቱ) ናትና አብ በብሩህ ደመና በደብረ ታቦር "በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" ብሎ የሚነግረንን ቃል እመቤታችን በቤተ ዶኪማስ ነገረችን።ሀሳቧ እንደ አምላክ ሀሳብ የሆነ፤መንፈሷም በልጇ በአምላኳ በመድኃኒቷ በኢየሱስ ክርስቶስ የምትደሰት(ሉቃ 1:47) እመቤታችን ማርያም "በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ" አለቻቸው።
እያንዳንዳቸው ከሁለት እስከ ሦስት እንሥራ የሚይዙ ስድስት የድንጋይ ጋኖችን ባቀረቡለት ጊዜ :
"ጌታችን ኢየሱስም ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው አላቸው።እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው አላቸው እስከ አፋቸውም ሞሏቸው።" አገልጋይነት እንዲህ ነው ሊቀ አእላፍ ጋሽ ተሰማ አየለ እንደሚሉት "ለምን?እንዴት?"
ሳይሉ፤ሳይማረሩ እግዚአብሔርን በፍጹም ትሕትና ማገልገል።በእንግድነት በሠርግ ቤት የተገኘ "እውነተኛ የወይን ግንድ" መድኃኔዓለም የወይን ጠጅ ለመስጠት ከአገልጋዮቹ ጋር ያገለግል ጀመር።
ለእግዚአብሔር ሰውን በሥራው ማሳተፉ ልማዱ ነው።ፍጥረቱን ሁሉ የሚጠብቅ ጌታ ለሰው ገነትን ፈጥሮ "ጠብቃት አበጃጃት" አለው፤ሰውን ፈጥሮ "ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት" ብሎ የሰውን ዘር ለማብዛት ለሰው የድርሻውን ሰጠው፤ሁሉን በባሕርይው የሚገዛ አምላክ ሰው ፍጥረቱን በጸጋ እንዲገዛና እንዲነዳ ሰጥቶታል።በዚህ ሠርግ ቤትም አገልጋዮቹን የሥራው ተሳተፊ አደረጋቸው።ቸር መሐሪ ሰውን ወዳጅ ነውና።
"አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው። ሰጡትም" ፡ አንዲት ቃል ሳይወጣ በሀሳቡ ብቻ ውኃውን ወደ ወይን ጠጅ ለውጦ ሰጣቸው።አስቀድሞ በሀሳቡ ብቻ ሰባት ፍጥረታትን የፈጠረ ጌታ አሁንም በሀሳቡ ብቻ ድንቅን ሠራ።በሀሳብ ስንኳ ልሥራ ብል ይቻለኛል ሲል ነው።
ፍጥረትን የሚያስተዳድረውን ጌታ ተአምር ይሥራ እንጂ አስተዳደር አያውቅም እንዳይሉት "ለአሳዳሪው" ስጡት አላቸው።ክቡር ጌታ ክብረ ሥጋን ክብረ ነፍስን የሚያድል ሁሉን የሚያከብር ነውና፤ለአገልጋዮቹ "ለሕዝቡ አድሉ" ማለት ሲቻለው መምህረ ትሕትና ኢየሱስ ክርስቶስ አሳዳሪውን ሳይንቅ "ለአሳዳሪው ስጡት" አለ።ሰጡትም።
"አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውኃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደመጣ አላወቀም፤ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር" : ሙሽሮቹን ለማገልገል የተሰየሙ አገልጋዮች ሰማያዊውን ሙሽራ ከፍጽምት እናቱ ጋር አገለገሉ።በዚህም የጌታ ምሥጢረኛ ሆኑ።አሳዳሪው የማያውቀውን አውቀዋልና።ሁሌም እንዲህ እግዚአብሔርን ከእናቱ ጋር በትሕትና የሚያገለግሉት ምሥጢርን ማወቅ ይሰጣቸዋል።
"አሳዳሪውም ሙሽራውን ጠርቶ ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፤ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስካሁን አቆይተሃል አለው።" የሰማያዊው ሙሽራ የክርስቶስ የወይን ጠጅ የሙሽራውን የወይን ጠጅ መናኛ ያሰኘ ነው።የጸሎት ጣዕም የስንፍናን ጣዕም፤የጾም ጣዕም የመብልን ጣዕም፤የምጽዋት ጣዕም የስስትን ጣዕም፤የትሕትና ጣዕም የትዕቢትን ጣዕም፤የቅዱስ ቁርባን ጣዕም የኃጢአትን ሁሉ ጣዕም መናኛ የሚያሰኝ ነው።የበለጠ ጣዕም እንዳለ ቢገባቸው "ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ፤ደማቸውንም ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ ስለ መንግሥተ ሰማያትም መራራ ሞትን ታገሱ።"
ይህ ቃል ለብዙዎቻችን አዲስ አይደለም።በቅዱስ ወንጌል ንባብ፣በሠርግ ዝማሬዎችና በመንፈሳዊ ስብከቶች ውስጥ ደጋግመን ሰምተነዋል።ምንም እንኳን "ቃና ዘገሊላ" የሚለው ቃል ለጆሮአችን አዲስ ባይሆንም አዲስ ምሥጢር የተፈጸመበት ቦታ ነው።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠምቆ፤በገዳመ ቆሮንጦስ ሦስቱን አርእስተ ኃጣውእ በሦስቱ አርእስተ ምግባራት ድል ነሥቶ፤ከገዳም በወጣ :
"በሦስተኛው ቀን በቃና ዘገሊላ ሠርግ ሆነ።የጌታችን የኢየሱስ እናትም በዚያ ነበረች።" ብሎ ፍቁረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስ ጻፈልን።ይህቺን "ቃና" የተባለች ስፍራ "ዘገሊላ" ወይም በገሊላ አውራጃ የምትገኝ በማለት ከሌሎች ቃናዎች ለይቶልናል።
ይህቺ መንደር(ቃና ዘገሊላ)ድሆችና አሕዛብ የሚበዙባት መንደር ናት።ጌታችን ጥንቱንም ሰው የሆነው ድሆችን ባለጠጎች አሕዛብንም ሕዝብ ሊያደርግ ነውና።
"የጌታችን የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች" ሲል ወንጌላዊው ትረካውን ይቀጥላል።"ሙሽራዋ ንጹሕ የሆነ ንጽሕት የሠርግ ቤት" በሠርግ ቤት ተገኘች።ከሠርጉ በኋላ የተጠቀሰችው የመጀመሪያዋ አካል እመቤታችን ናት።እንግዲህ ቅዱስ ዮሐንስ ነባቤ መለኮት ነውና እርሷን ያስቀደመበት ምክንያት አለው።
ከእርሷ ለሚገኘው ፀሐይ ሰማይ፤ከእርሷ ለሚወለደው ፍሬ አበባ፤ከእርሷ ለሚፈስስልን ወንዝ ምንጭ ናትና መሠረቲቱን አስቀድሞ ሕይወትን ሊያስከትል ነው።እሷ መሠረተ ሕይወት ናትና።የምትሠራውም ግሩም ሥራ አለና እሷን አስቀደመ።የሠርግ ቤቷ ስንዱ ከሆነች ዘንድ ሙሽራውንና ሙሽሪትን፣መብልና መጠጥን፣ከበሮንና መዝሙርን፤የሙሽራውንና የሙሽሪትን ዘመዶች አንድ መሆን እንጠብቃለን።
"ጌታችን ኢየሱስም ደግሞ ደቀመዛሙርቱም ወደ ሠርጉ ታደሙ።" እናት ካለች ልጅ መምህርም ካለ ደቀመዛሙርት አሉና፤ሠርገኞቹ እናትን ከልጇ መምህሩንም ከተማሪዎቹ ጋር ጠሯቸው።ጉባኤ ሐዋርያት ቅድስት ቤተክርስቲያንም በሠርጉ ተገኘች።
"የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የጌታችን የኢየሱስ እናት የወይን ጠጅኮ የላቸውም አለችው።" ምልዕተ ጸጋ ናትና ማንም ሳይነግራት ዐውቃ፤ርኅርኂተ ኅሊና ናትና ለሙሽሮቹና ለቤተ ዘመዶቻቸው ራርታ፤ትምክህተ ዘመድነ ድንግል ማርያም ልጇን ለመነች።መስጠት ስትችል ልጇ እንዲሰጣቸው አሳሰበች።የራሷ ክብር ከሚገለጥ የልጇ ክብር ቢገለጥ ትወዳለችና።
"መስጠትማ አትችልም" የሚል ማንም ቢኖር ግን ለስም አጠራሯ ክብር ስግደት ይግባትና እንኳን የወይን ጠጅ አማናዊውን (እውነተኛውን) ወይን በሥጋ ወልዳ ሰጥታን የለም ወይ እንለዋለን።ልጇ በማይታበል ቃሉ "እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ" ብሎ ነግሮናልና።"የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም" ባለችው አንዲት የልመና ቃል ብቻ ይህ ዓለም እስከሚያልፍ ድረስ እንደ ልጇ ፈቃድ ለሚጋቡ ሙሽሮች ሁሉ የፍቅር ወይንን ስታሰጥ ትኖራለች።
"ጌታችን ኢየሱስም አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት።" የጠይቅሽኝን እንዳላደርግልሽ ከአንቺ ምን ጸብ አለኝ? ማለቱ ነው።ሴት ማለት ምትክ ማለት ነው፤እርሷም የቀዳሚት ሔዋን ምትክ ናትና ሴት አላት።ሴት ማለት "ሥጋሽ ከሥጋዬ አጥንትሽ ከአጥንቴ ነው" ማለት ነውና ይህን ሥጋ የነሣሁት ከአንቺ ነው ለማለት ሴት አላት።
"በአንተና በሴቲቱ በዘርህና በዘሯ መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ።እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል አንተም ሰኮናውን ትነክሳለህ።"(ዘፍ 3:15) የሚለው ትንቢተ እግዚአብሔር የተፈጸመባት፤ ዘሯ(ልጇ) ኢየሱስ ክርስቶስም የዘንዶውን ራስ የቀጠቀጠ(መዝ 73:14)
የሴቶች ሁሉ ራስ ናትና "አንቺ ሴት" አላት።
"ጊዜዬ ገና አልደረሰም" ወይኑ ፈጽሞ አላለቀምና፤ተአምሩን(ክብሩን) የሚገልጥበት ሰዓት አልደረሰምና፤እግዚአብሔር ሥራ የሚሠራበት ጊዜ አለውና፤እውነተኛ ወይን የሆነ ወርቀ ደሙን የሚያፈስስበት ጊዜ አልደረሰምና እንዲህ አለ።ዓለም ሳይፈጠር የወይን ጠጁን ማለቅ የሚያወቅ አምላክ የርኅርኂት እናቱን ምልጃ ጠበቀ።
"እናቱም ለአገልጋዮቹ የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው"።"መርዓቱ ለአብ"(የአብ ሙሽሪቱ) ናትና አብ በብሩህ ደመና በደብረ ታቦር "በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" ብሎ የሚነግረንን ቃል እመቤታችን በቤተ ዶኪማስ ነገረችን።ሀሳቧ እንደ አምላክ ሀሳብ የሆነ፤መንፈሷም በልጇ በአምላኳ በመድኃኒቷ በኢየሱስ ክርስቶስ የምትደሰት(ሉቃ 1:47) እመቤታችን ማርያም "በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ" አለቻቸው።
እያንዳንዳቸው ከሁለት እስከ ሦስት እንሥራ የሚይዙ ስድስት የድንጋይ ጋኖችን ባቀረቡለት ጊዜ :
"ጌታችን ኢየሱስም ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው አላቸው።እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው አላቸው እስከ አፋቸውም ሞሏቸው።" አገልጋይነት እንዲህ ነው ሊቀ አእላፍ ጋሽ ተሰማ አየለ እንደሚሉት "ለምን?እንዴት?"
ሳይሉ፤ሳይማረሩ እግዚአብሔርን በፍጹም ትሕትና ማገልገል።በእንግድነት በሠርግ ቤት የተገኘ "እውነተኛ የወይን ግንድ" መድኃኔዓለም የወይን ጠጅ ለመስጠት ከአገልጋዮቹ ጋር ያገለግል ጀመር።
ለእግዚአብሔር ሰውን በሥራው ማሳተፉ ልማዱ ነው።ፍጥረቱን ሁሉ የሚጠብቅ ጌታ ለሰው ገነትን ፈጥሮ "ጠብቃት አበጃጃት" አለው፤ሰውን ፈጥሮ "ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት" ብሎ የሰውን ዘር ለማብዛት ለሰው የድርሻውን ሰጠው፤ሁሉን በባሕርይው የሚገዛ አምላክ ሰው ፍጥረቱን በጸጋ እንዲገዛና እንዲነዳ ሰጥቶታል።በዚህ ሠርግ ቤትም አገልጋዮቹን የሥራው ተሳተፊ አደረጋቸው።ቸር መሐሪ ሰውን ወዳጅ ነውና።
"አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው። ሰጡትም" ፡ አንዲት ቃል ሳይወጣ በሀሳቡ ብቻ ውኃውን ወደ ወይን ጠጅ ለውጦ ሰጣቸው።አስቀድሞ በሀሳቡ ብቻ ሰባት ፍጥረታትን የፈጠረ ጌታ አሁንም በሀሳቡ ብቻ ድንቅን ሠራ።በሀሳብ ስንኳ ልሥራ ብል ይቻለኛል ሲል ነው።
ፍጥረትን የሚያስተዳድረውን ጌታ ተአምር ይሥራ እንጂ አስተዳደር አያውቅም እንዳይሉት "ለአሳዳሪው" ስጡት አላቸው።ክቡር ጌታ ክብረ ሥጋን ክብረ ነፍስን የሚያድል ሁሉን የሚያከብር ነውና፤ለአገልጋዮቹ "ለሕዝቡ አድሉ" ማለት ሲቻለው መምህረ ትሕትና ኢየሱስ ክርስቶስ አሳዳሪውን ሳይንቅ "ለአሳዳሪው ስጡት" አለ።ሰጡትም።
"አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውኃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደመጣ አላወቀም፤ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር" : ሙሽሮቹን ለማገልገል የተሰየሙ አገልጋዮች ሰማያዊውን ሙሽራ ከፍጽምት እናቱ ጋር አገለገሉ።በዚህም የጌታ ምሥጢረኛ ሆኑ።አሳዳሪው የማያውቀውን አውቀዋልና።ሁሌም እንዲህ እግዚአብሔርን ከእናቱ ጋር በትሕትና የሚያገለግሉት ምሥጢርን ማወቅ ይሰጣቸዋል።
"አሳዳሪውም ሙሽራውን ጠርቶ ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፤ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስካሁን አቆይተሃል አለው።" የሰማያዊው ሙሽራ የክርስቶስ የወይን ጠጅ የሙሽራውን የወይን ጠጅ መናኛ ያሰኘ ነው።የጸሎት ጣዕም የስንፍናን ጣዕም፤የጾም ጣዕም የመብልን ጣዕም፤የምጽዋት ጣዕም የስስትን ጣዕም፤የትሕትና ጣዕም የትዕቢትን ጣዕም፤የቅዱስ ቁርባን ጣዕም የኃጢአትን ሁሉ ጣዕም መናኛ የሚያሰኝ ነው።የበለጠ ጣዕም እንዳለ ቢገባቸው "ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ፤ደማቸውንም ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ ስለ መንግሥተ ሰማያትም መራራ ሞትን ታገሱ።"
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
ከላይኛው የቀጠለ ...
"ጌታችን ኢየሱስ ይህንን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ።ክብሩንም ገለጠ።ደቀመዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።" ለሥራው ሁሉ መግቢያ ካደረጋት ጥምቀትና የበጎ ሥራዎች ሁሉ ጥንት ከሆነችው ከጾሙ በኋላ የመጀመሪያው ተአምር(ምልክት) ይህ ነው ለማለት ነው እንጂ ጥንቱንስ ጌታ ከፅንሰቱና ከሕፃንነቱ ዕድሜ አንሥቶ ተአምር ያላደረገበት ጊዜ የለም።የባሕርይ ክብሩን ገለጠ።ደቀመዛሙርቱም በባሕርይ አምላክነቱ አመኑ።
ሰይጣን "እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል" ሲለው ባለማድረግ ያሳፈረው ጌታ፤"እናቱ የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም" ስትለው ልመናዋን ተቀብሎ ውኃው የወይን ጠጅ በማድረግ ፈጽሞላታል።"ከእኔ ተማሩ"(ማቴ 11:29) ብሎናልና ዲያቢሎስ የሚለንን አምቢ እያልን(ያዕ 4:7) እመቤታችንን ግን እሺ እያልን እንኖራለን።እሷ "የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ" አይደል እንዴ ያለቺው የሚለን ሰው ቢኖር አዎ እርሷም እኮ የምትለን እሱ የሚለንን ነው ብለን እንመልስለታለን።"የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ" እንዳለችን አባቱም "እርሱን ስሙት" ብሎናልና።አብም የሚነግረን በወልድ ቃልነት ነውና(ዮሐ 1:1፤ዕብ 1:1-2) እሷን መስማት እርሱን መስማት ነው። ይቀጥላል ...
ኢዮብ ክንፈ
ጥር 29/2016 ዓ.ም
"ጌታችን ኢየሱስ ይህንን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ።ክብሩንም ገለጠ።ደቀመዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።" ለሥራው ሁሉ መግቢያ ካደረጋት ጥምቀትና የበጎ ሥራዎች ሁሉ ጥንት ከሆነችው ከጾሙ በኋላ የመጀመሪያው ተአምር(ምልክት) ይህ ነው ለማለት ነው እንጂ ጥንቱንስ ጌታ ከፅንሰቱና ከሕፃንነቱ ዕድሜ አንሥቶ ተአምር ያላደረገበት ጊዜ የለም።የባሕርይ ክብሩን ገለጠ።ደቀመዛሙርቱም በባሕርይ አምላክነቱ አመኑ።
ሰይጣን "እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል" ሲለው ባለማድረግ ያሳፈረው ጌታ፤"እናቱ የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም" ስትለው ልመናዋን ተቀብሎ ውኃው የወይን ጠጅ በማድረግ ፈጽሞላታል።"ከእኔ ተማሩ"(ማቴ 11:29) ብሎናልና ዲያቢሎስ የሚለንን አምቢ እያልን(ያዕ 4:7) እመቤታችንን ግን እሺ እያልን እንኖራለን።እሷ "የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ" አይደል እንዴ ያለቺው የሚለን ሰው ቢኖር አዎ እርሷም እኮ የምትለን እሱ የሚለንን ነው ብለን እንመልስለታለን።"የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ" እንዳለችን አባቱም "እርሱን ስሙት" ብሎናልና።አብም የሚነግረን በወልድ ቃልነት ነውና(ዮሐ 1:1፤ዕብ 1:1-2) እሷን መስማት እርሱን መስማት ነው። ይቀጥላል ...
ኢዮብ ክንፈ
ጥር 29/2016 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
+++ ማዕበሉ ካልተረጋጋ አንተ ተረጋጋ +++
(በወጀብና በዐውሎ ነፋስ መካከል መንገድ ያለው የድንግል ልጅ ቅዱስ አማኑኤል ፍጹም መረጋጋትን ያድለን!!)
ስለ ኑሮ፣ ስለ ትዳር፣ ተጨማሪ ገቢ ስለማግኘት፣ የሥራ ዘርፍ ስለመቀየር ወይም አልሞላ ባለህ አንዳች ነገር ደግሞም በውል ባላወቅኽው ነገር እየተጨነቅህ ውስጣህ አልረጋጋ ብሎህ ተቸግረሃል፡፡
ይኽ ብቻ አይደለም የምታልመውና ልትደርስበት የምትፈልገው ቦታ አሁን ከሆንከውና ካለህበት ሁኔታ ጋር አለመግጠሙም ናላህን አዙሮት ይሆናል፡፡ ባንተ ዕይታና ከሰዎች በታች ሆኜበታለው ብለህ አምነህ በተቀበልከው ነገርም ውስጥህ በሚሰማህ የዝቅተኝነት መንፈስ እየተሰቃየህ ነው፡፡ ያመንከው ጓደኛ ፍቅረኛ ወይም ዘመድ ፊታቸውን አዙረውብህ ፈጣሪ የተወኽ መስሎህም ዕረፍት ዐልባ ሆነህ ይሆናል፡፡
የትኛውም ዓይነት ችግር ከውጭ ቢከብህ ይኽን አስተውል∶− ባልተረጋጋህ ልክ ችግሮች እየከፉ ይሄዳሉ እንጂ አይቀሉም፡፡ አለመረጋጋት የተከሰተን ደስ የማያሰኝ ነገር ከድጡ ወደ ማጡ ይቀይራል፡፡ እንኳን የማታውቀውን የምታውቀውንም ያጠፋብሃል፡፡
ስትረጋጋ የችግሮች መፍትሔ የጥልፍልፎች ውል ወለል ብሎ ይታይሃል፡፡ ስትረጋጋ የተዘበራረቀው ሁሉ እንዴት ሊስተካከል እንደሚችል የምታይበት ዐይን የምታስተውልበትን ልቡና ታገኛለህ፡፡ ዛሬ በቤተሰብም በመንደርም በሀገርም እየተከሰተ ያለው ይኼ ሁሉ ትርምስ ምንጩ ምን ይመስልሃል? ተረጋግቶ ላይ ታች ፊት ኋላ ቀኝ ግራ የሚመለከት ስለጠፋ ነው፡፡
በእርግጥ እንዳትረጋጋ የሚያደርጉ ተንኳሽ አሳቦች፣ ያልተጠበቁ ክስተቶች፣ አስቸጋሪ ሰዎች ከየስፍራው ሊተኮሱና ሊገጥሙህ ይችላሉ፡፡ ቢሆንም ተረጋጋ!! እግዚአብሔርም ያረጋጋህ ዘንድ ተማጸነው። ካልተረጋጋህ ራስህን ብቻ ሳይሆን ዙሪያህ ያሉትን ሁሉ ታውካለህ፡፡ በመዋከብ የሚበተን እንጂ የሚሠበሠብ የሚሰበር እንጂ የሚጠገን የሚጎድል እንጂ የሚሞላ አንዳች የለም፡፡
ጌታችን ወደ ቤታቸው በገባ ጊዜ ሁለቱ እኅትማማች ማርያምና ማርታ ያደረጉትንና ጌታችንም የተናገረውን አስተውል፡፡ ጌታችን ወደ ቤታቸው ከገባበት ጊዜ አንሥቶ ማርታ ደፋ ቀና፤ ወጣ ገባ፤ ቁጭ ብድግ ማለት አብዝታ እጅጉን ባከነች፡፡ ማርያም ግን ተረጋግታ በመቀመጥ የጌታችንን የቃሉን ትምህርት በማድመጥ ጸናች፡፡ ማርታ የማርያም ተረጋግቶ በመቀመጥ ቃለ እግዚአብሔርን መስማት አልተዋጠላትምና "ጌታ ሆይ እኔ እንድሠራ እኅቴ ብቻዬን ስትተወኝ አይገድህምን " አለችው፡፡ ጌታችንም መልሶ "ማርታ ማርታ በብዙ ነገር ትጨነቂያለሽ ትታወኪማለሽ የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፡፡" አላት፡፡ (ሉቃ 10:40) ማርያም የምትሻውን ሁሉ ለማግኘት ተረጋጋች፤ ማርታ ግን ያላትንም ለመልቀቅና ላማጣት ባከነች፡፡ ወዳጄ ብትረጋጋ ጤናህ እስኪታወክ ደርሰህ ወዳጆችህንም እያስቀየምክ ቤተሰብህንም ጭምር ረስተህ የምትባክነው ለሚያስፈልግህ ሳይሆን ለፍላጎትህ መሆኑን ትረዳለህና ተረጋጋ፡፡
የድንግል ልጅ ቅዱስ አማኑኤል ፍጹም መረጋጋትን ያድለን!!
©️ መምህር ቢትወደድ ወርቁ
የካቲት 2 ቀን 2016 ዓ ም
(በወጀብና በዐውሎ ነፋስ መካከል መንገድ ያለው የድንግል ልጅ ቅዱስ አማኑኤል ፍጹም መረጋጋትን ያድለን!!)
ስለ ኑሮ፣ ስለ ትዳር፣ ተጨማሪ ገቢ ስለማግኘት፣ የሥራ ዘርፍ ስለመቀየር ወይም አልሞላ ባለህ አንዳች ነገር ደግሞም በውል ባላወቅኽው ነገር እየተጨነቅህ ውስጣህ አልረጋጋ ብሎህ ተቸግረሃል፡፡
ይኽ ብቻ አይደለም የምታልመውና ልትደርስበት የምትፈልገው ቦታ አሁን ከሆንከውና ካለህበት ሁኔታ ጋር አለመግጠሙም ናላህን አዙሮት ይሆናል፡፡ ባንተ ዕይታና ከሰዎች በታች ሆኜበታለው ብለህ አምነህ በተቀበልከው ነገርም ውስጥህ በሚሰማህ የዝቅተኝነት መንፈስ እየተሰቃየህ ነው፡፡ ያመንከው ጓደኛ ፍቅረኛ ወይም ዘመድ ፊታቸውን አዙረውብህ ፈጣሪ የተወኽ መስሎህም ዕረፍት ዐልባ ሆነህ ይሆናል፡፡
የትኛውም ዓይነት ችግር ከውጭ ቢከብህ ይኽን አስተውል∶− ባልተረጋጋህ ልክ ችግሮች እየከፉ ይሄዳሉ እንጂ አይቀሉም፡፡ አለመረጋጋት የተከሰተን ደስ የማያሰኝ ነገር ከድጡ ወደ ማጡ ይቀይራል፡፡ እንኳን የማታውቀውን የምታውቀውንም ያጠፋብሃል፡፡
ስትረጋጋ የችግሮች መፍትሔ የጥልፍልፎች ውል ወለል ብሎ ይታይሃል፡፡ ስትረጋጋ የተዘበራረቀው ሁሉ እንዴት ሊስተካከል እንደሚችል የምታይበት ዐይን የምታስተውልበትን ልቡና ታገኛለህ፡፡ ዛሬ በቤተሰብም በመንደርም በሀገርም እየተከሰተ ያለው ይኼ ሁሉ ትርምስ ምንጩ ምን ይመስልሃል? ተረጋግቶ ላይ ታች ፊት ኋላ ቀኝ ግራ የሚመለከት ስለጠፋ ነው፡፡
በእርግጥ እንዳትረጋጋ የሚያደርጉ ተንኳሽ አሳቦች፣ ያልተጠበቁ ክስተቶች፣ አስቸጋሪ ሰዎች ከየስፍራው ሊተኮሱና ሊገጥሙህ ይችላሉ፡፡ ቢሆንም ተረጋጋ!! እግዚአብሔርም ያረጋጋህ ዘንድ ተማጸነው። ካልተረጋጋህ ራስህን ብቻ ሳይሆን ዙሪያህ ያሉትን ሁሉ ታውካለህ፡፡ በመዋከብ የሚበተን እንጂ የሚሠበሠብ የሚሰበር እንጂ የሚጠገን የሚጎድል እንጂ የሚሞላ አንዳች የለም፡፡
ጌታችን ወደ ቤታቸው በገባ ጊዜ ሁለቱ እኅትማማች ማርያምና ማርታ ያደረጉትንና ጌታችንም የተናገረውን አስተውል፡፡ ጌታችን ወደ ቤታቸው ከገባበት ጊዜ አንሥቶ ማርታ ደፋ ቀና፤ ወጣ ገባ፤ ቁጭ ብድግ ማለት አብዝታ እጅጉን ባከነች፡፡ ማርያም ግን ተረጋግታ በመቀመጥ የጌታችንን የቃሉን ትምህርት በማድመጥ ጸናች፡፡ ማርታ የማርያም ተረጋግቶ በመቀመጥ ቃለ እግዚአብሔርን መስማት አልተዋጠላትምና "ጌታ ሆይ እኔ እንድሠራ እኅቴ ብቻዬን ስትተወኝ አይገድህምን " አለችው፡፡ ጌታችንም መልሶ "ማርታ ማርታ በብዙ ነገር ትጨነቂያለሽ ትታወኪማለሽ የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፡፡" አላት፡፡ (ሉቃ 10:40) ማርያም የምትሻውን ሁሉ ለማግኘት ተረጋጋች፤ ማርታ ግን ያላትንም ለመልቀቅና ላማጣት ባከነች፡፡ ወዳጄ ብትረጋጋ ጤናህ እስኪታወክ ደርሰህ ወዳጆችህንም እያስቀየምክ ቤተሰብህንም ጭምር ረስተህ የምትባክነው ለሚያስፈልግህ ሳይሆን ለፍላጎትህ መሆኑን ትረዳለህና ተረጋጋ፡፡
የድንግል ልጅ ቅዱስ አማኑኤል ፍጹም መረጋጋትን ያድለን!!
©️ መምህር ቢትወደድ ወርቁ
የካቲት 2 ቀን 2016 ዓ ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
የዝማሬ ሰዓት
https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆በዚህ ማስፈንጠሪያ ገብተው
" ወቅታዊ እና አዳዲስ ወረቦችን ዝማሬዎችን ከነግጥሞቻቸው እና የቤተክርስቲያናችንን ወቅታዊ ትምህርቶችን ያገኛሉ !!!!! "
ይቀላቀሉን!!!!!
https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆በዚህ ማስፈንጠሪያ ገብተው
" ወቅታዊ እና አዳዲስ ወረቦችን ዝማሬዎችን ከነግጥሞቻቸው እና የቤተክርስቲያናችንን ወቅታዊ ትምህርቶችን ያገኛሉ !!!!! "
ይቀላቀሉን!!!!!
Telegram
የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
" ወቅታዊ እና አዳዲስ ወረቦችን ዝማሬዎችን ከነግጥሞቻቸው እና የቤተክርስቲያናችንን ወቅታዊ ትምህርቶችን ያገኛሉ !!!!! "
Forwarded from Mikha Denagil ምክሐ ደናግል
MD || “ስለ እናንተ ሲያማልዱ ይናፍቁአችኋል። ” || ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Dn Henok Haile
https://youtube.com/watch?v=kcBXJ0sWoQY
https://youtube.com/watch?v=kcBXJ0sWoQY
YouTube
MD || “ስለ እናንተ ሲያማልዱ ይናፍቁአችኋል። ” || ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Dn Henok Haile
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ቴሌግራም ቻናል
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagil/?hl=en
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም የዩቱብ ቻናል
Youtube https://www.youtube.com/channel/UCIiCKAoZVHXJ2mlKGXDGyPg
የማኅበራችን…
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagil/?hl=en
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም የዩቱብ ቻናል
Youtube https://www.youtube.com/channel/UCIiCKAoZVHXJ2mlKGXDGyPg
የማኅበራችን…
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መዝሙር
የዋኅ መልአክ
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል
ታዳጊያችን ነህ ምክሩ ለልዑል
የአምላክ ኀይሉ መገለጫው ነህ
የእልፍ አእላፍ መላእክት መስፍናቸው ነህ
አዝ.........
ለሠራዊተ ሰማይ መላእክት አለቃቸው
ለፍጥረቱ ለባሕር ለየብሱ አጽንኦታቸው
የዋኅ ርኅሩህኅ መልአክ ኀዳጌ በቀል
በልመናው በጸሎቱ ያስምረናል ቅዱስ ሚካኤል
አዝ...........
የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ቅዱስ ሚካኤል
ለሰው ልጆች የምታዝን ምታማልድ ከልዑል
እነሆ ሕይወታችንን ባርክልን አደራህን
በኑሯችን ሁሉ ጠብቀን ባለን ዘመን
አዝ............
ሳለን በዓለም ዲያብሎስ እንዳይጥለን ጥንተ ጠላት
ድል አድራጊው ጠብቀን ሚካኤል ሆይ ሊቀ መላእክት
መካሬ ጽድቅ እውቀትን ሙላን ግለጥልን
በእምነት በተስፋ በፍቅር መኖርን
🛑 በዘማሪ ዳዊት ክብሩ /ዘምክሐ/ 🛑
ሙሉ ዝማሬውን በዚህ ተጭነው ይመልከቱት ይዘምሩ 👇👇👇
https://youtube.com/watch?v=mXiS3w0dARg&feature=share7
የዋኅ መልአክ
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል
ታዳጊያችን ነህ ምክሩ ለልዑል
የአምላክ ኀይሉ መገለጫው ነህ
የእልፍ አእላፍ መላእክት መስፍናቸው ነህ
አዝ.........
ለሠራዊተ ሰማይ መላእክት አለቃቸው
ለፍጥረቱ ለባሕር ለየብሱ አጽንኦታቸው
የዋኅ ርኅሩህኅ መልአክ ኀዳጌ በቀል
በልመናው በጸሎቱ ያስምረናል ቅዱስ ሚካኤል
አዝ...........
የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ቅዱስ ሚካኤል
ለሰው ልጆች የምታዝን ምታማልድ ከልዑል
እነሆ ሕይወታችንን ባርክልን አደራህን
በኑሯችን ሁሉ ጠብቀን ባለን ዘመን
አዝ............
ሳለን በዓለም ዲያብሎስ እንዳይጥለን ጥንተ ጠላት
ድል አድራጊው ጠብቀን ሚካኤል ሆይ ሊቀ መላእክት
መካሬ ጽድቅ እውቀትን ሙላን ግለጥልን
በእምነት በተስፋ በፍቅር መኖርን
🛑 በዘማሪ ዳዊት ክብሩ /ዘምክሐ/ 🛑
ሙሉ ዝማሬውን በዚህ ተጭነው ይመልከቱት ይዘምሩ 👇👇👇
https://youtube.com/watch?v=mXiS3w0dARg&feature=share7
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
YouTube
🛑አዲስ ዝማሬ "አንቺ ነሽ " ዘማሪ ዳዊት ክብሩ ◈New Mezmur "Anchi Nesh" Z Dawit Kibru (Lyrics)
መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ያመሰገነሽ፤
ወላዲተ አምላክ ድንግል አንቺ ነሽ።
የመለኮት ማደሪያ ነሽ የብርሃን ድንኳን፤
ለመላእክት እኅት መሪ የኾንሽ ለጻድቃን።
የሕዝብ ሁሉ ኸኸ እናት ኸኸ የሁሉ እመቤት፤
የዓዳም ተስፋ ስንቅ የሆንሽ የዳነብሽ ከሞት
አንቺ ነሽ /2/ ብፅዕት ኪዳነ ምሕረት፤
ለዓለም ሁሉ መዳን ምክንያት የቃል እናት ታቦት
ለዓለም ሁሉ መድኃኒት የቃልኪዳኑ ታቦት።
ወርቅ የተጎናጽፈሽ፥…
ወላዲተ አምላክ ድንግል አንቺ ነሽ።
የመለኮት ማደሪያ ነሽ የብርሃን ድንኳን፤
ለመላእክት እኅት መሪ የኾንሽ ለጻድቃን።
የሕዝብ ሁሉ ኸኸ እናት ኸኸ የሁሉ እመቤት፤
የዓዳም ተስፋ ስንቅ የሆንሽ የዳነብሽ ከሞት
አንቺ ነሽ /2/ ብፅዕት ኪዳነ ምሕረት፤
ለዓለም ሁሉ መዳን ምክንያት የቃል እናት ታቦት
ለዓለም ሁሉ መድኃኒት የቃልኪዳኑ ታቦት።
ወርቅ የተጎናጽፈሽ፥…
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
🛑አዲስ ዝማሬ🛑
"የፋርስ ኮከብ"
በዘማሪት ሰብለ ስፍር
በቅርብ ቀን ይጠብቁን !!!
"የፋርስ ኮከብ"
በዘማሪት ሰብለ ስፍር
በቅርብ ቀን ይጠብቁን !!!
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በቅርብ ቀን ይጠብቁን !!!!
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
የተከበራችሁ የቴሌግራም ቻናሌ ተከታዮቼ ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን አዲስ የከፈትኩትን የዩትዩብ ቻናሌን እንዲሁም የቲክቶክ ቻናሌን፤ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ሌሎችንም በመጋበዝ አዳዲስ ስራዎችን አገልግሎቶችንም በመከታተል አገልግሎቱን ያበረታቱልኝ ስል በእግዚአብሔር ስም እጠይቃለሁኝ እግዚአብሔር ያክብርልኝ !!! 🙏🙏🙏
Youtube - https://youtube.com/@ZemariDawitkibru2405?si=63myQkvvdUPGM8JY
Telegram - https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
Tiktok - https://www.tiktok.com/@davekb24?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram - https://www.instagram.com/dkibru402/?igshid=YTQwZjQ0NmI0OA%3D%3D
Facebook - https://www.facebook.com/deve.zman.9/
Youtube - https://youtube.com/@ZemariDawitkibru2405?si=63myQkvvdUPGM8JY
Telegram - https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
Tiktok - https://www.tiktok.com/@davekb24?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram - https://www.instagram.com/dkibru402/?igshid=YTQwZjQ0NmI0OA%3D%3D
Facebook - https://www.facebook.com/deve.zman.9/
Telegram
የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
" ወቅታዊ እና አዳዲስ ወረቦችን ዝማሬዎችን ከነግጥሞቻቸው እና የቤተክርስቲያናችንን ወቅታዊ ትምህርቶችን ያገኛሉ !!!!! "
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
❤መድኃኔዓለም❤
#"ከአዳም ጎን አንዲት አፅም መንሣት ምን ይደንቅ!? ከእርሱ ሴትን ፈጠረ።የሰው ፍጥረትንም ሁሉ ፈጠረ።ጌታ የአብ ቃል ተሰጠ።" (ቅዱስ ኤፍሬም)
#እንደ ክርስቲያን ይህንን ቃል በሐሙስ ውዳሴ ማርያም ላይ ባነበብን ቁጥር የቀራንዮ በግ መድኃኔዓለም በዕፀ መስቀል ላይ ከፍ ብሎ ተሰቅሎ ስለኛ ሲሞሸር እኛንም ሲሞሽረን እንመለከተዋለን።ጌታችን ይህንን ስቅለቱን "ክብር" በማለት ጠርቶታል።"ጌታችን ኢየሱስም መለሰላቸው እንዲህ ሲል የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ ሰዓቱ ደርሶአል።"(ዮሐ 12:23) እሰቀላለሁ እሞታለሁ ማለቱ ነው።ክብሩማ ለእኛ ነው፤ፍቅር ስለሆነ በሥጋ ማርያም ድንግል ስለተዛመድንም የእኛን ክብር የራሱ ክብር አድርጎ ተናገረ።"የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ" የሚለው አነጋገር የሰው ልጅ የተባለ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ሲከብር (ሲሰቀል)፤በእርሱ የባሕርይ አምላክነት (መድኃኒትነት) ያመኑ ሁሉ ከብረው በቀኙ እንደሚቆሙ (እንደሚድኑ) ያሳያል።ለዚህ ነው በቀኙ የተሰቀለው ወንበዴ በመድኃኒትነቱ አምኖ የዳነው።
እንዴት በዚህ ቃል የመድኃኔ ዓለምን የሙሽርነቱን በዓል እንመለከታለን? ቢሉ
#"ከአዳም ጎን አንዲት አፅም መንሣት ምን ይደንቅ!?" እውነት ነው ያለ ተረፈ ደዌ፣ያለ ሕማም፣ያለ ቁስል የሆነ ነውና ይደንቃል።ከዚህ በላይ ደዌአችንን ከመቀበል ጋር ፤ ሕማማችንን ከመሸከም ጋር ፤ ቁስላችንን ከመቁሰል ጋር የሆነ "ከዳግማዊ አዳም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጎን የንጹሕ ውኃና የትኩስ ደም መፍሰስ ምን ይደንቅ!!!?"
#"ከእርሱ ሴትን ፈጠረ" ከቀዳማዊ አዳም ጎን ከተነሣ አፅም ሴትን(ሔዋንን) በጥንተ ተፈጥሮ ፈጠረ።ዳግማዊ አዳም መድኃኒታችን ከጎኑ ባፈሰሰው ውኃና ደምም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በአዲስ ተፈጥሮ ሠራ።ሴትን ራሷ ከሆነው ወንድ እንዳስገኛት፤ቤተክርስቲያንንም ራሷ ከሆነላት ከራሱ አስገኝቷታል። አባታችን አዳም "ይህቺ አጥንት ከአጥንቴ ሥጋዋም ከሥጋዬ ነው ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል" እንዳለ፤ መድኃኔዓለምም "ይህቺ ጥምቀት ከጎኔ ከፈሰሰው ውኃ ፤ ማዕዷም ከእኔ ሥጋና ደም ነው ፤ ከእኔ ከክርስቶስ ተገኝታለችና ቤተክርስቲያን ትባል" ይላል።ሔዋን መባሏ የሕያዋን እናት በመሆኗ ነበር ፤ ቤተክርስቲያንም የሕያዋን (የክርስቲያኖች) እናት ናት።
#"የሰው ፍጥረትንም ሁሉ ፈጠረ" ከአዳምና ከሔዋን "ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት" ባለው አምላካዊ ቡራኬው የሰው ፍጥረትን ሁሉ እንደፈጠረ ፤ "ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ ስም አጥምቋቸው።" በሚለው አምላካዊ ትእዛዙ ክርስቲያኖችን ሁሉ ፈጠረ።
#"ጌታ የአብ ቃል ተሰጠ" የጌቶች ጌታ፣ ቃለ አብ ፣የዓለም መድኃኒት በሥጋ ማርያም ተገልጦ ለሕማም ፣ ለመስቀል ፣ ለሞት ተላልፎ ተሰጠልን።"ሕፃን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሰጥቶናል" እንዲል።እንዲህ ባለ መልኩ በዙፋኑ ዕፀ መስቀል ላይ ነግሦ አነገሠን፤ተሞሽሮ ሞሸረን፤ተርቦ አጠገበን፤ተጠምቶ አረካን፤ተራቁቶ አለበሰን፤ቆስሎ ፈወሰን፤ሞቶ ሕይወትን ሰጠን!!!
የመድኃኔዓለም ቸርነቱ አይለየን!!!
የመስቀሉን ፍቅር ያሳድርብን!!!
የካቲት 27/2016 ዓ.ም
ኢዮብ ክንፈ
#"ከአዳም ጎን አንዲት አፅም መንሣት ምን ይደንቅ!? ከእርሱ ሴትን ፈጠረ።የሰው ፍጥረትንም ሁሉ ፈጠረ።ጌታ የአብ ቃል ተሰጠ።" (ቅዱስ ኤፍሬም)
#እንደ ክርስቲያን ይህንን ቃል በሐሙስ ውዳሴ ማርያም ላይ ባነበብን ቁጥር የቀራንዮ በግ መድኃኔዓለም በዕፀ መስቀል ላይ ከፍ ብሎ ተሰቅሎ ስለኛ ሲሞሸር እኛንም ሲሞሽረን እንመለከተዋለን።ጌታችን ይህንን ስቅለቱን "ክብር" በማለት ጠርቶታል።"ጌታችን ኢየሱስም መለሰላቸው እንዲህ ሲል የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ ሰዓቱ ደርሶአል።"(ዮሐ 12:23) እሰቀላለሁ እሞታለሁ ማለቱ ነው።ክብሩማ ለእኛ ነው፤ፍቅር ስለሆነ በሥጋ ማርያም ድንግል ስለተዛመድንም የእኛን ክብር የራሱ ክብር አድርጎ ተናገረ።"የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ" የሚለው አነጋገር የሰው ልጅ የተባለ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ሲከብር (ሲሰቀል)፤በእርሱ የባሕርይ አምላክነት (መድኃኒትነት) ያመኑ ሁሉ ከብረው በቀኙ እንደሚቆሙ (እንደሚድኑ) ያሳያል።ለዚህ ነው በቀኙ የተሰቀለው ወንበዴ በመድኃኒትነቱ አምኖ የዳነው።
እንዴት በዚህ ቃል የመድኃኔ ዓለምን የሙሽርነቱን በዓል እንመለከታለን? ቢሉ
#"ከአዳም ጎን አንዲት አፅም መንሣት ምን ይደንቅ!?" እውነት ነው ያለ ተረፈ ደዌ፣ያለ ሕማም፣ያለ ቁስል የሆነ ነውና ይደንቃል።ከዚህ በላይ ደዌአችንን ከመቀበል ጋር ፤ ሕማማችንን ከመሸከም ጋር ፤ ቁስላችንን ከመቁሰል ጋር የሆነ "ከዳግማዊ አዳም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጎን የንጹሕ ውኃና የትኩስ ደም መፍሰስ ምን ይደንቅ!!!?"
#"ከእርሱ ሴትን ፈጠረ" ከቀዳማዊ አዳም ጎን ከተነሣ አፅም ሴትን(ሔዋንን) በጥንተ ተፈጥሮ ፈጠረ።ዳግማዊ አዳም መድኃኒታችን ከጎኑ ባፈሰሰው ውኃና ደምም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በአዲስ ተፈጥሮ ሠራ።ሴትን ራሷ ከሆነው ወንድ እንዳስገኛት፤ቤተክርስቲያንንም ራሷ ከሆነላት ከራሱ አስገኝቷታል። አባታችን አዳም "ይህቺ አጥንት ከአጥንቴ ሥጋዋም ከሥጋዬ ነው ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል" እንዳለ፤ መድኃኔዓለምም "ይህቺ ጥምቀት ከጎኔ ከፈሰሰው ውኃ ፤ ማዕዷም ከእኔ ሥጋና ደም ነው ፤ ከእኔ ከክርስቶስ ተገኝታለችና ቤተክርስቲያን ትባል" ይላል።ሔዋን መባሏ የሕያዋን እናት በመሆኗ ነበር ፤ ቤተክርስቲያንም የሕያዋን (የክርስቲያኖች) እናት ናት።
#"የሰው ፍጥረትንም ሁሉ ፈጠረ" ከአዳምና ከሔዋን "ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት" ባለው አምላካዊ ቡራኬው የሰው ፍጥረትን ሁሉ እንደፈጠረ ፤ "ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ ስም አጥምቋቸው።" በሚለው አምላካዊ ትእዛዙ ክርስቲያኖችን ሁሉ ፈጠረ።
#"ጌታ የአብ ቃል ተሰጠ" የጌቶች ጌታ፣ ቃለ አብ ፣የዓለም መድኃኒት በሥጋ ማርያም ተገልጦ ለሕማም ፣ ለመስቀል ፣ ለሞት ተላልፎ ተሰጠልን።"ሕፃን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሰጥቶናል" እንዲል።እንዲህ ባለ መልኩ በዙፋኑ ዕፀ መስቀል ላይ ነግሦ አነገሠን፤ተሞሽሮ ሞሸረን፤ተርቦ አጠገበን፤ተጠምቶ አረካን፤ተራቁቶ አለበሰን፤ቆስሎ ፈወሰን፤ሞቶ ሕይወትን ሰጠን!!!
የመድኃኔዓለም ቸርነቱ አይለየን!!!
የመስቀሉን ፍቅር ያሳድርብን!!!
የካቲት 27/2016 ዓ.ም
ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
❤ #በዓለ_ወልድ❤
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።የሚኰንንስ ማንነው?የሞተው ይልቁንም በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፤ደግሞም ስለኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።" (ሮሜ 8:34)
ይህ የብርሃነ ዓለም የቅዱስ ጳውሎስ ቃል የቅድስት ቤተክርስትያናችን የሃይማኖት ጸሎት ነው።
በቅድስት ቤተክርስቲያን የምናምነውን እንጸልያለን፤ የምንጸልየውን እናምናለን።በሌላ አነጋገር ሃይማኖታችንን እንጸልየዋለን ፤ ጸሎታችንም ሃይማኖታችን ነው።ሃይማኖት በእግዚአብሔር ማመን፤በእርሱ መታመን ፤ እርሱንም ብቻ ተስፋ ማድረግ ነው።ሃይማኖታችን ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።ሃይማኖትን የሰጠንም እግዚአብሔር ነው።"ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት" እንዲል (ይሁዳ 1:3)።በመሆኑም ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ሃይማኖት ( በእርሱ ማመንን ) ለሰጠን ለእርሱ በጸሎት መልክ እናቀርበዋለን።ይህንንም የምናደርገው እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን ነገር ፍለጋ ነው።"ያለ ሃይማኖት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም"ና (ዕብ 11:6)።
በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ የተመሠረተች የማዕዘኗ ራስ ድንጋይም ኢየሱስ ክርስቶስ የሆነላት (ኤፌ 2:20) ቅድስት ቤተክርስቲያን የሐዋርያው ሃይማኖት ሃይማኖቷ ነውና ትጸልየዋለች።የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይህንን እንዴት እንደምትጸልየው ከመመልከታችን በፊት የቃሉን መልእክት በአጭሩ እንመልከት።
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው" ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "ምስለ ጻድቅ ትጸድቅ" (ከጻድቅ ጋር ጻድቅ ትሆናለህ) ማለትም ለጻድቅ የጽድቁን ዋጋ ትሰጠዋለህ(መዝ 17:25) በማለት እንደተናገረው ለጻድቃን ጽድቃቸውን መስክሮ ዋጋቸው መንግሥተሰማያትን ሰጥቶ የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።
"የሚኰንንስ ማንነው?" አልመለስ የሚሉትን በሥጋ የሚቀስፋቸው በነፍስ የሚፈርድባቸው ማን ነው? አንድም በርቱዕ ፍርዱ ሥጋንም ነፍስንም በአንድነት በገሃነም የሚቀጣ ማንነው?(ማቴ 10:28)
"የሞተው" በዕፀ መስቀል ላይ ቅዱስ ሥጋውን ከክብርት ነፍሱ በመልካም ፈቃዱ የለየው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በሞቱ ጊዜም ፈርዷል።በቀኙ የተሰቀለውን ሲያጸድቀው (የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነውና) በግራው የተሰቀለውን ኰንኖታል።ሞቱም መፋረጃ ነው፤በሞቱ ያመኑ ሲድኑ ያላመኑት ግን ይኰነናሉ።
"ይልቁንም ከሙታን ተለይቶ የተነሣው" በኩረ ትንሣኤአችን ሆኖ በባሕርይ ሥልጣኑ ከሞት የተነሣው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በትንሣኤውም ጊዜ ፈርዷል።"እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ።የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው፤ጠላቶቹን በኋላቸው መታቸው የዘለዓለምን ኀሣር ሰጣቸው።"(መዝ 77:65-66) ተብሎ እንደተነገረ የትንሣኤው ተቃዋሚ የሆኑትን አይሁድን፣መናፍቃንንና አጋንንትን ሲፈርድባቸው በአንጻሩ ትንሣኤውን በፍጹም ልባቸው ያመኑትን ሐዋርያትን እስከ ምድር ዳር ድረስ የትንሣኤው ምስክሮች አድርጓቸዋል(ሐዋ 1:8 ና 21-22)የጌታ ትንሣኤውም መፋረጃ ነው።በትንሣኤው ያመኑት ሲድኑ ያላመኑት ግን ይፈረድባቸዋልና።
"በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው" በእግዚአብሔርነቱ ሥልጣን የሚኖር አንድም በአምላክነቱ ከአባቱ እኩል የሆነው ንጉሣችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።እንግዲህ እግዚአብሔር ከሆነ ሥራው ምንድንነው መሥራት መቅጻት፣ማምሸት ማንጋት፣መግደል ማዳን፣ማጽደቅ መኰነን፤ሥነፍጥረትን ሁሉ ማስተዳደር ነው።ይህ ሁሉ የፍርድ ሥራ ይባላል።ሞቱም ትንሣኤውም መፋራጃ የሆነው ከእርሱ ፈራጅነት (እግዚአብሔርነት ) የተነሣ ነው።
"ስለኛ የሚማልደው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" አንድ ጊዜ ፈጽሞ ባቀረባት የዘለዓለማዊ ክህነት አገልግሎት (ለዘለዓለም የሚሆን መሥዋዕት አቅራቢነት) ያዳነን ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።"የሚማልደው" የሚለው ቃል በትንቢት አንቀጽ (future tense) ቢጻፍም የሚገልጸው ግን የተፈጸመን ድርጊት ነው።እንዲህ ያሉ አገላለጾች በቅዱሳት መፃሕፍት ይገኛሉ።ለምሳሌ"ሕፃን ተወልዶልናልና" ተብሎ የተነገረው ወደፊት ስለሚወለደው አምላካችን ነው።"እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዓት አንተ ለዘለዓለም ካህን ነህ"(መዝ 109:4) ተብሎ የተነገረለት አምላካችን የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅ ይፈርድ እንደነበር ለዘለዓለሙ የሚፈርድ ነው።ይህች የክህነት አገልግሎቱም መፋረጃ ናት።በዚህ የዘለዓለም ክህነት አገልግሎቱ የሠዋውን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የተቀበለ ሲድን ያልተቀበለ ግን ይፈረድበታልና። ይህ ሁሉ በጥቅሉ የሚያጸድቅም የሚኰንንም እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ማለት ነው።ሞቱም፣ትንሣኤውም፣ዳግም ምጽአቱም በቅድስት ቤተክርስቲያን በዓላተ ወልድ (የወልድ በዓላት) ናቸው።
የካቲት 29/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።የሚኰንንስ ማንነው?የሞተው ይልቁንም በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፤ደግሞም ስለኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።" (ሮሜ 8:34)
ይህ የብርሃነ ዓለም የቅዱስ ጳውሎስ ቃል የቅድስት ቤተክርስትያናችን የሃይማኖት ጸሎት ነው።
በቅድስት ቤተክርስቲያን የምናምነውን እንጸልያለን፤ የምንጸልየውን እናምናለን።በሌላ አነጋገር ሃይማኖታችንን እንጸልየዋለን ፤ ጸሎታችንም ሃይማኖታችን ነው።ሃይማኖት በእግዚአብሔር ማመን፤በእርሱ መታመን ፤ እርሱንም ብቻ ተስፋ ማድረግ ነው።ሃይማኖታችን ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።ሃይማኖትን የሰጠንም እግዚአብሔር ነው።"ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት" እንዲል (ይሁዳ 1:3)።በመሆኑም ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ሃይማኖት ( በእርሱ ማመንን ) ለሰጠን ለእርሱ በጸሎት መልክ እናቀርበዋለን።ይህንንም የምናደርገው እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን ነገር ፍለጋ ነው።"ያለ ሃይማኖት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም"ና (ዕብ 11:6)።
በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ የተመሠረተች የማዕዘኗ ራስ ድንጋይም ኢየሱስ ክርስቶስ የሆነላት (ኤፌ 2:20) ቅድስት ቤተክርስቲያን የሐዋርያው ሃይማኖት ሃይማኖቷ ነውና ትጸልየዋለች።የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይህንን እንዴት እንደምትጸልየው ከመመልከታችን በፊት የቃሉን መልእክት በአጭሩ እንመልከት።
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው" ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "ምስለ ጻድቅ ትጸድቅ" (ከጻድቅ ጋር ጻድቅ ትሆናለህ) ማለትም ለጻድቅ የጽድቁን ዋጋ ትሰጠዋለህ(መዝ 17:25) በማለት እንደተናገረው ለጻድቃን ጽድቃቸውን መስክሮ ዋጋቸው መንግሥተሰማያትን ሰጥቶ የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።
"የሚኰንንስ ማንነው?" አልመለስ የሚሉትን በሥጋ የሚቀስፋቸው በነፍስ የሚፈርድባቸው ማን ነው? አንድም በርቱዕ ፍርዱ ሥጋንም ነፍስንም በአንድነት በገሃነም የሚቀጣ ማንነው?(ማቴ 10:28)
"የሞተው" በዕፀ መስቀል ላይ ቅዱስ ሥጋውን ከክብርት ነፍሱ በመልካም ፈቃዱ የለየው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በሞቱ ጊዜም ፈርዷል።በቀኙ የተሰቀለውን ሲያጸድቀው (የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነውና) በግራው የተሰቀለውን ኰንኖታል።ሞቱም መፋረጃ ነው፤በሞቱ ያመኑ ሲድኑ ያላመኑት ግን ይኰነናሉ።
"ይልቁንም ከሙታን ተለይቶ የተነሣው" በኩረ ትንሣኤአችን ሆኖ በባሕርይ ሥልጣኑ ከሞት የተነሣው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በትንሣኤውም ጊዜ ፈርዷል።"እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ።የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው፤ጠላቶቹን በኋላቸው መታቸው የዘለዓለምን ኀሣር ሰጣቸው።"(መዝ 77:65-66) ተብሎ እንደተነገረ የትንሣኤው ተቃዋሚ የሆኑትን አይሁድን፣መናፍቃንንና አጋንንትን ሲፈርድባቸው በአንጻሩ ትንሣኤውን በፍጹም ልባቸው ያመኑትን ሐዋርያትን እስከ ምድር ዳር ድረስ የትንሣኤው ምስክሮች አድርጓቸዋል(ሐዋ 1:8 ና 21-22)የጌታ ትንሣኤውም መፋረጃ ነው።በትንሣኤው ያመኑት ሲድኑ ያላመኑት ግን ይፈረድባቸዋልና።
"በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው" በእግዚአብሔርነቱ ሥልጣን የሚኖር አንድም በአምላክነቱ ከአባቱ እኩል የሆነው ንጉሣችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።እንግዲህ እግዚአብሔር ከሆነ ሥራው ምንድንነው መሥራት መቅጻት፣ማምሸት ማንጋት፣መግደል ማዳን፣ማጽደቅ መኰነን፤ሥነፍጥረትን ሁሉ ማስተዳደር ነው።ይህ ሁሉ የፍርድ ሥራ ይባላል።ሞቱም ትንሣኤውም መፋራጃ የሆነው ከእርሱ ፈራጅነት (እግዚአብሔርነት ) የተነሣ ነው።
"ስለኛ የሚማልደው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" አንድ ጊዜ ፈጽሞ ባቀረባት የዘለዓለማዊ ክህነት አገልግሎት (ለዘለዓለም የሚሆን መሥዋዕት አቅራቢነት) ያዳነን ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።"የሚማልደው" የሚለው ቃል በትንቢት አንቀጽ (future tense) ቢጻፍም የሚገልጸው ግን የተፈጸመን ድርጊት ነው።እንዲህ ያሉ አገላለጾች በቅዱሳት መፃሕፍት ይገኛሉ።ለምሳሌ"ሕፃን ተወልዶልናልና" ተብሎ የተነገረው ወደፊት ስለሚወለደው አምላካችን ነው።"እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዓት አንተ ለዘለዓለም ካህን ነህ"(መዝ 109:4) ተብሎ የተነገረለት አምላካችን የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅ ይፈርድ እንደነበር ለዘለዓለሙ የሚፈርድ ነው።ይህች የክህነት አገልግሎቱም መፋረጃ ናት።በዚህ የዘለዓለም ክህነት አገልግሎቱ የሠዋውን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የተቀበለ ሲድን ያልተቀበለ ግን ይፈረድበታልና። ይህ ሁሉ በጥቅሉ የሚያጸድቅም የሚኰንንም እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ማለት ነው።ሞቱም፣ትንሣኤውም፣ዳግም ምጽአቱም በቅድስት ቤተክርስቲያን በዓላተ ወልድ (የወልድ በዓላት) ናቸው።
የካቲት 29/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ