Forwarded from Mikha Denagil ምክሐ ደናግል
YouTube
' አትድከሚ ኢትዮጵያ " በዘማሪ ክብሮም ግዳይ | zemari kibrom giday | Atdekmi ethiopia | mahtot tube | new mezmur
አዲስ ዝማሬ ' አትድከሚ ኢትዮጵያ " በዘማሪ ክብሮም ግዳይ
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ቴሌግራም ቻናል
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagi...
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም የዩቱብ ቻናል
Youtube https://www.youtube.com/…
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ቴሌግራም ቻናል
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagi...
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም የዩቱብ ቻናል
Youtube https://www.youtube.com/…
"የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ።"(1ኛ ዮሐ 3:9)
ቅድስት ቤተክርስቲያን የክርስቲያኖች ጉባኤ ናት።ይህቺ ጉባኤ ደግሞ ለጌታዋ ለኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽሪት ናት።የሚስት ፈቃድ ወደ ባልዋ እንደሆነ ሁሉ የቅድስት ቤተክርስቲያን ፈቃድም ሙሽራዋ ወደ ሆነው ወደ ጌታዋ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።የእርሱን ፍለጋ እየተከተለች ፤ የእርሱን ዱካ እየረገጠች ፤ እርሱ ከገባበት ትገባለች።ይህንን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስንና የቅድስት ቤተክርስቲያንን ግንኙነት በራስና በአካል መግለጥም ይቻላል።ራስ(አእምሮ) አካልን እንደሚያዝዝ ፤ክርስቶስም ቅድስት ቤተክርስቲያንን ያዝዛታል።አካልም ለራስ (ለአእምሮ) እንደሚታዘዝ እንዲሁ ቅድስት ቤተክርስቲያንም ለራሷ ለኢየሱስ ክርስቶስ ትታዘዛለች።እርሱ ካዘዛትና ፤ ሠርቶ ካሳያት ፤ ከእርሱ ፈቃድ ውጪም የምታደርገው አንዳች ነገር የለም።አምላካችን ፈጽሞ ካስተማራት ትምህርት ሌላ እንግዳ ትምህርት ፤ ሠርቶ ካሳያትም ትሩፋት ውጪ የምትሠራ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን የለችም።
ጌታችን የፈጸማቸው ሥራዎች ሁሉ ዓላማቸው የዲያብሎስን ሥራ ማፍረስና እኛን ማዳን ነው።በሥጋ ማርያም ድንግል ተገልጦ ከፈጸማቸው ሥራዎች መካከል የሰውን መዳን የማይመለከት ምንም የለም።ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ ፤ እኛንም እንዲያድን ከፈጸማቸው ሥራዎች መካከል አንዱ ጾም ነው።
"ከዚያ ወዲያ ጌታችን ኢየሱስ ከዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው" : ከጥምቀቱ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ በሚሆን ፈቃዱ ወደ ገዳመ ቆሮንጦስ ገብቷል።በገዛ ፈቃዱ ተመርቶ የጠፋ አዳምን ፍለጋ ያድነው ዘንድ በፈቃዱ ወደ ገዳመ ቆሮንጦስ ገባ።"ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ" ማለቱም ቀዳማዊ አዳም ከዲያብሎስ ተፈትኖ የወደቀባቸውን ፈተናዎች ድል ይነሣ ዘንድ ነው።እርሱ ከጥምቀቱ በኋላ በሦስቱ አርእስተ ኃጣውእ (የኃጢአት ራሶች)ተፈትኖና ድል ነሥቶ የጥምቀት ልጆች ሁላችን እነዚህ ፈተናዎች እንዳሉብንና ድል መንሣት እንደምንችል ነገረን ። "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ።ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ" እንዳለው (ዮሐ 16:33)
"አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ" : ዘመን የማይቆጥርለት አምላክ እኛን ዘመን በማይቆጠርባት መንግሥተ ሰማያት ያኖረን ዘንድ አርባ ተብሎ ጊዜ ተቆጠረለት።በአርባ ቀን ያገኛትን ልጅነት አዳም አስወስዶ ነበርና ለሱ ለመካስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጦመ ።"ለፀሐይ ቀንን ያስገዛው ለጨረቃና ለከዋክብትም ሌሊትን ያስገዛቸው"(መዝ 135:8 ና 9) አምላክ ቀንና ሌሊት ጦመ።አዳም በመብል ቢወድቅ ጌታችን ግን በጾም አነሣው።በሥጋ የተራቡትን በተአምራት በነፍስ የተራቡትን በትምህርት የሚያጠግብ እርሱ በጽድቅ ያጠግበን ዘንድ ተራበ።
"ፈታኝም ቀርቦ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው" : ፈቅዶለት ነው እንጂ ዲያቢሎስማ ይህንን ያህል ድፍረት አይደፍርም ነበር።የእግዚአብሔር ባሕርይ ልጅ በዚህ ስስት ከመፈተኑ በፊት የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆቹ አዳምና ሔዋን ተፈትነው ነበር።በዚህ የስስት ፈተና "ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።"(ዘፍ 3:6) ዳግማዊ አዳም ኢየሱስ ክርስቶስ ግን፦
"ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።"
ጌታችን ይህንን የስስት ፈተና በትሕርምት ድል ነሥቶ የዲያቢሎስን ሐሳብና ሥራ አፈረሰ።የዲያቢሎስ ሐሳቡ የክርስቶስን "የእግዚአብሔር ልጅነቱን" ማረጋገጥና ዓለም እንዳይድን በአይሁድ እንዳይሰቀል ማከላከል ሲሆን ሥራው ደግሞ ስስት ነው።ጌታችን ድንጋዮቹን እንጀራ ቢያደርግለት ኖሮ፤የኋላ መናፍቃን ተነሥተው እንደ ጌታ የሰይጣንን ቃል መፈጸም ይገባል ባሉ ነበር ። አዳም የሚኖረው "ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል" ነበር ። ይህቺውም ትእዛዙ ናት።"መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና" (ዘፍ 2:17) ባለው ትእዛዝ ። አዳም ይህቺን ትእዛዝ ቢጠብቅ በሕይወት ይኖር ነበር።"ተብሎ ተጽፎአል"(ዘዳ 8:3) የሚለው አነጋገር ሰይጣን በቃለ መፃሕፍት እንደሚሸነፍ የሚያረጋግጥ ነው።
ስስት የሚበላውን፣የሚጠጣውን፣የሚለበሰውን እጅግ መውደድ (መሳሳት) ነው።ለሚያልፈው የዓለም ነገር ሁሉ መጎምጀት ስስት ነው።ይህንን ፈተና ልክ እንደ ጌታችን በትሕርምት ድል መንሣት ይጠበቅብናል።ሁልጊዜም ቢሆን ስስትን የምናሸንፈው "ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣውን ቃል ሁሉ" በማሰብ ነው።ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃልም፦
የመጀመሪያው በነፍስ የተራቡትን የሚያጠግብ የቅዱስ ወንጌል ትምህርት ነው።ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ "ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ነፍስ ከመብል ሰውነትስ ከልብስ አይበልጥምን?" በማለት አስተምሯል (ማቴ 6:25) እኔን የምትመስልን ነፍስ ካለመኖር ፈጥሬ ከሰጠኋችሁ ለጥቂት ጊዜ ነፍሳችሁ ከሥጋ ጋር ተዋሕዳ የምትቆይበትን መብል እንዴት እነሣችኋለሁ?፤ሥጋን ከአራቱ ባሕርያት ፈጥሬ ከሰጠኋችሁ ሥጋችሁ የሚለብሰውን አላቂ ልብስ እንዴት እነሣችኋለሁ? ማለቱ ነው።ይህም ብቻ አይደለም ለሰውነታችሁ ቤዛ የሚሆን ቅዱስ ሥጋዬን ክቡር ደሜን ከሰጣኋችሁ ፤ በመንግሥተ ሰማያትም የብርሃን ልብስን ካዘጋጀሁላችሁ ለሥጋችሁ የሚሆን መብልና ልብስን እንዴት እነሣችኋለሁ? ማለቱ ነው። እውነት ነው እጅግ ትልቁን የሰጠንን አምላክ በጥቂቱ የምንጠረጥረው ብዙዎች ነን።የጌታችን ተወዳጁ የሚሆን ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስም "ዓለምንና በዓለም ያለውን አትውደዱ፤ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት..." በማለት በስስት እንዳንሸነፍ መክሮናል።(1ኛ ዮሐ 2:15)
ስስትን "ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል" (ጌታችን ስለጾምና ምጽዋት ባስተማራት ትምህርት) ድል እናደርገዋለን ። " ስትጦሙም፥ እንደ ግብዞች አትጠውልጉ፤ ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠፋሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።አንተ ግን ስትጦም፥ በስውር ላለው አባትህ እንጂ እንደ ጦመኛ ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፊትህንም ታጠብ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።"(ማቴ 6:16) እኛ ያልሳሳንለትን መብልንና ልብስንም ለሌላቸው መስጠት አለብን።በዚህም ጾም ከምጽዋት ጋር ትተባበራለች።
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" ተአምር ነው።ስለዚህ ሰው በእግዚአብሔር ተአምር ጭምር እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም።ጌታችን በዘመነ ኤልያስ በነቢዩ ኤልያስ አድሮ በሰራፕታ ለነበረችው ባልቴት ጥቂቱን ዘይትና እፍኙን ዱቄት እንዳበረከተ እንዲሁ በዘመነ ሐዲስም ሁለት ዓሦችንና አምስት እንጀራዎችን አበርክቶ በተአምር አምስት ሺ ገበያ ሕዝብ አጥግቧል(1ኛ ነገ 17:7-17)።ራሱ ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስም የኖረው በእግዚአብሔር ተአምር ነው።"የእግዚአብሔርም ቃል እንዲህ ሲል ለእርሱ መጣለት።ከዚህ ተነሥተህ ወደ ምሥራቅ ሂድ፥ በዮርዳኖስም ትይዩ ባለው በኮራት ፈፋ ውስጥ ተሸሸግ።ከወንዙም ትጠጣለህ፥ ቍራዎችም በዚያ ይመግቡህ ዘንድ አዝዣለሁ። ሄደም እንደ እግዚአብሔር ቃልም አደረገ። ሄዶም በዮርዳኖስ ትይዩ ባለው በኮራት ፈፋ ውስጥ ተቀመጠ። ቍራዎቹ በየጥዋትና በየማታው እንጀራና ሥጋ ያመጡለት ነበር፤ ከወንዙም
ቅድስት ቤተክርስቲያን የክርስቲያኖች ጉባኤ ናት።ይህቺ ጉባኤ ደግሞ ለጌታዋ ለኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽሪት ናት።የሚስት ፈቃድ ወደ ባልዋ እንደሆነ ሁሉ የቅድስት ቤተክርስቲያን ፈቃድም ሙሽራዋ ወደ ሆነው ወደ ጌታዋ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።የእርሱን ፍለጋ እየተከተለች ፤ የእርሱን ዱካ እየረገጠች ፤ እርሱ ከገባበት ትገባለች።ይህንን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስንና የቅድስት ቤተክርስቲያንን ግንኙነት በራስና በአካል መግለጥም ይቻላል።ራስ(አእምሮ) አካልን እንደሚያዝዝ ፤ክርስቶስም ቅድስት ቤተክርስቲያንን ያዝዛታል።አካልም ለራስ (ለአእምሮ) እንደሚታዘዝ እንዲሁ ቅድስት ቤተክርስቲያንም ለራሷ ለኢየሱስ ክርስቶስ ትታዘዛለች።እርሱ ካዘዛትና ፤ ሠርቶ ካሳያት ፤ ከእርሱ ፈቃድ ውጪም የምታደርገው አንዳች ነገር የለም።አምላካችን ፈጽሞ ካስተማራት ትምህርት ሌላ እንግዳ ትምህርት ፤ ሠርቶ ካሳያትም ትሩፋት ውጪ የምትሠራ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን የለችም።
ጌታችን የፈጸማቸው ሥራዎች ሁሉ ዓላማቸው የዲያብሎስን ሥራ ማፍረስና እኛን ማዳን ነው።በሥጋ ማርያም ድንግል ተገልጦ ከፈጸማቸው ሥራዎች መካከል የሰውን መዳን የማይመለከት ምንም የለም።ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ ፤ እኛንም እንዲያድን ከፈጸማቸው ሥራዎች መካከል አንዱ ጾም ነው።
"ከዚያ ወዲያ ጌታችን ኢየሱስ ከዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው" : ከጥምቀቱ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ በሚሆን ፈቃዱ ወደ ገዳመ ቆሮንጦስ ገብቷል።በገዛ ፈቃዱ ተመርቶ የጠፋ አዳምን ፍለጋ ያድነው ዘንድ በፈቃዱ ወደ ገዳመ ቆሮንጦስ ገባ።"ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ" ማለቱም ቀዳማዊ አዳም ከዲያብሎስ ተፈትኖ የወደቀባቸውን ፈተናዎች ድል ይነሣ ዘንድ ነው።እርሱ ከጥምቀቱ በኋላ በሦስቱ አርእስተ ኃጣውእ (የኃጢአት ራሶች)ተፈትኖና ድል ነሥቶ የጥምቀት ልጆች ሁላችን እነዚህ ፈተናዎች እንዳሉብንና ድል መንሣት እንደምንችል ነገረን ። "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ።ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ" እንዳለው (ዮሐ 16:33)
"አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ" : ዘመን የማይቆጥርለት አምላክ እኛን ዘመን በማይቆጠርባት መንግሥተ ሰማያት ያኖረን ዘንድ አርባ ተብሎ ጊዜ ተቆጠረለት።በአርባ ቀን ያገኛትን ልጅነት አዳም አስወስዶ ነበርና ለሱ ለመካስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጦመ ።"ለፀሐይ ቀንን ያስገዛው ለጨረቃና ለከዋክብትም ሌሊትን ያስገዛቸው"(መዝ 135:8 ና 9) አምላክ ቀንና ሌሊት ጦመ።አዳም በመብል ቢወድቅ ጌታችን ግን በጾም አነሣው።በሥጋ የተራቡትን በተአምራት በነፍስ የተራቡትን በትምህርት የሚያጠግብ እርሱ በጽድቅ ያጠግበን ዘንድ ተራበ።
"ፈታኝም ቀርቦ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው" : ፈቅዶለት ነው እንጂ ዲያቢሎስማ ይህንን ያህል ድፍረት አይደፍርም ነበር።የእግዚአብሔር ባሕርይ ልጅ በዚህ ስስት ከመፈተኑ በፊት የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆቹ አዳምና ሔዋን ተፈትነው ነበር።በዚህ የስስት ፈተና "ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።"(ዘፍ 3:6) ዳግማዊ አዳም ኢየሱስ ክርስቶስ ግን፦
"ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።"
ጌታችን ይህንን የስስት ፈተና በትሕርምት ድል ነሥቶ የዲያቢሎስን ሐሳብና ሥራ አፈረሰ።የዲያቢሎስ ሐሳቡ የክርስቶስን "የእግዚአብሔር ልጅነቱን" ማረጋገጥና ዓለም እንዳይድን በአይሁድ እንዳይሰቀል ማከላከል ሲሆን ሥራው ደግሞ ስስት ነው።ጌታችን ድንጋዮቹን እንጀራ ቢያደርግለት ኖሮ፤የኋላ መናፍቃን ተነሥተው እንደ ጌታ የሰይጣንን ቃል መፈጸም ይገባል ባሉ ነበር ። አዳም የሚኖረው "ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል" ነበር ። ይህቺውም ትእዛዙ ናት።"መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና" (ዘፍ 2:17) ባለው ትእዛዝ ። አዳም ይህቺን ትእዛዝ ቢጠብቅ በሕይወት ይኖር ነበር።"ተብሎ ተጽፎአል"(ዘዳ 8:3) የሚለው አነጋገር ሰይጣን በቃለ መፃሕፍት እንደሚሸነፍ የሚያረጋግጥ ነው።
ስስት የሚበላውን፣የሚጠጣውን፣የሚለበሰውን እጅግ መውደድ (መሳሳት) ነው።ለሚያልፈው የዓለም ነገር ሁሉ መጎምጀት ስስት ነው።ይህንን ፈተና ልክ እንደ ጌታችን በትሕርምት ድል መንሣት ይጠበቅብናል።ሁልጊዜም ቢሆን ስስትን የምናሸንፈው "ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣውን ቃል ሁሉ" በማሰብ ነው።ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃልም፦
የመጀመሪያው በነፍስ የተራቡትን የሚያጠግብ የቅዱስ ወንጌል ትምህርት ነው።ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ "ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ነፍስ ከመብል ሰውነትስ ከልብስ አይበልጥምን?" በማለት አስተምሯል (ማቴ 6:25) እኔን የምትመስልን ነፍስ ካለመኖር ፈጥሬ ከሰጠኋችሁ ለጥቂት ጊዜ ነፍሳችሁ ከሥጋ ጋር ተዋሕዳ የምትቆይበትን መብል እንዴት እነሣችኋለሁ?፤ሥጋን ከአራቱ ባሕርያት ፈጥሬ ከሰጠኋችሁ ሥጋችሁ የሚለብሰውን አላቂ ልብስ እንዴት እነሣችኋለሁ? ማለቱ ነው።ይህም ብቻ አይደለም ለሰውነታችሁ ቤዛ የሚሆን ቅዱስ ሥጋዬን ክቡር ደሜን ከሰጣኋችሁ ፤ በመንግሥተ ሰማያትም የብርሃን ልብስን ካዘጋጀሁላችሁ ለሥጋችሁ የሚሆን መብልና ልብስን እንዴት እነሣችኋለሁ? ማለቱ ነው። እውነት ነው እጅግ ትልቁን የሰጠንን አምላክ በጥቂቱ የምንጠረጥረው ብዙዎች ነን።የጌታችን ተወዳጁ የሚሆን ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስም "ዓለምንና በዓለም ያለውን አትውደዱ፤ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት..." በማለት በስስት እንዳንሸነፍ መክሮናል።(1ኛ ዮሐ 2:15)
ስስትን "ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል" (ጌታችን ስለጾምና ምጽዋት ባስተማራት ትምህርት) ድል እናደርገዋለን ። " ስትጦሙም፥ እንደ ግብዞች አትጠውልጉ፤ ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠፋሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።አንተ ግን ስትጦም፥ በስውር ላለው አባትህ እንጂ እንደ ጦመኛ ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፊትህንም ታጠብ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።"(ማቴ 6:16) እኛ ያልሳሳንለትን መብልንና ልብስንም ለሌላቸው መስጠት አለብን።በዚህም ጾም ከምጽዋት ጋር ትተባበራለች።
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" ተአምር ነው።ስለዚህ ሰው በእግዚአብሔር ተአምር ጭምር እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም።ጌታችን በዘመነ ኤልያስ በነቢዩ ኤልያስ አድሮ በሰራፕታ ለነበረችው ባልቴት ጥቂቱን ዘይትና እፍኙን ዱቄት እንዳበረከተ እንዲሁ በዘመነ ሐዲስም ሁለት ዓሦችንና አምስት እንጀራዎችን አበርክቶ በተአምር አምስት ሺ ገበያ ሕዝብ አጥግቧል(1ኛ ነገ 17:7-17)።ራሱ ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስም የኖረው በእግዚአብሔር ተአምር ነው።"የእግዚአብሔርም ቃል እንዲህ ሲል ለእርሱ መጣለት።ከዚህ ተነሥተህ ወደ ምሥራቅ ሂድ፥ በዮርዳኖስም ትይዩ ባለው በኮራት ፈፋ ውስጥ ተሸሸግ።ከወንዙም ትጠጣለህ፥ ቍራዎችም በዚያ ይመግቡህ ዘንድ አዝዣለሁ። ሄደም እንደ እግዚአብሔር ቃልም አደረገ። ሄዶም በዮርዳኖስ ትይዩ ባለው በኮራት ፈፋ ውስጥ ተቀመጠ። ቍራዎቹ በየጥዋትና በየማታው እንጀራና ሥጋ ያመጡለት ነበር፤ ከወንዙም
ይጠጣ ነበር።(1ኛ ነገ 17:2-6) በጥቂት ብቻ በእግዚአብሔር ተአምር የኖሩ ቅዱሳን ብዙ ናቸው።በተለይም ርእሰ ባሕታውያን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ናቸው።562 ዓመት ሙሉ የእናታቸውን ጡት ጨምሮ ያለ ምግብ ፣ ያለ ልብስና ያለ መጠለያ በጾምና በጸሎት ያውም ከብዙ ሺ ስግደቶችና ተጋድሎዎች ጋር ተጸምዶ መኖር ያልተደነቀ ምን ይደነቃል!?ይኸውም የሆነው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል (በተአምር) ነው እንጂ በሌላ አይደለም።እግዚአብሔር "ይሁን" ያለው ይሆናል፤"ይሁን" ያላለውም አይሆንምና።በተፈጥሮ ለሰው ምግብ እንዲያስፈልገው ያደረገ አምላክ እንዳያስፈልገውም ማድረግ ይችላል።አሁንም ቢሆን በጥቂት ብቻ በበረከቱ የሚያኖራቸው ደጋግ ክርስቲያኖች ሞልተዋል።
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" አካላዊ ቃል ወልደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።ስለዚህ በእርሱ በማመን በሃይማኖት በር ገብተን፤በቀጠነችው መንገድ በፈቃደ ነፍስ ተጉዘን፤ሕይወት የሆነው እርሱ ጋር ደርሰን በሕይወት እንኖራለን።ይህንን ሐሳብ ራሱ አምላካችን እንዲህ ሲል ገልጦታል።"በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።" (ማቴ 7:13) ስለዚህ ሰው ጠባብ በር በተባለው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክነትና የዘለዓለም ሕይወትነት (1ኛ ዮሐ 5:20) አምኖ ፤ በቀጠነው መንገድ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተጉዞ ፤ የአካላዊ ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብሎ፤ራሱ ሕይወት የሆነው እግዚአብሔር ጋር ይደርሳል።መነሻውም መገስገሻውም መዳረሻውም እውነተኛ አምላኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል ማለት ነው።እግዚአብሔር በቸርነቱ ጾሙን ስስትን ድል የምንነሣበት ያድርግልን!!!
መጋቢት 2/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" አካላዊ ቃል ወልደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።ስለዚህ በእርሱ በማመን በሃይማኖት በር ገብተን፤በቀጠነችው መንገድ በፈቃደ ነፍስ ተጉዘን፤ሕይወት የሆነው እርሱ ጋር ደርሰን በሕይወት እንኖራለን።ይህንን ሐሳብ ራሱ አምላካችን እንዲህ ሲል ገልጦታል።"በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።" (ማቴ 7:13) ስለዚህ ሰው ጠባብ በር በተባለው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክነትና የዘለዓለም ሕይወትነት (1ኛ ዮሐ 5:20) አምኖ ፤ በቀጠነው መንገድ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተጉዞ ፤ የአካላዊ ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብሎ፤ራሱ ሕይወት የሆነው እግዚአብሔር ጋር ይደርሳል።መነሻውም መገስገሻውም መዳረሻውም እውነተኛ አምላኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል ማለት ነው።እግዚአብሔር በቸርነቱ ጾሙን ስስትን ድል የምንነሣበት ያድርግልን!!!
መጋቢት 2/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
http://www.youtube.com/@ZemariDawitkibru2405 Youtube channel - Zemari Dawit kibru | Official ዘማሪ ዳዊት ክብሩ
ሰላም የፌስቡክ ጓደኞቼ እና ወንድም እህቶቼ ለአገልግሎት መስፋፋት የዩትዩብ ገጽ መክፈቴን ያውቃሉ? ካላወቁስ መክፈቴን ላብስርዎ አገልግሎቱ እንዲበረታ እና የእኔን የዝማሬ አዳዲስ ሥራዎች በፍጥነት ያገኙ ዘንድ ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን እንዲቀላቀሉና ሌሎችም ቤተሰቦችን እንዲቀላቀሉ እንድታደርጉልኝ በአምላከ ተክለሃይማኖት ስም እጠይቃለሁኝ። ስለምታደርጉልኝ ሁሉ ጥረት እግዚአብሔር ይስጥልኝ ፤ እግዚአብሔር ያክብርልኝ!
Youtube channel - Zemari Dawit kibru | Official ዘማሪ ዳዊት ክብሩ
http://www.youtube.com/@ZemariDawitkibru2405
Youtube channel - Zemari Dawit kibru | Official ዘማሪ ዳዊት ክብሩ
http://www.youtube.com/@ZemariDawitkibru2405
"ከዚህ በኋላ ዲያብሎስ ወደ ቅድስት ከተማ ወሰደውና እርሱን በመቅደስ ጫፍ ላይ አቁሞ፤መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል እግርህንም በድንጋይ ከቶ እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሡሃል ተብሎ ተጽፎአልና የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፤ ወደ ታች ራስህን ወርውር አለው።"(ማቴ 4:5-6)
በፈቃዱ ሄደለት ለማለት ነው እንጂ ዲያቢሎስስ ጌታን መውሰድ አይቻለውም።ዲያቢሎስ ካህናትን ድል በምነሣበት መቅደስ ቢሆን እኔ ነበርኩ የማሸንፈው ብሎ ቢያሰብ ጌታችን ፈቃዱን ዐውቆ ሄደለት።መዝ 90:11-12 ላይ የተጻፈውን ቃል ጠቅሶ ፈተነው፤ዳዊት ደጋሚ አይመስልም!?ዳዊት ሲደገም ብን ብሎ የሚጠፋ ጠላት ለፈተና ግን ከዳዊት ጠቀሰ።
አስቀድሞ በማኅበረ መላእክት ውስጥ ትዕቢትን ከልቡናው አመንጭቶ ሐሰትን በአንደበቱ የተናገረ "የሐሰት አባቷ" ዲያቢሎስ ነው።የሌለውን የባሕርይ አምላክነት ፈልጎ በትዕቢት ወድቋል።ትዕቢት ማለትም ራስን ብቅ (ከፍ) ሌላውን ዝቅ ማድረግ ነው።ሳጥናኤል በልቡ ራሱን ከፍ አድርጎ ከሥላሴ እንደ አንዱ ለመሆን ከጅሏል።ለዚህ ነው ያልፈጠራቸውን መላእክት ፈጠርኳችሁ ብሎ "ሐሰትን" የተናገረው።ትዕቢትና ሐሰት ጓደኛሞች ናቸው፤ተለያይተውም አያውቁም።
እሱ በወደቀበት ትዕቢት እናታችን ሔዋንን ፈትኗታል።ከትዕቢት የማትለይ ሐሰትንም ነግሯታል።"እባብም ለሴቲቱ አላት፦ ሞትን አትሞቱም፤ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ።" (ዘፍ 3:4-5) ዲያቢሎስ ቀድሞም ለሔዋን ኋላም ለጌታችን ያቀረበው ፈተና ያልኳችሁን ብታደርጉ ምንም አትሆኑም የሚል ነው።ዛሬም ይህ ፈተና አይቀርልንም። "ይህን ኃጢአት ብታደርግ ምን ትሆናለህ?የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ ራስህን ወደ ፈተና ወርውር እግርህ በኃጢአት እንዳትሰነካከል መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዝልሃል።" በማለት በትዕቢት ይፈትነናል።
ከሌሎች የተሻለ ጥበቃና ከለላ እንደሚደረግልን ማሰብ፤ወይም በአንዳች ነገር ከሌሎች እንደምንሻል መገመት፤ይህን ኃጢአት ብሠራ ማን ያየኛል?ማንስ ከልካይ አለብኝ? ማለት ትዕቢት ነው።ትዕቢት ከእግዚአብሔር ለይቶ ከሰይጣን ያወዳጃል።"በዓይኑ ትዕቢተኛ የሆነውና በልቡ የሚሳሳው ከእኔ ጋር አይተባበርም"(መዝ 100:5) ተብሎ የተጻፈውም ለዚህ ነው።ይህ ማለት በትዕቢትና በስስት የተሸነፈ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር አንድ አይሆንም ማለት ነው።በዘመነ ፍዳ "የባለጠጎችን ስድብና የትዕቢተኞችን ንቀት ነፍሳችን እጅግ ጠገበች" ተብሎ እስኪጻፍ ድረስ ባለጠጎችና ትዕቢተኞች የተባሉ አጋንንት እጅጉን በርትተውብን ነበር።(መዝ 122:4)
"ጌታችን ኢየሱስም፦ ጌታን አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል አለው።" (ማቴ 4:7)መምህረ ትሕትና ኢየሱስ ክርስቶስ ትዕቢተኛውን በትሕትና አዋረደው።"ምንም አይሳነኝም" ብሎ ራሱን ከመቅደሱ ጫፍ ላይ አልወረወረም።በተአምር ሳይሆን በመጽሐፍ ቃል ድል ነሣው።ልበ አምላክ ክቡር ዳዊትም "አንተ የተጠቃውን ሕዝብ ታድናለህና፤የትዕቢተኞችን ዓይን ግን ታዋርዳለህ" (መዝ 17:27) በማለት እንደዘመረው 5500 ዘመን ሙሉ በአጋንንት የተጠቃውን ሕዝብ ለማዳን የትዕቢተኞቹን (የአጋንንትን) ዓይን በትሕትና አዋርዷል።
እመ ትሕትና ድንግል ማርያም"ትዕቢተኞችን በልባቸው ሐሳብ በትኖአል ...ትሑታንንም ከፍ አድርጎአል"(ሉቃ 1:51-52) ስትል ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ያዕቆብ በአንድ ቃል "እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል"(1ኛ ጴጥ 5:5፤ያዕ 4:6) በማለት ከአምላካቸው እናት ጋር አንድ ዓይነት ሐሳብን ገልጠዋል።ቅዱስ ጳውሎስ "አንተ እንድትበልጥ ማን አድርጎሃል?ያልተቀበልኸውስ ምን አለ?የተቀበልኽ ከሆንክስ እንዳልተቀበለ የምትመካ ስለ ምንድነው?"(1ኛ ቆሮ 4:7) በማለት ከሌላው እንደማንበልጥ፤ያለን ነገር ሁሉ ተሰጥቶን እንጂ ከራሳችን የሆነ እንዳልሆነ፤ባለን ነገርም መመካት እንደማይገባ የትሕትናን ነገር አስተምሮናል።
በትዕቢት (ሌሎችን በመናቅ) የምናገለግለውን አገልግሎት እግዚአብሔር ስለማይቀበለው እጅግ ጠንቃቆች ልንሆን ያስፈልገናል።"ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁና።"(ማቴ 18:10)ጌታችን እኛ ታናሽ ናቸው ብለን ልንንቃቸው የምንፈልጋቸውን ሰዎች ክብራቸውን በማሳየት "ከመናቅ" እንድንጠነቀቅ አሳስቦናል።ትዕቢት የተሸነፈበትን የጌታችንን ጾም እየጾምን እንኳን የምንታበይ ብዙዎች ነን።ከሌሎች በተሻለ ረዘም ላለ ሰዓት ከእህል ከውኃ ስለተከለከልን የተሻልን ጿሚዎች አይደለንም።ብዙ ገንዘብ ስለመጸወትንም የተለየን መጽዋቾች አይደለንም።በየዕለቱ ለረጅም ሰዓት የተለያዩ ጸሎቶችን ስለጸለይንም ልዩ ክርስቲያኖች አይደለንም።ይህንን ከልብ ማመን ያስፈልጋል።እግዚአብሔር የሚያውቃቸው እኛ የማናውቃቸው በዙሪያችን ያሉ (ከምንም የማንቆጥራቸውን) ወዳጆቹን ትሩፋት ቢገልጽልን፤ገና የጽድቅን "ሀ ፡ ሁ" እንደማናውቅ ይገባን ነበር።ለዚህ ነው "እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቁጠር" (ፊል 2:3) በማለት ሐዋርያው ያስጠነቀቀን!!!ጾሙን የትሕትና ያድርግልን አሜን!!!
ኢዮብ ክንፈ
መጋቢት 17/2016 ዓ.ም
በፈቃዱ ሄደለት ለማለት ነው እንጂ ዲያቢሎስስ ጌታን መውሰድ አይቻለውም።ዲያቢሎስ ካህናትን ድል በምነሣበት መቅደስ ቢሆን እኔ ነበርኩ የማሸንፈው ብሎ ቢያሰብ ጌታችን ፈቃዱን ዐውቆ ሄደለት።መዝ 90:11-12 ላይ የተጻፈውን ቃል ጠቅሶ ፈተነው፤ዳዊት ደጋሚ አይመስልም!?ዳዊት ሲደገም ብን ብሎ የሚጠፋ ጠላት ለፈተና ግን ከዳዊት ጠቀሰ።
አስቀድሞ በማኅበረ መላእክት ውስጥ ትዕቢትን ከልቡናው አመንጭቶ ሐሰትን በአንደበቱ የተናገረ "የሐሰት አባቷ" ዲያቢሎስ ነው።የሌለውን የባሕርይ አምላክነት ፈልጎ በትዕቢት ወድቋል።ትዕቢት ማለትም ራስን ብቅ (ከፍ) ሌላውን ዝቅ ማድረግ ነው።ሳጥናኤል በልቡ ራሱን ከፍ አድርጎ ከሥላሴ እንደ አንዱ ለመሆን ከጅሏል።ለዚህ ነው ያልፈጠራቸውን መላእክት ፈጠርኳችሁ ብሎ "ሐሰትን" የተናገረው።ትዕቢትና ሐሰት ጓደኛሞች ናቸው፤ተለያይተውም አያውቁም።
እሱ በወደቀበት ትዕቢት እናታችን ሔዋንን ፈትኗታል።ከትዕቢት የማትለይ ሐሰትንም ነግሯታል።"እባብም ለሴቲቱ አላት፦ ሞትን አትሞቱም፤ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ።" (ዘፍ 3:4-5) ዲያቢሎስ ቀድሞም ለሔዋን ኋላም ለጌታችን ያቀረበው ፈተና ያልኳችሁን ብታደርጉ ምንም አትሆኑም የሚል ነው።ዛሬም ይህ ፈተና አይቀርልንም። "ይህን ኃጢአት ብታደርግ ምን ትሆናለህ?የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ ራስህን ወደ ፈተና ወርውር እግርህ በኃጢአት እንዳትሰነካከል መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዝልሃል።" በማለት በትዕቢት ይፈትነናል።
ከሌሎች የተሻለ ጥበቃና ከለላ እንደሚደረግልን ማሰብ፤ወይም በአንዳች ነገር ከሌሎች እንደምንሻል መገመት፤ይህን ኃጢአት ብሠራ ማን ያየኛል?ማንስ ከልካይ አለብኝ? ማለት ትዕቢት ነው።ትዕቢት ከእግዚአብሔር ለይቶ ከሰይጣን ያወዳጃል።"በዓይኑ ትዕቢተኛ የሆነውና በልቡ የሚሳሳው ከእኔ ጋር አይተባበርም"(መዝ 100:5) ተብሎ የተጻፈውም ለዚህ ነው።ይህ ማለት በትዕቢትና በስስት የተሸነፈ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር አንድ አይሆንም ማለት ነው።በዘመነ ፍዳ "የባለጠጎችን ስድብና የትዕቢተኞችን ንቀት ነፍሳችን እጅግ ጠገበች" ተብሎ እስኪጻፍ ድረስ ባለጠጎችና ትዕቢተኞች የተባሉ አጋንንት እጅጉን በርትተውብን ነበር።(መዝ 122:4)
"ጌታችን ኢየሱስም፦ ጌታን አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል አለው።" (ማቴ 4:7)መምህረ ትሕትና ኢየሱስ ክርስቶስ ትዕቢተኛውን በትሕትና አዋረደው።"ምንም አይሳነኝም" ብሎ ራሱን ከመቅደሱ ጫፍ ላይ አልወረወረም።በተአምር ሳይሆን በመጽሐፍ ቃል ድል ነሣው።ልበ አምላክ ክቡር ዳዊትም "አንተ የተጠቃውን ሕዝብ ታድናለህና፤የትዕቢተኞችን ዓይን ግን ታዋርዳለህ" (መዝ 17:27) በማለት እንደዘመረው 5500 ዘመን ሙሉ በአጋንንት የተጠቃውን ሕዝብ ለማዳን የትዕቢተኞቹን (የአጋንንትን) ዓይን በትሕትና አዋርዷል።
እመ ትሕትና ድንግል ማርያም"ትዕቢተኞችን በልባቸው ሐሳብ በትኖአል ...ትሑታንንም ከፍ አድርጎአል"(ሉቃ 1:51-52) ስትል ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ያዕቆብ በአንድ ቃል "እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል"(1ኛ ጴጥ 5:5፤ያዕ 4:6) በማለት ከአምላካቸው እናት ጋር አንድ ዓይነት ሐሳብን ገልጠዋል።ቅዱስ ጳውሎስ "አንተ እንድትበልጥ ማን አድርጎሃል?ያልተቀበልኸውስ ምን አለ?የተቀበልኽ ከሆንክስ እንዳልተቀበለ የምትመካ ስለ ምንድነው?"(1ኛ ቆሮ 4:7) በማለት ከሌላው እንደማንበልጥ፤ያለን ነገር ሁሉ ተሰጥቶን እንጂ ከራሳችን የሆነ እንዳልሆነ፤ባለን ነገርም መመካት እንደማይገባ የትሕትናን ነገር አስተምሮናል።
በትዕቢት (ሌሎችን በመናቅ) የምናገለግለውን አገልግሎት እግዚአብሔር ስለማይቀበለው እጅግ ጠንቃቆች ልንሆን ያስፈልገናል።"ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁና።"(ማቴ 18:10)ጌታችን እኛ ታናሽ ናቸው ብለን ልንንቃቸው የምንፈልጋቸውን ሰዎች ክብራቸውን በማሳየት "ከመናቅ" እንድንጠነቀቅ አሳስቦናል።ትዕቢት የተሸነፈበትን የጌታችንን ጾም እየጾምን እንኳን የምንታበይ ብዙዎች ነን።ከሌሎች በተሻለ ረዘም ላለ ሰዓት ከእህል ከውኃ ስለተከለከልን የተሻልን ጿሚዎች አይደለንም።ብዙ ገንዘብ ስለመጸወትንም የተለየን መጽዋቾች አይደለንም።በየዕለቱ ለረጅም ሰዓት የተለያዩ ጸሎቶችን ስለጸለይንም ልዩ ክርስቲያኖች አይደለንም።ይህንን ከልብ ማመን ያስፈልጋል።እግዚአብሔር የሚያውቃቸው እኛ የማናውቃቸው በዙሪያችን ያሉ (ከምንም የማንቆጥራቸውን) ወዳጆቹን ትሩፋት ቢገልጽልን፤ገና የጽድቅን "ሀ ፡ ሁ" እንደማናውቅ ይገባን ነበር።ለዚህ ነው "እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቁጠር" (ፊል 2:3) በማለት ሐዋርያው ያስጠነቀቀን!!!ጾሙን የትሕትና ያድርግልን አሜን!!!
ኢዮብ ክንፈ
መጋቢት 17/2016 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
ለዚህ የበረከት ሥራ ዝግጁ የሆናችሁ በዕለቱ በመገኘት እንድትሳተፉ እንላለን !!!
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የቁርሳችንን በማስገባት የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ ወዳጆች !!!!
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
http://www.youtube.com/@ZemariDawitkibru2405 Youtube channel - Zemari Dawit kibru | Official ዘማሪ ዳዊት ክብሩ