ስለ ጥያቄዎ ከልብ እናመሰግናለን የሕይወትን ቃል ያሰማልን
#የናሆም መድኃኒት ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሃውልት ፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ ፣የነቢያት ትንቢትና ምሳሌ የሆነች እመቤታችንን የመሰሏትን ነገሮች (ምሳሌዎቿን) መጨረስ አይቻልም ነገር ግን ጥቂቶቹን ከመጠነኛ ማብራሪያ ጋር እነሆ
#የአዳም_ተስፋ_ሔዋን ዘፍ 2፥24
እጸ በለስን ከበሉ በኃላ አዳም አንቺ ነሽ ያሳሳትሽኝ ብሎ ሔዋንን ተጣልቶ አባሯት ነበር መላእከ እግዚአብሔር ተገልጾ ዳግመኛም የምትድነው በእርሷ ነውና ሄደህ ፈልገህ አምጣት ብሎታል ፈልጎም አምጥቷታል። ከዚህ በኃላ ዳግሚት ሔዋን እመቤታችን ተስፋ ሆና እንደምትሰጠው አውቆ አባታችን አዳም ሚስቱ ሔዋንን ሕይወቴ ነሽ ብሎ በአንጻር በምሳሌ ይጠራት ነበር። ስለዚህ ዳግሚት ሔዋን እመቤታችን በቀዳማዊት ሔዋን በአዳም ሚስት ትመሰላለች ምሳሌ ከሚመሰልለት ዋና ነገር እንደሚያንስ ሁሉ ምሳሌዋ ቀዳሚት ሔዋንም(የአዳም ሚስት)ከዳግሚቱ ሔዋን(ከእመቤታችን) በእጅጉ ታንሳለች ።
-ቀዳሚት ሔዋን የዲቢሎስን የሐሰት ቃል ሰማች
- #ዳግሚት_ሔዋን የመላእኩ የእውነት ቃል አደመጠች
-ቀዳሚት ሔዋን የሞት ፍሬ በላች
- #ዳግሚት_ሔዋን ኤፍራታ ግን የሕይወት ፍሬ አፈራች
-ቀዳሚት ሔዋን እንደ ስሞ የሕያዋን እናት መሆን ተሳናት
- #ዳግሚት_ሔዋን የሕያዋን ሁሉ ሕያው እናት መሆን ተቻላት
-ቀዳሚት ሔዋን በአዳም ምክንያት በዘር ጸነሰች
- #ዳግሚት_ሔዋን በመንፈስ ቅድስ ምክንያት ያለ ዘር ጸነሰች
-ቀዳሚት ሔዋን እንደ ተፈጥሮ ድንግልናዋን አጥታ ጸነሰች
- #ዳግሚት_ሔዋን በድንግና ጸነሰ
-ቀዳሚት ሔዋን በሕማምና በምጥ ወለደች
- #ዳግሚት_ሔዋን ያ ሕማምና ያለ ምጥ ወለደች
-ቀዳሚት ሔዋን ታላቅና ታናሽ የሆኑ እርስ በእርስ የሚገዳደሉ ሞችና ገዳይ ልጆችን ወለደች
- #ዳግሚት_ሔዋን ግን ቀዳሚ ተከታይ የሌለው አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስን ብቻ በድንግልና ወለደች
#የአቤል የዋህት ዘፍ 4÷8
ወንድሙ ቃየን ና ውኃ እንጠጣ ብሎ በድንጋይ ጭኖ የገደለው አቤል እጅግ የዋሕ በመሆኑ ነው ። ይህ የአቤል የዋህነት የእመቤታችን ምሳሌ ናት ። የአቤል ልቡና የዋህት ፣ቅን ፣ደግ እንደሆነች እመቤታችንም እንኳን ለሰው ለተጠማ ጥቁር ውሻ የምትራራ እርርይተ ልቡና ነችና የአቤል የዋህት (ደግነቱ ፣ቅንነቱ) ትባላለች። ለቅኖች ደግሞ ምሥጋና ይገባልና በሰማይ በማሕበረ መላእክት በምድር በደቂቀ አዳም ሁሉ ለዘለዓለሙ ትመሰገናለች።መዝ32(33)፥1
#የጌዲዮን ጸምር መጻ መሳ(6)(7)
#የኤልሳዕ_አዲስ_ማሰሮ 2ነገ 2፥20
የፀነሱ ሴቶች ሲጠጡት የሚያሶርዳቸው ወላድ ወንዶችን በጠጡት ጊዜ የሚያኮላሻቸውን የተመረዘውን ማየ ግብጽ (የግብጽን ውኃ) ኤልሳዕ የፈወሰላቸው ጨው የተጨመረባት አዲስ ማሰሮ በመጠቀም ነበር :: ጨው የጨመረበትን ማሰሮ የተመረዘውን ውኃ ቀድቶ ከጨመረበት በኃላ መልሶ ወደ ወንዙ ቢያፈሰው ወንዙ እንደ ቀድሞ ደህነኛ ውኃ ሆነ አዲሷ ማሰሮ የእመቤታችን በውጧ የጨመረው ጨው የልጇ የክርስቶስ ምሳሌ ነው :: ስለዚህ እመቤታችን አልጫው ዓለም የጣፈጠባት፤ የመጣፈጣችን ምክንያት የሆነች ጨው ክርስቶስ የተገኘባት አዲስ ማሰሮ ነች ::
#የሙሴ ጽላት ዘጸአት 24፥12
ታቦት ማደሪያ ሲሆን ጽላት ደግሞ ሰሌዳ መጻፊያ የፊደሉ ቅርጽ ማረፊያ ወይም ያረወበት ማለት ነው ። እመቤታችን ታዲያ የአምላክ ማደሪያ ማህደረ መለኮት በመሆኗ ታቦት የፊደል ክርቶስ መቀረጫ ጽሌ በመሆኗ ደግሞ ጽላት እየተባለች በሁለቱም በማስተባበር ትጠራበታለች ። በጽላት አስርቱ ትዕዛዛቶ እንደተቀረጸ በእመቤታችንም የሕይወት ፊደል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተቀርጾባታልና ይልቁኑ እርሷ በንጽሕና የተጻፈች ፊደል ናት ማ ር ያ ም!
#ሙሴ ያያት የሲና ዕፀ ጳጦስ ዘጽ3፥2
አመልማል ከነበልባል ነበልባልም ከአመልማል ተዋሕደው በአንድነት ሆነው ሙሴ በደብረ ሲና ተመልከቶ ነበር የሚገርመው አመልማሉ ዘነበልባሉ አይቃጠልም ነበር ነበልባሉም በአመልማሉ አይጠፋም ነበር :: ምነው እንዴት ቢሉ ምሥጢረ ተዋሕዶ ነውና አመልማል የሥጋ ፤ነበልባል ደግሞ የመለኮት አምሳል ነው :: ነበልባሉ አመልማሉን እንዳላቃጠለው ነበልባል የሚባል መለኮትም በድንግል ማርያም ማህፀን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሶም ነፍስ ነስቶ 9ወር ከ5 ቀን ሲቆይ ድንግል ማርያምን አላቃጠላትም ስለዚህ ሙሴ ነበልባል ታቅፋ ያያት አመልማል የእመቤታችን ምሳሌ ናት:: (ማርያም ተአቢይ እምኩሉ ፍጥረት ሕያዋያ አሳተ መለኮት) ማርያም ትበልጣለች ከሁሉም ፍጥረት ስለ ያዘች እሳተ መለኮት እያልንም እንዘምርላት ዘንድ ተገባት።
#የአብርሃም_ድንኳን ዘፍ 13÷1-18
በአብርሃም ድንኳን ቅድስት ሥላሴ ተስተናግደዋል በእመቤታችንም በቅድስት ድንግል ማርያም ሥላሴ በጉልዕ ተገልጠዋል :: ከእመቤታችን መገኘት በፊት የሥላሴ ምሥጢር በጎላ በተረዳ ነገር አይታወቅም ነበር የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በፍጥረቱ ዘንድ በእጅጉ የጎላውና የተረዳው በድንግል ማርያም ምክንያት ነው:: እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የአብ ማረፊያ የሆነ ማነው ? እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የወልድ ማደሪያ የሆነ ማነው ? እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የመንፈስ ቅዱስ ንጽሕ አዳራሽ የሆነስ ማነው? /እንዲል ተአምረ ማርያም መቅድም/
#በጉ_የተያዘበት_ዕፀ_ሳቤቅ ዘፍ 22፥13
አብርሃም የእምነቱ ጽናት እንዲገለጥ አንድ ልጅህን ሰዋልኝ የሚል ጥያቄ ከእግዚአብሔር ቀረበለት በእስተ እርጅናዬ ያገነውት የምወደው አንድ ልጄን አልሰዋልህም ሳይል የምትነሳኝ ከሆነ ለምን ሰጠህኝ ብሎም ሳያማርር እሺ በጄ ብሎ ልጁ ይስሐቅን የመሰዋይቱን እንጨት አሸክሞ እራሱ ደግሞ ቢላዋን ይዞ ወደ ሞሪያም ተራራ ወጣ ይስሐቅም አባቴ የመሰዋቱን እንጨት እኔ ይዣለሁ መሰዊያውንም ቢላዋ አንተ ይዘሃል መሰዋይቱ ግን አይታየኝም የታለ? አለው አብርሃምም እርሱን #እግዚአብሔር ያዘጋጃል አለው የልጁ የይስሐቅ አሳዛኝ የልጅነት ንግግር ሳያባባው ምሰዋይት አድርጎ ያቀርበው ዘንድ ቆረጠ ለእግዚአብሔር በፍጹም ታምኟልና ከፍቅረ ልጅ ይልቅ ፍቅረ እግዚአብሔር አገብሮታልና። በደረሱ ጊዜም ልጄ ይስሐቅ ሆይ መሰዋይቱ አንተ ነህ እግዚአብሔር አንተን እሰዋለት ዘንድ ወዷል አለው ይስሐቅም አንተ ጨካኝ አባት ሳይል በእሺታ በመሰዊያው ላይ ወጣ አባቴ ዐይን ዐይኔን እያየህ ስቁለጨለጭብህ አዝነህ ትተወኝና ከፈጣሪ እንዳትጣላ በጀርባዬ ገልብጠህ ሰዋኝ አለው እዳለውም አድርጎ ሊሰዋው ሲዘጋጅ አብርሃም አብርሃም በልጅህ ላይ አዳች እንዳታደርግ ተባለ ዞር ሲልም ቀንዶቹ በእጸ ሳቤቅ የተያዘ በግ አየና በይስሐቅ ፈንታ እርሱን መሰዋት አቀረበ:: በዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት የአብርሃም እምነት የይስሐቅም ፍጽም ታዛዢነት ተገለጠ።
#አብርሃም የእግዚአብሔር አብ
#ይስሐቅ የአዳም
#በጉ የእግዚአብሔር ወልድ(የኢየሱስ ክርስቶስ )
#በጎን በቀንዱ በኩል አስራ የያዘችሁ እፀ ሳቤቅ የእመቤታችን ምሳሌ ናቸው።
ሥልጣን ኃይል ብርታት በመጻሕፍ ቅዱስ አገላለጽ " ቀንድ " ተብሎ ይገለጻል ። “ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች፦ ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል።” 1ኛ ሳሙኤል 2፥1
“ቀንዴ አንድ ቀንድ እንዳለው ከፍ ከፍ ይላል፤ ሽምግልናዬም በዘይት ይለመልማል።” መዝ 92፥10
ቀንድ በከብቶች ሕይወት ውስጥ ሰፊ ሚና አለው ከብቶች የቀንድ ከብት እና የጋማ ከብት ተብለው ለሁለት ይከፈላሉ ታዲያ የቀንድ ከብቶች እራሳቸውን ከጥቃት
#የናሆም መድኃኒት ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሃውልት ፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ ፣የነቢያት ትንቢትና ምሳሌ የሆነች እመቤታችንን የመሰሏትን ነገሮች (ምሳሌዎቿን) መጨረስ አይቻልም ነገር ግን ጥቂቶቹን ከመጠነኛ ማብራሪያ ጋር እነሆ
#የአዳም_ተስፋ_ሔዋን ዘፍ 2፥24
እጸ በለስን ከበሉ በኃላ አዳም አንቺ ነሽ ያሳሳትሽኝ ብሎ ሔዋንን ተጣልቶ አባሯት ነበር መላእከ እግዚአብሔር ተገልጾ ዳግመኛም የምትድነው በእርሷ ነውና ሄደህ ፈልገህ አምጣት ብሎታል ፈልጎም አምጥቷታል። ከዚህ በኃላ ዳግሚት ሔዋን እመቤታችን ተስፋ ሆና እንደምትሰጠው አውቆ አባታችን አዳም ሚስቱ ሔዋንን ሕይወቴ ነሽ ብሎ በአንጻር በምሳሌ ይጠራት ነበር። ስለዚህ ዳግሚት ሔዋን እመቤታችን በቀዳማዊት ሔዋን በአዳም ሚስት ትመሰላለች ምሳሌ ከሚመሰልለት ዋና ነገር እንደሚያንስ ሁሉ ምሳሌዋ ቀዳሚት ሔዋንም(የአዳም ሚስት)ከዳግሚቱ ሔዋን(ከእመቤታችን) በእጅጉ ታንሳለች ።
-ቀዳሚት ሔዋን የዲቢሎስን የሐሰት ቃል ሰማች
- #ዳግሚት_ሔዋን የመላእኩ የእውነት ቃል አደመጠች
-ቀዳሚት ሔዋን የሞት ፍሬ በላች
- #ዳግሚት_ሔዋን ኤፍራታ ግን የሕይወት ፍሬ አፈራች
-ቀዳሚት ሔዋን እንደ ስሞ የሕያዋን እናት መሆን ተሳናት
- #ዳግሚት_ሔዋን የሕያዋን ሁሉ ሕያው እናት መሆን ተቻላት
-ቀዳሚት ሔዋን በአዳም ምክንያት በዘር ጸነሰች
- #ዳግሚት_ሔዋን በመንፈስ ቅድስ ምክንያት ያለ ዘር ጸነሰች
-ቀዳሚት ሔዋን እንደ ተፈጥሮ ድንግልናዋን አጥታ ጸነሰች
- #ዳግሚት_ሔዋን በድንግና ጸነሰ
-ቀዳሚት ሔዋን በሕማምና በምጥ ወለደች
- #ዳግሚት_ሔዋን ያ ሕማምና ያለ ምጥ ወለደች
-ቀዳሚት ሔዋን ታላቅና ታናሽ የሆኑ እርስ በእርስ የሚገዳደሉ ሞችና ገዳይ ልጆችን ወለደች
- #ዳግሚት_ሔዋን ግን ቀዳሚ ተከታይ የሌለው አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስን ብቻ በድንግልና ወለደች
#የአቤል የዋህት ዘፍ 4÷8
ወንድሙ ቃየን ና ውኃ እንጠጣ ብሎ በድንጋይ ጭኖ የገደለው አቤል እጅግ የዋሕ በመሆኑ ነው ። ይህ የአቤል የዋህነት የእመቤታችን ምሳሌ ናት ። የአቤል ልቡና የዋህት ፣ቅን ፣ደግ እንደሆነች እመቤታችንም እንኳን ለሰው ለተጠማ ጥቁር ውሻ የምትራራ እርርይተ ልቡና ነችና የአቤል የዋህት (ደግነቱ ፣ቅንነቱ) ትባላለች። ለቅኖች ደግሞ ምሥጋና ይገባልና በሰማይ በማሕበረ መላእክት በምድር በደቂቀ አዳም ሁሉ ለዘለዓለሙ ትመሰገናለች።መዝ32(33)፥1
#የጌዲዮን ጸምር መጻ መሳ(6)(7)
#የኤልሳዕ_አዲስ_ማሰሮ 2ነገ 2፥20
የፀነሱ ሴቶች ሲጠጡት የሚያሶርዳቸው ወላድ ወንዶችን በጠጡት ጊዜ የሚያኮላሻቸውን የተመረዘውን ማየ ግብጽ (የግብጽን ውኃ) ኤልሳዕ የፈወሰላቸው ጨው የተጨመረባት አዲስ ማሰሮ በመጠቀም ነበር :: ጨው የጨመረበትን ማሰሮ የተመረዘውን ውኃ ቀድቶ ከጨመረበት በኃላ መልሶ ወደ ወንዙ ቢያፈሰው ወንዙ እንደ ቀድሞ ደህነኛ ውኃ ሆነ አዲሷ ማሰሮ የእመቤታችን በውጧ የጨመረው ጨው የልጇ የክርስቶስ ምሳሌ ነው :: ስለዚህ እመቤታችን አልጫው ዓለም የጣፈጠባት፤ የመጣፈጣችን ምክንያት የሆነች ጨው ክርስቶስ የተገኘባት አዲስ ማሰሮ ነች ::
#የሙሴ ጽላት ዘጸአት 24፥12
ታቦት ማደሪያ ሲሆን ጽላት ደግሞ ሰሌዳ መጻፊያ የፊደሉ ቅርጽ ማረፊያ ወይም ያረወበት ማለት ነው ። እመቤታችን ታዲያ የአምላክ ማደሪያ ማህደረ መለኮት በመሆኗ ታቦት የፊደል ክርቶስ መቀረጫ ጽሌ በመሆኗ ደግሞ ጽላት እየተባለች በሁለቱም በማስተባበር ትጠራበታለች ። በጽላት አስርቱ ትዕዛዛቶ እንደተቀረጸ በእመቤታችንም የሕይወት ፊደል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተቀርጾባታልና ይልቁኑ እርሷ በንጽሕና የተጻፈች ፊደል ናት ማ ር ያ ም!
#ሙሴ ያያት የሲና ዕፀ ጳጦስ ዘጽ3፥2
አመልማል ከነበልባል ነበልባልም ከአመልማል ተዋሕደው በአንድነት ሆነው ሙሴ በደብረ ሲና ተመልከቶ ነበር የሚገርመው አመልማሉ ዘነበልባሉ አይቃጠልም ነበር ነበልባሉም በአመልማሉ አይጠፋም ነበር :: ምነው እንዴት ቢሉ ምሥጢረ ተዋሕዶ ነውና አመልማል የሥጋ ፤ነበልባል ደግሞ የመለኮት አምሳል ነው :: ነበልባሉ አመልማሉን እንዳላቃጠለው ነበልባል የሚባል መለኮትም በድንግል ማርያም ማህፀን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሶም ነፍስ ነስቶ 9ወር ከ5 ቀን ሲቆይ ድንግል ማርያምን አላቃጠላትም ስለዚህ ሙሴ ነበልባል ታቅፋ ያያት አመልማል የእመቤታችን ምሳሌ ናት:: (ማርያም ተአቢይ እምኩሉ ፍጥረት ሕያዋያ አሳተ መለኮት) ማርያም ትበልጣለች ከሁሉም ፍጥረት ስለ ያዘች እሳተ መለኮት እያልንም እንዘምርላት ዘንድ ተገባት።
#የአብርሃም_ድንኳን ዘፍ 13÷1-18
በአብርሃም ድንኳን ቅድስት ሥላሴ ተስተናግደዋል በእመቤታችንም በቅድስት ድንግል ማርያም ሥላሴ በጉልዕ ተገልጠዋል :: ከእመቤታችን መገኘት በፊት የሥላሴ ምሥጢር በጎላ በተረዳ ነገር አይታወቅም ነበር የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በፍጥረቱ ዘንድ በእጅጉ የጎላውና የተረዳው በድንግል ማርያም ምክንያት ነው:: እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የአብ ማረፊያ የሆነ ማነው ? እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የወልድ ማደሪያ የሆነ ማነው ? እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የመንፈስ ቅዱስ ንጽሕ አዳራሽ የሆነስ ማነው? /እንዲል ተአምረ ማርያም መቅድም/
#በጉ_የተያዘበት_ዕፀ_ሳቤቅ ዘፍ 22፥13
አብርሃም የእምነቱ ጽናት እንዲገለጥ አንድ ልጅህን ሰዋልኝ የሚል ጥያቄ ከእግዚአብሔር ቀረበለት በእስተ እርጅናዬ ያገነውት የምወደው አንድ ልጄን አልሰዋልህም ሳይል የምትነሳኝ ከሆነ ለምን ሰጠህኝ ብሎም ሳያማርር እሺ በጄ ብሎ ልጁ ይስሐቅን የመሰዋይቱን እንጨት አሸክሞ እራሱ ደግሞ ቢላዋን ይዞ ወደ ሞሪያም ተራራ ወጣ ይስሐቅም አባቴ የመሰዋቱን እንጨት እኔ ይዣለሁ መሰዊያውንም ቢላዋ አንተ ይዘሃል መሰዋይቱ ግን አይታየኝም የታለ? አለው አብርሃምም እርሱን #እግዚአብሔር ያዘጋጃል አለው የልጁ የይስሐቅ አሳዛኝ የልጅነት ንግግር ሳያባባው ምሰዋይት አድርጎ ያቀርበው ዘንድ ቆረጠ ለእግዚአብሔር በፍጹም ታምኟልና ከፍቅረ ልጅ ይልቅ ፍቅረ እግዚአብሔር አገብሮታልና። በደረሱ ጊዜም ልጄ ይስሐቅ ሆይ መሰዋይቱ አንተ ነህ እግዚአብሔር አንተን እሰዋለት ዘንድ ወዷል አለው ይስሐቅም አንተ ጨካኝ አባት ሳይል በእሺታ በመሰዊያው ላይ ወጣ አባቴ ዐይን ዐይኔን እያየህ ስቁለጨለጭብህ አዝነህ ትተወኝና ከፈጣሪ እንዳትጣላ በጀርባዬ ገልብጠህ ሰዋኝ አለው እዳለውም አድርጎ ሊሰዋው ሲዘጋጅ አብርሃም አብርሃም በልጅህ ላይ አዳች እንዳታደርግ ተባለ ዞር ሲልም ቀንዶቹ በእጸ ሳቤቅ የተያዘ በግ አየና በይስሐቅ ፈንታ እርሱን መሰዋት አቀረበ:: በዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት የአብርሃም እምነት የይስሐቅም ፍጽም ታዛዢነት ተገለጠ።
#አብርሃም የእግዚአብሔር አብ
#ይስሐቅ የአዳም
#በጉ የእግዚአብሔር ወልድ(የኢየሱስ ክርስቶስ )
#በጎን በቀንዱ በኩል አስራ የያዘችሁ እፀ ሳቤቅ የእመቤታችን ምሳሌ ናቸው።
ሥልጣን ኃይል ብርታት በመጻሕፍ ቅዱስ አገላለጽ " ቀንድ " ተብሎ ይገለጻል ። “ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች፦ ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል።” 1ኛ ሳሙኤል 2፥1
“ቀንዴ አንድ ቀንድ እንዳለው ከፍ ከፍ ይላል፤ ሽምግልናዬም በዘይት ይለመልማል።” መዝ 92፥10
ቀንድ በከብቶች ሕይወት ውስጥ ሰፊ ሚና አለው ከብቶች የቀንድ ከብት እና የጋማ ከብት ተብለው ለሁለት ይከፈላሉ ታዲያ የቀንድ ከብቶች እራሳቸውን ከጥቃት
የሚከላከሉትና ጥቃት የሚያደርሱት በቀንዶቻቸው አማካኝነት ነው ስለዚህ ቀንዳቸው ኃይላቸው ሥልጣናቸው ነው :: ታዲያ ይህ ለአብርሃም በይስሐቅ ፈንታ ይሰዋው ዘንድ የተሰጠው በግ እንደማንኛውም የቀንድ ከብት እራሱን ከአራጁ የሚከላከልበት ኃይልና ሥልጣን ያለው ቀንዳም በግ ቢሆንም ቀንዱ ግን በ አፀ ሳቤቅ ስለተያዘ ያን ያደርግ ዘንድ አላስቻለውም ። በሕልውና ፣በሥልጣን ፣በኃይል ከባሕሪ አባቱ ከአብ እና ከባሕሪ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ትክክል (እኩል ፣የተተካከለ) ቢሆንም ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስም በሰው ልጆች የፍቅር እጸ ሳቤቅ ተይዟልና ከልዕልና ወደ ትዕትና ዝቅ አለ ባሕሪውንም ሰውሮ እንደኛ የተገዢ የሰውን አራዐያ ነሳ። ፍቅር ሰአቡ ኃያል ወልድ እም መንበሩ ወአብጽዮ እስከ እለ ሞት / #ፍቅር ኃያል ወልድን ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው"/ የበጉ ቀንድ በእጸ ሳቤቅ ስለተያዘ ከመታረድ እንዳልሸሸ ና በቀንዴም ተዋግቼ ላምልጥ ብሎ የቀንዱን ሥልጣን እንዳልተጠቀመ ሁሉ ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስም በፍቃዱ በሰው ፍቅር ተይዟልና ሥልጣን ሁሉ የእርሱ ሆኖ ሳለ ሥልጣኑን ሳይሆን ፍቅሩን ተጠቅሞ ለኛ ተሰውቶ አዳነን:: "ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?" ኢሳ 53፥7-8
#የአሮን በትር ዘኁልቁ 17÷8
ሙሴም ለእስራኤል ልጆች ተናገራቸው፤ አለቆቻቸው ሁሉ አሥራ ሁለት በትሮች፥ እያንዳንዱም አለቃ በየአባቱ ቤት አንድ አንድ በትር፥ ሰጡት፤ የአሮንም በትር በበትሮቻቸው መካከል ነበረች። ሙሴም በትሮቹን በእግዚአብሔር ፊት በምስክሩ ድንኳን ውስጥ አኖራቸው። እንዲህም ሆነ፤ በነጋው ሙሴ ወደ ምስክሩ ድንኳን ውስጥ ገባ፤ እነሆም፥ ለሌዊ ቤት የሆነች #የአሮን_በትር_አቈጠቈጠች_ለመለመችም_አበባም_አወጣች የበሰለ ለውዝም አፈራች። ሙሴም በትሮችን ሁሉ ከእግዚአብሔር ፊት ወደ እስራኤል ልጆች ሁሉ አወጣቸው፤ እነርሱም አዩ፥ እያንዳንዱም በትሩን ወሰደ። እግዚአብሔርም ሙሴን፦ የአሮንን በትር ወደ ምስክሩ ፊት መልስ፤ ማጕረምረማቸው ከእኔ ዘንድ እንዲጠፋ እነርሱም እንዳይሞቱ ለሚያምፁብኝ ልጆች ምልክት ሆና ትጠበቅ አለው።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የማክሰኞ እርሻ ትባላለች የማክሰኞ እርሻ ገበሬ ሳይኮተኩታት ውኃም ሳያጠጣት አብባ አፍርታ ተገኝታለች ይህች የማክሰኞ ዕለት እርሻ የመጀመሪያይቱ ምድር ወይም ጥንተ ምድርም እየተባለች ትጠራለች የሶሪያው ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊም አክሎ በውዳሴው እንዲ ብሏታል #ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበር እንቺ እንደርሷ ነሽ" #አባ ኤፍሬም ሶሪያዊ #ውዳሴ_ማርያም ዘ እሁድ
#የኖህ መርከብ ዘፍ 6፥14
በኖህ መርከብ ፍጥረት ከጥፋት እንደተረፈ በእመቤታችንም ከጥፋት ድኗል ። የኖህ መርከብ ሦስት ክፍሎች ነበሯት እመቤታችንም በሦስት ነገሯ ንጽሕት ነች በሥጋዋ ፣በነፍሷ፣ በሕሊናዋ የጋስጫ ፍሬ አባ ጊዮርጊስ "በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " ድንግል ሆይ በምንና በምን እንመስልሻለን ምሳሌን የለሽም" እንዳለ ምሳሌዎች ሁሉ እመቤታችንን አይመስሏትም(አይመጥኗትም)
#የኖህ መርከብ ስምንት ሰዎችና ብዙ ዐይነት እንሰሳት ገብተውባታል ወጥተውባታል
#በእመቤታች ግን ከኃያላ ከጌታ በቀር ወደ እርሷ ገብቶ የወጣ የለም
#በኖህ መርከብ ሲገባም ሲወጣም በሮቹአን ከፍተው ዘግተው ነው
#እመቤታችን ግን ማንም ለዘላለሙ የተዘጋች ገነት የታተመች ፈሳሽ ነችና ዘላለም እትዕምት ፣ዝግ ፣ድንግል ነች ። ጌታችንንም የጸነሰችው እንዲሁ ዝግ ሆና ነው ስትወልደውም እንዲሁ ዝግ ሆና ነው። " ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ፤ ተዘግቶም ነበር። እግዚአብሔርም፦ ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፥ ሰውም አይገባበትም፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል።" ሕዝ 44÷1-2
#ወደ ኖህ መርከብ የገቡት እንሰሳት እንሰሳዊ ጠባያቸውን ሳይለቁ ነው የወጡት ለምሳሌ ወደ ኖህ መርከብ የገባ አንበሳ ሲወጣም የአንበሳነቱን ሥጋ ቦጫቂነቱን ሳይለቅ ወጣ ፣ነብሩም ደም መጣጭነቱን ሳይተው ወጣ ፣በግም ውኃም መጎንጨቱን ሳር ጋጪነቱን ሰይለውጥ ወጣ ::
#በእመቤታችን ምልጃ አምኖና ተማምኖ አማልጂኝ ብሎ በሥሯ የተጠለለባት ሰው ግን እንዲሁ እንደ ኖህ መርከብ በቀደመ ግብሩ አይቆይም ንፉጉ ለጋሽ፣ጨካኙ እሩሩ ፣ ዘማዊው ድንግል ሆኖ ተለወጦ ይገኛል ስለዚህ እመቤታችን ከኖህ መርከብ በእጅጉ ትልቃለች ትበልጥማለች :: ዝም ብለን እንደ ሊቁ
......በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ........ እንበላት።
.............ይቆየን..............
እረድኤትና ቃልኪዳኗ አማላጅነቷም ለዘለዓለሙ ከኛ አይራቅ ...አሜን!
ኃ/ማርያም
👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
#ዓውደ ምሕረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
👆👆👆👆👆👇
#የአሮን በትር ዘኁልቁ 17÷8
ሙሴም ለእስራኤል ልጆች ተናገራቸው፤ አለቆቻቸው ሁሉ አሥራ ሁለት በትሮች፥ እያንዳንዱም አለቃ በየአባቱ ቤት አንድ አንድ በትር፥ ሰጡት፤ የአሮንም በትር በበትሮቻቸው መካከል ነበረች። ሙሴም በትሮቹን በእግዚአብሔር ፊት በምስክሩ ድንኳን ውስጥ አኖራቸው። እንዲህም ሆነ፤ በነጋው ሙሴ ወደ ምስክሩ ድንኳን ውስጥ ገባ፤ እነሆም፥ ለሌዊ ቤት የሆነች #የአሮን_በትር_አቈጠቈጠች_ለመለመችም_አበባም_አወጣች የበሰለ ለውዝም አፈራች። ሙሴም በትሮችን ሁሉ ከእግዚአብሔር ፊት ወደ እስራኤል ልጆች ሁሉ አወጣቸው፤ እነርሱም አዩ፥ እያንዳንዱም በትሩን ወሰደ። እግዚአብሔርም ሙሴን፦ የአሮንን በትር ወደ ምስክሩ ፊት መልስ፤ ማጕረምረማቸው ከእኔ ዘንድ እንዲጠፋ እነርሱም እንዳይሞቱ ለሚያምፁብኝ ልጆች ምልክት ሆና ትጠበቅ አለው።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የማክሰኞ እርሻ ትባላለች የማክሰኞ እርሻ ገበሬ ሳይኮተኩታት ውኃም ሳያጠጣት አብባ አፍርታ ተገኝታለች ይህች የማክሰኞ ዕለት እርሻ የመጀመሪያይቱ ምድር ወይም ጥንተ ምድርም እየተባለች ትጠራለች የሶሪያው ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊም አክሎ በውዳሴው እንዲ ብሏታል #ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበር እንቺ እንደርሷ ነሽ" #አባ ኤፍሬም ሶሪያዊ #ውዳሴ_ማርያም ዘ እሁድ
#የኖህ መርከብ ዘፍ 6፥14
በኖህ መርከብ ፍጥረት ከጥፋት እንደተረፈ በእመቤታችንም ከጥፋት ድኗል ። የኖህ መርከብ ሦስት ክፍሎች ነበሯት እመቤታችንም በሦስት ነገሯ ንጽሕት ነች በሥጋዋ ፣በነፍሷ፣ በሕሊናዋ የጋስጫ ፍሬ አባ ጊዮርጊስ "በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " ድንግል ሆይ በምንና በምን እንመስልሻለን ምሳሌን የለሽም" እንዳለ ምሳሌዎች ሁሉ እመቤታችንን አይመስሏትም(አይመጥኗትም)
#የኖህ መርከብ ስምንት ሰዎችና ብዙ ዐይነት እንሰሳት ገብተውባታል ወጥተውባታል
#በእመቤታች ግን ከኃያላ ከጌታ በቀር ወደ እርሷ ገብቶ የወጣ የለም
#በኖህ መርከብ ሲገባም ሲወጣም በሮቹአን ከፍተው ዘግተው ነው
#እመቤታችን ግን ማንም ለዘላለሙ የተዘጋች ገነት የታተመች ፈሳሽ ነችና ዘላለም እትዕምት ፣ዝግ ፣ድንግል ነች ። ጌታችንንም የጸነሰችው እንዲሁ ዝግ ሆና ነው ስትወልደውም እንዲሁ ዝግ ሆና ነው። " ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ፤ ተዘግቶም ነበር። እግዚአብሔርም፦ ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፥ ሰውም አይገባበትም፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል።" ሕዝ 44÷1-2
#ወደ ኖህ መርከብ የገቡት እንሰሳት እንሰሳዊ ጠባያቸውን ሳይለቁ ነው የወጡት ለምሳሌ ወደ ኖህ መርከብ የገባ አንበሳ ሲወጣም የአንበሳነቱን ሥጋ ቦጫቂነቱን ሳይለቅ ወጣ ፣ነብሩም ደም መጣጭነቱን ሳይተው ወጣ ፣በግም ውኃም መጎንጨቱን ሳር ጋጪነቱን ሰይለውጥ ወጣ ::
#በእመቤታችን ምልጃ አምኖና ተማምኖ አማልጂኝ ብሎ በሥሯ የተጠለለባት ሰው ግን እንዲሁ እንደ ኖህ መርከብ በቀደመ ግብሩ አይቆይም ንፉጉ ለጋሽ፣ጨካኙ እሩሩ ፣ ዘማዊው ድንግል ሆኖ ተለወጦ ይገኛል ስለዚህ እመቤታችን ከኖህ መርከብ በእጅጉ ትልቃለች ትበልጥማለች :: ዝም ብለን እንደ ሊቁ
......በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ........ እንበላት።
.............ይቆየን..............
እረድኤትና ቃልኪዳኗ አማላጅነቷም ለዘለዓለሙ ከኛ አይራቅ ...አሜን!
ኃ/ማርያም
👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
#ዓውደ ምሕረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
👆👆👆👆👆👇
ባለ ታሪክ ኃያሉ ሶምሶም
#ለፍቅር_የተከፈለ መሰዋህትነት
ሶምሶም ከተወለደ ጀምሮ በእራሱ ላይ ምላጭ አርፎበት የማያውቅ የእግዚአብሔር ኃይል በጸጉሩ ላይ ያደረበት እስራኤላውያንን ይጠብቁ ዘንድ ከተነሱ መሳፍንት መካከል ኃያሉ ናዝራዊ ሰው ነበር ::
ከዚህም በኋላ በሶሬቅ ሸለቆ የነበረች ደሊላ የተባለች አንዲት ሴትን ወደደ። የፍልስጥኤማውያንም መኳንንት ወደ እርስዋ ወጥተው፦ እርሱን ሸንግለሽ በእርሱ ያለ ታላቅ ኃይል በምን እንደ ሆነ፥ እኛስ እርሱን ለማዋረድ እናስረው ዘንድ የምናሸንፈው በምን እንደ ሆነ እወቂ፤ እኛም እያንዳንዳችን ሺህ አንድ መቶ ብር ሺህ አንድ መቶ ብር እንሰጥሻለን አሏት።
ደሊላም ሶምሶምን ይህ ከሰው ሁሉ ልዮ የሚያደርግህ የኃይል ምሥጢር ምንድን ነው ? ከወደድከኝ ንገረኝ እያለች ዕለት ዕለት ትነዘንዘው ጀመር ። መጻሕፍ ቅዱስ እንደውም ይህን ንዝነዛዋን እንዲ ሲል ይገልጠዋል “ዕለት ዕለትም በቃልዋ ነዘነዘችው አስቸገረችውም፥ ነፍሱም እስከ ሞት ድረስ ተጨነቀች”መሳ 16፥16
ሶምሶም ከደሊላ ምሥጢር ከሚያስወጣ ጥያቄዋ ለማምለጥ የራሱን ጥረት አድርጓል:: በእርጥብ ጠፈር ብታስሪኝ፣ በአዲስ ገመድም ብትቋጥሪኝ፣ የእራስ ፀጉሬን በችንካር ብትቸነክሪው ኃይሌ ከእኔ ይጠፋል እንደ ሌላም ሰው እሆናለሁ እያለ ምሥጢርም ሳያወጣ ደሊላንም ሳያጣ እስከ ጊዜው ለመቆየት ችሎ ነበር :: “ልባም ሴት ለባልዋ ዘውድ ናት፤ አሳፋሪ ሴት ግን በአጥንቱ ውስጥ እንደ ቅንቅን ናት።” ምሳሌ 12፥4 እንዲል መጻሕፍ አንተ፦ እወድሻለሁ እንዴት ትለኛለህ፥ ልብህ ከእኔ ጋር አይደለም? ስታታልለኝ ይህ ሦስተኛ ጊዜህ ነው፥ ታላቅ ኃይልህም በምን እንደ ሆነ አልነገርኸኝም አለችው። ዕለት ዕለትም በቃልዋ ነዘነዘችው አስቸገረችውም፥ ነፍሱም እስከ ሞት ድረስ ተጨነቀች።
ንዝነዛዋ የበዛበት ሶምሶም የልቡን ሁሉ ገለጠላት የኃይሉ ምንጭ ጸጉሩ እንደሆነና ጸጎሩን ቢላጭ ኃይሉ ከእርሱ እደሚርቅ ነገራት ደሊላም የልቡን ሁሉ እንደገለጠላት ባየች ጊዜ በጕልበትዋ ላይ አስተኛችው በተኛበትም፤ አንድ ሰውም ጠራች፥ እርሱም ሰባቱን የራሱን ጕንጕን (ቁንድላ) ላጨው። ልታዋርደውም ጀመረች፥ ኃይሉም ከእርሱ ሄደ።” ከተኛበት ቀስቅሳም ሶምሶም ሆይ ፍልስጤማውያን መጡብህ አለችው ተነስቼ እንደ ቀድሞ እሆናለው ቢል ኃይል ከእርሱ እርቆልና አንዱን በጡጫ ሌላውን በርግጫ ማለት ተሳነው::ሶምሶምም ለምርኮ ተዳረገ ፍልስጥኤማውያንም ይዘው ዓይኖቹን አወጡት፤ ወደ ጋዛም አምጥተው በናስ ሰንሰለት አሰሩት፤ በግዞትም ሆኖ እህል ይፈጭ ነበር። መሳፍ 16፥21
በጣም ያሳዝናል ሶምሶም ስለ ሴት ፍቅር ሲል ፍቅር እግዚአብሔርን አጥቶታል ኃይሉም ከእርሱ እርቆ ዐይኖቹ ወጥተው ለግዞትም ተዳርጓል
👉ወንድሞች ሶምሶምን ብትሆኑ ምን ታደርጉ ነበር! ?
*ስለ ወደዳችዋት ሴት ምሥጢሩን ታወጡ ነበር?
👉እህቶችስ ደሊላን ብትሆኑ ምን ታደርጉ ነበር?
*ለገንዘብ ብላችሁ ሶምሶምን ትከዱትና ታዋርዱት ነበርን?
❤ እርሶ ቢሆኑ ምን ያደርጋሉ?
#ለነፃ_ሀሳብዎ_እነዚህን_ይጠቀሙ
👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
🤦♀ደሊላና ሶምሶም ዛሬም በጸጸት ሆነው ሀሳቦቻችሁን እየጠበቁ ነው🤦♂
#ዓውደ_ምሕረት_የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
👆👆👆👆👆👆
#ለፍቅር_የተከፈለ መሰዋህትነት
ሶምሶም ከተወለደ ጀምሮ በእራሱ ላይ ምላጭ አርፎበት የማያውቅ የእግዚአብሔር ኃይል በጸጉሩ ላይ ያደረበት እስራኤላውያንን ይጠብቁ ዘንድ ከተነሱ መሳፍንት መካከል ኃያሉ ናዝራዊ ሰው ነበር ::
ከዚህም በኋላ በሶሬቅ ሸለቆ የነበረች ደሊላ የተባለች አንዲት ሴትን ወደደ። የፍልስጥኤማውያንም መኳንንት ወደ እርስዋ ወጥተው፦ እርሱን ሸንግለሽ በእርሱ ያለ ታላቅ ኃይል በምን እንደ ሆነ፥ እኛስ እርሱን ለማዋረድ እናስረው ዘንድ የምናሸንፈው በምን እንደ ሆነ እወቂ፤ እኛም እያንዳንዳችን ሺህ አንድ መቶ ብር ሺህ አንድ መቶ ብር እንሰጥሻለን አሏት።
ደሊላም ሶምሶምን ይህ ከሰው ሁሉ ልዮ የሚያደርግህ የኃይል ምሥጢር ምንድን ነው ? ከወደድከኝ ንገረኝ እያለች ዕለት ዕለት ትነዘንዘው ጀመር ። መጻሕፍ ቅዱስ እንደውም ይህን ንዝነዛዋን እንዲ ሲል ይገልጠዋል “ዕለት ዕለትም በቃልዋ ነዘነዘችው አስቸገረችውም፥ ነፍሱም እስከ ሞት ድረስ ተጨነቀች”መሳ 16፥16
ሶምሶም ከደሊላ ምሥጢር ከሚያስወጣ ጥያቄዋ ለማምለጥ የራሱን ጥረት አድርጓል:: በእርጥብ ጠፈር ብታስሪኝ፣ በአዲስ ገመድም ብትቋጥሪኝ፣ የእራስ ፀጉሬን በችንካር ብትቸነክሪው ኃይሌ ከእኔ ይጠፋል እንደ ሌላም ሰው እሆናለሁ እያለ ምሥጢርም ሳያወጣ ደሊላንም ሳያጣ እስከ ጊዜው ለመቆየት ችሎ ነበር :: “ልባም ሴት ለባልዋ ዘውድ ናት፤ አሳፋሪ ሴት ግን በአጥንቱ ውስጥ እንደ ቅንቅን ናት።” ምሳሌ 12፥4 እንዲል መጻሕፍ አንተ፦ እወድሻለሁ እንዴት ትለኛለህ፥ ልብህ ከእኔ ጋር አይደለም? ስታታልለኝ ይህ ሦስተኛ ጊዜህ ነው፥ ታላቅ ኃይልህም በምን እንደ ሆነ አልነገርኸኝም አለችው። ዕለት ዕለትም በቃልዋ ነዘነዘችው አስቸገረችውም፥ ነፍሱም እስከ ሞት ድረስ ተጨነቀች።
ንዝነዛዋ የበዛበት ሶምሶም የልቡን ሁሉ ገለጠላት የኃይሉ ምንጭ ጸጉሩ እንደሆነና ጸጎሩን ቢላጭ ኃይሉ ከእርሱ እደሚርቅ ነገራት ደሊላም የልቡን ሁሉ እንደገለጠላት ባየች ጊዜ በጕልበትዋ ላይ አስተኛችው በተኛበትም፤ አንድ ሰውም ጠራች፥ እርሱም ሰባቱን የራሱን ጕንጕን (ቁንድላ) ላጨው። ልታዋርደውም ጀመረች፥ ኃይሉም ከእርሱ ሄደ።” ከተኛበት ቀስቅሳም ሶምሶም ሆይ ፍልስጤማውያን መጡብህ አለችው ተነስቼ እንደ ቀድሞ እሆናለው ቢል ኃይል ከእርሱ እርቆልና አንዱን በጡጫ ሌላውን በርግጫ ማለት ተሳነው::ሶምሶምም ለምርኮ ተዳረገ ፍልስጥኤማውያንም ይዘው ዓይኖቹን አወጡት፤ ወደ ጋዛም አምጥተው በናስ ሰንሰለት አሰሩት፤ በግዞትም ሆኖ እህል ይፈጭ ነበር። መሳፍ 16፥21
በጣም ያሳዝናል ሶምሶም ስለ ሴት ፍቅር ሲል ፍቅር እግዚአብሔርን አጥቶታል ኃይሉም ከእርሱ እርቆ ዐይኖቹ ወጥተው ለግዞትም ተዳርጓል
👉ወንድሞች ሶምሶምን ብትሆኑ ምን ታደርጉ ነበር! ?
*ስለ ወደዳችዋት ሴት ምሥጢሩን ታወጡ ነበር?
👉እህቶችስ ደሊላን ብትሆኑ ምን ታደርጉ ነበር?
*ለገንዘብ ብላችሁ ሶምሶምን ትከዱትና ታዋርዱት ነበርን?
❤ እርሶ ቢሆኑ ምን ያደርጋሉ?
#ለነፃ_ሀሳብዎ_እነዚህን_ይጠቀሙ
👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
🤦♀ደሊላና ሶምሶም ዛሬም በጸጸት ሆነው ሀሳቦቻችሁን እየጠበቁ ነው🤦♂
#ዓውደ_ምሕረት_የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
👆👆👆👆👆👆
Forwarded from ፅሐይ
እኔ ደሊላን ብሆን ለገንዘብ ብዬ አልክደዉም ምክንያቱም ብር አላፊ ጠፊ ነው ስለዚህ እሱን ከምክድ ገንዘቡን ቢቀርብኝ እመርጣለሁ
Forwarded from Deleted Account
ሰላም ለእናንተ የክርስቶስ ቤተሰቦች የእማምላክ ወዳጆች በያላችሁበት ሰላማችሁ ብዝት ይበል
እኔ ደሊላ ብሆን ለገንዘብ ብዬ ሶምሶምን አሳልፌ አልሰጠውም ፍልስጤማውያንም እጅጉን ቢያስቸግሩኝ ሊገድሉኝም ቢመጡ እንኳን ሶምሶን የእግዚአብሔር ሀይል ስላለው ይከላከልልኛል ።
ፀጋውን ለማወቅ ፈልጌ እጠይቀዋለሁ ቢነግረኝ ባነግረኝም ግን በምንም ምክንያት አሳልፌ አልሰጠውም ።
እኔ ደሊላ ብሆን ለገንዘብ ብዬ ሶምሶምን አሳልፌ አልሰጠውም ፍልስጤማውያንም እጅጉን ቢያስቸግሩኝ ሊገድሉኝም ቢመጡ እንኳን ሶምሶን የእግዚአብሔር ሀይል ስላለው ይከላከልልኛል ።
ፀጋውን ለማወቅ ፈልጌ እጠይቀዋለሁ ቢነግረኝ ባነግረኝም ግን በምንም ምክንያት አሳልፌ አልሰጠውም ።