#Re #post
‹‹ ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ ፀሃይና ጨረቃን ተመልከት፡፡ ሁለቱንም ማወዳደር አትችልም፡፡ ምክንያቱም ሁለቱም በየጊዜያቸው ዓለምን ያበራሉና፡፡ ››
የእኔ፣ የአንተ፣ የእሱ፣ የእሷ እና የሁላችንም የሕይወት ፍሠት፣ የደስታ ስኬት፣ የኑሮ ተዳፋት፣ እጣ ፋንታ እና ዕድል አንድ አይደለም፡፡ እንደየተፈጥሯችን፣ እንደየመልካችን፣ እንደየአስተሳሰባችን፣ እንደየፍላጎታችን፣ እንደየስጦታችን፣ እንደየአካሄዳችን፣ እንደአጠቃቀማችን ሁለነገራችን፣ ዕጣ ፋንታችን፣ ዕድል ገጠመኛችን ፍፁም የተለያየ ነው፡፡ ከአንድ እናት የወጡ መንታ ልጆች እንኳን ስኬታቸውም ሆነ ውድቀታቸው ይለያያል፡፡ ስለዚህ ራስን ከሌሎች ጋር ማወዳደር አይቻልም፡፡
ለአንዳንዱ በቀለም ትምህርት በሕይወቱ ስኬትን ለመጎናፀፍ ይቀለዋል፡፡ ለሌላው ደሞ ዳገት ይሆንበታል፡፡ ለእከሌ ንግድ የሚሳካለት ሲሆን ለእንቶኔ ደሞ ንግድ ኪሳራ በኪሳራ ያደርጋታል፡፡ ይሄ ማለት ግን በጥረትና በልፋት ነገሮችን ማሳካት አይቻልም ማለት አይደለም፡፡ በልፋትና በጥረት የሚሳካላቸው ሠዎች እንዳሉ ሁሉ የማይሳካለቸውም እልፍ ናቸው፡፡ ስንት ዓመት ለፍተው ፍሬውን ሊያዩ ትንሽ ሲቀራቸው ገደ-ቢስ ሆነው ልፋታቸው መና የቀረ ጥቂቶች አይደሉም፡፡
ለዚህ ጥሩ ምሣሌ የሚሆነው የጨረቃና የፀሃይን ተፈጥሮ ማየት ነው፡፡ አንዱን ካንዱ ማበላለጥ አይቻልም፡፡ ጨረቃን ከፀሃይ ብናሳንስ በድቅድቅ ጨለማ የምታበራውን ብርሃን መካድ ይሆናል፡፡ ጨረቃንም ከፀሃይ ብናስበልጥ የፀሃይን ውለታ አይቶ እንዳላየ ማለፍ ነው የሚሆነው፡፡ ሁለቱም በየራሳቸው ጠቃሚዎቻችን ናቸው፡፡ ሠውን ከሠው ማሳነስም ሆነ ማበላለጥ የተገባ አይደለም፡፡ ሁሉም ሠው ለሃገሩም ሆነ ለዓለም የሚታይና የማይታይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ አለውና፡፡ ምንም እንኳን ታዋቂ ሠዎች ቢሞገሱም በነሱ ስር ግን ብዙ ተራ ሠዎች ለእነሱ እውቅና የድርሻቸውን አዋጥተዋል፡፡ ለዚች ዓለም በየትኛውም ደረጃ ያለ ሠው አስፈላጊ ነው፡፡ አምላክ የሠው ልጅን ወዶና ፈቅዶ ነው የፈጠረው፡፡ በመሆኑም ሁሉም የራሱን አሻራ ጥሎ ያልፋል፡፡
ስለዚህ አበበን ከከበደ ማወዳደር አይቻልም፡፡ አበበም የሚበረታበት ነገር እንዳለው ሁሉ ከበደም የራሱ ጠንካራ ጎን አለው፡፡ በርግጥ ከበደ የሚደክምበትን አበበ ሊበረታበት ይችል ይሆናል፡፡ ይሄ ደሞ ከበደ ከአበበ ያነሠ ነው ማለት አይደለም፡፡ ከበደም በራሱ አቅምና ተፈጥሮ ብርታቱን የሚያሳይበትና የሚነሳበት ጊዜ አለውና፡፡
‹‹ለሁሉም ጊዜ አለው›› እንዳለው ጠቢቡ ሠለሞን እከሌ በስኬት ፏ ብሎ እኔ እስካሁን እዛው ነኝ ብለህ አትዘን፡፡ አንተም ጠንክረህ ከሠራህ ኑሮህን ታበራ ዘንድ ስኬት ካንተ ጎን የሚቆምበት ጊዜ ሩቅ አይደለም፡፡ ዋናው ነገር በስራ እየተጉ ጊዜውን በትዕግስት መጠባበቅ ብቻ ነው፡፡
💚መልካም 💛ቀን ለሁላችን❤️
‹‹ ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ ፀሃይና ጨረቃን ተመልከት፡፡ ሁለቱንም ማወዳደር አትችልም፡፡ ምክንያቱም ሁለቱም በየጊዜያቸው ዓለምን ያበራሉና፡፡ ››
የእኔ፣ የአንተ፣ የእሱ፣ የእሷ እና የሁላችንም የሕይወት ፍሠት፣ የደስታ ስኬት፣ የኑሮ ተዳፋት፣ እጣ ፋንታ እና ዕድል አንድ አይደለም፡፡ እንደየተፈጥሯችን፣ እንደየመልካችን፣ እንደየአስተሳሰባችን፣ እንደየፍላጎታችን፣ እንደየስጦታችን፣ እንደየአካሄዳችን፣ እንደአጠቃቀማችን ሁለነገራችን፣ ዕጣ ፋንታችን፣ ዕድል ገጠመኛችን ፍፁም የተለያየ ነው፡፡ ከአንድ እናት የወጡ መንታ ልጆች እንኳን ስኬታቸውም ሆነ ውድቀታቸው ይለያያል፡፡ ስለዚህ ራስን ከሌሎች ጋር ማወዳደር አይቻልም፡፡
ለአንዳንዱ በቀለም ትምህርት በሕይወቱ ስኬትን ለመጎናፀፍ ይቀለዋል፡፡ ለሌላው ደሞ ዳገት ይሆንበታል፡፡ ለእከሌ ንግድ የሚሳካለት ሲሆን ለእንቶኔ ደሞ ንግድ ኪሳራ በኪሳራ ያደርጋታል፡፡ ይሄ ማለት ግን በጥረትና በልፋት ነገሮችን ማሳካት አይቻልም ማለት አይደለም፡፡ በልፋትና በጥረት የሚሳካላቸው ሠዎች እንዳሉ ሁሉ የማይሳካለቸውም እልፍ ናቸው፡፡ ስንት ዓመት ለፍተው ፍሬውን ሊያዩ ትንሽ ሲቀራቸው ገደ-ቢስ ሆነው ልፋታቸው መና የቀረ ጥቂቶች አይደሉም፡፡
ለዚህ ጥሩ ምሣሌ የሚሆነው የጨረቃና የፀሃይን ተፈጥሮ ማየት ነው፡፡ አንዱን ካንዱ ማበላለጥ አይቻልም፡፡ ጨረቃን ከፀሃይ ብናሳንስ በድቅድቅ ጨለማ የምታበራውን ብርሃን መካድ ይሆናል፡፡ ጨረቃንም ከፀሃይ ብናስበልጥ የፀሃይን ውለታ አይቶ እንዳላየ ማለፍ ነው የሚሆነው፡፡ ሁለቱም በየራሳቸው ጠቃሚዎቻችን ናቸው፡፡ ሠውን ከሠው ማሳነስም ሆነ ማበላለጥ የተገባ አይደለም፡፡ ሁሉም ሠው ለሃገሩም ሆነ ለዓለም የሚታይና የማይታይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ አለውና፡፡ ምንም እንኳን ታዋቂ ሠዎች ቢሞገሱም በነሱ ስር ግን ብዙ ተራ ሠዎች ለእነሱ እውቅና የድርሻቸውን አዋጥተዋል፡፡ ለዚች ዓለም በየትኛውም ደረጃ ያለ ሠው አስፈላጊ ነው፡፡ አምላክ የሠው ልጅን ወዶና ፈቅዶ ነው የፈጠረው፡፡ በመሆኑም ሁሉም የራሱን አሻራ ጥሎ ያልፋል፡፡
ስለዚህ አበበን ከከበደ ማወዳደር አይቻልም፡፡ አበበም የሚበረታበት ነገር እንዳለው ሁሉ ከበደም የራሱ ጠንካራ ጎን አለው፡፡ በርግጥ ከበደ የሚደክምበትን አበበ ሊበረታበት ይችል ይሆናል፡፡ ይሄ ደሞ ከበደ ከአበበ ያነሠ ነው ማለት አይደለም፡፡ ከበደም በራሱ አቅምና ተፈጥሮ ብርታቱን የሚያሳይበትና የሚነሳበት ጊዜ አለውና፡፡
‹‹ለሁሉም ጊዜ አለው›› እንዳለው ጠቢቡ ሠለሞን እከሌ በስኬት ፏ ብሎ እኔ እስካሁን እዛው ነኝ ብለህ አትዘን፡፡ አንተም ጠንክረህ ከሠራህ ኑሮህን ታበራ ዘንድ ስኬት ካንተ ጎን የሚቆምበት ጊዜ ሩቅ አይደለም፡፡ ዋናው ነገር በስራ እየተጉ ጊዜውን በትዕግስት መጠባበቅ ብቻ ነው፡፡
💚መልካም 💛ቀን ለሁላችን❤️
👍3
#እኔ_እሷና_እሱ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
#ማስታወቅያ
እንደሚታወቀው አባል ለመጨመር በምናደርገው ማስታወቅያ አትሰልቹ እባካችሁ እኔ በቀን ውስጥ #post የማደርግበትን ሰአት በቻልኩት መጠን ሁሌ ተመሳሳይ #ሰዓት ላይ ለማድረግ እሞክራለው እናንተም ያቺን ሰዓት ለመከታተል እንዲያመቻችሁ ያዙልኝ #ምርጦቼ በተረፈ መልካም #ንባብ
።።።።።።።
አዲስ ፀባይ ካመጣች ሰነባበተች፡፡
ስሙን ለመጥራት ሰበብ መፈለግ እስክታቆም ወደዋለች።
ይሉኝታዋን እንደ ቆሻሻ ልብስ እስክታወልቅ ልቧን ሰጥታዋለች::
ፍቅር ይሉኝታ ያስጥል የለ? ምን ይሉኝ ፍርኀትን ይገፍ የለ?
እህ... እንደሱ፡፡
የጀማመራት ሰሞን፣ “በረከት እኮ... ሂ ኢዝ ሶ ስማርት... እኛ ቢሮ የሚቆይ አይመስለኝም... ማስተርሱን ይጨርስ እንጂ ዩኤን ይጋደሉበታል... እጁን ስመው ነው የሚቀበሉት”
“ባለፈው ከነ በረከት ጋር ሄድንበት ያልኩህ ካፌ ትዝ ይልሃል? እዚያ ውሰደኝ...”
“በረከት እኮ ካለ ቶሞካ ቡና አይጠጣም...እስቲ አንተም የዚህን
የመንደር ቡና ተውና እዛ ጠጣ...”
“እስቲ ይሄን ዲኦ ተቀባው... የዛሬ ወንዶች እኮ ካለዚህ አይቀቡም ... አሽተውማ... ወንዳ ወንድ ሽታ... ደስ አይልም?”
እያለች ነው የጀመረችው።
አብረን ብዙ ቆይተናል፣ ብዙ ነገሬን አስታምማ ነው የምትኖረው፡እወዳታለሁ፣ “ከእሷ የተሸለ ሴት አላገኝም” እያልኩ ተውኳት፡፡ አለ አይደል... ሲጋራ አጨሳለሁ፤ ጫት እቅማለሁ እጠጣለሁ...
ትወቅ አትወቅ አላውቅም እንጂ ሌላ ሴት ጋር ሄጄም ዐውቃለሁ...
ቢሆን እንደ ሌሎች ሴቶች፣ “ተው...” እያለች አተነዘንዘኝም... “ከነምናምኔ ትወደኛለች...” እያልኩ፡፡
የሚያልፍ ነገር ይሆናል. ትረሳዋለች.. ብዬ ተውኳት፡፡ እሷ ግን ባሰባት፡፡ ስሙን በየቦታው ከመሰንቀር ዘልላ፣ በሐሳብ በመንፈሷ ተሸክማው ትገባና ትወጣ ጀመር፡፡
ሳምንታት ሲያልፉ ነገሩ አድጎ ይሰረስረኝ፤ ይገዘግዘኝ ጀመር፡፡ሁለመናዋ ይቀየር ጀመር፡፡
አንዱን እሑድ ምሽት፣ መጽሐፌን ትቼ አስተውላት ነበር፡፡ አብረን
መኖር ከጀመርን ሦስት ዓመታትን ስላለፈን የምሽት - የቀን የአዘቦት ድርጊቷን ቅደም ተከተሉ ሳይዛነፍ ዐውቀዋለሁ፡፡ ሳምሪ ግዴለሽ ሴት ናት፡፡ ጸጉሯን በየሳምንቱ የውበት ሳሎን ሄዳ
የማታቃጥል፣ ልብሷን ተኩሳ የማትለብስ፣ ኩልና ቻፒስቲክ የሜክአፕ ጥግ የሚመስላት፣ አዲስ ልብስና ጫማ በቀጠሮ የማትገዛ ግዴለሽ ሴት ናት፡፡
ያን ማታ ስታደርግ ያየሁት ነገር፣ እንግዳ የሆነብኝ ለዚህ ነው፡፡
በመተኛትና በመቀመጥ መሃል ሆኜ መጽሐፍ የማነብበት አልጋ ጫፍ ላይ ዕይቼ የማላውቀውን፣ ቄንጠኛና ውድ የሚመስል ፓንት ከመሳዩ ጡት መያዣ ጋር ዘርግታ፣ ልክ ቢለበስ ምን
እንደሚመስል በሚያሳይ ሁኔታ ለረጅም ደቂቃዎች ታየዋለች፡፡ ከዚያ ደግሞ ሁለቱንም ታነሳና፣ ጡት መያዣውን ባደረገችው አሮጌ
የሌሊት ካናቴራ ላይ ደርባ፤ ፓንቱን ደግሞ በተግባቢው ቦታ ላይ፣በሁለት እጆቿ ደገፍ አድርጋ መስታወት ታያለች፡፡
“አዲስ ነው አይደል ይሄ ነገር....?” አልኳት፣ ትኩረቷን ለመስበር፡፡
“እ...?” አለች፣ ፓንቱን ወደ አልጋው ጥላ፣ ከነጡት መያዣዋ ወደ
እኔ እየዞረች፡፡
“ፓንቱና ጡት መያዣው... አዲስ ነው ወይ..?” ራሴን ደገምኩ፡፡
“እ... አዎ... ያምራል አይደል?”
“አዎ... ግን እንዲህ ዓይነት ነገር ስታደርጊ ዐይቼሽ አላውቅም...
ነይ እስቲ...” አልኳት፣ መጽሐፌን ወደ አንደኛው የአልጋው ጥግ ወርውሬ ቀኝ እጄን ዘርግቼ... መጣች፡፡
“ለኔ ነው...?” ፈገግ ብዬ ጠየቅኩ፡፡
“ሃ.ሃ... ታዲያ ለማን ይሆናል...?” እጆቼን ይዛ መለሰች፡፡
“ልበሺውና ልየዋ...”
“አይ... ለነገ ነው ... ማታ ታየዋለህ ...”
ተስፈንጥራ ወደ ቁምሳጥኑ ሄዳ ልብሶቿን አለቅጥ ማተራመስ ጀመረች፡፡
“ምነው...? ምን ሆንሽ...?” አልኩ፣
ባካሄዷ ድንገተኝነት ተገርሜ፡፡
“አይ... ለነገ ልብስ ልምረጥ... ጠዋት መተራመስ አልፈልግም...”
ነገ ስለምትለብሰው ልብስ ስትጨነቅ ዐይቻት አላውቅም፡፡ ጠዋት
ላይ፣ እጇ የገባውን ልብስ አድርጋ፤ እንደነገሩ ሆና እንደምትወጣ
ነው የማውቀው፡፡
ለአፍታ የረሳሁት ጥርጣሬ ሆዴ ውስጥ ተገላበጠ፡፡
ያ ሁሉ ግዴለሽነትዋ የት ገባ? ያልፋል ያልኩት ተባራሪ ስሜቷ መቼ ሥር ሰድዶ ባሕርይዋን መቀየር ጋር ደረሰ? ያን ቀን ነገር እያላመጥኩ አድሬ ነጋልኝ፡፡
ሲነጋ፣ ከጠዋቱ አንድ ሰዐት አልፎ በታክሲ አናገኝም ጭንቀት ተሰቅፌ፣ ቶሎ እንውጣ እያልኩ እማጸናታለሁ፡፡
“ረፈደ ሳምሪ... ቶሎ በይ...”
“በናትህ ልብሴ ሁሉ አስጠላኝ...”
“ትላንት መረጥኩ አላልሽም?”
“አዎ ግን አስጠላኝ...”
“ያ ስኩዌር ስኩዌሩ ሱሪሽ አሪፍ አይደል? እሱን ልበሺ ሳምሪ...”
“አንተ ደግሞ... እሱ በጣም ሰፊ ነው...”
“ሰፊ ልብስ የምትወጂ መስሎኝ?”
“እወድ ነበር አዎ... ግን ሰፊ ልብስ ይበልጥ ያወፍርሻል ብሎኛል..
ማለቴ ብለውኛል... ጓደኞቼ”
ተንተባተበች፡፡ ሲጋራ ልለኩስ በረንዳ ወጣሁ፡፡
የሁለት ሲጋራ ዕድሜ ጠበቅኳት፡፡ አልወጣችም፡፡ በጥልቅ ተነፈስኩና ወደቤት ገባሁ፡፡
"ሳምሪ!”
“ጨርሻለሁ!”
እየተንደፋደፈች ሁሉ ነገሯን አጣብቆ ይዞ፣ ጾታዋን በአንድ ዕይታ ብቻ የሚያረጋግጥ እጅግ ጠባብ ቢጫ ሱሪ ለብሳለች፡፡
ዐይቼው አላውቅም፡፡
ጸጉሯን ሙልጭ አድርጋ አሲዛዋለች፡፡
ይሄንንም አላውቀውም፡፡
ማታ ያየሁት ጡት መያዣዋ ጫፍ ከለበሰችው ነጭ ሹራብ አፈንግጦ ይታያል፡፡ ይሄንንም አልለመድኩትም፡፡
ያለ ቦታዋ የምትወድቅ አንዲት ዘለላ ጸጉር እስክትረብሻት ድረስ፣
ተጨንቃና ተጠባ፣ ያመለጡ ጸጉሮች እንደሌሉ ለማረጋገጥ ጸጉሯን ትሞዥቃለች፡፡ ከኩል ውጪ የማታውቀው ሚስቴ... በሜክአፕ ተዥጎርጉራ የአውሮፓ እግር ኳስ ቡድን ደጋፊ መስላ መጥታለች፡፡
“ምንድነው ዛሬ እንደዚህ ለየት ያልሽው?” አልኩ፣ ታክሲው መጠበቂያው ጋር ስንደርስ፡፡
“ስብሰባ አለን... እኔ፣ ቃልኪዳንና በረከት፤ ስብሰባ አለን..."
በረከት....!
ጥርሴን እያንገጫገጭኩ ታክሲ ውስጥ ገባሁ፡፡
****
በዚያ ሳምንት ቅዳሜ ጠዋት ለአራተኛ ጊዜ ቃልኪዳንና በረከት ቤታችን እንደሚመጡ ነገረችኝ፡፡
“ያው እንዳልኩህ በረከትም ይመጣል... ስምንት ሰዐት ነው የሚደርሱት... ጥቁር ስንዴ ዳቦ እወዳለሁ ሲል ስለነበር እሱን
ከባልትናው ቤት አዝኜለታለሁ... ማለቴ ቃልም ስለምትወድ...ይዤ እመጣለሁ ... ልጅቷን ቤቱን በጠዋት መጥተሽ አጽጂ ብያት ነበር... የት አባቷ ናት በናትህ?...”
ለስምንት ሰዐት ቀጠሮ፣ ከጠዋቱ ሁለት ሰዐት ተኩል ላይ ምን እንዲህ እንደሚያደርጋት ዐውቃለሁ፡፡
ድፎ ዳቦው... ጽዳቱ... ለወትሮው ከሰዐት የምትመጣውን ተመላላሽ
ሰራተኛችንን በሌሊት ድረሺ ማለቱ... ከሁለት ቀን በፊት የተጀመረው ባለ ስድስት ወጡ ድግስ...ግልጽ ነበር፡፡
ዳቦውን ይዛ ስትመጣ ሦስት ሰዐት አልፎ፣ ልጅቱም መጥታ ጽዳቱን አጧጡፋ ነበር፡፡
ስምንት ሰዐት ከሩብ ሆነ፡፡
ተሞልጮ የታሰረ ጸጉሯን ዐሥር ጊዜ እየነካካች፣ ጥብቅ ያለ ቀሚሷ
ያወጣውን ሞላላ ቂጧን ሠላሳ ጊዜ በመስታወት እያየች፣ በሜክአፕ
ያበደ ፊቷን መቶ ጊዜ እያስተካከለች፣ በመቁነጥነጥ ስትጠብቅ ቆይታ ስምንት ከሩብ ላይ በራችን ተንኳኳ፡፡
ሚስቴን ሳይነጥቀኝ የወሰደውን፣ ሳይቀማኝ ያገኛትን ሰው ላየው ነው፡፡ ፍቅሬን አጠገቤ እያለች እንቁልልጭ ያደረገብኝን ሰው ልተዋወቀው ነው፡፡
በሩን ከፍታ ቃልኪዳንን (በኔ ግምት ብቻውን መጣ እንዳይባል የገባች ሰበብ ናት) ካቀፈቻት በኋላ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
#ማስታወቅያ
እንደሚታወቀው አባል ለመጨመር በምናደርገው ማስታወቅያ አትሰልቹ እባካችሁ እኔ በቀን ውስጥ #post የማደርግበትን ሰአት በቻልኩት መጠን ሁሌ ተመሳሳይ #ሰዓት ላይ ለማድረግ እሞክራለው እናንተም ያቺን ሰዓት ለመከታተል እንዲያመቻችሁ ያዙልኝ #ምርጦቼ በተረፈ መልካም #ንባብ
።።።።።።።
አዲስ ፀባይ ካመጣች ሰነባበተች፡፡
ስሙን ለመጥራት ሰበብ መፈለግ እስክታቆም ወደዋለች።
ይሉኝታዋን እንደ ቆሻሻ ልብስ እስክታወልቅ ልቧን ሰጥታዋለች::
ፍቅር ይሉኝታ ያስጥል የለ? ምን ይሉኝ ፍርኀትን ይገፍ የለ?
እህ... እንደሱ፡፡
የጀማመራት ሰሞን፣ “በረከት እኮ... ሂ ኢዝ ሶ ስማርት... እኛ ቢሮ የሚቆይ አይመስለኝም... ማስተርሱን ይጨርስ እንጂ ዩኤን ይጋደሉበታል... እጁን ስመው ነው የሚቀበሉት”
“ባለፈው ከነ በረከት ጋር ሄድንበት ያልኩህ ካፌ ትዝ ይልሃል? እዚያ ውሰደኝ...”
“በረከት እኮ ካለ ቶሞካ ቡና አይጠጣም...እስቲ አንተም የዚህን
የመንደር ቡና ተውና እዛ ጠጣ...”
“እስቲ ይሄን ዲኦ ተቀባው... የዛሬ ወንዶች እኮ ካለዚህ አይቀቡም ... አሽተውማ... ወንዳ ወንድ ሽታ... ደስ አይልም?”
እያለች ነው የጀመረችው።
አብረን ብዙ ቆይተናል፣ ብዙ ነገሬን አስታምማ ነው የምትኖረው፡እወዳታለሁ፣ “ከእሷ የተሸለ ሴት አላገኝም” እያልኩ ተውኳት፡፡ አለ አይደል... ሲጋራ አጨሳለሁ፤ ጫት እቅማለሁ እጠጣለሁ...
ትወቅ አትወቅ አላውቅም እንጂ ሌላ ሴት ጋር ሄጄም ዐውቃለሁ...
ቢሆን እንደ ሌሎች ሴቶች፣ “ተው...” እያለች አተነዘንዘኝም... “ከነምናምኔ ትወደኛለች...” እያልኩ፡፡
የሚያልፍ ነገር ይሆናል. ትረሳዋለች.. ብዬ ተውኳት፡፡ እሷ ግን ባሰባት፡፡ ስሙን በየቦታው ከመሰንቀር ዘልላ፣ በሐሳብ በመንፈሷ ተሸክማው ትገባና ትወጣ ጀመር፡፡
ሳምንታት ሲያልፉ ነገሩ አድጎ ይሰረስረኝ፤ ይገዘግዘኝ ጀመር፡፡ሁለመናዋ ይቀየር ጀመር፡፡
አንዱን እሑድ ምሽት፣ መጽሐፌን ትቼ አስተውላት ነበር፡፡ አብረን
መኖር ከጀመርን ሦስት ዓመታትን ስላለፈን የምሽት - የቀን የአዘቦት ድርጊቷን ቅደም ተከተሉ ሳይዛነፍ ዐውቀዋለሁ፡፡ ሳምሪ ግዴለሽ ሴት ናት፡፡ ጸጉሯን በየሳምንቱ የውበት ሳሎን ሄዳ
የማታቃጥል፣ ልብሷን ተኩሳ የማትለብስ፣ ኩልና ቻፒስቲክ የሜክአፕ ጥግ የሚመስላት፣ አዲስ ልብስና ጫማ በቀጠሮ የማትገዛ ግዴለሽ ሴት ናት፡፡
ያን ማታ ስታደርግ ያየሁት ነገር፣ እንግዳ የሆነብኝ ለዚህ ነው፡፡
በመተኛትና በመቀመጥ መሃል ሆኜ መጽሐፍ የማነብበት አልጋ ጫፍ ላይ ዕይቼ የማላውቀውን፣ ቄንጠኛና ውድ የሚመስል ፓንት ከመሳዩ ጡት መያዣ ጋር ዘርግታ፣ ልክ ቢለበስ ምን
እንደሚመስል በሚያሳይ ሁኔታ ለረጅም ደቂቃዎች ታየዋለች፡፡ ከዚያ ደግሞ ሁለቱንም ታነሳና፣ ጡት መያዣውን ባደረገችው አሮጌ
የሌሊት ካናቴራ ላይ ደርባ፤ ፓንቱን ደግሞ በተግባቢው ቦታ ላይ፣በሁለት እጆቿ ደገፍ አድርጋ መስታወት ታያለች፡፡
“አዲስ ነው አይደል ይሄ ነገር....?” አልኳት፣ ትኩረቷን ለመስበር፡፡
“እ...?” አለች፣ ፓንቱን ወደ አልጋው ጥላ፣ ከነጡት መያዣዋ ወደ
እኔ እየዞረች፡፡
“ፓንቱና ጡት መያዣው... አዲስ ነው ወይ..?” ራሴን ደገምኩ፡፡
“እ... አዎ... ያምራል አይደል?”
“አዎ... ግን እንዲህ ዓይነት ነገር ስታደርጊ ዐይቼሽ አላውቅም...
ነይ እስቲ...” አልኳት፣ መጽሐፌን ወደ አንደኛው የአልጋው ጥግ ወርውሬ ቀኝ እጄን ዘርግቼ... መጣች፡፡
“ለኔ ነው...?” ፈገግ ብዬ ጠየቅኩ፡፡
“ሃ.ሃ... ታዲያ ለማን ይሆናል...?” እጆቼን ይዛ መለሰች፡፡
“ልበሺውና ልየዋ...”
“አይ... ለነገ ነው ... ማታ ታየዋለህ ...”
ተስፈንጥራ ወደ ቁምሳጥኑ ሄዳ ልብሶቿን አለቅጥ ማተራመስ ጀመረች፡፡
“ምነው...? ምን ሆንሽ...?” አልኩ፣
ባካሄዷ ድንገተኝነት ተገርሜ፡፡
“አይ... ለነገ ልብስ ልምረጥ... ጠዋት መተራመስ አልፈልግም...”
ነገ ስለምትለብሰው ልብስ ስትጨነቅ ዐይቻት አላውቅም፡፡ ጠዋት
ላይ፣ እጇ የገባውን ልብስ አድርጋ፤ እንደነገሩ ሆና እንደምትወጣ
ነው የማውቀው፡፡
ለአፍታ የረሳሁት ጥርጣሬ ሆዴ ውስጥ ተገላበጠ፡፡
ያ ሁሉ ግዴለሽነትዋ የት ገባ? ያልፋል ያልኩት ተባራሪ ስሜቷ መቼ ሥር ሰድዶ ባሕርይዋን መቀየር ጋር ደረሰ? ያን ቀን ነገር እያላመጥኩ አድሬ ነጋልኝ፡፡
ሲነጋ፣ ከጠዋቱ አንድ ሰዐት አልፎ በታክሲ አናገኝም ጭንቀት ተሰቅፌ፣ ቶሎ እንውጣ እያልኩ እማጸናታለሁ፡፡
“ረፈደ ሳምሪ... ቶሎ በይ...”
“በናትህ ልብሴ ሁሉ አስጠላኝ...”
“ትላንት መረጥኩ አላልሽም?”
“አዎ ግን አስጠላኝ...”
“ያ ስኩዌር ስኩዌሩ ሱሪሽ አሪፍ አይደል? እሱን ልበሺ ሳምሪ...”
“አንተ ደግሞ... እሱ በጣም ሰፊ ነው...”
“ሰፊ ልብስ የምትወጂ መስሎኝ?”
“እወድ ነበር አዎ... ግን ሰፊ ልብስ ይበልጥ ያወፍርሻል ብሎኛል..
ማለቴ ብለውኛል... ጓደኞቼ”
ተንተባተበች፡፡ ሲጋራ ልለኩስ በረንዳ ወጣሁ፡፡
የሁለት ሲጋራ ዕድሜ ጠበቅኳት፡፡ አልወጣችም፡፡ በጥልቅ ተነፈስኩና ወደቤት ገባሁ፡፡
"ሳምሪ!”
“ጨርሻለሁ!”
እየተንደፋደፈች ሁሉ ነገሯን አጣብቆ ይዞ፣ ጾታዋን በአንድ ዕይታ ብቻ የሚያረጋግጥ እጅግ ጠባብ ቢጫ ሱሪ ለብሳለች፡፡
ዐይቼው አላውቅም፡፡
ጸጉሯን ሙልጭ አድርጋ አሲዛዋለች፡፡
ይሄንንም አላውቀውም፡፡
ማታ ያየሁት ጡት መያዣዋ ጫፍ ከለበሰችው ነጭ ሹራብ አፈንግጦ ይታያል፡፡ ይሄንንም አልለመድኩትም፡፡
ያለ ቦታዋ የምትወድቅ አንዲት ዘለላ ጸጉር እስክትረብሻት ድረስ፣
ተጨንቃና ተጠባ፣ ያመለጡ ጸጉሮች እንደሌሉ ለማረጋገጥ ጸጉሯን ትሞዥቃለች፡፡ ከኩል ውጪ የማታውቀው ሚስቴ... በሜክአፕ ተዥጎርጉራ የአውሮፓ እግር ኳስ ቡድን ደጋፊ መስላ መጥታለች፡፡
“ምንድነው ዛሬ እንደዚህ ለየት ያልሽው?” አልኩ፣ ታክሲው መጠበቂያው ጋር ስንደርስ፡፡
“ስብሰባ አለን... እኔ፣ ቃልኪዳንና በረከት፤ ስብሰባ አለን..."
በረከት....!
ጥርሴን እያንገጫገጭኩ ታክሲ ውስጥ ገባሁ፡፡
****
በዚያ ሳምንት ቅዳሜ ጠዋት ለአራተኛ ጊዜ ቃልኪዳንና በረከት ቤታችን እንደሚመጡ ነገረችኝ፡፡
“ያው እንዳልኩህ በረከትም ይመጣል... ስምንት ሰዐት ነው የሚደርሱት... ጥቁር ስንዴ ዳቦ እወዳለሁ ሲል ስለነበር እሱን
ከባልትናው ቤት አዝኜለታለሁ... ማለቴ ቃልም ስለምትወድ...ይዤ እመጣለሁ ... ልጅቷን ቤቱን በጠዋት መጥተሽ አጽጂ ብያት ነበር... የት አባቷ ናት በናትህ?...”
ለስምንት ሰዐት ቀጠሮ፣ ከጠዋቱ ሁለት ሰዐት ተኩል ላይ ምን እንዲህ እንደሚያደርጋት ዐውቃለሁ፡፡
ድፎ ዳቦው... ጽዳቱ... ለወትሮው ከሰዐት የምትመጣውን ተመላላሽ
ሰራተኛችንን በሌሊት ድረሺ ማለቱ... ከሁለት ቀን በፊት የተጀመረው ባለ ስድስት ወጡ ድግስ...ግልጽ ነበር፡፡
ዳቦውን ይዛ ስትመጣ ሦስት ሰዐት አልፎ፣ ልጅቱም መጥታ ጽዳቱን አጧጡፋ ነበር፡፡
ስምንት ሰዐት ከሩብ ሆነ፡፡
ተሞልጮ የታሰረ ጸጉሯን ዐሥር ጊዜ እየነካካች፣ ጥብቅ ያለ ቀሚሷ
ያወጣውን ሞላላ ቂጧን ሠላሳ ጊዜ በመስታወት እያየች፣ በሜክአፕ
ያበደ ፊቷን መቶ ጊዜ እያስተካከለች፣ በመቁነጥነጥ ስትጠብቅ ቆይታ ስምንት ከሩብ ላይ በራችን ተንኳኳ፡፡
ሚስቴን ሳይነጥቀኝ የወሰደውን፣ ሳይቀማኝ ያገኛትን ሰው ላየው ነው፡፡ ፍቅሬን አጠገቤ እያለች እንቁልልጭ ያደረገብኝን ሰው ልተዋወቀው ነው፡፡
በሩን ከፍታ ቃልኪዳንን (በኔ ግምት ብቻውን መጣ እንዳይባል የገባች ሰበብ ናት) ካቀፈቻት በኋላ
👍5