አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
573 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#እውር_እና_እውር
:
:
:

«ሲመሽም ጠጣለው ባንቺ ምክንያት፣
ሲነጋም ጠጣለው ባንቺ ምክንያት፣
ግን ዛሬም አልቻልኩም አንቺን መርሳት።»
:
:

እንደዚህ ሚለውን እርባነ ቢስ ዘፈን ከሰማ በኋላ፣
አፍቃሪው በሞላ፣
ፍቅረኛዬ ባላት ገና እንደተከዳ፣
ባለጌ ወንበር ላይ እግሩን አነባብሮ ጂኑን እያስቀዳ፣
ጠዋትና ማታ መጠጣት ጀመረ፣
እንቶ ፈንቶ ሰምቶ ሱሰኛ ሆኖ ቀረ።
:
:

እውር እና እውር ተያይዞ ገደል፣
ማለት ይሄስ አይደል።
:
:

ሲመሽ እየጠጣ ሲነጋ እየጠጣ እንዲ ብሎ መቀኘት፣
«ሱሰኛ» ነው እንዳይባል ሴትን ማመካኘት፣
የራስን ደካማ በሰው ላይ መለጠፍ፣
በሴት ላይ መለጠፍ፣
እንኳን ለንጉርጉሮ ለማውራትም ሲቀፍ።
:
:

በርግጥ ሰው ይጎዳል በርግጥ ሰው ያደማል፣
በጊዜ ሂደት ውስጥ ሁሉም ይታከማል።
ያመኑት ሲከዳ ምንም ቢቆረጥም፣
ላያስችል አይሰጥም።
:
:

ላንድ ሰሞን ቁስል ቀናቶች ሲያልፉ ለሚሽር ዳግመኛ፣
ጠዋትና ማታ መጠጥ እየላፉ ከመሆን ሱሰኛ፣
ብቅልና ብሶት ሆድን ከሚፈጀው፣
ባለን መደሰቱ እሱ ነው ሚበጀው።
:
:

በዛሬ መገፋት ዛሬን የወደቁ፣
ነገ ካልተነሱ ሊያውም እየሳቁ፣
ይቺን ቀን ለመርሳት መጠጥ ቤት ከሮጡ፣
ቀን በቀን ከጠጡ፣
የነጋቸው ገዳይ የራሳቸው ዓለም፣
እራሳቸው እንጂ ትናንት የጣላቸው ገፊው እጅ አይደለም።
:
:

ሰውን አመካኝቶ ቀን በቀን መጠጣት፣
እራስን ማታለል ማንነትን ማጣት፣
ወድቆ አለመነሳት፣
በጣም ትልቅ ጥፋት፣
ከመሆን ባሻገር፣
ከቶ አያስደፍርም ጥምብዝ ብሎ ሰክሮ
እሷ ናት ምክንያቴ ብሎ ለመናገር።

🔘ሄኖክ ብርሃኑ🔘


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👏128😢1