#አድዋ
የሰው ልጅ ክቡር
ሰው መሆን ክቡር
ሰው ሞቷል – ሰው ሊያድን፣
ሰውን ሲያከብር
በደግነት፣ በፍቅር፣ በክብር ተጠርቶ፣
በክብር ይሄዳል፥ ሰው ሊኖር ሰው ሞቶ፤
የተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነፃነት፣
ሰው ተከፍሎበታል ከደምና ካአጥንት፣
ስንት ወገን ወደቀ በነፃነት ምድር
ትናገር አድዋ፣ ትናገር ትመስክር፣
ትናገር አድዋ፣ ትናገር አገሬ፤
እንዴት እንደቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬ፤
በኩራት፣ በክብር፣ በደስታ፣ በፍቅር፣
በድል እኖራለሁ ይኧው በቀን በቀን
ደሞ መከራውን ያን ሁሉ ሰቀቀን።
አድዋ ዛሬ ናት አድዋ ትናንት፣
መቼ ተነሱና የወዳደቁት፣
ምስጋና ለእነሱ ለአድዋ ጀግኖች፣
ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች
የጥቁር ድል አምባ፣ አድዋ
አፍሪካ፣
እምዬ ኢትዮጵያ
ተናገሪ…
የድል ታሪክሽን አውሪ።
#እጅጋየሁ_ሽባባው
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
የሰው ልጅ ክቡር
ሰው መሆን ክቡር
ሰው ሞቷል – ሰው ሊያድን፣
ሰውን ሲያከብር
በደግነት፣ በፍቅር፣ በክብር ተጠርቶ፣
በክብር ይሄዳል፥ ሰው ሊኖር ሰው ሞቶ፤
የተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነፃነት፣
ሰው ተከፍሎበታል ከደምና ካአጥንት፣
ስንት ወገን ወደቀ በነፃነት ምድር
ትናገር አድዋ፣ ትናገር ትመስክር፣
ትናገር አድዋ፣ ትናገር አገሬ፤
እንዴት እንደቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬ፤
በኩራት፣ በክብር፣ በደስታ፣ በፍቅር፣
በድል እኖራለሁ ይኧው በቀን በቀን
ደሞ መከራውን ያን ሁሉ ሰቀቀን።
አድዋ ዛሬ ናት አድዋ ትናንት፣
መቼ ተነሱና የወዳደቁት፣
ምስጋና ለእነሱ ለአድዋ ጀግኖች፣
ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች
የጥቁር ድል አምባ፣ አድዋ
አፍሪካ፣
እምዬ ኢትዮጵያ
ተናገሪ…
የድል ታሪክሽን አውሪ።
#እጅጋየሁ_ሽባባው
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
#አድዋ
ዋ! ... ያቺ ዓድዋ
ዋ! ...
ዓድዋ ሩቋ፣
የአለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋ፣
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ።
ዓድዋ...
ባንቺ ብቻ ሕልውና፣
በትዝታሽ ብፅዕና፣
በመስዋዕት ክንድሽ ዜና፣
አበው ታደሙ እንደገና።
ዋ!
ዓድዋ የዘር ዐፅመ ርስቷ፣
የደም ትቢያ መቀነቷ።
በሞት ከባርነት ሥርየት፣
በደም በነፃነት ስለት፣
አበው የተሰውብሽ ለት።
ዓድዋ!
የኩሩ ትውልድ ቅርስዋ፣
የኢትዮጵያነት ምስክርዋ።
ዓድዋ
የኩሩ ደም ባንቺ ጽዋ፣
ታድማ በመዘንበልዋ።
ዐፅምሽ በትንሳኤ ንፋስ፣
ደምሽ በነፃነት ሕዋስ።
ሲቀሰቀስ ትንሳኤዋ፣
ተግ ሲል ሲንር ትቢያዋ፣
ብር ትር ሲል ጥሪዋ፣
ድው እልም ሲል ጋሻዋ፣
ሲያስተጋባ ከበሮዋ፣
ሲያስገመግም ዳኘው መድፍዋ።
ያባ መቻል ያባ ዳኘው፣
ያባ ነፍሶ ያባ ቃኘው፣
ያባ በለው በለው ሲለው፣
በለው በለው በለው በለው።
ዋ! ... ዓድዋ ...
ያንቺን ፅዋ ያንቺን አይጣል፣
ማስቻል ያለው አባ መቻል።
በዳኘው ልብ በአባ መላው፣
በገበየሁ በአባ ጎራው፣
በአባ ነፍሶ በአባ ቃኘው፣
በለው ብሎ በለው በለው።
ዋ! ... ዓድዋ ...
ዓድዋ የትናንትናዋ፣
ይኸው ባንቺ ሕልውና፣
በትዝታሽ ብፅዕና፣
በመስዋዕት ክንድሽ ዝና፣
በነፃነት ቅርስሽ ዜና፣
አበው ተነሱ እንደገና።
ዋ! ... ያቺ ዓድዋ፣
ዓድዋ ሩቅዋ ፣
የአለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋ፣
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ።
ዓድዋ ...
🔘ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን🔘
💚 💛 ❤️
ዋ! ... ያቺ ዓድዋ
ዋ! ...
ዓድዋ ሩቋ፣
የአለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋ፣
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ።
ዓድዋ...
ባንቺ ብቻ ሕልውና፣
በትዝታሽ ብፅዕና፣
በመስዋዕት ክንድሽ ዜና፣
አበው ታደሙ እንደገና።
ዋ!
ዓድዋ የዘር ዐፅመ ርስቷ፣
የደም ትቢያ መቀነቷ።
በሞት ከባርነት ሥርየት፣
በደም በነፃነት ስለት፣
አበው የተሰውብሽ ለት።
ዓድዋ!
የኩሩ ትውልድ ቅርስዋ፣
የኢትዮጵያነት ምስክርዋ።
ዓድዋ
የኩሩ ደም ባንቺ ጽዋ፣
ታድማ በመዘንበልዋ።
ዐፅምሽ በትንሳኤ ንፋስ፣
ደምሽ በነፃነት ሕዋስ።
ሲቀሰቀስ ትንሳኤዋ፣
ተግ ሲል ሲንር ትቢያዋ፣
ብር ትር ሲል ጥሪዋ፣
ድው እልም ሲል ጋሻዋ፣
ሲያስተጋባ ከበሮዋ፣
ሲያስገመግም ዳኘው መድፍዋ።
ያባ መቻል ያባ ዳኘው፣
ያባ ነፍሶ ያባ ቃኘው፣
ያባ በለው በለው ሲለው፣
በለው በለው በለው በለው።
ዋ! ... ዓድዋ ...
ያንቺን ፅዋ ያንቺን አይጣል፣
ማስቻል ያለው አባ መቻል።
በዳኘው ልብ በአባ መላው፣
በገበየሁ በአባ ጎራው፣
በአባ ነፍሶ በአባ ቃኘው፣
በለው ብሎ በለው በለው።
ዋ! ... ዓድዋ ...
ዓድዋ የትናንትናዋ፣
ይኸው ባንቺ ሕልውና፣
በትዝታሽ ብፅዕና፣
በመስዋዕት ክንድሽ ዝና፣
በነፃነት ቅርስሽ ዜና፣
አበው ተነሱ እንደገና።
ዋ! ... ያቺ ዓድዋ፣
ዓድዋ ሩቅዋ ፣
የአለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋ፣
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ።
ዓድዋ ...
🔘ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን🔘
💚 💛 ❤️
#አድዋ_ዛሬ_ናት_አድዋ_ትላንት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
(አንቀፅ 17 ፡ እኛም መስኮታችንን አንከፍትም፣ እናንተም ሚስቶቻችንን አትዩ ፡)
ጣሊያን ኢትዮጵያን ወርራ አምስት ዓመት ፍዳዋን በልታ፣ ፍዳችንን ስታሰበላን አያቴ እሳት የላሰ
የውስጥና የውጭ አርበኛ ነበር። በጦር ሜዳ ብትሉ አንድ ባታሊዮን ጦር ጭጭ ምጭጭ ያደረገ
ጀግና ሲሉት፣ “ኤዲያ ምን አላት እቺ” ይላል !! በከተማ ብትሉ" ጠላት መኝታ ቤት ሳይቀር የተቀመጠ ሚስጥር ፈልፍሎ ሲያወጣ አጀብ ያስብል ነበር። ታዲያ በአያቴና በቆራጥ አርበኞች ትግል ፋሺስት ኢጣሊያንን ከሀገር ከተባረረ በኋላ፣ ለአገር በሠራው ታላቅ ጀብዱ፣ በድል አጥቢያ ጃንሆይ ራሳቸው አስጠርተው አሁን የጣልያን ኤምባሲ የሚባለው የተገነባበትን ቦታ በሙሉ ከታላቅ ክብርና ምስጋና
ጋር በሽልማት ለኢያቴ ሰጡት !
አያቴ እዚሁ በሽልማት የተሰጠው ቦታ ላይ ትንሽ ጎጆ ቀልሶና፣ የተረፈው ሜዳ ላይ የቆሎ ዘርቶ
ሲኖር፣ አንድ ቀን የጃንሆይ መልዕክተኞች ሲገሰግሱ ቤቱ ድረስ መጡና፣
“እዚህ በቆሎ የዘራህበት ቦታ ላይ የንባሲዮን ሊሰራሰት ነውና መድረሻህን ፈልግ ብለውሃል ጃንሆይ አሉት።
“ኧረ ውሰዱት ደሞ ለሞላ ቦታ አላቸው። ትንሽ ቆይቶ፣ “ይሄ ግን 'የንምባሲዮን' ያላችሁት ነገር መንግስት ነው ?” ሲል ጠየቀ።
“አይደለም !"
“አሃ ተማሪ ቤት መሆን አለበት :"
“አይደለም!”
ታዲያ ምንደን ነው ቤተስክያን ይሆን እንዴ ?" ሲል ግር ብሎት ጠየቀ።
"ኤማቢሲዎን ማለትንጉሥ የፈቀዱላቸው የውጭ አገር መኳንት እና መሳፍንት አገራቸውን
መስለው የሚቀመጡበት እና አንዳንድ የመንግሥት ሥራዎችን የሚከውኑበት ማረፊያ ነው" አሉት
ሳኔ ዕክተኞቹ አንዱ። ከመልክተኞቹ አንዱ።
"በቃ ?" ሲል ጠየቀ አያቴ በግርምት።
"በቃ!"
"እኮ ፈረንጆች ይሄን ሁሉ ቦታ አጥረው ቁጭ ሊሉ ነው” አለ እንደገና በታላቅ ግርምት።
"አዎ ! ይሄ የምባሲዮን ... የወከላቸው አገር የማይደፈር ግዛት ነው”
እንዲያ ድንበራችን ላይ ያባረርነውን ጠላት መናገሻችን ላይ አርደንለት ጋርደንለት ልናስቀምጠው ነው በለኛ አለ አያቴ በቁጭት።
መልዕከተኞቹ አያቴ ላይ ሳቁበት። ስለኤምባሲ ያለው እውቀት አነስተኛ መሆኑን በመገንዘባቸው
ድፍን ሁለት ሰዓት ስለኤምባሲ ተግባርና ለአጎራችን ስላለው ጠቀሜታ በዝርዝር አወሩት።
ተግባብተው ሊለያዩ ሲሉ ግን ነገር ተበላሽ።ጉድፈላ። አገር ተሸበረ።ድንገት ነው ነገሩ የተመሰቃቀለው
ከሆነስ ሆነና የማን አገር ኤምባሲዮን ነው ?" ሲል ጠየቀ አያቴ፣
“ጥልያን” ብለው መለሱለት።
"ጥልያን ጥሊያን ... እኮ ጥሊያን ይሄ ፋሽስት የነበረው" አለ አያቴ ማመን አቅቶት።
"እንዴታ አሁን በሰላም መጥተዋል”
አያቴ ሰይጣኑ ተነሳ። ተንደርድሮ ምንሽሩን መዥረጥ አደረገና ለግማሽ ሰዓት ያህል ፎክሮ ሲያበቃ፣
"ባንዳ ሁላ…” ብሎ የጃንሆይን መልዕክተኞች ማሳደድ ጀመረ !
ጥሎብን መከተል እንወዳለን። መንገድ ላይ ድንገት አያቴን ያዩ ሁሉ፡ ገና የአርበኝነት ስሜቱ
ያልበረደላቸው፣ እንዲሁም አርበኝነት ያመለጣቸው፣ እንደገና እድሉን አገኘን በማለት ምንሽራቸውን አፈፍ እያደረጉ፣ “ያዘው…" እያሉ ላይጠቅማቸው አያቴን ተቀላቅለው የንጉሱን መልእክተኞች ማሳደድ ጀመሩ። መቼስ አዲሳባ እንደዛን ቀን ተፎክሮባትም፣ ተሸልሎባትም አያውቅም ሲሉ ሁኔታውን የታዘቡ፡፡
አያቴ ቁጣው መለስ ሲል ዞሮ ቢመሰከት ድፍን የአዲስ አበባ ወንድ ተከትሎታል።
“ምን ሆናችሁ” ቢላቸው አያቴ፣ “አይ ሩጫው ወደ ቤተ መንግሥት መሆኑን ስንሰማ ነው
የተከተልኛችሁ” አሉ !!
አያቴ የተከታዩን ብዛት አየና በዛው ሸፈተ ! ስሙ የገነነ ሽፍታም ሆነ ! ስሙ ከተጠራ እንኳን ኢትዮጵያ
ምድር ያሉት ሮም የተቀጡትም ጥልያኖች ወባ እንደያዘው እየተንዘፈዘፉ ንሰሃ ይገባሉ ! ጭራሽ የኤምባሲው ግንባታ ሲጀመር በወርም በሳምንትም በል ሲለው በየሦስት ቀኑ ብቅ እያለ ይሄን ጣልያን ሁሉ ይፈጀው ጀመረ !!
ጃንሆይ በበኩላቸው አያቴን በዲፕሎማሲ ማሳመን መርጠው መልዕክት ላኩበት። በድፍረት ከነጎፈረ ጸገሩና ከነምንሽሩ ፊታቸው ቀርቦ፤ "ጃንሆይ ትላንት ይሄን ፋሽስት፣ እንኳን አሳረርከው' ብዬ የሸለሙኝን ቦታ ዛሬ ከኔ ነጥቀው ላባረርኩት ሰላቶ በመስጠትዎ ተቀይሜዎታለሁ !! እማምላክን ተቀይሜዎታለሁ። እንዴት እንዴት ነው ነገሩ ... እዚህች አገር አባራሪው ከተባራሪው ተደባለቀ እኮ
ዳር ላይ ያባረርነው ከመሐል እያባረረን ተቸገር?" አለ።
ጃንሆይ በጥሞና ሲያደምጡ ቆዩና፣ “ቅሬታህን ሰምተናል። ካንተ የሚበልጥብን የለም። ያው አንተ ዳር ላይ ልክ ያስገባሃቸው ናቸው ዛሬ ወዳጅነታችንን ፈልገው በእንብርክክ ደጅ የጠኑን
እንደምታውቀው ጀግና በጠብ የመጡበትን አንጂ በፍቅር የመጣን አይነኩም አሉና የአያቴን ቁጣ አበረዷት።
“በል አሁን በቃህ ለማን ብለህ ነው መሬትህን ጥለህ የምትሄደው፡፡ እነሱ እያዩህ ይሸማቀቁ እንጂ ብለው እዛው ኤምባሲው ጎን ለአያቴ ሰፊ ቦታ ሰጡት።
እርቅ ወረደ! ንጉሡ ብልህ ነበሩ። አንዳንዴ አያቴን ይጠሩትና፣ ጎረቤቶችህ ሰላም ናቸው ? ብለው
ይጠይቁታል። አያቴን ሰላይ አደረጉት እንግዲህ የአያቴ ጎጆ እና የጣሊያን ኤምባሲ በግንብ አጥር ብቻ ነበር የሚለያዩት። አያቴ ጣልያኖቹን ባያቸው ቁጥር ደሙ እየፈላ፣ "ወይ ነዶ የማንም ፋሽስት ጋር እንዲህ ትከሻ ለትካሻ እየተጋፋሁ ልኖር” እያለ በብስጭት ሲግል ሚስቱ ወይዘሮ በልጅጌ መኮንን (የፊታውራሪ መኮንን እጅጉ የመጀመሪያ
ልጅ እያባበለች ወደ መኝታ ቤታቸው ትወስደውና ከብስጭቱ አብርዳ በሌላ ጉዳይ ትለኩሰዋለች ! አቤት ማባበል ስታውቅበት …. ገና ስትታይ ነገር ታበርዳለች ... እሳት ፈገግታዋ እሳት ያጠፋል ... ይች ውብና አስተዋይ ሴት ሲበሳጭ ስታባብለው፣ ሲበሳጭ ስታባብለው .… አምስት ሴትና አንድ ወንድ ልጅ ወለዱ። ይሄ ብቸኛ ወንድ ልጅ የእኔ አባት ነበር።
አያቴ ምንም እንኳን የልጆቹን አእምሮ በምክር አርሶና አለስልሶ የጣሊያንን ጥላቻ ቢዘራበትም
አልፀደቀም። በተለይ ሴት ልጆቹ ያማረ መኪና ይዘው የሚገቡና የሚወጡ የጣልያን ጎረምሶች ላይ
ልባቸው አልጨክን እያለ፣ ዓይናቸውም እየተንከራተተ አስቸገረው። ጭራሽ ይለይልህ
ብለው ከአባቴ በስተቀር ሁሉም ሶላቶ' አግብተው ቁጭ አሉ። በዚሁ ብስጭት ሙሉ ቦታውን ለአባቴ ብቻ አውርሶና ጥልያን ያገቡ ልጆቹን ሁሉ ክዶ ሚስኪን አያቴ በደም ግፊት ሞተ !! አባቴም፡ 'ሙሉ' የምትባል ውብ
ሴት አግብቶ እዚሁ ነገረኛ የወርስ ቦታ ላይ ቤት ሰርቶ መኖር ጀመረ (ሙሉ እናቴ ናት…)።
እናቴ ሙሉ መቼስ ወላ በቁንጅና፣ወላ ሰባሕሪ ቢባል ይሄ ቀረሽ የማትባል ውብ ናት። ስትገባ ስትመጣ ተመልካቹ በዛ፣ የሚመኛት እልፍ ነበር። አባቴ ታዲያ እናቴ ስትደነቅና ስትሞገስ ደስ ቢለውም፣ ከተመልካቹ ሁሉ ደሙን የሚያፈላው የጣልያኖቹ አስተያየት ነበረ። እንግዲህ ጣልያኖቹ እናቴ ስታልፍ ፊታቸው እንደ ቲማቲም ቀልቶ አፋቸውንም፣ ዓይናቸውንም በልጥጠው በአጥራቸው ላይ እየተንጠላጠሉ በአጉል ምኞት ሲመለከቷት አባቴ ይሰሳጫል፤ በላቸው በላቸው ይለዋል። (ደግሞ ለማለት፣ አያቴ እንደሆነ ምንሽሩን አውርሶታል- መታገስ ደግ ነው ብሎ እንጂ…)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
(አንቀፅ 17 ፡ እኛም መስኮታችንን አንከፍትም፣ እናንተም ሚስቶቻችንን አትዩ ፡)
ጣሊያን ኢትዮጵያን ወርራ አምስት ዓመት ፍዳዋን በልታ፣ ፍዳችንን ስታሰበላን አያቴ እሳት የላሰ
የውስጥና የውጭ አርበኛ ነበር። በጦር ሜዳ ብትሉ አንድ ባታሊዮን ጦር ጭጭ ምጭጭ ያደረገ
ጀግና ሲሉት፣ “ኤዲያ ምን አላት እቺ” ይላል !! በከተማ ብትሉ" ጠላት መኝታ ቤት ሳይቀር የተቀመጠ ሚስጥር ፈልፍሎ ሲያወጣ አጀብ ያስብል ነበር። ታዲያ በአያቴና በቆራጥ አርበኞች ትግል ፋሺስት ኢጣሊያንን ከሀገር ከተባረረ በኋላ፣ ለአገር በሠራው ታላቅ ጀብዱ፣ በድል አጥቢያ ጃንሆይ ራሳቸው አስጠርተው አሁን የጣልያን ኤምባሲ የሚባለው የተገነባበትን ቦታ በሙሉ ከታላቅ ክብርና ምስጋና
ጋር በሽልማት ለኢያቴ ሰጡት !
አያቴ እዚሁ በሽልማት የተሰጠው ቦታ ላይ ትንሽ ጎጆ ቀልሶና፣ የተረፈው ሜዳ ላይ የቆሎ ዘርቶ
ሲኖር፣ አንድ ቀን የጃንሆይ መልዕክተኞች ሲገሰግሱ ቤቱ ድረስ መጡና፣
“እዚህ በቆሎ የዘራህበት ቦታ ላይ የንባሲዮን ሊሰራሰት ነውና መድረሻህን ፈልግ ብለውሃል ጃንሆይ አሉት።
“ኧረ ውሰዱት ደሞ ለሞላ ቦታ አላቸው። ትንሽ ቆይቶ፣ “ይሄ ግን 'የንምባሲዮን' ያላችሁት ነገር መንግስት ነው ?” ሲል ጠየቀ።
“አይደለም !"
“አሃ ተማሪ ቤት መሆን አለበት :"
“አይደለም!”
ታዲያ ምንደን ነው ቤተስክያን ይሆን እንዴ ?" ሲል ግር ብሎት ጠየቀ።
"ኤማቢሲዎን ማለትንጉሥ የፈቀዱላቸው የውጭ አገር መኳንት እና መሳፍንት አገራቸውን
መስለው የሚቀመጡበት እና አንዳንድ የመንግሥት ሥራዎችን የሚከውኑበት ማረፊያ ነው" አሉት
ሳኔ ዕክተኞቹ አንዱ። ከመልክተኞቹ አንዱ።
"በቃ ?" ሲል ጠየቀ አያቴ በግርምት።
"በቃ!"
"እኮ ፈረንጆች ይሄን ሁሉ ቦታ አጥረው ቁጭ ሊሉ ነው” አለ እንደገና በታላቅ ግርምት።
"አዎ ! ይሄ የምባሲዮን ... የወከላቸው አገር የማይደፈር ግዛት ነው”
እንዲያ ድንበራችን ላይ ያባረርነውን ጠላት መናገሻችን ላይ አርደንለት ጋርደንለት ልናስቀምጠው ነው በለኛ አለ አያቴ በቁጭት።
መልዕከተኞቹ አያቴ ላይ ሳቁበት። ስለኤምባሲ ያለው እውቀት አነስተኛ መሆኑን በመገንዘባቸው
ድፍን ሁለት ሰዓት ስለኤምባሲ ተግባርና ለአጎራችን ስላለው ጠቀሜታ በዝርዝር አወሩት።
ተግባብተው ሊለያዩ ሲሉ ግን ነገር ተበላሽ።ጉድፈላ። አገር ተሸበረ።ድንገት ነው ነገሩ የተመሰቃቀለው
ከሆነስ ሆነና የማን አገር ኤምባሲዮን ነው ?" ሲል ጠየቀ አያቴ፣
“ጥልያን” ብለው መለሱለት።
"ጥልያን ጥሊያን ... እኮ ጥሊያን ይሄ ፋሽስት የነበረው" አለ አያቴ ማመን አቅቶት።
"እንዴታ አሁን በሰላም መጥተዋል”
አያቴ ሰይጣኑ ተነሳ። ተንደርድሮ ምንሽሩን መዥረጥ አደረገና ለግማሽ ሰዓት ያህል ፎክሮ ሲያበቃ፣
"ባንዳ ሁላ…” ብሎ የጃንሆይን መልዕክተኞች ማሳደድ ጀመረ !
ጥሎብን መከተል እንወዳለን። መንገድ ላይ ድንገት አያቴን ያዩ ሁሉ፡ ገና የአርበኝነት ስሜቱ
ያልበረደላቸው፣ እንዲሁም አርበኝነት ያመለጣቸው፣ እንደገና እድሉን አገኘን በማለት ምንሽራቸውን አፈፍ እያደረጉ፣ “ያዘው…" እያሉ ላይጠቅማቸው አያቴን ተቀላቅለው የንጉሱን መልእክተኞች ማሳደድ ጀመሩ። መቼስ አዲሳባ እንደዛን ቀን ተፎክሮባትም፣ ተሸልሎባትም አያውቅም ሲሉ ሁኔታውን የታዘቡ፡፡
አያቴ ቁጣው መለስ ሲል ዞሮ ቢመሰከት ድፍን የአዲስ አበባ ወንድ ተከትሎታል።
“ምን ሆናችሁ” ቢላቸው አያቴ፣ “አይ ሩጫው ወደ ቤተ መንግሥት መሆኑን ስንሰማ ነው
የተከተልኛችሁ” አሉ !!
አያቴ የተከታዩን ብዛት አየና በዛው ሸፈተ ! ስሙ የገነነ ሽፍታም ሆነ ! ስሙ ከተጠራ እንኳን ኢትዮጵያ
ምድር ያሉት ሮም የተቀጡትም ጥልያኖች ወባ እንደያዘው እየተንዘፈዘፉ ንሰሃ ይገባሉ ! ጭራሽ የኤምባሲው ግንባታ ሲጀመር በወርም በሳምንትም በል ሲለው በየሦስት ቀኑ ብቅ እያለ ይሄን ጣልያን ሁሉ ይፈጀው ጀመረ !!
ጃንሆይ በበኩላቸው አያቴን በዲፕሎማሲ ማሳመን መርጠው መልዕክት ላኩበት። በድፍረት ከነጎፈረ ጸገሩና ከነምንሽሩ ፊታቸው ቀርቦ፤ "ጃንሆይ ትላንት ይሄን ፋሽስት፣ እንኳን አሳረርከው' ብዬ የሸለሙኝን ቦታ ዛሬ ከኔ ነጥቀው ላባረርኩት ሰላቶ በመስጠትዎ ተቀይሜዎታለሁ !! እማምላክን ተቀይሜዎታለሁ። እንዴት እንዴት ነው ነገሩ ... እዚህች አገር አባራሪው ከተባራሪው ተደባለቀ እኮ
ዳር ላይ ያባረርነው ከመሐል እያባረረን ተቸገር?" አለ።
ጃንሆይ በጥሞና ሲያደምጡ ቆዩና፣ “ቅሬታህን ሰምተናል። ካንተ የሚበልጥብን የለም። ያው አንተ ዳር ላይ ልክ ያስገባሃቸው ናቸው ዛሬ ወዳጅነታችንን ፈልገው በእንብርክክ ደጅ የጠኑን
እንደምታውቀው ጀግና በጠብ የመጡበትን አንጂ በፍቅር የመጣን አይነኩም አሉና የአያቴን ቁጣ አበረዷት።
“በል አሁን በቃህ ለማን ብለህ ነው መሬትህን ጥለህ የምትሄደው፡፡ እነሱ እያዩህ ይሸማቀቁ እንጂ ብለው እዛው ኤምባሲው ጎን ለአያቴ ሰፊ ቦታ ሰጡት።
እርቅ ወረደ! ንጉሡ ብልህ ነበሩ። አንዳንዴ አያቴን ይጠሩትና፣ ጎረቤቶችህ ሰላም ናቸው ? ብለው
ይጠይቁታል። አያቴን ሰላይ አደረጉት እንግዲህ የአያቴ ጎጆ እና የጣሊያን ኤምባሲ በግንብ አጥር ብቻ ነበር የሚለያዩት። አያቴ ጣልያኖቹን ባያቸው ቁጥር ደሙ እየፈላ፣ "ወይ ነዶ የማንም ፋሽስት ጋር እንዲህ ትከሻ ለትካሻ እየተጋፋሁ ልኖር” እያለ በብስጭት ሲግል ሚስቱ ወይዘሮ በልጅጌ መኮንን (የፊታውራሪ መኮንን እጅጉ የመጀመሪያ
ልጅ እያባበለች ወደ መኝታ ቤታቸው ትወስደውና ከብስጭቱ አብርዳ በሌላ ጉዳይ ትለኩሰዋለች ! አቤት ማባበል ስታውቅበት …. ገና ስትታይ ነገር ታበርዳለች ... እሳት ፈገግታዋ እሳት ያጠፋል ... ይች ውብና አስተዋይ ሴት ሲበሳጭ ስታባብለው፣ ሲበሳጭ ስታባብለው .… አምስት ሴትና አንድ ወንድ ልጅ ወለዱ። ይሄ ብቸኛ ወንድ ልጅ የእኔ አባት ነበር።
አያቴ ምንም እንኳን የልጆቹን አእምሮ በምክር አርሶና አለስልሶ የጣሊያንን ጥላቻ ቢዘራበትም
አልፀደቀም። በተለይ ሴት ልጆቹ ያማረ መኪና ይዘው የሚገቡና የሚወጡ የጣልያን ጎረምሶች ላይ
ልባቸው አልጨክን እያለ፣ ዓይናቸውም እየተንከራተተ አስቸገረው። ጭራሽ ይለይልህ
ብለው ከአባቴ በስተቀር ሁሉም ሶላቶ' አግብተው ቁጭ አሉ። በዚሁ ብስጭት ሙሉ ቦታውን ለአባቴ ብቻ አውርሶና ጥልያን ያገቡ ልጆቹን ሁሉ ክዶ ሚስኪን አያቴ በደም ግፊት ሞተ !! አባቴም፡ 'ሙሉ' የምትባል ውብ
ሴት አግብቶ እዚሁ ነገረኛ የወርስ ቦታ ላይ ቤት ሰርቶ መኖር ጀመረ (ሙሉ እናቴ ናት…)።
እናቴ ሙሉ መቼስ ወላ በቁንጅና፣ወላ ሰባሕሪ ቢባል ይሄ ቀረሽ የማትባል ውብ ናት። ስትገባ ስትመጣ ተመልካቹ በዛ፣ የሚመኛት እልፍ ነበር። አባቴ ታዲያ እናቴ ስትደነቅና ስትሞገስ ደስ ቢለውም፣ ከተመልካቹ ሁሉ ደሙን የሚያፈላው የጣልያኖቹ አስተያየት ነበረ። እንግዲህ ጣልያኖቹ እናቴ ስታልፍ ፊታቸው እንደ ቲማቲም ቀልቶ አፋቸውንም፣ ዓይናቸውንም በልጥጠው በአጥራቸው ላይ እየተንጠላጠሉ በአጉል ምኞት ሲመለከቷት አባቴ ይሰሳጫል፤ በላቸው በላቸው ይለዋል። (ደግሞ ለማለት፣ አያቴ እንደሆነ ምንሽሩን አውርሶታል- መታገስ ደግ ነው ብሎ እንጂ…)
👍15🥰1
#አድዋ_በአፍ_አይገባም
አድዋ የደም ግብር ነው፤ አበው የለኮሱት ቀንዲል
አድዋ የአፍሪካ ዱካ ነው፤ አበሽ የከተበው ፊደል
ላጥፋህ ቢሉት መች ይጠፋል፤ ጠላት በልቶ ያፈራ ተክል
ለዛሬም ታሪክ አባት ነው፤ “ነገም ሌላ ቀን ነው” ለሚል
አድዋ ሰው ዛብ፣ የደም ድልድይ
አንድም ፍልሚያ፣ አንድም ራእይ
ልብ ላለው ልብ ያነዳል
ለምር ቀን ስንቅ ይሆናል!!
ነጻነት አይለመንም
ያው ጥንትም ተጽፏል በደም
አገር ድንበሯ ሲነደል፣
ያው ዛሬም ተማግሯል በፍም
የአጋም አጥር ተደግፎ
ጎረምሳ ኮረዳም ቢስም
በወርቅ አልጋ በእርግብ ላባ
ተኝቶ ማደር ቢቻልም
አገር ከፍቷት ሰላም የለም
አድዋ ሞተው ሲኖሩ እንጂ ተተርኮ በአፍ አይገባም!
ዱሮም ዛሬም በአፍ አይገባም!
🔘በነቢይ መኮንን🔘
አድዋ የደም ግብር ነው፤ አበው የለኮሱት ቀንዲል
አድዋ የአፍሪካ ዱካ ነው፤ አበሽ የከተበው ፊደል
ላጥፋህ ቢሉት መች ይጠፋል፤ ጠላት በልቶ ያፈራ ተክል
ለዛሬም ታሪክ አባት ነው፤ “ነገም ሌላ ቀን ነው” ለሚል
አድዋ ሰው ዛብ፣ የደም ድልድይ
አንድም ፍልሚያ፣ አንድም ራእይ
ልብ ላለው ልብ ያነዳል
ለምር ቀን ስንቅ ይሆናል!!
ነጻነት አይለመንም
ያው ጥንትም ተጽፏል በደም
አገር ድንበሯ ሲነደል፣
ያው ዛሬም ተማግሯል በፍም
የአጋም አጥር ተደግፎ
ጎረምሳ ኮረዳም ቢስም
በወርቅ አልጋ በእርግብ ላባ
ተኝቶ ማደር ቢቻልም
አገር ከፍቷት ሰላም የለም
አድዋ ሞተው ሲኖሩ እንጂ ተተርኮ በአፍ አይገባም!
ዱሮም ዛሬም በአፍ አይገባም!
🔘በነቢይ መኮንን🔘
👍4
#አድዋ
የሰው ልጅ ክቡር
ሰው መሆን ክቡር
ሰው ሞቷል – ሰው ሊያድን፣
ሰውን ሲያከብር
በደግነት፣ በፍቅር፣ በክብር ተጠርቶ፣
በክብር ይሄዳል፥ ሰው ሊኖር ሰው ሞቶ፤
የተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነፃነት፣
ሰው ተከፍሎበታል ከደምና ካአጥንት፣
ስንት ወገን ወደቀ በነፃነት ምድር
ትናገር አድዋ፣ ትናገር ትመስክር፣
ትናገር አድዋ፣ ትናገር አገሬ፤
እንዴት እንደቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬ፤
በኩራት፣ በክብር፣ በደስታ፣ በፍቅር፣
በድል እኖራለሁ ይኧው በቀን በቀን
ደሞ መከራውን ያን ሁሉ ሰቀቀን።
አድዋ ዛሬ ናት አድዋ ትናንት፣
መቼ ተነሱና የወዳደቁት፣
ምስጋና ለእነሱ ለአድዋ ጀግኖች፣
ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች
የጥቁር ድል አምባ፣ አድዋ
አፍሪካ፣
እምዬ ኢትዮጵያ
ተናገሪ…
የድል ታሪክሽን አውሪ።
#እጅጋየሁ_ሽባባው
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
#Share and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
የሰው ልጅ ክቡር
ሰው መሆን ክቡር
ሰው ሞቷል – ሰው ሊያድን፣
ሰውን ሲያከብር
በደግነት፣ በፍቅር፣ በክብር ተጠርቶ፣
በክብር ይሄዳል፥ ሰው ሊኖር ሰው ሞቶ፤
የተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነፃነት፣
ሰው ተከፍሎበታል ከደምና ካአጥንት፣
ስንት ወገን ወደቀ በነፃነት ምድር
ትናገር አድዋ፣ ትናገር ትመስክር፣
ትናገር አድዋ፣ ትናገር አገሬ፤
እንዴት እንደቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬ፤
በኩራት፣ በክብር፣ በደስታ፣ በፍቅር፣
በድል እኖራለሁ ይኧው በቀን በቀን
ደሞ መከራውን ያን ሁሉ ሰቀቀን።
አድዋ ዛሬ ናት አድዋ ትናንት፣
መቼ ተነሱና የወዳደቁት፣
ምስጋና ለእነሱ ለአድዋ ጀግኖች፣
ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች
የጥቁር ድል አምባ፣ አድዋ
አፍሪካ፣
እምዬ ኢትዮጵያ
ተናገሪ…
የድል ታሪክሽን አውሪ።
#እጅጋየሁ_ሽባባው
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
#Share and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍24🥰7🤩1