አትሮኖስ
283K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
504 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

#አውጉስታ

ቅዱስ ገብርኤል የሚከበርበት የዓመቱ በአል ደረሰ፡፡ ይህንን በዓል የእንደሻው ወላጆች የሚያከብሩት ሐረርጌ ቁልቢ ገብርኤል በመሄድ ነው። ለዓመቱ ገብርኤል የተሳሉትን ስለት ይዘው፣ ትንሹ ልጃቸው ሲሳይን አስከትለው፤ ለመሄድ የባቡር ትኬት ቀደም ብሎ ተቆርጧል።
ገብርኤል የሚከበርበት ቀን እንደ ነገ ሆኖ፤ ትህትና ሥራዋን በምታከናውንበት ወቅት ደግሞ አንድ ደስ የሚል ዜና ሰማች፡፡ ትናንትና ሻምበል ብሩክን በስልክ ስታነጋግረው የድሮው ሻምበል ብሩክ ሳይሆን ትንሽ የመቀዝቀዝና፤ የመለወጥ ስሜት ስላየችበት ብስጭትጭት ብላ
ነበር የዋለችው። ይህንን ብስጭቷን ሲያካክስላት ነው መሰል የደስደስ
ያለው ወሬ ከአበራ ሰማች፡፡
የምስራች!” አላት አበራ እየፈነደቀ።
“ምስር ብላ” አለችው የምሥራቹ ናፍቋት፡፡
“ጋሼን ምን እንዳስነካሻቸው አላውቅም፡፡ለማንም ያላደረጉትን ነው ላንቺ እያደረጉ ያሉት፡፡የገቡልሽን ቃላቸውን ጠብቀዋል፡፡ ከነገ ጀምሮ ደመወዝሽ አንድ መቶ ብር ሆኖ በገንዘብ ያዥነት እንድትሰሪ ተወስኗል”
በደስታ ብዛት ሄዳ አበራን እቅፍ አደረገችው። እሱም እቅፍ አደረጋት።

“ዛሬ እቤት ይዘሀት ትምጣና አዲስ ውል ትፈርም ብለውኝ ነበር። ዛሬ ሥራ ስለሚበዛ ለነገ ይሻላል ብያቸዋለሁ” አላት ድምጹን ዝቅ አድርጎ፡፡
ትህትና በእርግጥም በሥራዋ ቀልጣፋና ደከመኝን የማታውቅ ልጅ መሆኗን ማንም ይመሰክርላታል።
“ለማንም እንዳትናገሪ ታዲያ! በተለይ ይህቺ አሮጊት ከሰማች ታብዳለች” :: ይህቺ አሮጊት የሚለው ወ/ሮ አረጋሽን ነው። በእርግጥም ወይዘሮ አረጋሽ በዚህ የጫማ መሸጫ አዳራሽ ውስጥ ዘጠኝ ዓመት ሙሉ ሰርታ ደመወዟ አሁንም ዘጠና ብር ብቻ ነበር፡፡
“ጋሼ አበራ ሙት ለማንም አልናገርም” ቃል ገባችለት፡፡ በዚሁ መሠረት ተደስታ ውላ፤ ተደስታ አደረች፡፡ ትንሽ ቅር ያላት ሻምበል ብሩክ በስልክ ስታነጋግረው ከወትሮው የቀዘቀዘበት ምክንያት ግራ
ስላጋባት ነበር።ምክንያቱን ለማወቅ
ሄዳ እስከምታገኘውና የሳምንቱ
"መጨረሻ እስከሚደርስ ድረስ ከመቸኮሏ በስተቀር ሁሉም ነገር ሰላም ነው፡፡ እናቷ በጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለችው። አንዱዓለም ጠንካራ ተማሪ ሆኗል። ይኸውና እሷ ደግሞ ዛሬ ዕድገት የማግኘቷን ዜና ሰማች፡፡ ይህንን የዕድገት ውሏን ለመፈረም አቶ በቀለ ከመኖሪያ
ቤታቸው ድረስ እንድትመጣ በሥራ አስኪያጁ በአበራ በኩል የላኩባትን
መልዕክት ተቀብላ ለመሄድ ተዘጋጀች፡፡
በማግሥቱ ሥራ እንደገቡ አበራ ወደ
ወ/ሮ አረጋሽ ጠጋ ብሎ ከትህትና ጋር አንድ ግዜ ወደ ፋብሪካ ደርሰን እንመጣለን” አለና ምክንያቱን አሳውቆ ትህትናን ጠራትና መኪና ውስጥ አስገባት፡፡ ሞቅ ባለ ፍጥነት ከአውጉስታ ፋብሪካ በስተጀርባ ወደሚገኘው ወደ አቶ በቀላ መኖርያ ቤት በረሩ።
ከዚያ ደርሰው የመኪና ጥሩንባ ሲያሰሙ፤ አንዲት ጠቆር ያለች ልጅ እግር የቤት ሠራተኛ የአጥሩን ብረት በር ወለል አድርጋ ከፈተችው፡፡
ቤቱ በዚያ ሰፊ ቦታ ላይ በግርማ ሞገስ ጉብ ብሎ ሲታይ ይማርካል። በልዩ ልዩ አበቦችና ዛፎች አጊጧል። ከትልቁ ቪላ ፊት ለፊት በሰፊው ተንጣሎ የሚታየው የወይን ዛፍ ቀዝቃዛ ጥላን አጐናጽፎት
ምድረ ገነት አስመስሎታል።
በግቢው ውስጥ የማይታይ የአበባ ዓይነት የለም፡፡ ትህትና በአጠቃላይ የቤቱ ውበት ተማርካለች፡፡ ከዚያም ተያይዘው ከመኪናው ወረዱ።
የወጣ ሰው የለም፡፡ አበራ “ቆይ ጠብቂኝ” አለና በጓሮ በኩል ዞረ።እሷ በፊት ለፊቱ በር ቆማ እየጠበቀችው ነበር፡፡
የቤት ሠራተኛዋ አንድ ጊዜ ብቅ ብላ ትህትናን ሰረቅ አድርጋ አየቻትና ተመልሳ ገባች።
“ነይ ትህትና በዚህ በኩል”፡፡ በፊት ለፊቱ ሳይሆን በጓሮው በር አስገባት፡፡
እዚያ ፈቅ ብሎ በተሠራ የውሻ ቤት ውስጥ የታሰረው ትንሽ የፈረንጅ ውሻ ቡፍ ቡፍ አለ። ትህትና ውሻውን ስታየው ግንባሩ ፍጥጥ ብሎ ወደ ውጭ የወጣ ከመሆኑም በላይ ፤ የሆነ የምታውቀው ሰው መልክ አስታወሳትና፤ ትንሽ ሳቅ ብላ አበራን ተከተለችው::

ቁጭ በይ ወንበር ጋበዛት፡፡ ሄዳ ወንበሩ ላይ ተቀመጠች።
“እስከዚያው ምን ይምጣልሽ?” ፊቱ ጥርስ በጥርስ እንደሆነ።
“ጋሽአበራ ምንም አያስፈልግኝም” እሷም በፈገግታ እንደተዋጠች፡፡
ዕድገትን ለመሰለ ፀጋ መጥቶ ባይበላ፤ ባይጠጣስ? ልቧ ያለው በውሉ ሁኔታ ላይ ነበር። በዚህ ላይ የቤቱ ውበት አስደንቋት ዙሪያ ገባውን እየቃኘች ነበር፡፡
“እንደሱ አይባልም፡፡ ምንም ቢሆን እኮ ለቤቱ እንግዳ ነሽ፡፡
እንዳይለምድብሽ፡፡ ለስላሳ ይምጣልሽ?”
“ይሁን እሺ ጋሽ አበራ፡፡”
ትህትና እዛ ክፍል ውስጥ ሆና በዚያች የምታምር ክፍል ውስጥ የተሰቀለውንም፤ የተንጠለጠለውንም፤ በዐይኖቿ እየቃኘች አቶ በቀላ ብቅ ብለው ውሉን እስከሚያስፈርሟት ድረስ በናፍቆት ስትጠባበቅ፤ በግራ በኩል ውስጥ ለውስጥ የተሠራው ባለመስታወት በር ንቅናቄ አሳየ።
እስከዚያን ጊዜ ድረስ አንዳችም ጥርጣሬ ያልተሰማት ልጅ ልቧ እንደመዝለል አለባትና ዐይኖቿ በበሩ ላይ ተተክለው እንደቀሩ፤ ፒጃማ የለበሰ ወጣት ብቅ!!..... አለ፡፡
ያንን ሰው ስትመለከት፤ እጅግ ከመደንገጧ የተነሳ አፏ ተከፍቶ ቀረ። ከዚያም ነፍሷን ስትገዛ “ዋይ!” ብላ እሪታዋን ልታቀልጠው ስትል፡-
“ፀጥ በይ!! ያለበለዚያ!!” አለና ደብቆ የያዘውን እህል ውሃ የማያሰኝ ጩቤ መዘዘው። ዐይኖቿ ተጎልጉለው ወጡ
በድንጋጤ ደምስሮቿ በግንባሯ ላይ ተገታተሩ፡፡ ትንፋሽ ሳታወጣ ፀጥ አለች፡፡
ከዚያም ሁኔታዎች በእንደሻው ፍላጐት መስመር ያለችግር ይቀላጠፉ ጀመር።
ጠጋ አላትና በግራ በኩል በቃሪያ ጥፊ ቢያላጋት ዐይኖቿ በእጥፉ ተጎልጉለው ከመውጣታቸውና ፊቷ ሳምባ ከመምሰሉ በስተቀር ቃል አልተነፈሰችም።የሚያርዳት ነው የመሰላት፡፡
“የምትታዘዥውን የማታደርጊ ከሆነ ይሄ!” አለና በጡቶቿ ሥር ጩቤውን አሳርፎ “ወደ ውስጥ እንዲዘልቅልሽ ይደረጋል!” አላት በጭካኔ ስሜት።
“ተነሽ!!” አለና አንቧረቀባት።
ሹክክ ብላ ተነሳች። ከኋላ በኩል ዞሮ ያንን ዞማ ፀጉሯን ጨመደደና፤ የገባበትን በር በእርግጫ በረገደው፡፡ ከዚያም ወደ ውስጥ ሲገፈትራት፤ ተንገዳግዳ የገባችበት ክፍል ጨለማ ዋጣት...
እዚያ ጨለማ ውስጥ ሆና የገባችበትን ሲኦል ለማየት ዐይኖቿን ስትገልጥ፧ ሄዶ ማብሪያና ማጥፊያውን ቢጫነው፤ እዚያ ክፍል ውስጥ ከዳር እስከዳር የተንጣለለ ሞዝቮልድ አልጋ ተነጥፎ አየች። ይህንን
የምታተኩርበት ስሜትም፤ ጊዜም፤ አልነበራትም፡፡ ማንስ ጊዜ ሰጥቷት?
እንደዚያ ሲለምናት፤ ሲያስለምናት ከርሞ፤ እንቢ ስለአለችው፤ በቀየሰው ዘዴ የገባችለትን ወጣት ሊሰቀላት ቆርጦ ተነስቷል።
“አውልቂ!! አለና ጮኸባት፡፡
ጩቤውን እንደያዘው ነው፡፡ እየተንፈቀፈቀች ዝም ብላ ቆማ
ዐይን ፤ ዐይኑን፤ ታየው ጀመር፡፡ እንባዋን አይቶ የሚያዝንላት መሰላት፡፡
እንባዋ እንደጎርፍ ፈሰሰ፡፡ አቤት በዚያን ሰዓት የተሰማት ስሜት!? ሻምበል ብሩክ መጣባት፡፡
“እውነት ልታደርጊው ትሁትዬ?” የሚላት መሰላት፡፡
“ተይ! ተይ! ትሁት!” በአካል የቀረባት መሰላት። ስቅስቅ ብላ አለቀሰች
“አውልቂ!” አለና እንደገና አንቧረቀባት። በዚህ ጊዜ በእልህና ተውጣ፤ : እንደቆሰለ
አውሬ እየጓጎረች፤ ልታንቀው በሲቃ
ተንደረደረችበት፡፡
እንደሻው አመጣጧን አይቶ ካፈገፈገ በኋላ እዚያ ከመንጋጋዋ በታች የሆነ ደም ስሯ ላይ ክፉኛ ቢመታት፤ ሄዳ በአፍ ጢሟ ተደፋች፡፡
ከዚያም ያንን ሲቋምጥለት የነበረው ገላዋን እርቃኑን ለማየት ተጣድፎ
ልብሶቿን በፍጥነት አወላለቃቸው፡፡ እራሷን ስታ ነበር፡፡ ሙሉ በሙሉ
ልብሷን ካወለቀ በኋላ ወስዶ አልጋው ላይ ዘረራት.... ከዚያም ያንን
👍3