አትሮኖስ
281K subscribers
110 photos
4 videos
41 files
480 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ምርጫ_አልባ_ምርጫ


#ክፍል_አንድ


#በሜሪ_ፈለቀ

ሁሌም ዛሬ ላይ ቆመህ ሁለት ምርጫ አለክ ትናንት ወይም ነገ ትዝታ ወይም ተስፋ!
።።።።።
#ረቂቅ

ከወንድምና ከህሊና የቱ ይበልጣል? ወይም ከእናት እና ከህሊና?
እሺ ከነገና ከህሊና ?ህሊና እንጀራ ይሆናል?

የህሊና ንፅህና ለነፍስ ምግብ ይሆን ይሆናል። በነፍስ እርካታ ስጋ ይጠግባል እንዴ? ነፍስ ጠገበች ብሎስ ሆድ ይጠግባል?
ኸረ እንደውም ነፍስ ስጋ ውስጥ ነው የምታድረው። ማደሪያዋ የህልውና ጥያቄ ውስጥ ሲገባ ነፍስም ህልውናዋ አጠያያቂ ነው።በእጅ አዙር እንጀራ ትፈልጋለች።በእርግጥ ነፍስ ለማደሪያነት
የቱን ትመርጣለች? የሚለው ወሳኝ ጥያቄ ይሆናል። ስጋን ወይስ ከስጋ ከተለየች በኋላ የምታድርበት መኖሪያዋን?ሀይማኖተኛ ወይም የሞራል ሰው ሆኜ አይደለም ይህን
መዘላበዴ እንደው ከፀፀት ለመዳን ታክል እንጂ፡፡

ከዚህ ሁሉ ውዝግብ በፊት ለመልስ ሳትቸኩሉ ራሴን ላስተዋውቃችሁ።

ስሜ ረቂቅ ነው:: በእርግጠኝነት የእኔን ስም እናቴ እንጂ መላዕክት አላወጡትም

እድሜዬ አስራ ሰባት ዓመት
የማልቆጥራቸው
ነው:: (በእርግጥ ከመኖር ከማልቆጥራቸው ሰባት የቀነስኳቸው ዓመታት አሉ እንተዋወቅና ከመኖር ከቆጠራችሁት ደምሩበት፡፡)

የስራ ሁኔታ ገንዘብ ብቻ ላላቸው ድሀ ወንዶች ደስታና ሳቅን መለገስ (በእርግጥ ማማለልም አለበት። መተኛትም።)

የአገልግሎት ዘመን ከንቱ፡፡

ዛሬ የተለየ ጉዳይ ገጥሞኛል፡፡ የኢትዮጵያ አማርኛ ፊልሞች ላይ ብቻ ያሉ ዓይነት ታሪኮች የሚመስል ስራ ነው።ስራው አንድ
ጋግርታም ሰውዬ ማማለል።
ኤፍሬም ይባላል።ለየት የሚያደርገው እርሱ ለመማለልም ለመሳቅ ፍቃደኛ አይደለም።የአባቱ ጓደኛ የሆነ አያሌው የሚባል ሰው ነው።እንዳማልለው የቀጠረኝ፡፡ ክፍያው አምስት መቶ ሺህ የኢትዮጵያ ብር ነው።

አፌዛችሁ አይደል? እኔም የሰማሁኝ ሰዓት በፌዝ ስቄ ነበር።በትክክል ኤፍሬምን ማማለል ብቻውኝን በቂ አይደለም።አብሮ መተኛትም ይሄን ብር አያስገኝም።

ነገርየው በደንብ ፌዝ የሚመስለው ዋናውን ዓላማ ስታውቁት ነው።
ኤፍሬም የተለያዩ ሴክተሮች ያሉት ትልቅ ኩባንያ ባለቤት ነው።

አዲስ አበባ ውስጥ የኩባንያውን ስም ከተለያዩ ምርቶችና አገልግሎቶች ጋር ተያይዞ መስማት እንደ አንዱ
የቤተስባችሁ ስም የተለመደ ነው። ብነግራችሁ ታውቁታላችሁ እኮ! አቶ አያሌው የቆዳ ውጤቶች፣ ከብት ማደለቢያ፣ ማተሚያ ቤት እና በተጨማሪም የኤፍሬም አባትና አቶ አያሌው (የአባቱ ጓደኛ) በሼር ይሰሩት የነበረ አሁን ለኤፍሬም የተላለፈ ትልቅ
የሳሙና ፋብሪካ በኩባንያው ስር እንደሚጠቃለል ዘረዘረልኝ፡፡
እንግዲህ ኤፍሬምን በእጅ በእግሩ ገብቶ የፋብሪካውን ሼር ለአያሌው እንዲሸጥ ማሳመን ነው ስራዬ፡፡ የሆነ ቧልት ነገር
አለው አይደል? እኔም ያልኩት እንደዛ ነው፡፡

እንዴት ብታስበው ነው ይሄን ያህል ከባድ ውሳኔ ላስወስነው እንደምችል ያስብከው?" ነበር የጠየቅኩት።

ያንቺ ስራ እንዲወድሽ ማድረግ ብቻ ነው:: ሰውየው ከወደደሽ፣
እንኳን በንብረቱ በነፍሱ ይደራደርልሻል:: ለሚስቱ እንደዛ ነበር::" ነበር ያለኝ አያሌው፡፡

ሰውየው(አቶ አያሌው) አንቱ ለማለት የሆነ ቀላል ነገር ስላለው
አንቱ ማለት ከብዶኝ ነው አንተ የምለው እንጂ አንተ የሚሉት ሰውስ አልነበረም።

"ማንም ምራቁን የሚውጥልሽ ቆንጆ ነሽ፣ ተግባቢ ነሽ፣ በምንም ምክንያት ይሁን ተግባብተሽዋል።" ቀጠለ።


ሰውየው ማወቅ ስላለብኝ የኤፍሬም ባህርያትና ይጠቅምሻል ያለኝን የቤተሰቡን እና የኤፍሬምን ያለፈ ታሪኮች ነገረኝ፡
አያሌው ሂሳብ ክፍለ ጊዜ ላይ ብቻ የፃፍኩትን ቁጥር መጠን ብር ሳይጠራልኝም በፊት ኤፍሬምን ለመጥበስ አስቤ ነበር።ተጨማሪ ስራ ስለተደረበልኝ የመሳካት እድሉ የእስራኤሎችን የተስፋይቱ ምድር ከንዓን ያህል ሩቅ እንደሆነ ቢሰማኝም
እያወሩላት እያዩዋት፣ እየተዋጉላት
አርባ ዓመት እንደመባተል፣ ዘምረውላት ሳይኖሩባት ምድረ በዳ
እንደመቅለጥ) ባይሳካልኝ የምጎዳው ነገር የለም ከዚህ በፊት እንደነበረኝ አይነት ሽግግር ወደ ሌላ ሀብታም ቀን መሰስ ብዬ እገባለሁ፡፡ ቢሳካልኝ ደግሞ ፐ! መሞከር ከምንም ይሻላል።

“ሁሌም ቢሆን ደግሞ የአዳም ድክመቱ ሄዋን ናት! አይደል?

ቆዩማ ስራዬን ከመጀመሬ በፊት ኤፍሬምን እና ቤተሰቡን
እንዴት እንዳወቅኳቸው ልንገራችሁ:: ከአስማማው ጋር አንድ ትልቅ የሀብታሞች እና የቦርጫሞች እራት ላይ ታደምኩ።
አስማማው የሆነች ሴትዮ ባል፣ የእኔ ስም የሌለው ነገሬ ነው።
እናስ አብሬው ምን እያደረግኩ እንደሆነ ከጠየቃችሁኝ የስራ ልምድ እየደመርኩ ነዋ! ቅምጡ ነኝ! ለስራዬ ተገቢውን ክፍያ ይከፍለኛል አንዳንዶች ያው ሽርሙጥና ነው ልትሉት ትችላላችሁ። እኔ አልስማማም:: ሽርሙጥና የሚሆነው ከተለያየ ወንድ ክፍያ ሲገኝበት ነው የሚመስለኝ።እኔ ቢያንስ በአንዴ

ከተለያየ ወንድ ጋር አልሆንም።በአንድም ቀን ይሂድ በአንድ ዓመት አንዱ
ካልሄደ ሌላ አልጠብስም።

እየሽረሞጥኩ እንዳይመስለኝ ደሞ እንደ እነዚህ ያሉ ዝግጅቶችን ጨምሮ
የሰውየው የተለያየ የቀን እንቅስቃሴዎች ውስጥ ጥልቅ እላለሁ።

ለነገሩ የፈለጋችሁትን በሉት ጉዳዬ አይደለም፡፡ ድንግል ናት ብላችሁኝም ቢሆን ኖሮ ለድንግልናዬ የአንድ ቀን
ቀለብ አትሰፍሩልኝም። አልያም ለክብሬ ብላችሁ የአንድ ወር የቤት ኪራይ አትከፍሉልኝም ነበር። ለምግባሬ የፈለጋችሁን ስድብ ብትለጥፉበትም ነፍስ ገለመሌ ህሊና ቅብርጥሶ እያልኩ
ባልፈላሰፍም ለስጋዬ መደበኛ የእለት ፍላጎቱን እየሞላሁለት ነው። የእለት መደበኛ ፍላጎቴ ምን መሰላችሁ? ወንድሜና እናቴ ናቸው።

ከአስማማው ጋር የታደምኩበት እራት የኤፍሬም ሽንጣም ስም ያለው ድርጅት ዓመታዊ ሪፓርት እና የአዲስ በጀት ዓመት አንኳር እቅዶች የሚወሱበት ስብሰባ ነገር ነው።

ጠቅላላው የድርጅቱ ሰራተኞችን እና ድርሻ ተጋሪዎችን እንዲሁም አጋር ድርጅት ሀላፊዎችን ያሰባሰበ እራት ነበር፡፡

ሁሉንም የኤፍሬምን ቤተሰቦች ለመጀመሪያ ጊዜ ያየኋቸው እዛ
ነው። አያሌውንም አይቼው ነበር። ወሬያቸው፣ አለባበሳቸው፣ቄንጣቸው፣ ሳቃቸው፣ የሚያጨሱት ፒፓ አህ! ይጨንቃሉ።
ሁሉም ነገራቸው ቄንጥ ስለሚበዛበት ለበጣ ይመስላል፡፡ ሰው ሳመሳቅ ቄንጥ እያበጀ ይስቃል? እነርሱን ለመምሰል አስማማው የገዛልኝ ሰውነቴን አጣብቆ እግሬ ድረስ የዘለቀው ቀሚስ
ጨንቆኛል፡፡ ከዚህ ስብስብ ወጥቶ ማጨስ አምሮኛል።

“ዓለምሽን አሳየሁሽ አይደል?" አለኝ አስማማው:: ዓለሜ ይህቺን ታክል ጠባብ አለመሆኗን ላስረዳው ባስብም፣ ለእንደአስማማው አይነት ሰው ይሄ አይነገርም ብነግረውም አይገባውም
_ የሚገርማችሁ አብዛኛዎቹ የአዲስ አበባ ሀብታሞች በአንድ ፋብሪካ ተመርተው የተተፉ እስኪመስሉ ድረስ

የሚያመሳስላቸው ነገር ይበዛል። ቦርጫቸው፣ ሳቃቸው፣ ክፍት
አፍነታቸው፣ ከእውቀትና ከምግባር ነፃ መሆናቸው፣ ሴት መውደዳቸው
በገንዘባቸው የማይገዙት ነገር እንደሌለ
ማመናቸው..... ኸረ ብዙ ነገራቸው ይመሳሰላል። አስማማው
ስለተሰበሰቡት ሰዎች ማንነት የሚደሰኩረው ዲስኩር ከምግቡ
ይልቅ ሆዴን ነፋኝ፡፡ ወሬውን ሳያስመልሰኝ በፊት ማቆም ፈልጌ ስለ ሲደመር
አንገብጋቢው ጉዳዬ ስለነበር ርዕስ ቀየርኩ።

“ብሩን አስገባህልኝ?" አልኩት::

"ረቂቅ ብር ካስገባሁልሽ እኮ ገና አስራ አምስት ቀን አልሆነም::" ግን እንደ እሱ ዓይነት ደርዘን ደነዝ ሀብታሞች ስለሚያወጡት ገንዘብ ማማረር ከጀመሩ መሄጃቸው መድረሱን ከስራ ልምዴ
አውቃለሁ፡፡ ሲጀመር ሰሞን ገንዘብ እስኪጠየቁ አይጠብቁም።

ራሴ ተነጥፌልሽ ተራመጂብኝ ማለት ነው የሚቀራቸው።ከወራት በኋላ ወይ ሌላ
👍4😁41