#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
... ሎርድ ማውንት አስቨርን ኢስትሊን ለመሰንበት ያሰበው የሁለት ሳምንት ጊዜ ከማለፉ በፊት የእግሩ በሽታ ክፉኛ ስለ ተቀስቀሰበት ወቶ ሊሔድ አልቻለም ሚስቸር ካርይልን ግን
ሁኔታውን በማየት አስከ ፈለገበት ጊዜ ድረስ ሳይሰቀቅ ቢቆይ እንደማይከፋው ገለጸለት ኧርሎም ቶሎ ሽሎት በእግፋ እንደሚቆም ተስፋ በማድረግ ሚስተር ካርላይልን አመሰግነው።
ቢሆንም እንዳሰበው አልተሻለውም " በሽታው ሙሉ በሙሉ ባያስተኛውም ከቤት መውጣት ሳይችል እስከ ጥቅምት ቆየና ትንሽ ምልስ አለለት »
በአጥቢያው የታወቁ ሰዎችም በሽኛውን ተመላልስው ከመጠየቃቸውም ሌላ ሳቤላንም ከቤታቸው እየጠሩ በማነጋገርና በማስተናድ መልካም ጉርብትናቸውን አሳዩዋት " ከሁሉ የበለጠ የርሱ ዋና ጠያቂ ግን ሚስተር ካርላይል ነበር "
ከኧርሎና ከሳቤላ ጋር በጣም ተቀራረቡ " ኧርሎ ከመጠን በላይ ስላላመደወና ስለ ወደደው አንዳንድ ቀን ብቅ ሳይል የቀረ እንዴሆነ በጣም ቅር ይለው ነበር
« እኔ ከኅብረተሰብ የቶለየሁ ብቸኛ ነኝ » አላት ለልጁ " « ሚስትር ካርላይል ይህን ችግሬን ዐውቆ እዚህ ድረስ እየተመለሰ የብቸኝነት በሺታዬን ሲያቀልልኝ ደግነቱና ለሰው አሳቢነቱ በጣም ይሰማኛል።
« በጣም ደግ ሰው ነው እኔማ በጣም ነው የምወደው..አባባ » አለችው
« እኔ ልጄ . . . የሱን ያህል የምወደው ሰው የለኝም » ሚስተር ካርላይል እንደ
ልማዱ በሽተኛውን ለማነጋገር መጥቶ ሳለ አባቷ ሳቤላን እንድትዘምርላቸው
ጠየቃት።
«ካልክ እሺ ... አባባ " ግን የፒያኖው ቅኝት በጣም ስለ ተበላሸ ምቱ ከድምፄ ጋር አይስማማም ደስ አይልም ዌስትሊን ውስጥ እዚህ ድረስ መጥቶ ፒያኖ የሚያይልኝ ሰው አይገኝም ... ሚስተር ካርላይል ?
« ኧረ አለ ሚስተር ኬን ሊያስተካክለው ይችላል » ነገ ልላከው ? »
« የማያስቸግርህ ከሆነ በጣም ደስ ይለኛል " ዕቃው እንኳ ስለ አረጀ ለጊዜው እንጂ ቅኝቱ እምብዛም አይረዳውም " ኢስት ሊን ውስጥ ብዙ የምንሰነብት ከሆነ በአዲስ እንዲተካው አባባን እጠይቀዋለሁ»
ምስኪኗ ሳቤላ ' ፒያኖው የሚስተር ካርላይል እንጂ የሷ አለመሆኑን አላወቀችም » ኧርሎ እንደ መሳል አለና ከሚስተር ካርላይል ጋር በፊት ፈገግታና በዐይን ጥቅሻ ተነጋገሩ ።
ሚስተር ኬን የቤተ ክርስቲያን ኦርጋኖን ተጫዋችና ተማሪ ነበር በበነጋው ወደ ኢስት ሊን ሲመጣ ሳቤላ እንዳጋጣሚ ፒያኖ ስትጫወት አገኛት " በትሕትና
በፈገግታ ተቀበለችው ለማንም ቢሆን ትሑትና ማራኪ ጠባይ ነበራት አታስፈራም " አትከብድም " ሙዚቀኛዋ በፈገግታዋ በመበራታት ድፍረት ተሰማውና
የራሱን የኑሮ ስንክሳር ይተርክላት ጀመር " ምንም ያልነበረው ድሃ መሆኑን ብዙ እየተጨነቀ ነገራት " ከችግሩ ጥናት የተነሣም ትንሽ ገንዘብ ቢያገኝ ብሎ በተከታይ ሳምንት አንድ የሙዚቃ ትርዒት ለማሳየት ተዘጋጅቶ ነበር " ስለዚህ ሳቤላና አባቷ ቢገኙለት ' የነሱን አርዓያ በመከተል ብዙ ሕዝብ እንደሚገባለትና ደኅና ገንዘብም ማግኘት እንደሚችል ገልጾ ለመናት " የሙዚቃው ትርዒት የተሳካ እንደሆነ ኑሮውን በደኅና ለመቀጠል እንደሚችል ካልተሳካ ግን ካለበት ቤት እንኳን ከነቤተሰቡ እንደሚባረር የቤት ዕቃውም ለተቀመጠበት የሁለት ዓመት ውዝፍ ኪራይ በሐራጅ እንደሚሸጥ እያስተዛዘነ አወጋት ሚስተር ኬን የሰባት ልጆች አባት ነበር" ሳቤላ የሰውየውን ታሪክ ስትሰማና ሁኔታውን ስትረዳ አንጀቷ ተንሰፈሰፈና
አባቷን ለመነችው "
« አባባ . . . አንድ ትልቅ ነገር እንድታደርግልኝ ብለምንህ እሺ ትለኛለህ ? »
« ምናለ ልጄ ... ብዙ ጊዜ ጠይቀሽኝ አታውቂም ምንድነው እሱ ? »
« ዌስት ሊን ውስጥ በቅርቡ ከሚታይ አንድ የሙዚቃ ትርዒት እንድትወሰደኝ እፈልግ ነበር " »
ኧርሎ በመገረም ሳቤላን ዐይኑን አፍጥጦ ተመለከታት
«ዌስት ሊን ላይ የሚታይ የሙዚቃ ትርዒት? » አለና ሳቀ « ባላገር ጅማት ሲከረክር ለመስማት ? ላቤላ ልጄ ምን ነካሽ ? »
ሳቤላ የሰማችውን የዚያን ሰው ታሪክና የራሷንም እያከለች አብራርታ ተረከችለት "
« ሰባት ልጆች . . . አባባ ! የሙዚቃው ትርዒት ካልተዋጣለት ያለበትን ቤት ለቆ እነዚያን ልጆች ሁሉ እንደያዘ ከአውራ መንገድ መፍሰሱ ነው ለሱ የሞትና
የሕይወት ጉዳይ ነው #ምናምኒት የሌለው ድሃ ነው»
« እኔም ድሃ ነኝ » አላት አባቷ "
«ሲናገር ብትሰማው አባባ ... ፊቱ ዐሥር ጊዜ ሲለዋወጥ ፡ የችግሩን ጥናት ስለገለጸ ኃፍረት እያስጨነቅው ትንፋሹን ያዝ ለቀቅ ሲያዶርግ ንግግሩ ቁርጥ
ቁርጥ ሲል አንጀት ይበላል እርግጠኛ ነኝ ሰውየው ቀን የጣለው የሀብታም ወገን
ነው »
« አዬ ጉድ የመንዶር ሙዚቃ ! በይ ደግ ነው የአንድ ፓውንድ ቲኬቶች ገዝተሽ ለትልልቆቹ አሽከሮች መስጠት ትችያለሽ »
« እንደሱ አይዶለም እኮ አባባ ( አንተና እኔ እንደምንገኝለት ቃል ከገባንለት በዌስት ሊን አካባቢ ያሉ ታላላቅ ሰዎች ስለሚመጡ አዳራሹ ሊሞላ ይችላል " አሽከሮቻችንን ልከን እኛ እንደምንቀር ከሰሙ ግን ለመገኘት ያሰቡት ሁሉ ይቀራሉ ።እስኪ አንተም አስበው . . . አባባ " አሁን ይኸን ቤትህን ከነዕቃው እንዳለ ቢወስዱብህ ምን ይሰማሃል ? ሰው አዳራሹ እስኪሞላ ከገባለት ግን ከዚህ ጉድ ሊድን ይችላል " አባባ ...እንደ ምንም ብለህ ለአንድ ሰዓት ቢሆንም ተገኝለት እኔ የታምቡር ጓጓታና የክራር ክርከራ ብቻ ቢሆንም ያስደስተኛል
« መንቻካ ለማኝ ነሽ ! በይ ለግማሽ ሰዓት ያህል ተገኝተን እናይለታለን ንገሪው»
ወደ ሚስተር ኬን እየሮጠች ሔደችና« ሚስተር ኬን... አባቴ ጥያቄህን ተቀብሎታል እሱ አራት ቲኬቶች ይገዛል " አባባና እኔ እንገኛለን » አለችው።
የሚስተር ኬን ዐይኖች የደስታ እንባ አቀረሩ ። ሳቤላም የሰውየውን ደስታ ስታይ የእሷም ዐይኖች እንባ ማቅረር አማራቸው።
« ብዙ ሰው እንዲባልህ የሚረዳህ ከሆነ ለምታገኘው ሁሉ ንገር « እኔም ለሰው ሁሉ እንደምንግባ እየነገርኩ እነሱም እንዲገኙ እጠይቅልሀለው አለችው።
ማታ ሚስተር ካርላይል ሎርድ ዊልያም ቬንን ለመጠየቅ መጣ ኧርሎ ለጊዜው ከክፍሉ አልነበረም ሳቤላ ስለ ሚስተር ኬን ትርዒት አነሣችለት "
« ሚስተር ኬን ከባድ ድፍረት ነው ያደረገው» አለ ሚስተር ካርላይል"
« ይልቅ የበለጠ ገንዘብ እንዳያወጣና በችግሩ ላይ ችግር እንዳይጨምር እፈራለታለሁ
« ለምንድነው ይኸ ሥጋት የተሰማህ ? »
« እሱ ዌስት ሊን ውስጥ ሙዚቃ ለማሳየት ቢሞክር ሰው አያደንቅለትም ሕዝቡ የሱን ችግር ደጋግሞ የሰማውና የሚያውቀው ስለሆነ አንድም ሰው ዞሮ አያየውም አንድ ያልታወቀ እንግዳ ተጫዋች ከውጭ ቢመጣ ግን የዌስት ሊን ሕዝብ ይጐርፍለት ነበር»
«ግን ድህነቱ እሱ እንደሚናገረው እውነት ነው ? » አለችው ሳቤላ "
«በጣም በርግጥ እንጀራ ሊኖረው ይችላል ግን የተሟላ ምግብ አያገኝም በኦርጋኖ ተጨዋችነቱ ባመት ሠላላ ፖውንድ ያገኛል ! ዐልፎ ዐልፎ በማስተማር
ይደጎማል ሚስቱና ልጆቹ የሚኖሩት በዚህ ገቢ ነው " ቤተሰቡ ሥጋ የሚባል ነገር ቀምሰው የሚያውቁ አይመስለኝም»
« ሰውዬውን ሳየው ሚስተር ካርላይል የትልቅ ሰው ልጅ ይመስላል»
« እውነትሽን ነው " የትልቅ ሰው ልጅ ነበር " አባቱ ካህን ነበሩ " እሱ ሙዚቃ በመውደዱ ነው ኑሮው የተበላሸው ደኅና ክፍያ ከሚገኝበት ሥፍራ እንዳይረጋ
አደረገው " ሌላው የውድቀቱ ምክንያት ደግሞ ገና በልጅነቱ በማግባቱ ነው . .
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
... ሎርድ ማውንት አስቨርን ኢስትሊን ለመሰንበት ያሰበው የሁለት ሳምንት ጊዜ ከማለፉ በፊት የእግሩ በሽታ ክፉኛ ስለ ተቀስቀሰበት ወቶ ሊሔድ አልቻለም ሚስቸር ካርይልን ግን
ሁኔታውን በማየት አስከ ፈለገበት ጊዜ ድረስ ሳይሰቀቅ ቢቆይ እንደማይከፋው ገለጸለት ኧርሎም ቶሎ ሽሎት በእግፋ እንደሚቆም ተስፋ በማድረግ ሚስተር ካርላይልን አመሰግነው።
ቢሆንም እንዳሰበው አልተሻለውም " በሽታው ሙሉ በሙሉ ባያስተኛውም ከቤት መውጣት ሳይችል እስከ ጥቅምት ቆየና ትንሽ ምልስ አለለት »
በአጥቢያው የታወቁ ሰዎችም በሽኛውን ተመላልስው ከመጠየቃቸውም ሌላ ሳቤላንም ከቤታቸው እየጠሩ በማነጋገርና በማስተናድ መልካም ጉርብትናቸውን አሳዩዋት " ከሁሉ የበለጠ የርሱ ዋና ጠያቂ ግን ሚስተር ካርላይል ነበር "
ከኧርሎና ከሳቤላ ጋር በጣም ተቀራረቡ " ኧርሎ ከመጠን በላይ ስላላመደወና ስለ ወደደው አንዳንድ ቀን ብቅ ሳይል የቀረ እንዴሆነ በጣም ቅር ይለው ነበር
« እኔ ከኅብረተሰብ የቶለየሁ ብቸኛ ነኝ » አላት ለልጁ " « ሚስትር ካርላይል ይህን ችግሬን ዐውቆ እዚህ ድረስ እየተመለሰ የብቸኝነት በሺታዬን ሲያቀልልኝ ደግነቱና ለሰው አሳቢነቱ በጣም ይሰማኛል።
« በጣም ደግ ሰው ነው እኔማ በጣም ነው የምወደው..አባባ » አለችው
« እኔ ልጄ . . . የሱን ያህል የምወደው ሰው የለኝም » ሚስተር ካርላይል እንደ
ልማዱ በሽተኛውን ለማነጋገር መጥቶ ሳለ አባቷ ሳቤላን እንድትዘምርላቸው
ጠየቃት።
«ካልክ እሺ ... አባባ " ግን የፒያኖው ቅኝት በጣም ስለ ተበላሸ ምቱ ከድምፄ ጋር አይስማማም ደስ አይልም ዌስትሊን ውስጥ እዚህ ድረስ መጥቶ ፒያኖ የሚያይልኝ ሰው አይገኝም ... ሚስተር ካርላይል ?
« ኧረ አለ ሚስተር ኬን ሊያስተካክለው ይችላል » ነገ ልላከው ? »
« የማያስቸግርህ ከሆነ በጣም ደስ ይለኛል " ዕቃው እንኳ ስለ አረጀ ለጊዜው እንጂ ቅኝቱ እምብዛም አይረዳውም " ኢስት ሊን ውስጥ ብዙ የምንሰነብት ከሆነ በአዲስ እንዲተካው አባባን እጠይቀዋለሁ»
ምስኪኗ ሳቤላ ' ፒያኖው የሚስተር ካርላይል እንጂ የሷ አለመሆኑን አላወቀችም » ኧርሎ እንደ መሳል አለና ከሚስተር ካርላይል ጋር በፊት ፈገግታና በዐይን ጥቅሻ ተነጋገሩ ።
ሚስተር ኬን የቤተ ክርስቲያን ኦርጋኖን ተጫዋችና ተማሪ ነበር በበነጋው ወደ ኢስት ሊን ሲመጣ ሳቤላ እንዳጋጣሚ ፒያኖ ስትጫወት አገኛት " በትሕትና
በፈገግታ ተቀበለችው ለማንም ቢሆን ትሑትና ማራኪ ጠባይ ነበራት አታስፈራም " አትከብድም " ሙዚቀኛዋ በፈገግታዋ በመበራታት ድፍረት ተሰማውና
የራሱን የኑሮ ስንክሳር ይተርክላት ጀመር " ምንም ያልነበረው ድሃ መሆኑን ብዙ እየተጨነቀ ነገራት " ከችግሩ ጥናት የተነሣም ትንሽ ገንዘብ ቢያገኝ ብሎ በተከታይ ሳምንት አንድ የሙዚቃ ትርዒት ለማሳየት ተዘጋጅቶ ነበር " ስለዚህ ሳቤላና አባቷ ቢገኙለት ' የነሱን አርዓያ በመከተል ብዙ ሕዝብ እንደሚገባለትና ደኅና ገንዘብም ማግኘት እንደሚችል ገልጾ ለመናት " የሙዚቃው ትርዒት የተሳካ እንደሆነ ኑሮውን በደኅና ለመቀጠል እንደሚችል ካልተሳካ ግን ካለበት ቤት እንኳን ከነቤተሰቡ እንደሚባረር የቤት ዕቃውም ለተቀመጠበት የሁለት ዓመት ውዝፍ ኪራይ በሐራጅ እንደሚሸጥ እያስተዛዘነ አወጋት ሚስተር ኬን የሰባት ልጆች አባት ነበር" ሳቤላ የሰውየውን ታሪክ ስትሰማና ሁኔታውን ስትረዳ አንጀቷ ተንሰፈሰፈና
አባቷን ለመነችው "
« አባባ . . . አንድ ትልቅ ነገር እንድታደርግልኝ ብለምንህ እሺ ትለኛለህ ? »
« ምናለ ልጄ ... ብዙ ጊዜ ጠይቀሽኝ አታውቂም ምንድነው እሱ ? »
« ዌስት ሊን ውስጥ በቅርቡ ከሚታይ አንድ የሙዚቃ ትርዒት እንድትወሰደኝ እፈልግ ነበር " »
ኧርሎ በመገረም ሳቤላን ዐይኑን አፍጥጦ ተመለከታት
«ዌስት ሊን ላይ የሚታይ የሙዚቃ ትርዒት? » አለና ሳቀ « ባላገር ጅማት ሲከረክር ለመስማት ? ላቤላ ልጄ ምን ነካሽ ? »
ሳቤላ የሰማችውን የዚያን ሰው ታሪክና የራሷንም እያከለች አብራርታ ተረከችለት "
« ሰባት ልጆች . . . አባባ ! የሙዚቃው ትርዒት ካልተዋጣለት ያለበትን ቤት ለቆ እነዚያን ልጆች ሁሉ እንደያዘ ከአውራ መንገድ መፍሰሱ ነው ለሱ የሞትና
የሕይወት ጉዳይ ነው #ምናምኒት የሌለው ድሃ ነው»
« እኔም ድሃ ነኝ » አላት አባቷ "
«ሲናገር ብትሰማው አባባ ... ፊቱ ዐሥር ጊዜ ሲለዋወጥ ፡ የችግሩን ጥናት ስለገለጸ ኃፍረት እያስጨነቅው ትንፋሹን ያዝ ለቀቅ ሲያዶርግ ንግግሩ ቁርጥ
ቁርጥ ሲል አንጀት ይበላል እርግጠኛ ነኝ ሰውየው ቀን የጣለው የሀብታም ወገን
ነው »
« አዬ ጉድ የመንዶር ሙዚቃ ! በይ ደግ ነው የአንድ ፓውንድ ቲኬቶች ገዝተሽ ለትልልቆቹ አሽከሮች መስጠት ትችያለሽ »
« እንደሱ አይዶለም እኮ አባባ ( አንተና እኔ እንደምንገኝለት ቃል ከገባንለት በዌስት ሊን አካባቢ ያሉ ታላላቅ ሰዎች ስለሚመጡ አዳራሹ ሊሞላ ይችላል " አሽከሮቻችንን ልከን እኛ እንደምንቀር ከሰሙ ግን ለመገኘት ያሰቡት ሁሉ ይቀራሉ ።እስኪ አንተም አስበው . . . አባባ " አሁን ይኸን ቤትህን ከነዕቃው እንዳለ ቢወስዱብህ ምን ይሰማሃል ? ሰው አዳራሹ እስኪሞላ ከገባለት ግን ከዚህ ጉድ ሊድን ይችላል " አባባ ...እንደ ምንም ብለህ ለአንድ ሰዓት ቢሆንም ተገኝለት እኔ የታምቡር ጓጓታና የክራር ክርከራ ብቻ ቢሆንም ያስደስተኛል
« መንቻካ ለማኝ ነሽ ! በይ ለግማሽ ሰዓት ያህል ተገኝተን እናይለታለን ንገሪው»
ወደ ሚስተር ኬን እየሮጠች ሔደችና« ሚስተር ኬን... አባቴ ጥያቄህን ተቀብሎታል እሱ አራት ቲኬቶች ይገዛል " አባባና እኔ እንገኛለን » አለችው።
የሚስተር ኬን ዐይኖች የደስታ እንባ አቀረሩ ። ሳቤላም የሰውየውን ደስታ ስታይ የእሷም ዐይኖች እንባ ማቅረር አማራቸው።
« ብዙ ሰው እንዲባልህ የሚረዳህ ከሆነ ለምታገኘው ሁሉ ንገር « እኔም ለሰው ሁሉ እንደምንግባ እየነገርኩ እነሱም እንዲገኙ እጠይቅልሀለው አለችው።
ማታ ሚስተር ካርላይል ሎርድ ዊልያም ቬንን ለመጠየቅ መጣ ኧርሎ ለጊዜው ከክፍሉ አልነበረም ሳቤላ ስለ ሚስተር ኬን ትርዒት አነሣችለት "
« ሚስተር ኬን ከባድ ድፍረት ነው ያደረገው» አለ ሚስተር ካርላይል"
« ይልቅ የበለጠ ገንዘብ እንዳያወጣና በችግሩ ላይ ችግር እንዳይጨምር እፈራለታለሁ
« ለምንድነው ይኸ ሥጋት የተሰማህ ? »
« እሱ ዌስት ሊን ውስጥ ሙዚቃ ለማሳየት ቢሞክር ሰው አያደንቅለትም ሕዝቡ የሱን ችግር ደጋግሞ የሰማውና የሚያውቀው ስለሆነ አንድም ሰው ዞሮ አያየውም አንድ ያልታወቀ እንግዳ ተጫዋች ከውጭ ቢመጣ ግን የዌስት ሊን ሕዝብ ይጐርፍለት ነበር»
«ግን ድህነቱ እሱ እንደሚናገረው እውነት ነው ? » አለችው ሳቤላ "
«በጣም በርግጥ እንጀራ ሊኖረው ይችላል ግን የተሟላ ምግብ አያገኝም በኦርጋኖ ተጨዋችነቱ ባመት ሠላላ ፖውንድ ያገኛል ! ዐልፎ ዐልፎ በማስተማር
ይደጎማል ሚስቱና ልጆቹ የሚኖሩት በዚህ ገቢ ነው " ቤተሰቡ ሥጋ የሚባል ነገር ቀምሰው የሚያውቁ አይመስለኝም»
« ሰውዬውን ሳየው ሚስተር ካርላይል የትልቅ ሰው ልጅ ይመስላል»
« እውነትሽን ነው " የትልቅ ሰው ልጅ ነበር " አባቱ ካህን ነበሩ " እሱ ሙዚቃ በመውደዱ ነው ኑሮው የተበላሸው ደኅና ክፍያ ከሚገኝበት ሥፍራ እንዳይረጋ
አደረገው " ሌላው የውድቀቱ ምክንያት ደግሞ ገና በልጅነቱ በማግባቱ ነው . .
👍13❤2