#ምርጫ_አልባ_ምርጫ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
እኔ ወደ ህይወቱ ብቅ ማለቴን አክሎ ነገረኝ።
እናቱ በግልፅ “ስራህን ከቁስልህ መደበቂያ አድርገኸዋል። ያንተን
ድርቅናና የሟች ሚስትህን ትዝታ ማስታመም እየሰለቸኝ ነው::"
ብለውት ልቡ መድቀቁን ሲነግረኝ ግን ያቺ ከቀናት በፊት ሊያያት እንደማይፈልግ ሲሆንባት ለነበረችው ረቂቅ እየተናገረ አይመስልም።
"በዚህ ከቀጠልኩ እነርሱ እንደሚፈሩት ከዓመታት በኋላ የድርጅቱንም ሆነ የቤተሰባችንን ህልውና አደጋ ላይ ልጥለው እንደምችል ማሰቤ ይባስ ውጥንቅጥ ውስጥ ይከተኛል::" ሲለኝ
ይሄን ሀሳብ ለጥዝጠዛ ለማመቻቸት ወሳኙ ጊዜ መሆኑን አሳሰበኝ።
"ጥቅሙ የሚያመዝን ከሆነ ለምን በቤተሰቦችህ ሀሳብ አትስማማም?"
"አንደኛ አሳማኝ አይደለም፡፡ በግሌ ከማስተዳድራቸው ዘርፎች
በላይ ፋብሪካው ትርፋማ እየሆነ በመጣበት ወቅት በተለይ የእማዬ እንዲሸጥ መወትወት አልዋጥልህ ነው ያለኝ፡፡ ሁለተኛኀአባዬ ያስረከበኝን ምንም
ነገር ማብዛት እንጂ ማጉደል አልፈልግም።
መቃብሩ ጋር ጥዬው የሄድኩ ዕለት ራሱን ስቶ ሀኪም ቤት ገብቶ ነበር፡፡ ማረፍ እንዳለበት በሀኪም ስለታዘዘ ለወንድሙ
ውክልና ፈርሞለት እረፍት መሆኑን እና ላይደውልልኝ ከራሱ ጋር ብዙ ቢሟገትም ቀኖቹ አላልቅ ብለውት አማራጭ ሲያጣ
እነደደወለልኝ ሳይደብቅ ነገረኝ።
አሁን ጓደኝነቴን አምነህ ብትቀበል ነው የሚያዋጣህ።"
"ምን ያህል “ኮስት ያደርገኛል?"
እንነጋገርበታለን::" አልኩት:: ፈገግ አለ፡፡ መስማማቱ ነው።
"ስለሴት ልጅ የምትወደውን ሶስት ነገሯን ንገረኝ እስቲ?" አልኩት እራት መብላት ጨርሰን ወደ ቤት እየሸኘኝ፡፡ ጠዋት
ወደ ላንጋኖ ልንሄድ ተቀጣጥረናል።
"እናትነቷን"
ሶስት ነው ያልኩህ::"
"እኔ ስለሴት ልጅ ይሄ የምለው የተለየ ነገር አልወድም። ራሷን ስትሆን፣ የራሷ እምነት ፣ የራሷ ፋሽን፣ የራሷ ኩራት! በቃ
የራሷ ነገር ሲኖራት ራሷን ስትሆን ደስ ትለኛለች:: የሰው ልጅ ምርጥ እየሆነ የሚመስለኝ ራሱን ወደ መሆን ሲያድግ ነው።"
“ለምሳሌ?"
“ለምሳሌ እንዳንቺ!! እራት ቀጥሬሽ ቁምጣ በቲሸርት ለብሰሽ
ትመጫለሽ" አለኝ ቁምጣዬን እያየ::" ቤዚካሊይ የራስሽ የሆነውን ነገር ሰው ለማስደሰት ብለሽ አትቀይሪውም::"
"በቻይንኛ ወድጄሻለሁ እንደማለት”
ባህሪሽ ደስ ይለኛል ማለት በቻይንኛ ወድጄሻለሁ እንደማለት መሆኑን አላውቅም ነበር።" ፈገግ አለ።"አንቺስ?"
"እኔ ምን?"
"አባትነቱን"
"ሶስት ነው ያልኩሽ?" አለ እየተንፈቀፈቀ::
"ባክህ የወንድ ሁሉ ተምሳሌቴ ወንድሜ ነው፡፡ ዓይንህን ብቻ አይቶ ጥልቅ ስሜትህ የሚገባው አይነት ነው። የወንድ መለኪያዬ እሱ ነው።
ወዲያው ስልኬ ጠራ። አያሌው ነው። ኤፍሬምን ቀና ብዬ አየሁት። አንሺው፣ ችግር የለውም::” እንደማለት ምልክት
አሳየኝ፡፡ ለኔ ግን የገባኝ፡፡ 'አምንሻለሁ እንዳለኝ ነበር:: አነሳሁት።
"እድል ካንቺ ጋር የሆነች ይመስላል፡፡ ተጠቀሚባት:: እንደሌሎቹ
ወንዶች አጣጥሞሽ ሲበቃው ከነድህነትሽ ጥሎሽ እንዲሄድ
አትፍቀጂለት" አለኝ፡
፡መልስ ሳልሰጠው ዘጋሁት።
"ምን እያሰብክ ነው?" አልኩት ላንጋኖ ሀይቁ ዳር አሸዋው ላይ እንደተቀመጥን፡፡ እኩለ ለሊት ሆኗል፡፡ ከመጣን ሶስተኛ ቀናችን ነው።
"አንቺን" አለኝ፡፡ በኤፍሬም ድምፅ ይሄን መስማት ብዙ ነገር ነበር፡፡
"እቀፈኝ!"
ግን እንደዛ አላደረገም:: ከአጠገቤ ተነስቶ ከጀርባዬ በኩል እግሮቹ
መሃል አድርጎኝ ተቀመጠ። በግዙፍ ሰውነቱ ሙሉ ውስጡ ደበቀኝ። ከብዙ ክፋቶች የተጠበቅኩ መሰለኝ፡፡ አንገቴ ስር የሚሰማኝ ሞቅታ ትንፋሹ እጠብቅሻለሁ፣ አለሁልሽ' ያለኝ
መሰለኝ፡፡ የማንም ወንድ ገላ በዚህ መጠን ናፍቆኝ ማወቁን እጠራጠራለሁ
"እንግባ?" ከማለቱ እኔ ተነስቻለሁ። ገብቶታል።እንደህፃን ልጅ ብድግ አድርጎ ከመሬት አንስቶ እንደታቀፈኝ አልጋው ጋረሸ አደረሰኝ።
መች ነው እንዲህ ለሱ የተሰማኝ? ከዛሬ በፊት በነበሩት ቀናት?፣ከአዲስ አበባ ስንመጣ እግሮቹ ላይ እንቅልፌን ተኝቼ መኪና ሲነዳ?፣ ሀይቁ ውስጥ ስንዋኝ?፣ የጠረጴዛ ቴኒስ ስንጫወት?፣
ቼዝ ሲያለማምደኝ?፣ ካንፋየር አጠገብ እራት እየበላን ውስኪ ስንጠጣ? ክፍላችን ውስጥ በድሮ ሙዚቃ የድሮ ዳንስ ስንደንስ?እግሩ ስር አስቀምጦኝ ፀጉሬን ሲያበጥርልኝ ካርታ ተጫውተን አሸንፌው በውርርዱ አዝሎኝ ጊቢውን ዞር በአንዱ ወይም በሁሉም ሰዓት የተለየ ስሜት ተሰምቶኛል።
ቁርስ መብላት ደስ የሚለኝ ፍርፍር በሻይ ነው::" አለኝ ጠዋት እቅፉ ውስጥ እንዳለሁ።
"ፍርፍር? ፍርፍር? ስጋ ሳይኖረው?"
ቢኖረው ጥሩ! ባይኖረውም ከሌላ ምግብ ፍርፍር ምርጫዬ ነው:" አለኝ ከአልጋው ለመነሳት ያቀፈኝን እጁን በቀስታ እያነሳ።
"እንቆይ? እንደዚህ ትንሽ እንቆይ? አቅፈኸኝ ትንሽ እንተኛ?" አልኩት:: ተመልሶ አጥብቆ አቅፎኝ ተኛ።
መታቀፍ የተለየ ትርጉም እና ስሜት የሚሰጠኝ ነገር ነው። ለአቃፊው የምሰጠው ዋጋ የትርጉሙን ልኬት የሚያወጣና የሚያወርደው ቢሆንም ያቀፈኝ ሰው ስሜቴን ብነግረው ባልነግረውም ያጋባሁበት እነደሆነ ነው የሚሰማኝ።ባቀፈኝ ቅፅበት ሸክሜን የተጋራልኝ፣ ካለሁበት ትርምስ የደበቀኝ ነው የሚመስለኝ፡፡ ይሄን ትርጉም በትክክል የሚያሟላልኝ የእማዬና
የበርዬ እቅፍ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ተሰምቶኝ በማያውቅ ልክ የኤፍሬም።
ከሶስት ቀናት በኋላ ከራሴ እውነት ጋር መላተም ጀመርኩ::አያሌው እቤት ድረስ መጥቶ አስር ሺህ ብር አስቀምጦልኝ
መሄዱን በርዬ ነገረኝ፡፡
"እሺ ልመልስለት:: ከዛስ? ከዛ ምን እንብላ? ከዛ ለእማዬ ምን
እንሰርላት? ከዛ ገንዘብ ፍለጋ የማልወደው ገላ ላይ ልጣድ?
ንገረኛ?" ብሩን መልሺለት ስላለኝ ነው በርዬ ላይ የምጮኸው።ለኤፍሬም እውነቱን እንድነግረው ሲወተውተኝ፡፡
በርዬ አቀረቀረ:: አድርጌው እንደማላውቅ
ሁሉ ለገንዘባቸው ከምተኛላቸው ወንዶች ጋር መሆን ቀፋፊ ነገር ሆነብኝ፡፡
ከኤፍሬም ጋር የስራሁትን ፍቅር ማርከስ መሰለኝ፡፡ የሆነ ልክ ከኤፍሬም ጋር ከተኛሁ በኋላ ገላዬ የተቀደሰ ነገር መሰለኝ፡፡ ያንን ማርከስ መሰለኝ፡፡ በእርግጥ ኤፍሬምን ገንዘብ ብጠይቀው
ይከለክለኝ ነበር? አይከለክለኝም ይሆናል፡፡ በግልፅ ምክንያት
የአያሌውን ገንዘብ ብመልስለት ለኤፍሬም እውነቱን እንደሚነግረው አስፈራርቶኛል፡፡ በድብቅ ምክንያቴ ግን ኤፍሬም ጋር ያለኝ ነገር ከዚህ በፊት ከማውቃቸው ወንዶች ጋር እንደነበረኝ ስራ እንደሆነ እንዲሰማኝና እንዲቀልብኝ
አልፈለግኩም:: ሌላው አማራጭ ግን እንደገሃነም አስፈሪ ነው፡፡እውነቱን መናገር! ለኤፍሬም የቀረብኩህ ተከፍሎኝ ነውኀልበለው? ከዛስ? ጥሎኝ ሲሄድ ትርፌ ምንድነው? ፊልም ላይ
ብቻ ነው ይሄ የሚሰራው:: አባዬ ራሱን ያጠፋው የቤተሰቡን ምስቅልቅል መሸከም ስለከበደው ነበር:: ያንን የተሸናፊ ፊቱን ልረሳው አልችልም፡፡ እኔ እማዬንና በርዬን የራሳቸው ጉዳይ ብዬ
ህሊናን መምረጥ አልችልም።የኔ ህሊና
ንፅህና የቤት ኪራያችንን አይከፍልም ወይም የበርዬን ትምህርት ቤት ክፍያ
አያጠናቅቅም አልያም ለእማዬ ስንቅ አይሆንም።ህሊና በአገልግል አይቆጠርም።
ከኤፍሬም ጋር ሳንገናኝ የዋልንበት ቀን ጠፋ። እቤት ከማድርበት ከኤፍሬም ጋር የማድርበት ቀን በለጠ፡፡ ሀኪም ያዘዘለትን ሀያ የእረፍት ቀን አረፍንበት። አብሬው አሳለፍኩ፡ እሱ በትክክል ምን እንደሚሰማው ግን አሁንም ማወቅ አልቻልኩም:: ከነዚህ ቀናት በኋላ አሁን ጥያቄዬ ህሊና ብቻ አይደለም ኤፍሬምን ማጣት ማሰብ ያስፈራኝ ጀምሯል። ኤፍሬም ሊዲያ የሞተችበት
ረቡዕ ዕለት ሁሌም መቃብሯጋ እንደሚሄድ ስለማውቅ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
እኔ ወደ ህይወቱ ብቅ ማለቴን አክሎ ነገረኝ።
እናቱ በግልፅ “ስራህን ከቁስልህ መደበቂያ አድርገኸዋል። ያንተን
ድርቅናና የሟች ሚስትህን ትዝታ ማስታመም እየሰለቸኝ ነው::"
ብለውት ልቡ መድቀቁን ሲነግረኝ ግን ያቺ ከቀናት በፊት ሊያያት እንደማይፈልግ ሲሆንባት ለነበረችው ረቂቅ እየተናገረ አይመስልም።
"በዚህ ከቀጠልኩ እነርሱ እንደሚፈሩት ከዓመታት በኋላ የድርጅቱንም ሆነ የቤተሰባችንን ህልውና አደጋ ላይ ልጥለው እንደምችል ማሰቤ ይባስ ውጥንቅጥ ውስጥ ይከተኛል::" ሲለኝ
ይሄን ሀሳብ ለጥዝጠዛ ለማመቻቸት ወሳኙ ጊዜ መሆኑን አሳሰበኝ።
"ጥቅሙ የሚያመዝን ከሆነ ለምን በቤተሰቦችህ ሀሳብ አትስማማም?"
"አንደኛ አሳማኝ አይደለም፡፡ በግሌ ከማስተዳድራቸው ዘርፎች
በላይ ፋብሪካው ትርፋማ እየሆነ በመጣበት ወቅት በተለይ የእማዬ እንዲሸጥ መወትወት አልዋጥልህ ነው ያለኝ፡፡ ሁለተኛኀአባዬ ያስረከበኝን ምንም
ነገር ማብዛት እንጂ ማጉደል አልፈልግም።
መቃብሩ ጋር ጥዬው የሄድኩ ዕለት ራሱን ስቶ ሀኪም ቤት ገብቶ ነበር፡፡ ማረፍ እንዳለበት በሀኪም ስለታዘዘ ለወንድሙ
ውክልና ፈርሞለት እረፍት መሆኑን እና ላይደውልልኝ ከራሱ ጋር ብዙ ቢሟገትም ቀኖቹ አላልቅ ብለውት አማራጭ ሲያጣ
እነደደወለልኝ ሳይደብቅ ነገረኝ።
አሁን ጓደኝነቴን አምነህ ብትቀበል ነው የሚያዋጣህ።"
"ምን ያህል “ኮስት ያደርገኛል?"
እንነጋገርበታለን::" አልኩት:: ፈገግ አለ፡፡ መስማማቱ ነው።
"ስለሴት ልጅ የምትወደውን ሶስት ነገሯን ንገረኝ እስቲ?" አልኩት እራት መብላት ጨርሰን ወደ ቤት እየሸኘኝ፡፡ ጠዋት
ወደ ላንጋኖ ልንሄድ ተቀጣጥረናል።
"እናትነቷን"
ሶስት ነው ያልኩህ::"
"እኔ ስለሴት ልጅ ይሄ የምለው የተለየ ነገር አልወድም። ራሷን ስትሆን፣ የራሷ እምነት ፣ የራሷ ፋሽን፣ የራሷ ኩራት! በቃ
የራሷ ነገር ሲኖራት ራሷን ስትሆን ደስ ትለኛለች:: የሰው ልጅ ምርጥ እየሆነ የሚመስለኝ ራሱን ወደ መሆን ሲያድግ ነው።"
“ለምሳሌ?"
“ለምሳሌ እንዳንቺ!! እራት ቀጥሬሽ ቁምጣ በቲሸርት ለብሰሽ
ትመጫለሽ" አለኝ ቁምጣዬን እያየ::" ቤዚካሊይ የራስሽ የሆነውን ነገር ሰው ለማስደሰት ብለሽ አትቀይሪውም::"
"በቻይንኛ ወድጄሻለሁ እንደማለት”
ባህሪሽ ደስ ይለኛል ማለት በቻይንኛ ወድጄሻለሁ እንደማለት መሆኑን አላውቅም ነበር።" ፈገግ አለ።"አንቺስ?"
"እኔ ምን?"
"አባትነቱን"
"ሶስት ነው ያልኩሽ?" አለ እየተንፈቀፈቀ::
"ባክህ የወንድ ሁሉ ተምሳሌቴ ወንድሜ ነው፡፡ ዓይንህን ብቻ አይቶ ጥልቅ ስሜትህ የሚገባው አይነት ነው። የወንድ መለኪያዬ እሱ ነው።
ወዲያው ስልኬ ጠራ። አያሌው ነው። ኤፍሬምን ቀና ብዬ አየሁት። አንሺው፣ ችግር የለውም::” እንደማለት ምልክት
አሳየኝ፡፡ ለኔ ግን የገባኝ፡፡ 'አምንሻለሁ እንዳለኝ ነበር:: አነሳሁት።
"እድል ካንቺ ጋር የሆነች ይመስላል፡፡ ተጠቀሚባት:: እንደሌሎቹ
ወንዶች አጣጥሞሽ ሲበቃው ከነድህነትሽ ጥሎሽ እንዲሄድ
አትፍቀጂለት" አለኝ፡
፡መልስ ሳልሰጠው ዘጋሁት።
"ምን እያሰብክ ነው?" አልኩት ላንጋኖ ሀይቁ ዳር አሸዋው ላይ እንደተቀመጥን፡፡ እኩለ ለሊት ሆኗል፡፡ ከመጣን ሶስተኛ ቀናችን ነው።
"አንቺን" አለኝ፡፡ በኤፍሬም ድምፅ ይሄን መስማት ብዙ ነገር ነበር፡፡
"እቀፈኝ!"
ግን እንደዛ አላደረገም:: ከአጠገቤ ተነስቶ ከጀርባዬ በኩል እግሮቹ
መሃል አድርጎኝ ተቀመጠ። በግዙፍ ሰውነቱ ሙሉ ውስጡ ደበቀኝ። ከብዙ ክፋቶች የተጠበቅኩ መሰለኝ፡፡ አንገቴ ስር የሚሰማኝ ሞቅታ ትንፋሹ እጠብቅሻለሁ፣ አለሁልሽ' ያለኝ
መሰለኝ፡፡ የማንም ወንድ ገላ በዚህ መጠን ናፍቆኝ ማወቁን እጠራጠራለሁ
"እንግባ?" ከማለቱ እኔ ተነስቻለሁ። ገብቶታል።እንደህፃን ልጅ ብድግ አድርጎ ከመሬት አንስቶ እንደታቀፈኝ አልጋው ጋረሸ አደረሰኝ።
መች ነው እንዲህ ለሱ የተሰማኝ? ከዛሬ በፊት በነበሩት ቀናት?፣ከአዲስ አበባ ስንመጣ እግሮቹ ላይ እንቅልፌን ተኝቼ መኪና ሲነዳ?፣ ሀይቁ ውስጥ ስንዋኝ?፣ የጠረጴዛ ቴኒስ ስንጫወት?፣
ቼዝ ሲያለማምደኝ?፣ ካንፋየር አጠገብ እራት እየበላን ውስኪ ስንጠጣ? ክፍላችን ውስጥ በድሮ ሙዚቃ የድሮ ዳንስ ስንደንስ?እግሩ ስር አስቀምጦኝ ፀጉሬን ሲያበጥርልኝ ካርታ ተጫውተን አሸንፌው በውርርዱ አዝሎኝ ጊቢውን ዞር በአንዱ ወይም በሁሉም ሰዓት የተለየ ስሜት ተሰምቶኛል።
ቁርስ መብላት ደስ የሚለኝ ፍርፍር በሻይ ነው::" አለኝ ጠዋት እቅፉ ውስጥ እንዳለሁ።
"ፍርፍር? ፍርፍር? ስጋ ሳይኖረው?"
ቢኖረው ጥሩ! ባይኖረውም ከሌላ ምግብ ፍርፍር ምርጫዬ ነው:" አለኝ ከአልጋው ለመነሳት ያቀፈኝን እጁን በቀስታ እያነሳ።
"እንቆይ? እንደዚህ ትንሽ እንቆይ? አቅፈኸኝ ትንሽ እንተኛ?" አልኩት:: ተመልሶ አጥብቆ አቅፎኝ ተኛ።
መታቀፍ የተለየ ትርጉም እና ስሜት የሚሰጠኝ ነገር ነው። ለአቃፊው የምሰጠው ዋጋ የትርጉሙን ልኬት የሚያወጣና የሚያወርደው ቢሆንም ያቀፈኝ ሰው ስሜቴን ብነግረው ባልነግረውም ያጋባሁበት እነደሆነ ነው የሚሰማኝ።ባቀፈኝ ቅፅበት ሸክሜን የተጋራልኝ፣ ካለሁበት ትርምስ የደበቀኝ ነው የሚመስለኝ፡፡ ይሄን ትርጉም በትክክል የሚያሟላልኝ የእማዬና
የበርዬ እቅፍ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ተሰምቶኝ በማያውቅ ልክ የኤፍሬም።
ከሶስት ቀናት በኋላ ከራሴ እውነት ጋር መላተም ጀመርኩ::አያሌው እቤት ድረስ መጥቶ አስር ሺህ ብር አስቀምጦልኝ
መሄዱን በርዬ ነገረኝ፡፡
"እሺ ልመልስለት:: ከዛስ? ከዛ ምን እንብላ? ከዛ ለእማዬ ምን
እንሰርላት? ከዛ ገንዘብ ፍለጋ የማልወደው ገላ ላይ ልጣድ?
ንገረኛ?" ብሩን መልሺለት ስላለኝ ነው በርዬ ላይ የምጮኸው።ለኤፍሬም እውነቱን እንድነግረው ሲወተውተኝ፡፡
በርዬ አቀረቀረ:: አድርጌው እንደማላውቅ
ሁሉ ለገንዘባቸው ከምተኛላቸው ወንዶች ጋር መሆን ቀፋፊ ነገር ሆነብኝ፡፡
ከኤፍሬም ጋር የስራሁትን ፍቅር ማርከስ መሰለኝ፡፡ የሆነ ልክ ከኤፍሬም ጋር ከተኛሁ በኋላ ገላዬ የተቀደሰ ነገር መሰለኝ፡፡ ያንን ማርከስ መሰለኝ፡፡ በእርግጥ ኤፍሬምን ገንዘብ ብጠይቀው
ይከለክለኝ ነበር? አይከለክለኝም ይሆናል፡፡ በግልፅ ምክንያት
የአያሌውን ገንዘብ ብመልስለት ለኤፍሬም እውነቱን እንደሚነግረው አስፈራርቶኛል፡፡ በድብቅ ምክንያቴ ግን ኤፍሬም ጋር ያለኝ ነገር ከዚህ በፊት ከማውቃቸው ወንዶች ጋር እንደነበረኝ ስራ እንደሆነ እንዲሰማኝና እንዲቀልብኝ
አልፈለግኩም:: ሌላው አማራጭ ግን እንደገሃነም አስፈሪ ነው፡፡እውነቱን መናገር! ለኤፍሬም የቀረብኩህ ተከፍሎኝ ነውኀልበለው? ከዛስ? ጥሎኝ ሲሄድ ትርፌ ምንድነው? ፊልም ላይ
ብቻ ነው ይሄ የሚሰራው:: አባዬ ራሱን ያጠፋው የቤተሰቡን ምስቅልቅል መሸከም ስለከበደው ነበር:: ያንን የተሸናፊ ፊቱን ልረሳው አልችልም፡፡ እኔ እማዬንና በርዬን የራሳቸው ጉዳይ ብዬ
ህሊናን መምረጥ አልችልም።የኔ ህሊና
ንፅህና የቤት ኪራያችንን አይከፍልም ወይም የበርዬን ትምህርት ቤት ክፍያ
አያጠናቅቅም አልያም ለእማዬ ስንቅ አይሆንም።ህሊና በአገልግል አይቆጠርም።
ከኤፍሬም ጋር ሳንገናኝ የዋልንበት ቀን ጠፋ። እቤት ከማድርበት ከኤፍሬም ጋር የማድርበት ቀን በለጠ፡፡ ሀኪም ያዘዘለትን ሀያ የእረፍት ቀን አረፍንበት። አብሬው አሳለፍኩ፡ እሱ በትክክል ምን እንደሚሰማው ግን አሁንም ማወቅ አልቻልኩም:: ከነዚህ ቀናት በኋላ አሁን ጥያቄዬ ህሊና ብቻ አይደለም ኤፍሬምን ማጣት ማሰብ ያስፈራኝ ጀምሯል። ኤፍሬም ሊዲያ የሞተችበት
ረቡዕ ዕለት ሁሌም መቃብሯጋ እንደሚሄድ ስለማውቅ
👍6❤1🔥1
#ምርጫ_አልባ_ምርጫ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
“ወንድ ልጅ! ስራ አልናፈቀህም ማለት እኮ ፍቅር አስይዤሃለሁ ማለት ነው።" አልኩት እንደመደነስ እያደረገኝ።
"አልወጣኝም::" አለ በሁኔታዬ ፈገግ እያለ፡፡
"ጉረኛ!! አታምንም አይደል?"
ስራ በጀመረባቸው ቀናት ለየት ያለ የምሳ ግብዣ ላይ አብሬው እንድሄድ ጋበዘኝ፡፡ ከአንድ ባለሀብት ጋር የንግድ ድርድር ነው።የባለሀብቱን ሚስት ተከትዬ መፀዳጃ ቤት ገባሁ:: ኤፍሬም
የገዛልኝ ቀሚስ ፕሮቶኮላም አድርጎኛል፡፡ እንደዛ የለበስኩት እርሱ በሰጠኝ ክብር ልክም ባይሆን የሚገባውን ላደርግላት
ስለፈለግኩ ነው:: የወንዶቹ ወሬ እንደኔ ካሰለቻት ከሰውየው ሚስት ጋር ቀላል ወሬዎች ተጫወትን። ከኔ የባሰች ለፍላፊ
ነገር ስለነበረች በደቂቃዎች ውስጥ ብዙ ነገር አወራችኝ፡፡ ወደ ጠረጴዛው ስመለስ የወንዶቹ ድርድር ቀልቤን ሳበው:: ባለሀብቱ ከነኤፍሬም የእንስሳት ማደለቢያ ማዕከል ወደውጪ የከብት ስጋ ለመላክ ነው በሚያዋጣቸው ድርሻ የሚደራደሩት፡፡ ሰውየው የሚያዋጣኝ ስድሳ አምስት በመቶ ድርሻ ሲኖረኝ ነው ብሎ ግግም አለ፡፡ የተቀረው ሰላሳ አምስት በመቶ ድርሻ የኛ ሊሆን
ማለት ነው። (ቡፍፍ! የኛ አልኩ እንዴ? እኔ ከስሙኝ ብዙ አወራ የለ? ባልስማ እለፉኝ፡፡) ኤፍሬም ሲያቅማማ አየሁት፡፡
የኛ ድርጅት አያዋጣውም።አርባ አምስት በሃምሳ አምስት ካዋጣህ መቀጠል እንችላለን፡፡" አልኩኝ ጣልቃ ገብቼ፡፡ ኤፍሬም ዘወር ብሎ የተናገርኩትን ባለማመን አየኝ፡፡
"እመነኝ እሺ ያዋጣዋል፡፡" አልኩት በጆሮው።
"እመቤት አንቺ የገባሽ አልመሰለኝም።" አለ ባለሃብቱ እንደማፌዝ እያደረገው።
“ምኑ ነው የገባኝ ያልመሰለህ? መልካም እንግዲህ፡፡ ሀሳብህን ከቀየርክ ደውልልን።" ብዬው ተነሳሁ:: ኤፍሬም ግራ በመጋባት ተከተለኝ። ሰውየው እየተበሳጨ ጠረጴዛውን ከነረተ በኋላ "እሺ ተቀመጡ!!" አለ።
"ምንድነበር ያደረግሽው?" አለኝ ኤፍሬም ተፈራርመው ከሆቴሉ ወጥተን መኪና ውስጥ እየገባን።
“ከሚስቱ ጋር የሴቶች ወሬ አውርተን ነበር። ብታያት ከኔ የባሰች ቀዳዳ ናት! ለባሏ በጣም አንገብጋቢ ድርድር መሆኑን ፣የሚወዳት ልጁን ልደት ትቶ እንደአምላክ ቀጠሮ የማይሰረዝ
ያለው ምሳ ላይ መምጣቱን ምናምን ነገረችኝ፡፡ አንተ ግን እንዴት አመንከኝ?
"አላውቅልሽም:: ሁሌም ሳምንሽ ከራሴ ጋር አልማከርም::" አለኝ እየገረመው አፍጥጦብኝ፡፡
ቆይ ግን የምር እስከምንድነው የተማርሽው?" አለኝ ለጥያቄው ተገቢ ይሆናል ያለውን ቃል እየመረጠ።
እውይ! አራተኛ ክፍል ሳይንስ መፅሃፍ ላይ እባብ በከለር አይቼ ደንብሬ እንደቀረሁ ነው::" መለስኩለት፡፡
'የምር? የምር ንገሪኝ?" አለኝ እየሳቀ፡፡ እስከ አስር መማሬን እና ውጤት ቢመጣልኝም ለመማር እንዳልተመቸኝ ነገርኩት።ገብቶት ይመስለኛል '
ለምን?” ብሎ አላጨናነቀኝም!
"የጭንቅላትሽ ከፍታ እኮ። ግን ማትሪክት የመንጣብሽ አይመሰልም።ብሎኝ የሽቶ እቃ እያቀበለኝ ቅድም ነው የገዛሁልሽ አለኝ።ሽቶውን ከፍቼ እያሸተትኩት ዝም ብዬ አየሁት፡፡
"አንተ ግን በእናትህ እመን ፍቅር ይዞሃል አይደል?" አልመለሰልኝም።ዝም ብሎ ብቻ ሳመኝ።
እስከማስታውሰው ማታ ደህና እደሪልኝ እንዲለኝ ጠዋት ደህና ዋይልኝ እንዲለኘሸ ስልኩን በናፍቆት የጠበቅኩትን ሰው
አላስታውስም፡፡ ኤፍሬም ሳይደውል ያረፈደ ቀን በእንቅልፍ ልቡ የእናቱን ጡት እንደሚፈልግ ህፃን ያንሰፈስፈኛል።
በስህተት ደህና ዋይልኝ ያላለኝ ቀን ቀኔ ደህና ቀኔ ደህና አይሆንልኝም የሆነ እሁድ ቀን ጠዋት ስልኩን እንደዘጋው ከሊ.ዲ.ያ ጋር ይኖር የነበረበት
ቤት ለመሄድ ታክሲ ተሳፈርኩ፡፡
እንዴት እዚህ መሆኔን አወቅሽ?" አለኝ የአጥሩን በር እየከፈተ።
"ደበረኝ አላልከኝም? ሲደብርህ ከዚህ ቤትና ከኔ ውጪ የትም እባክ መሄጃ እንደሌለህ አውቃለሁኣ።” መለስኩለት፡፡ አቀፈኝ።ወዲያውኑ ለቤተክርስቲያን የለበስኩትን ረዥም ቀሚስና ነጠላ
በጥያቄ እየሆኑ።
ዛሬ የዓመቷ ኪዳነ-ምህረት ናት፡፡”
ስለውም ጥያቄውን የጨረሰ አልመሰለም።
"ባክህ የእግዜር ሰው ሆኜ አይደለም። እማዬ ስለምታደርገው ነው::" አልኩት። ቤተክርስቲያን ሄደን አረፈድን። አመሻሹን
የሊዲያን አትክልቶች መኮትኮት ልምድ ስለነበረው ወደ ቤት ተመለስን። አበቦቿን የሚነካበት መንገድ ቅጠል ሳይሆን
የእርሷን ሰውነት እየነካ ነው የሚመስለው። እዛው ቤት ሳሎኑ ውስጥ ፍራሽ አንጥፈን አደርን ጠዋት እንዳልረብሸው ተጠንቅቄ ተነስቼ የእርሱን ሸሚዝ ብቻ ለብሼ ፍርፍር አበሰልኩለት።ሲነቃ የሚደሰት ነው የመሰለኝ።የተፈጠረው ግን ተቃራኒው ነው።አበደብኝ!የእርሷን ቦታ ለመተካት ያሰብኩት እራሴን እንደምን ቆጥሬው እንደሆነ አፈጠጠብኝ።
"እኔ እንዳልደርስበት የምትጠብቀው የህይወትህ ክፍል እንዳለ ይገባኛል እኮ የቀረብኩህ ስለመሰለኝ እንጂ እኔ ለሷ ያለህን ፍቅርና ዋጋ አከብርልሃለሁ:: ግን አበዛኸው....." አልኩት ትቼው ልሄድ እየለባበስኩ።
"ለሷ ልሰጣት የሚገባኝን የፍቅር ልክ አንቺ አትነግሪኝም::" አለኝ
ልሄድ መነሳቴ እንኳን ግድ ሳይለው።
ኡኡቴ እንደምትሉ አውቃለሁ። እኔም ማነኝ ብዬ እንዳስብኩ እንጃ! ሳይገባኝ ግን በሟች ሚስቱ ቀናሁ። ወደቤቴ
እንደሄድኩ ስልኬን አጠፋሁ።
የተፈጠረውን ለበርዬ ነገርኩት። የሚያባብለኝ ነበር የመሰለኝ፡፡
እሱ ግን ያለማቋረጥ ሳቀ፡፡ ከልቡ ሳቀ፡፡
"ምን ያስገለፍጥሃል? አሁን ይሄ ምን የሚያስቅ ነገር አለው?"
ፍቅር ይዞሻል!" አለኝ አንዳንዴ እንደሚያደርገው አንደታላቅ ወንድም እያየኝ፡፡
የማደርገው ሳይገባኝ ከበርዬ መፅሃፍቶች ውስጥ የሊዲያን መፅሀፍት ለይቼ አንዱን ማንበብ ጀመርኩ፡፡ በርዬ ይፅፋል። እኔ
አነባለሁ። በመሃል እናወራለን፡፡
ከሁለት ቀን በኋላ ስልኬን ስከፍተው ኤፍሬም ስምንት የይቅርታ መልዕክት ልኮልኛል። ደወልኩለት፡፡
"ላግኝሽ?"
“አሪፍ ምክንያት ካቀረብክ?"
ካንቺ ጋር መሆን ደስ ስለሚያሰኘኝ!"
“ቀሽም ምክንያት"
"ይህን አይደል መስማት የምትፈልጊው? አዎን ካንቺ ፍቅር
"እሺ ይቅርታ ልጠይቅሽ ስለምፈልግ
"ጭራሽ የወረደ ምክንያት"
"እሺ ስለናፈቅሽኝ"
"የት እንገናኝ?"
"ቢሮ ነኝ ነይና አብረን ምሳ እንወጣለን።"
“
"ቢሮ?"
አዎን!"
ሳየው ምን ያህል እንደናፈቀኝ ገባኝ፡፡ ስስመው በሩን እንኳን ያለመዝጋቴን ያወቅኩት ፀሃፊው ስትገባ ነው።ምሳ በልተን እቤቱ ይዞኝ ሄደ።እቃዎቹን በአዲስ እቃ ቀይሯቸዋል።
የቤቱንም ቀለም ቀይሮታል፡፡
"እርግጠኛ ነህ?" አልኩት በመገረም እያየሁት።
"እንደዚህ እርግጠኛ የሆንኩበት ነገር የለም::" መለሰልኝ።
"ይህን አይደል መስማት የምትፈልጊው? አዎን ካንቺ ፍቅር ይዞኛል።" አለኝ ከመቀመጣችን፡፡
ከንፈሩን ያለማቋረጥ ሳምኩት፡፡ ምክንያቱም ዝም እንዲለኝ ፈለግኩ።ገና መናገር እንደለመደ ህፃን እየቦረቀ ነው።
የሚያወራው። ድንገት መሳሙን አቁሞ "ሩካ?" አለኝ፡፡ ጥሪው ውስጥ ምንድነው አብሬ የሰማሁት? ልቤን ምን አስደለቀው? ሰውነቴን ምን አሞቀው?
"ወይዬ?"
“አንቺ ለኔ ከፈጣሪ እንደተላከ መላዕክ በመጥፎ ሰዓቶቼ ሁሉ ከጎኔ አገኝሻለሁ፣ እያስቀየምኩሽ እንኳን ትረጂኛለሽ:፡ እኔ ግን ላንቺ ጥሩ ጓደኛሽ እንኳን አይደለሁም::"
“በምን ምክንያት?" አልኩት፡፡
"ስላንቺ የማውቀው አንድ ነገር ቢኖር ለመኖር እንድጓጓ እንዳደረግሽኝ ብቻ ነው።"
"ታዲያ መላዕክ እኮ ጥሩም መጥፎም ቀን የለውም፡፡ አንተ ደስተኛ እንድትሆንልኝ ብቻ ከሆነስ የታዘዝኩት?" ይሄን በአፌ ልበለው እንጂ በእርግጥ
ለምን ስለራሴ እንዳልነገርኩት
ምክንያቴን
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
“ወንድ ልጅ! ስራ አልናፈቀህም ማለት እኮ ፍቅር አስይዤሃለሁ ማለት ነው።" አልኩት እንደመደነስ እያደረገኝ።
"አልወጣኝም::" አለ በሁኔታዬ ፈገግ እያለ፡፡
"ጉረኛ!! አታምንም አይደል?"
ስራ በጀመረባቸው ቀናት ለየት ያለ የምሳ ግብዣ ላይ አብሬው እንድሄድ ጋበዘኝ፡፡ ከአንድ ባለሀብት ጋር የንግድ ድርድር ነው።የባለሀብቱን ሚስት ተከትዬ መፀዳጃ ቤት ገባሁ:: ኤፍሬም
የገዛልኝ ቀሚስ ፕሮቶኮላም አድርጎኛል፡፡ እንደዛ የለበስኩት እርሱ በሰጠኝ ክብር ልክም ባይሆን የሚገባውን ላደርግላት
ስለፈለግኩ ነው:: የወንዶቹ ወሬ እንደኔ ካሰለቻት ከሰውየው ሚስት ጋር ቀላል ወሬዎች ተጫወትን። ከኔ የባሰች ለፍላፊ
ነገር ስለነበረች በደቂቃዎች ውስጥ ብዙ ነገር አወራችኝ፡፡ ወደ ጠረጴዛው ስመለስ የወንዶቹ ድርድር ቀልቤን ሳበው:: ባለሀብቱ ከነኤፍሬም የእንስሳት ማደለቢያ ማዕከል ወደውጪ የከብት ስጋ ለመላክ ነው በሚያዋጣቸው ድርሻ የሚደራደሩት፡፡ ሰውየው የሚያዋጣኝ ስድሳ አምስት በመቶ ድርሻ ሲኖረኝ ነው ብሎ ግግም አለ፡፡ የተቀረው ሰላሳ አምስት በመቶ ድርሻ የኛ ሊሆን
ማለት ነው። (ቡፍፍ! የኛ አልኩ እንዴ? እኔ ከስሙኝ ብዙ አወራ የለ? ባልስማ እለፉኝ፡፡) ኤፍሬም ሲያቅማማ አየሁት፡፡
የኛ ድርጅት አያዋጣውም።አርባ አምስት በሃምሳ አምስት ካዋጣህ መቀጠል እንችላለን፡፡" አልኩኝ ጣልቃ ገብቼ፡፡ ኤፍሬም ዘወር ብሎ የተናገርኩትን ባለማመን አየኝ፡፡
"እመነኝ እሺ ያዋጣዋል፡፡" አልኩት በጆሮው።
"እመቤት አንቺ የገባሽ አልመሰለኝም።" አለ ባለሃብቱ እንደማፌዝ እያደረገው።
“ምኑ ነው የገባኝ ያልመሰለህ? መልካም እንግዲህ፡፡ ሀሳብህን ከቀየርክ ደውልልን።" ብዬው ተነሳሁ:: ኤፍሬም ግራ በመጋባት ተከተለኝ። ሰውየው እየተበሳጨ ጠረጴዛውን ከነረተ በኋላ "እሺ ተቀመጡ!!" አለ።
"ምንድነበር ያደረግሽው?" አለኝ ኤፍሬም ተፈራርመው ከሆቴሉ ወጥተን መኪና ውስጥ እየገባን።
“ከሚስቱ ጋር የሴቶች ወሬ አውርተን ነበር። ብታያት ከኔ የባሰች ቀዳዳ ናት! ለባሏ በጣም አንገብጋቢ ድርድር መሆኑን ፣የሚወዳት ልጁን ልደት ትቶ እንደአምላክ ቀጠሮ የማይሰረዝ
ያለው ምሳ ላይ መምጣቱን ምናምን ነገረችኝ፡፡ አንተ ግን እንዴት አመንከኝ?
"አላውቅልሽም:: ሁሌም ሳምንሽ ከራሴ ጋር አልማከርም::" አለኝ እየገረመው አፍጥጦብኝ፡፡
ቆይ ግን የምር እስከምንድነው የተማርሽው?" አለኝ ለጥያቄው ተገቢ ይሆናል ያለውን ቃል እየመረጠ።
እውይ! አራተኛ ክፍል ሳይንስ መፅሃፍ ላይ እባብ በከለር አይቼ ደንብሬ እንደቀረሁ ነው::" መለስኩለት፡፡
'የምር? የምር ንገሪኝ?" አለኝ እየሳቀ፡፡ እስከ አስር መማሬን እና ውጤት ቢመጣልኝም ለመማር እንዳልተመቸኝ ነገርኩት።ገብቶት ይመስለኛል '
ለምን?” ብሎ አላጨናነቀኝም!
"የጭንቅላትሽ ከፍታ እኮ። ግን ማትሪክት የመንጣብሽ አይመሰልም።ብሎኝ የሽቶ እቃ እያቀበለኝ ቅድም ነው የገዛሁልሽ አለኝ።ሽቶውን ከፍቼ እያሸተትኩት ዝም ብዬ አየሁት፡፡
"አንተ ግን በእናትህ እመን ፍቅር ይዞሃል አይደል?" አልመለሰልኝም።ዝም ብሎ ብቻ ሳመኝ።
እስከማስታውሰው ማታ ደህና እደሪልኝ እንዲለኝ ጠዋት ደህና ዋይልኝ እንዲለኘሸ ስልኩን በናፍቆት የጠበቅኩትን ሰው
አላስታውስም፡፡ ኤፍሬም ሳይደውል ያረፈደ ቀን በእንቅልፍ ልቡ የእናቱን ጡት እንደሚፈልግ ህፃን ያንሰፈስፈኛል።
በስህተት ደህና ዋይልኝ ያላለኝ ቀን ቀኔ ደህና ቀኔ ደህና አይሆንልኝም የሆነ እሁድ ቀን ጠዋት ስልኩን እንደዘጋው ከሊ.ዲ.ያ ጋር ይኖር የነበረበት
ቤት ለመሄድ ታክሲ ተሳፈርኩ፡፡
እንዴት እዚህ መሆኔን አወቅሽ?" አለኝ የአጥሩን በር እየከፈተ።
"ደበረኝ አላልከኝም? ሲደብርህ ከዚህ ቤትና ከኔ ውጪ የትም እባክ መሄጃ እንደሌለህ አውቃለሁኣ።” መለስኩለት፡፡ አቀፈኝ።ወዲያውኑ ለቤተክርስቲያን የለበስኩትን ረዥም ቀሚስና ነጠላ
በጥያቄ እየሆኑ።
ዛሬ የዓመቷ ኪዳነ-ምህረት ናት፡፡”
ስለውም ጥያቄውን የጨረሰ አልመሰለም።
"ባክህ የእግዜር ሰው ሆኜ አይደለም። እማዬ ስለምታደርገው ነው::" አልኩት። ቤተክርስቲያን ሄደን አረፈድን። አመሻሹን
የሊዲያን አትክልቶች መኮትኮት ልምድ ስለነበረው ወደ ቤት ተመለስን። አበቦቿን የሚነካበት መንገድ ቅጠል ሳይሆን
የእርሷን ሰውነት እየነካ ነው የሚመስለው። እዛው ቤት ሳሎኑ ውስጥ ፍራሽ አንጥፈን አደርን ጠዋት እንዳልረብሸው ተጠንቅቄ ተነስቼ የእርሱን ሸሚዝ ብቻ ለብሼ ፍርፍር አበሰልኩለት።ሲነቃ የሚደሰት ነው የመሰለኝ።የተፈጠረው ግን ተቃራኒው ነው።አበደብኝ!የእርሷን ቦታ ለመተካት ያሰብኩት እራሴን እንደምን ቆጥሬው እንደሆነ አፈጠጠብኝ።
"እኔ እንዳልደርስበት የምትጠብቀው የህይወትህ ክፍል እንዳለ ይገባኛል እኮ የቀረብኩህ ስለመሰለኝ እንጂ እኔ ለሷ ያለህን ፍቅርና ዋጋ አከብርልሃለሁ:: ግን አበዛኸው....." አልኩት ትቼው ልሄድ እየለባበስኩ።
"ለሷ ልሰጣት የሚገባኝን የፍቅር ልክ አንቺ አትነግሪኝም::" አለኝ
ልሄድ መነሳቴ እንኳን ግድ ሳይለው።
ኡኡቴ እንደምትሉ አውቃለሁ። እኔም ማነኝ ብዬ እንዳስብኩ እንጃ! ሳይገባኝ ግን በሟች ሚስቱ ቀናሁ። ወደቤቴ
እንደሄድኩ ስልኬን አጠፋሁ።
የተፈጠረውን ለበርዬ ነገርኩት። የሚያባብለኝ ነበር የመሰለኝ፡፡
እሱ ግን ያለማቋረጥ ሳቀ፡፡ ከልቡ ሳቀ፡፡
"ምን ያስገለፍጥሃል? አሁን ይሄ ምን የሚያስቅ ነገር አለው?"
ፍቅር ይዞሻል!" አለኝ አንዳንዴ እንደሚያደርገው አንደታላቅ ወንድም እያየኝ፡፡
የማደርገው ሳይገባኝ ከበርዬ መፅሃፍቶች ውስጥ የሊዲያን መፅሀፍት ለይቼ አንዱን ማንበብ ጀመርኩ፡፡ በርዬ ይፅፋል። እኔ
አነባለሁ። በመሃል እናወራለን፡፡
ከሁለት ቀን በኋላ ስልኬን ስከፍተው ኤፍሬም ስምንት የይቅርታ መልዕክት ልኮልኛል። ደወልኩለት፡፡
"ላግኝሽ?"
“አሪፍ ምክንያት ካቀረብክ?"
ካንቺ ጋር መሆን ደስ ስለሚያሰኘኝ!"
“ቀሽም ምክንያት"
"ይህን አይደል መስማት የምትፈልጊው? አዎን ካንቺ ፍቅር
"እሺ ይቅርታ ልጠይቅሽ ስለምፈልግ
"ጭራሽ የወረደ ምክንያት"
"እሺ ስለናፈቅሽኝ"
"የት እንገናኝ?"
"ቢሮ ነኝ ነይና አብረን ምሳ እንወጣለን።"
“
"ቢሮ?"
አዎን!"
ሳየው ምን ያህል እንደናፈቀኝ ገባኝ፡፡ ስስመው በሩን እንኳን ያለመዝጋቴን ያወቅኩት ፀሃፊው ስትገባ ነው።ምሳ በልተን እቤቱ ይዞኝ ሄደ።እቃዎቹን በአዲስ እቃ ቀይሯቸዋል።
የቤቱንም ቀለም ቀይሮታል፡፡
"እርግጠኛ ነህ?" አልኩት በመገረም እያየሁት።
"እንደዚህ እርግጠኛ የሆንኩበት ነገር የለም::" መለሰልኝ።
"ይህን አይደል መስማት የምትፈልጊው? አዎን ካንቺ ፍቅር ይዞኛል።" አለኝ ከመቀመጣችን፡፡
ከንፈሩን ያለማቋረጥ ሳምኩት፡፡ ምክንያቱም ዝም እንዲለኝ ፈለግኩ።ገና መናገር እንደለመደ ህፃን እየቦረቀ ነው።
የሚያወራው። ድንገት መሳሙን አቁሞ "ሩካ?" አለኝ፡፡ ጥሪው ውስጥ ምንድነው አብሬ የሰማሁት? ልቤን ምን አስደለቀው? ሰውነቴን ምን አሞቀው?
"ወይዬ?"
“አንቺ ለኔ ከፈጣሪ እንደተላከ መላዕክ በመጥፎ ሰዓቶቼ ሁሉ ከጎኔ አገኝሻለሁ፣ እያስቀየምኩሽ እንኳን ትረጂኛለሽ:፡ እኔ ግን ላንቺ ጥሩ ጓደኛሽ እንኳን አይደለሁም::"
“በምን ምክንያት?" አልኩት፡፡
"ስላንቺ የማውቀው አንድ ነገር ቢኖር ለመኖር እንድጓጓ እንዳደረግሽኝ ብቻ ነው።"
"ታዲያ መላዕክ እኮ ጥሩም መጥፎም ቀን የለውም፡፡ አንተ ደስተኛ እንድትሆንልኝ ብቻ ከሆነስ የታዘዝኩት?" ይሄን በአፌ ልበለው እንጂ በእርግጥ
ለምን ስለራሴ እንዳልነገርኩት
ምክንያቴን
👍7