አትሮኖስ
281K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
481 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
:
ድርሰት:-በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ህይወት ወራጅ ወንዝ ነው-ክንውኑ ያስደምማል
ምንም ቋሚ ነገር የለም -ሁሉም ይጐርፋል…ይተማል
ተነባብሮ ተደራርቦ- ይፈናጠቃል ይፈሳል
በአጋጣሚ ያጣብቃል-ሳይታሰብ ያላቅቃል
ህይወት ወራጅ ወንዝ ነው -ድንገት ይጠባል… ይሰፋል
መዋኘት መፍሰስ የቻለን- ከአድማስ ባሻገር ያደርሳል
ተንፈራግጦ የታገለን -ከግንድ ያጋጫል ያጠፋል
ህይወት ወራጅ ወንዝ ነው- ነፍስ ይሰጣል…ነፍስ ይነጥቃል፡፡
--------------------------------------------------------------
‹‹ደከመሽ አይደል ?ብዙ ሰዓት እኮ ሰራን››አላት ከጐኗ ተነስቶ ፊት ለፊቷ በመቀመጥ
‹‹አረ አልደከመኝም አምስት ደቂቃም የቆየን አልመሰለኝም››በደስታ በተፍለቀለቀ እና በሚያበራ ፈገግታ መለሰችለት….
ኩማደር መሀሪ ለሄለን በገባላት ቃል መሰረት ፒያኖ ያሰለጥናት ከጀመረ ሳምንት አለፈው..በየቀኑ ከአንድ ሰዓት እስከ አንድ ሰዓት ተኩል… አንዳንዴም እስከ ሁለት ሰዓት በራሱ በተዘጋ የወንደላጤ ቤት ውስጥ ያሳልፍሉ..ሰዓቱ ደግሞ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ያለው ወደ ምሽቱ አካባቢ የተጠጋው ሰዓት ነው የመረጠጡት
ሄለን በመጀመሪያዎቹ ቀናት የኩማደርን ማንነት እና የት እንደምታውቀው ስለምታዉቅ ደንግጣ እና ግራ ተጋብታ ነበር…አዎ ዲላ ይኖር እንደነበረ እና ከሮዝ ጋር ግንኙነት እንደነበረው እሷንም ፍለጋ እቤት ድረስ መጥቶ በነበረበት ሰዓት አግኝታውዋለች በዚህም የተነሳ ያቀረበላትን ጥያቄ ለመቀበል እና ላለመቀበል ከራሷ ጋር ብዙ ተታግላ ነበር..ቡኃላ ግን እስኪ ልሞክረው ብላ ጀመረች..ዋል አደር ስትል ግን ጭራሽ ነገሩን እየዘነጋችው መጣች…አቀራረቡ …ለእሷ የሚያደርገው እንክብካቤ ልክ ተወዳጅ ታላቅ ወንድሞ መስሎ እንዲታያት ማድረግ ችሎል፡፡በአጠቃላይ ስሜቷን ተቆጣጥሯል ፡፡
…ኩማንደር መሀሪ ደግሞ እስከአሁን ብዙ ነገር እያነሳ ከእሷ ጋር ማውራት ቢችልም ስለዲላ ትንፍሽ ብሎላት አያውቅም…ስለእሷ ባሰበ ቁጥር ግራ ይጋባል..በጣም ታሳዝነዋለች…ከክፉ መሀፀን በቅላ….ክፉ እጅ ላይ ወደቀች…ምንም ማድረግ አይችልም..ይሄ በአለም ያለ ነባራዊ ሁኔታ እና በየእለቱ የሚከሰት ተግባር ነው..በዚህን አይነት ጊዜ ለሀጥአን መቀጣጫ ታስቦ የዘነበ መአት ጻድቃኖችን መለብለቡ አይቀርም…..
አብረው ፒያኖ ከመለማመድ ውጭ ስለእናቷ አውርተው አያውቁም ስለእሷ ብታወራ ጥሩ ስሜት እንደማይሰማው ታውቃለች ሄለን ብዙ ነገር ይቀርብኛል ብላም ታስባለች በጋራ እንኳን አቅድውት ስለነበረው ሄለን ስለአባቷ ጉዳይ በራሷ ድምፅ ቀድታ ለሷ እንዲያሰማት አቅደው ነበር ስለሱ እንኳን አንስታ ማውራት አልፈለገችም
ሙዚቃ መለማመዱ ብቻ አይደለም የሚቀርባት…ለአባትነት የቀረበው ወንድምነቱ ይቀርባታል..በጣም ለምዳዋለች…ሰው እንዴት በሳምንት እንዲህ ሰውን ይለምዳል..?ለራሷም እየገረማት ነው…
‹‹ትኩስ ሀይል አይደለሽ…መች በቀላሉ ትደክሚያለሽ››አላት
አልመለሰችለትም..እንደማፈር ብላ አንገቷን አቀረቀረች..
ለደቂቃዎች ዝም ተባባሉ…ዝም ሲል ተፈራዋለች….‹‹ምነው ዝም አልክ?››
‹‹ኦ ይቅርታ በሀሳብ እኮ ጭልጥ አልኩ..ስለአባ ሽፍንፍን እያሰብኩ ነበር››
‹‹ስለእሷቸው ምን የሚያሳስብ ጉዳይ አለ? ምነው የሚያሳስር ወንጀል አገኘህባቸው እንዴ?››
‹‹በፍጹም ….ፃድቅ ናቸው ይባሉ የለ እንዴ .. ?እንዴት ወንጃል ላገኝባቸው እችላለው..?ደግሞስ ወንጀል አገኘውባቸው ብልስ እንደ መላአክ የሚያያቸው የሻሸመኔ ኑዋሪ የሚያምነኝ ይመስልሻል…?ሰላማዊ ሰልፍ ነው የሚወጡብኝ፡፡ ››
‹‹እና ሌላ ስለእሷቸው ምን አሳሰበህ?››
‹‹ብዙ ብዙ ነገር ነዋ..ለመሆኑ አሁን ወደ እኔ ስትመጪ እቤት ነበሩ?››
‹‹አዎ …ትናንት ፀሎት ቤታቸው ገብተው እንደጠረቀሙ ናቸው››
‹‹ለዚህን ያህል ረጂም ጊዜ ይፀልያሉ ማለት ነው?››
‹‹ሁለት ቀን ምን አላት …?ሶስት እና አራት ቀን ነው የሚቆዩት ….እንዴት ሰው ለዚህ ሁሉ ቀን ያለምግብ እና መጠጥ ብቻውን ቤት ዘግተው ማሳለፍ ይችላል?ለእኔም በጣም የሚገርም ተአምር ነው፡፡በቃ የከተማ መናኝ በላቸው››
‹‹አንቺስ አብረሻቸው አትፀልይም?››
‹‹አረ በፍጹም …ወደ ጸሎት ክፍላቸው ሲያስገቡኝ አይደል?››ብላ አይኗን ወደ ኩማንደሩ አንድ የተዘጋ ክፍል ወረወረች…ይህቺ ክፍል ልክ እንደ አባ የፀሎት ክፍል ሁሌ በመጣች ቁጥር ተቆልፎ ነው የምታገኘው..ደግሞ ይህቺ ዝግ ክፍል እታች ምድር ላይ ከሚገኘው የአባ ፀሎት ቤት ጋር በትይዩ አቅጣጫ መገኘቱ ግርምት ይፈጥርባታል…
‹‹ጥሩ ነው…ግን አሁን አሁን እየወደድኮቸው መጥቼያለው መሰለኝ››
ከት ብላ ሳቀችና ‹‹እንዴ …በፊት ትጠላቸው ነበር እንዴ?››
‹‹እንደ እሱ ማለቴ እንኳን አይደለም…በፊት ስለእሷ
ስለእሳቸው ፍቅርም ሆነ ጥላቻ በውስጤ አልነበረም..አሁን ግን..››
‹‹እሺ አሁን እንዴት ልትወዳቸው ቻልክ?››
‹‹ባንቺ ምክንያት ነዋ..እሷ
እሳቸው ወደ እዚህ ባያመጡሽ ከእኔ ጋር አንገናኘም ነበር…››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው››አለችው እንደመተከዝ ብላ
‹‹ይገርምሻል ሄለን አንዳንዴ ሳስበው በውሳኔዬ ላይ ጥርጣሬ ያድርብኛል››
‹‹በየትኛው ውሳኔህ?››
‹‹አንቺን ፒያኖ ላሰልጥንሽ ብዬ መጀመሬን….››ብሩህ የነበረው የሄለን የፊት ገጽታ በአንዴ ጭላሼት ለበሰ
‹‹እሱ እንኳን ትክክል ነህ… እኔም በጣም እራስ ወዳድ እንደሆንኩ እየተሰማኝ ነው….. ጊዜህን በጣም እየተሸማውብህ ነው..››
‹‹ኖ..ኖ እንደእዛ ማለቴ አይደለም…ካንቺ ጋር ማሳልፋት እያንዳዶ ደቂቃ ለስጋዬም ሆነ ለመንፈሴ ምን ያህል መነቃቃት እና ደስታ እንደሚፈጥርብኝ መገመት አትቺይም…አነቺ እዚህ ቤት ስትገቢ እናቴ እንደመጣችነው መስሎ ነው ሚሰማኝ››
ድፍርስ ብሎ የነበረው ስሜቷ በሰኮንዶች ውስጥ መልሶ አንሰራራ‹‹እና ታዲያ ውሳኔህ ላይ እንዴት ጥርጣሬ ሊያድርብህ ቻለ?››
‹‹አየሽ..ፍቅር ያስፈራኛል…አባቴን እና እናቴን በሞት ከተነጠቅኩ ብኃላ ሌላ ሰው የእኔ ነው ብዬ መቅረብ እና መልመድ ፈራለው…ምክንያም ከመልመድ ውስጥ ፍቅር ተፈልፍሎ መውጣቱ አይቀርም….ያንን ፍቅር ደግሞ በሆነ አጋጣሚ መልሶ የማጣት ዕጣ ቢያጋጥመኝ ዳግም መቋቋም የምችል አይመስለኝም..በዚህ የተነሳ ከእናቴ ሞት ጀምሮ ላለፉት ሶስት አመታት ሰውን ስሸሽ እና በራሴ የብቸኝነት ዋሻ ውስጥ ስወሸቅ ነው የከረምኩት፤ አሁን ግን በዚህች አንድ ሳምንት ውስጥ በጣም እየለመድኩሽ መሆኑን ሳስብ እየፈራው ነው…ማታ ሸኝቼሽ በማግስቱ የመለማመጃ ሰዓታችን ደርሷ እስክትመጪ ጊዜው በጣም ይረዝምብኝ ጀምሯል….››በማለት ከእሱ አንደበት እሰማዋለው ብላ ያላሰበችውን ..የጉርምስና ልቧን በአንዴ የሚደረማምስ የማላውቀው አባቴ አንድ ቀን መጥቶ ይነግረኛል ብላ በተስፋ ትጠብቀው የነበረውን የሚያቀልጥ የፍቅር እና የመፈለግ ዜና የሚያበስሩ ቃላቶችን ለአንድ ሳምንት የተወዋወቀችው ይሄ ኩማደር አበሰራት..ውስጦ በደስታ እረሰረሰ..እንባዋም በአይኖቾ ከፍቃዷ ውጭ ተነኮለለ…
‹‹ኩማደር..ከዚህ በፊት ስለደረሰብህ ሀዘን እና ብቸኝነት በእውነት በጣም አዝናለው..ፍቅርን ማጣት ምን ማለት እንደሆነና በልብ ውስጥ ምን አይነት ሽንቁር እንደሚፈጥር በደንብ አውቃለው..እኔም ሙሉ የቤተሰብ ፍቅር አግኝቼ አይደለም እየኖርኩ ያለውት ..ግን አሁን ያልከው ፍቅርን የመፍራት አባዜህ እኔን ፒያኖ ከማሰልጠን ጋር ምን እንዳቆራኘው አሁንም አልገባኝም?››ጠየቀችው ይበልጥ ሚያመሞቅ ንግግር ከእሱ መስማት ፈልጋ…
‹‹አየሽ ሄለን ይሄ ፒያኖ ልምዳችን ለሶስት ወር ወይም ለአራት
👍1
#ሮዛ_2


#ክፍል_ሀያ_ሶስት( 🔞)
(የመጨረሻ ክፍል)


#የሰው_ ልጅ_ዓለምን_ አትርፎ #ነፍሱን_ቢበድል....

ቤይሩት፣ ራፊቅ ሀሪሪ አየር መንገድ

አርብ ሌሊት

በምድር ላይ እጅግ ከምጠላቸው ሕዝቦች መሀል እገኛለሁ፤ ሊባኖስ ቤይሩት አየር መንገድ ውስጥ፤
ወደ አቡዳቢ ለመብረር። አየርመንገዱ በአረቦች ታፍኗል። አረብ አረብ ይሸታል። የተቀቡት ሽቶ አልተስማማኝም፤ እነሱን እንዲህ በጅምላ ማየት ራሱ ያቅለሸልሻል። አመመኝ።

ክትፎ የሚወድ ሰው ጣባውን ሲከፍተው የሚዝለገለጉ ትላትሎች ታጭቀው ቢያይ ሊሰማው የሚችለው ስሜት እኔ አረቦችን እንዲህ ብዙ ሆነው በማየቴ ተሰምቶኛል። አዲስ አበባ በተናጥል አገኛቸው ስለነበር
ለነሱ ያለኝ የጥላቻ ስሜት የዛሬውን ያህል አልበረታብኝም ነበር። አሁን አንድ ሙሉ ተርሚናል በሺ በሚቆጠሩ አረቦች ተሞልቶ ብመለከት ምግብ አልረጋ አለኝ። አመመኝ።

ከአረቦቹ መሀል ብዙ መልካምና ደጋግ ሊኖሩ እንደሚችሉ እረዳለሁ፤ የበርካታ ሺህ ወገኖቼ ህይወት በነሱ ላይ እንደተመሰረተም አውቃለሁ፤ ወላጅ አልባ ህጻናት የሚያሳድጉ ደጋግ አረቦች ብዙ አሉ፤ ይህንንም አልከድም። በሀገሬም ሆነ በሀገራቸው ከወገኖቼ ጋ ፍቅር መስርተው የወለዱና የከበዱ አረቦች
እንዳሉም አልክድም።ለወደዱት ሰው ቤት ንብረታቸውን በሙሉ የሚሰጡ፣ ሀበሻ ሰራተኞቻቸው ሲታመሙ ሚሊዮን ብር ከስከሰው ያሳከሙ አረቦች እንዳሉም ከዚያ የተመለሱ ጓደኞቼ ሲያወሩ
ሰምቻለሁ። እርግጥ ነው፤ የትኛውም ህዝብ ሰናይና እኩይ ሰዎች አሉት፤ አረቦቹም ከዚያ የተለዩ እንዳልሆኑ ጠንቅቄ አውቀዋለሁ።ይህን ሁሉ እየተረዳሁ ግን ለአረቦች ስር የሰደደ ጥላቻ ደሜ ዉስጥ ገብቷል፤ ምን ላድርግ?

ህሊናዬን በብርቱ ከፈተነ ማሰላሰልና መብሰልሰል በኋላ የህይወቴ ቀጣዩ ምእራፍ በአረብ ምድር እንዲሆን ወሰንኩ። በተባበሩት ኢምሬትስ ርእሰ መዲና አቡዳቢ ሬስቶራንትና የውበት ሳሎን ያላትን የአብሮ አደጌን የቢዝነስ አጋርነት ግብዣ ለአመታት አሻፈረኝ ብልም ሰሞኑን ውሳኔዬን ከብዙ የአእምሮ
ጂምናስቲከ በኋላ ቀየርኩ፤ ከዚህ በኋላ እንዴትም ብዬ የህይወት አቅጣጫዬን መለወጥ እንዳለብኝ ተሰምቶኛል።

#ተርሚናሉ_ዉስጥ
.
አረብ ወንዶች ያለመጠን የተርከፈከፉት ሽቶ ራሴ ላይ ወጣ። ተርሚናሉ ዉስጥ እየተዝለገለጉ ወዲያ ወዲህ ሲሉ ሆዴ ታወከ። መታጠቢያ ቤት ሄጄ ፊቴን በቀዝቃዛ ዉኃ ነከርኩ። ትንሽ ሻል ያለ
ስሜት ሲሰማኝ በወርቅ የተለበጠ ከሚመስል አግዳሚ ወንበር ላይ አንድ ጥግ ይዤ አረፍ አልኩኝ።
ለጊዜው በዙርያዬ የሚሆነውን ከማየት ዉጭ ሌላ እድል አልነበረኝም። አይኔን ብጨፍንም አረቦችን አያለሁ። አይኔን ብገልጥም አረቦችን አያለሁ። አማራጭ አልነበረኝም። ለካንስ አይንን መጨፈን ማየት የሚፈልጉትን ከማየት አይጋርድም። ዳያሪዬን ከእጅ ቦርሳዬ ዉስጥ ብታቀፈውም አእምሮዬ ባልተለመደ ሁኔታ ደንዝዞብኛል። በአየር መንገዱ አግዳሚ ቁጭ ብዬ ወጪ ወራጁን ስሜት አልባ ሆኜ አያለሁ።
የአረብ ጎታታ ወንዶች፣ በዚያ በሚዝለገለግ ነጭ ቀሚሳቸው ዉስጥ ሆነው አውሮፕላን ለመሳፈር እንደ
ግመል ይጎተታሉ። የቀሚሳቸው መጎተት ላያንስ በሩዝ የተወደረ ከርሳቸውን ይጎትታሉ፤ የከርሳቸው ሳያንስ ኩንታል ሻንጣቸውን ይጎትታሉ። የሻንጣቸው ሳያንስ ነጠላ ጫማቸውን ይጎትታሉ፤ የነጠላ ጫማቸው ሳያንስ ከረፈፍ ሚስቶቻቸውን ይጎትታሉ፣ የሚስቶቻቸው ሳያንስ ያልተቆነጠጡ አስራ ምናምን ልጆቻቸውን ይጎትታሉ። አራት ሚስቶቻቸውን እየነዱም ቢሆን አምስተኛ ሴት ከማየት አይመለሱም። ከአንድም ሁለት ሦስት አጁዛ አረቦች ከወዲያኛው የተርሚናሉ ሬስቶራንት ሆነው

እየሰረቁ ሲመለከቱኝ ዐይቻለሁ፡፡

በድጋሚ መታጠቢያ ቤት ሄጄ ተመለስኩ። ዛሬ ምግብ አልረጋ ብሎኛል።

ቀልቤ አይወዳቸውም። በተለይ እንዲህ ነጭ ቆብ በነጭ ቀሚስ ለብሰው ሳያቸው፣ በነጭ ኩባያ ወተት ከአናታቸው እየፈሰሰባቸው ስለሚመስለኝ የዝንብ አየር ማረፍያዎች እንጂ ሰዎች ሆነው አይታዩኝም።ሰው ነጭ ለብሶም ንፁህ ሆኖ ካልታየኝ መቼስ የሆነ ችግር አለበት ማለት ነው። ለምንድነው ፈጣሪ እኛን
ድሐ እነሱን ሐብታም ያረገው? እግዜር ምናቸው ማርኮት ይሆን አሻዋቸውን የባረከው? በረሃቸውን ያረጠበው?!

“የአረብ ጥላቻ የተፈጠረብኝ መቼ ነው?” ብዬ ለማስታወስ ሞከርኩ። ትዝ የሚለኝ ነገር የለም። ምናልባት ኡስማን ዘ ፒምፕ ስለሚጠላቸው እሱ ሳያውቀው አጋብቶብኝ ይሆን? አይደለም። ኡስማንን
ሳላውቀው በፊት አረብ የሚባል ፍጥረት ያስጠላኝ ነበር። ልጅ እያለሁ የጀመረኝ ይመስለኛል። አያቴ በነበረችበት ሰፈር። ባደኩበት ሰፈር፣ በነእማማ ዙበይዳ ሰፈር።

ልጅ እያለሁ ለተወሰነ ጊዜ ሴት አያቴ ታሳድገኝ ነበር። በሰፈራችን የምንወዳቸው፣ እማማ ዙበይዳ
የሚባሉ ሴት ነበሩ። የሆኑ ደርባባ አሮጊት ሴትዬ። ሰው ዝም ብሎ ይወዳቸው ነበር። ጎመን መንገድ ላይ ይሸጣሉ። በክረምት ደግሞ በቆሎ ይሸጣሉ። እማማ ዙበይዳን ሰፈሩ ሁሉ ለምን ይወዳቸው እንደነበር ግን በትክክል አላውቅም። እኔም እወዳቸው ነበር። ለምን እንደነበር ግን አላውቅም። “ነይ እስቲ አንቺ
ጎራዳ!" እያሉ ግንባሬን ይስሙኝ እንደነበር ብቻ ነው ትዝ የሚለኝ።

እማማ ዙበይዳ ባልም ዘመድም የላቸውም። በምድር ላይ ያለቻቸው ፋጤ ቀጮ ናት። የሳቸው ብቸኛ ልጅ ፉጤ ቀጮ ጅዳ ሄደች ተባለ። ሰፈሩ ሁሉ እማማ ዙበይዳ በቃ ሻሩ፣ አሁን ወርቅ በወርቅ ሊሆኑ ነው ብሎ ተነበየ። እሳቸውን ያገኘ ሰው ሁሉ “ፋጤ ቀጮ ጅዳ ነው አይደል የሄደችው?”፣
ትደውላለች”፣ “ደህና ናት ታዲያ፣ “አሁን ለመድኩ አለችፖ፣ ግህም፣ “በርቺ በሏት እንግዲህ!
ይለመዳል.ይለመዳል”፣ “ዋናው መበርታት ነውታዲያ”፣ “እ!” እያለ ከእማማ ዙበይዳ የበቆሎ እሸት
ወይ ጎመን ገዝቷቸው ያልፋል። በበጋ ጎመን በከረምት የበቆሎ እሸት በመሸጥ ነበር የሚተዳደሩት።
በዚያ ሁሉ የሰፈር ሰው ሳይታክቱ በዚያ እናታዊ ፈገግታቸው ታጅበው ስለ ልጃቸው ደኅንነት ምላሽ ይሰጣሉ። “እላሙዲሊላ አላሂ ወላሂ ደህና ናት!ዱዋ አርጉላት." ይላሉ፤ መልሰው መላልሰው።

ሲኖሩ ሲኖሩ.…የሆነ ጊዜ ላይ ልጃቸው ስልክ ደውላ አለቀሰች ተባለ። “ምን ሆንሽ” ሲሏት አትናገርም
ሲኖሩ ሲኖሩ…የሆነ ጊዜ ላይ ደግሞ መደወል አቆመች ተባለ። ደህንነቷን የሚነግራቸው ጠፋ። ጎመን ወይ
በቆሎ ለሚገዛቸው የሰፈር ሰው ሁሉ “አረብ አገር ስልክ ማድረግ ታውቅበታለህ?” እያሉ ይጠይቃሉ።
የተማረ የሚመስል ወጣት ሲመለከቱ ደግሞ “ልጄ! እስኪ ባክህ የጅዳ ስልክ ቁጥር ጽፈህ አምጣልኝ? ልጄ ናፈቀችኝ ይሉታል። የሷ ስልክ ቁጥር ግን የላቸውም። አንዳንድ ሰው ነገሩን ሊያስረዳቸው ሞከረ።ኾኖም ሊገባቸው አልቻለም። የሰፈሩን ሰው መሄጃ መቀመጫ አሳጡት። እርስዎ ስልኳን ፈልገው ያምጡ! እኛ እንደውልሎታለን” ሲባሉ እኔ ቁጥሯን ከየት አዉቄ” ነው መልሳቸው። እሷ ካልደወለች
እሳቸው ወደየት ብለው ይደውላሉ? አድራሻዋ አይታወቅ ነገር።

የሰፈሩ ሰው በሙሉ እማማ ዙበይዳ ሲያዝኑ አይቶ አዘነ። እማማ ዙበይዳ የደግነት ምሳሌ ነበሩ። ፋጤ
ቀጮ እጅግ ስትናፍቃቸው ግን ሰው ሰላም ሳይሉ ማለፍ ሁሉ ጀመሩ። የሚሸጡት ጎመን ጠወለገ።
ወዲያው ደግሞ ወገባቸው ጎበጠ። ከመቼው በእድሜያቸው ላይ ምዕተ ዓመት እንደጨመሩ። ሰው የልጁ ናፍቆት እንደ ኤድስ አመንምኖ ሊገድለው እንደሚችል ያየሁት በእማማ ዙበይዳ ነው።

ከ5 ዓመታት በኋላ ልጃቸው ፋጤ መጣች ተባለ። በዊልቸር ላይ ሆና። በጣም ከመወፍሯ የተነሳ ዊልቸሩ ጠበባት። ፋጤ ቀጮ ትባል የነበረችው የሆነች ሲንቢሮ በረሮ ስለበረች ነበር።ታዲያ ለምን ወፈረች? ተስማምቷት ነበር ማለት ነው?
👍4