#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...“ስለሷ መናግር አትችይም ማዳም ቬን ”አላት ዊልያም ድርቅ ብሎ „'' አንቺ
እማማን አታውቂያትም " ከዚህ አልነበርሽም "
ትወዳችሁ እንደ ነበር በርግጥ እተማመናለሁ " እኔ ከዚህ የቆየሁት አንድ
ቀን ብቻ ነው ግን ባንድ ጊዜ ለመድኳችሁ " አሁን በጣም እወዳችኋለሁ ” አለችና
በትኩሳት የሚቃጠሉት ጐንጮቹን ሳመችው ይህ ሲሆን 0መፀኛው እንባዋን
ልትገታው ስለ አልቻለች እሱም እንዳሻው እየወረደ ከልጁ ጉንጭ ላይ ያርፍ
ጀመር ።
“እና ምን ያስለቅሻል ? አላት ዊልያም "
"አንተን የመሰለ ልጅ ነበረኝ ሞተብኝ " አሁን በምትኩ አንተን በማግኘቴ የስ ስለአለኝ ነው እሱ ከሞተ ጀምሮ ምንም የምወደው አላገኘሁም ነበር " አለችው
“ ስሙ ማን ነበር ? አላት ዊልያም በጕጕት "
'' ዊልያም ብላ ቃሉ ካፋ ከመውጣቁ አንደዚህ በማለቷ መሳሳቷ ተሰማት
ባርባራ ከቤት ካለች ራት እንደ ተበላ ወደ ሳሎን ከመግባቷ በፊት ከፎቅ ወጥታ ልጅዋን ለጥቂት ደቂቃዎች አይታ መውረድ የዘወትር ልማዷ ነበር » ዛሬ ማታም ልማዷን አድርሳ ስትወርድ ሉሲን በግራ ሳሎን ስታጮልቅ አየቻት "
አሁን መምጣት እንችላለን . . . እማማ ?
አዎን ! ማዳም ቬንም ጥቂት ዘፈኖች እንድትጫወትልን ንገሪያት "
ማዳም ቬን ቆየት ብላ በግድ እየተጨነች ከሳሎኑ በር ስትደርስ ሚስተር
ካርላይል ከምግብ ቤት ተነሥቶ ወደ ሳሎን ሲሔድ ፊት ለፊት ግጥም አሉ " ስታየው ቀጥ አለች ልታፈገፍግም አማራት ሉሲ አስቀድማ ዐልፋ ገብታ ነበር
እሱም እንድታልፍ ከጐን ቁሞ ጠበቃት።
“ማዳም ቬን " አላት እጁን ከመዝጊያው እጄታ አሳርፎ ንግግሩን ዝቅ አድርጎ
ስለ ልጆች በሽታ ብዙ ልምድ ነበረሽ ?” አላት
ልጆቿ አብረዋት በነበሩ ጊዜ ሙሉ ጤነኞች እንደ ነበሩ በማስታወስ “የለም” ብላ ልትመልስለት አሰበችና ሌላ ነገር ትዝ አላት " አራት ልጆች እንደ ሞቱባት
ተናግራ ስለ ነበር ፡ የምትሰጠው መልስ ከዚህ ጋር መስማማት እንዳለበት አሰበች
"የዊልያምን ሳል ስታይው ይህን ያህል አሥጊ ይመስልሻል ?"
“ብዙ ጥንቃቄ የሚያስፌልገው ይመስለኛል በተለይ ሌሊት እኔስ ከኔ ክፍል ውስጥ እንዲተኛ እንዲፈቀድለት ልጠይቅ ነበር " አልጋው በቀላሉ ይዛወራል እኔም ከማንኛዋም የበለጠ እጠብቀዋለሁ "
ምንም ቢሆን ይህን ያሀል ልናስቸግርሽ አንፈልግም ልጁ ደግሞ የሌሊት ጥበቃ እስከሚያስፈልገው ድረስ አልታመመም ቢያስፈልግም ሠራተኞቹ እምነት ሚጣልባቸው ናቸው
“ እኔ ልጆች እወዳለሁ ይህንን ልጅም ካየሁት ጀምሮ ወደድኩት " ስለዚህ
ጤንነቱን ቀንና ሌሊት ብንከባከበው ደስ ይለኛል "
"አንቺ በውነት በጣም ደግ ሰው ነሽ " ነገር ግን ሚስዝ ካርላይል ሐሳብሺን እንደማትቀበለው እርግጠኛ ነኝ ችግርና ድካም ልትፈጥርብሽ አትፈልግም ”
አነጋገሩ ቁርጥ ያለ ነበር " ከዚያ በሩን ከፍቶ አሳለፋት።
አሁን ደግሞ ከሁሉ ይበልጥ የፈራችው ፒያኖ መጫወቱን ነው ድሮ ለባሏ ስትዘፍንለት ነበር አሁን ልዝፈን ብትል ድምጿ ትዝ ይለው እንደሆነ ብላ ሠጋች ስለዚህም ከድሮ ዘፈኖቿ አንዳቸውንም ላትሞክራቸው ወሰነች ደግነቱ ወዲያው ከመግባቷ ጀስቲስ ሔር መጣ ሙዚቃ የሚባል ነገር ምንም ስሜት ስለማይስጠው እሱ ካለ ዘፈን የለም ሚስተርና ሚስዝ ካርላይል ተነሥተው ተቀበሉት ወደ መቀመጫው ሲያመራ በማዳም ቬን አጠገብ ስለ ዐለፈ ባርባራ አስተዋወቀችው።
" እኔ ፌረንሳይኛ መናገር አልችል ” አላት መላቅጥ በሌለው የቃላት አገባብና ድምፅ።
« እኔ እንግሊዛዊት እንጂ ፈረንሳዊት አይደለሁም ስለዚህ ፈረንሳይኛ
እንዲናገሩ የሚያስገድድዎ ነገር የለም ” አለችው እንደ መሣቅ ብላ "
“እኔ ኮ አንዲት ፈረንሳዊት ልትመጣ ነው ሲባል ሰምቸ ነው " አንቺም ብትሆኚ በስምሽ ጭምር ፈረንሳዊት ትመስያለሽ" ሆኖም ባለመሆንሽ በጣም ደስ አለኝ ፈረንሳዊት መምህር ከቤት ማስገባት ደግ አይደለም " እነሱን በሩቁ ነው ” አለና ዱሮ ለልጆቹ መምህርነት የቀጠራት አንዲት አስተማሪ በምግብ ጊዜ እንቁራሪት እየተሠራ ካልቀረበ እያለች ስታስቸግር መኖሯንና በኋላም ከጦር ሜዳ ቆስሎ ከሱ ቤት ይቀመጥ ከነበረው አንድ ወንድሙ ጋር ፍቅር ገጥማ ስለ አገኛት ' ሁለቱንም
ማባረሩን ነገራቸ “ ኧረ እንኳን አልሆንሽ እኔ አሁን ፈረንሳይ አገር ብቀመጥና
መስዬ ሔር እየተባልኩ ብጠራ ለልጄ እንኳን የፈረንሳይ እንቁራሪት መስዬ ብታየው አልቀየመውም " አለቸው "
ሉሲ ባነጋገሩ እያጨበጨበች ከትከት ብላ ሣቀች "
"አንቺ ግድ የለም ሣቂ " ግን ለፈረንሳዊት አስተማሪ ቢሰጡሽ እስካሁን ወደ
አንቁራሪትነት ወይም ከዚያ ወደባሰ ነገር ትለወጭ ነበር " ያቺ ያልታደለች እናትሽ እንኳን በልጅነቷ ፈረንሳዊት አስተማሪ ባትኖራት ኖሮ በመጨረሻ እንዲያ ያለ ሥራ አትሠራም ነበር ። በሉ ይብቃን " ስሚ እስኪ ባርባራ ምን ነገር ነው ያሳሰብሻት ?”
“ ምን ማለትህ እንደሆነ አልገባኝም " እኔና አርኪባልድ አንተ ከለንደን እስክትመለስ ድረስ ከእኛ ጋር እንድትሰነብት እንፈልጋለን " ምናልባት የጠየቅኸው ይኸን ከሆነ ?
“ ጌትዮውም እመቤቲቱም በሌሉባት ቤቴ የሠራተኞች መጨፈሪያ እንዲሆን ነው " እናንተ ወጣቶችኮ ከጥጆች የተሻለ አታስቡም " እናንተ ዘንድ ከአንድ ቀን በላይ እንድትቆይ ከፈለጋችሁ ለምን እኔ እያለሁ እንድትመጣ አታደርጓትም?
“ እንደሱ እንዳይሆንማ እሷም ትታህ ለመምጣት እሺ እንደማትል አንተም
ታውቃለህ » እሷን የመሰለች ሚስት እኮ ታይታ አታውቅም " አሁን እኔ ለአርኪባልድ ከብዙ ዘመን በኋላ የሷን ግማሽ ያህል እንኳን ብሆንለት ዕድሌን ማመስገን ይኖርበታል አባባ
ሁልጊዜ አንተ ባልከው ነው የሚሆንልህ !እስኪ ዛሬ
ደግሞ የኛን ፈቃድ ፈጽምልን እማማ እኛ ዘንድ ለመምጣት ትፈልጋለችና እባክህ እሽ በል " ቤቱና የቤቱ ሠራተኞች ምንም አይሆኑም ፤ በኔ ይሁንብህ"
"ለውጥ እኮ ያስፈልጋቸዋል ጌታዬ አለ ሚስተር ካርላይል የባለቤቱዎን የጭንቀት ኑሮ ያውቁታል"
"ሁልጊዜ ስለዚያ ወሮበላ ስታስብ ነዋ !ለምን አትተወውም "
"እሳቸውኮ ለእርስዎ አዛኝና አፍቃሪ ሚስትም ናቸው "
አይደለችም አላልኩም "
“ እንግዳያውማ ጥቂት ቀን ከእኛ ጋር እንዲቆዩ ይንገሯቸው " ለውጡ ራሱ
በጣም ይበጃቸዋል " ከባርባራ ጋር ሲሆኑ ብዙ ይረዳቸዋል " እንዴት እንደሚወዷት እርስዎ ያውቃሉ ።
“ አዎን ከሚገባት በላይ ትወዳታለች » አሁንማ ይችም ከኔ ቁጥጥር ውጭ
የሆነች መሰላትና ያለመጠን ተዝናናችብኝ " አለ ጀስቲስ ሔር
"በኔ ቁጥጥር ውስጥ ስለሆነች ልክ አስገባታለሁ በዚህ አያስቡ ' አለ ሚስተር ካርሳይል ።
ዐውቃለሁ አለ አባትዮው ቆጣ ብሉ ። እሷን ልክ ከማስገባትህ በፊት
መረን ለቀሀ አቅብጠህ ትገድላታለህ ”
ለጀስቲስ ሔር መጠጥ ቀረበለት " በዚህ መኻል ሳቤላ ወደ ሚስዝ ካርላይል
ጠጋ ብላ ለመሔድ ይፈቀድላት እንደሆነ ጠየቀች ሚስዝ ካርላይል በጎ ፈቃዷ ሆኖ ጥያቄዋን ተቀብላ ለቀቀቻት "
ከግራጫዉ ሳሎን ገብታ ብቻዋን አመሸች " በጸጸት በኀዘን በንዴት በቁጭት የተመላ መራራ ምሽት በሦስትና በአራት ሰዓት መካከል ከመኝታ ቤቷ ገብታ ለማረፍ እየተሳበች ወደ ፎቅ ወጣች ከክፍሏ ልትግባ ስትል የዊልሰንን ረዳት ላራን ስታልፍ ብታገኛት ድንገተኛ ሐሳብ ድቅን አለባት -የዊልያምን መኝታ ቤት ጠይቃት አሳየቻትና ወርዳ ወደዚያው ሔደች ሳቤላ የሳራን መሔድ አረጋግጣ ከዊልያም ክፍል ቀስ ብላ ገባች ዊልያም አንድ ትንሽ ነጭ አልጋ ላይ ተኝቷል " ፊቱ ቦግ ብሎ ወዝቷል ። ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...“ስለሷ መናግር አትችይም ማዳም ቬን ”አላት ዊልያም ድርቅ ብሎ „'' አንቺ
እማማን አታውቂያትም " ከዚህ አልነበርሽም "
ትወዳችሁ እንደ ነበር በርግጥ እተማመናለሁ " እኔ ከዚህ የቆየሁት አንድ
ቀን ብቻ ነው ግን ባንድ ጊዜ ለመድኳችሁ " አሁን በጣም እወዳችኋለሁ ” አለችና
በትኩሳት የሚቃጠሉት ጐንጮቹን ሳመችው ይህ ሲሆን 0መፀኛው እንባዋን
ልትገታው ስለ አልቻለች እሱም እንዳሻው እየወረደ ከልጁ ጉንጭ ላይ ያርፍ
ጀመር ።
“እና ምን ያስለቅሻል ? አላት ዊልያም "
"አንተን የመሰለ ልጅ ነበረኝ ሞተብኝ " አሁን በምትኩ አንተን በማግኘቴ የስ ስለአለኝ ነው እሱ ከሞተ ጀምሮ ምንም የምወደው አላገኘሁም ነበር " አለችው
“ ስሙ ማን ነበር ? አላት ዊልያም በጕጕት "
'' ዊልያም ብላ ቃሉ ካፋ ከመውጣቁ አንደዚህ በማለቷ መሳሳቷ ተሰማት
ባርባራ ከቤት ካለች ራት እንደ ተበላ ወደ ሳሎን ከመግባቷ በፊት ከፎቅ ወጥታ ልጅዋን ለጥቂት ደቂቃዎች አይታ መውረድ የዘወትር ልማዷ ነበር » ዛሬ ማታም ልማዷን አድርሳ ስትወርድ ሉሲን በግራ ሳሎን ስታጮልቅ አየቻት "
አሁን መምጣት እንችላለን . . . እማማ ?
አዎን ! ማዳም ቬንም ጥቂት ዘፈኖች እንድትጫወትልን ንገሪያት "
ማዳም ቬን ቆየት ብላ በግድ እየተጨነች ከሳሎኑ በር ስትደርስ ሚስተር
ካርላይል ከምግብ ቤት ተነሥቶ ወደ ሳሎን ሲሔድ ፊት ለፊት ግጥም አሉ " ስታየው ቀጥ አለች ልታፈገፍግም አማራት ሉሲ አስቀድማ ዐልፋ ገብታ ነበር
እሱም እንድታልፍ ከጐን ቁሞ ጠበቃት።
“ማዳም ቬን " አላት እጁን ከመዝጊያው እጄታ አሳርፎ ንግግሩን ዝቅ አድርጎ
ስለ ልጆች በሽታ ብዙ ልምድ ነበረሽ ?” አላት
ልጆቿ አብረዋት በነበሩ ጊዜ ሙሉ ጤነኞች እንደ ነበሩ በማስታወስ “የለም” ብላ ልትመልስለት አሰበችና ሌላ ነገር ትዝ አላት " አራት ልጆች እንደ ሞቱባት
ተናግራ ስለ ነበር ፡ የምትሰጠው መልስ ከዚህ ጋር መስማማት እንዳለበት አሰበች
"የዊልያምን ሳል ስታይው ይህን ያህል አሥጊ ይመስልሻል ?"
“ብዙ ጥንቃቄ የሚያስፌልገው ይመስለኛል በተለይ ሌሊት እኔስ ከኔ ክፍል ውስጥ እንዲተኛ እንዲፈቀድለት ልጠይቅ ነበር " አልጋው በቀላሉ ይዛወራል እኔም ከማንኛዋም የበለጠ እጠብቀዋለሁ "
ምንም ቢሆን ይህን ያሀል ልናስቸግርሽ አንፈልግም ልጁ ደግሞ የሌሊት ጥበቃ እስከሚያስፈልገው ድረስ አልታመመም ቢያስፈልግም ሠራተኞቹ እምነት ሚጣልባቸው ናቸው
“ እኔ ልጆች እወዳለሁ ይህንን ልጅም ካየሁት ጀምሮ ወደድኩት " ስለዚህ
ጤንነቱን ቀንና ሌሊት ብንከባከበው ደስ ይለኛል "
"አንቺ በውነት በጣም ደግ ሰው ነሽ " ነገር ግን ሚስዝ ካርላይል ሐሳብሺን እንደማትቀበለው እርግጠኛ ነኝ ችግርና ድካም ልትፈጥርብሽ አትፈልግም ”
አነጋገሩ ቁርጥ ያለ ነበር " ከዚያ በሩን ከፍቶ አሳለፋት።
አሁን ደግሞ ከሁሉ ይበልጥ የፈራችው ፒያኖ መጫወቱን ነው ድሮ ለባሏ ስትዘፍንለት ነበር አሁን ልዝፈን ብትል ድምጿ ትዝ ይለው እንደሆነ ብላ ሠጋች ስለዚህም ከድሮ ዘፈኖቿ አንዳቸውንም ላትሞክራቸው ወሰነች ደግነቱ ወዲያው ከመግባቷ ጀስቲስ ሔር መጣ ሙዚቃ የሚባል ነገር ምንም ስሜት ስለማይስጠው እሱ ካለ ዘፈን የለም ሚስተርና ሚስዝ ካርላይል ተነሥተው ተቀበሉት ወደ መቀመጫው ሲያመራ በማዳም ቬን አጠገብ ስለ ዐለፈ ባርባራ አስተዋወቀችው።
" እኔ ፌረንሳይኛ መናገር አልችል ” አላት መላቅጥ በሌለው የቃላት አገባብና ድምፅ።
« እኔ እንግሊዛዊት እንጂ ፈረንሳዊት አይደለሁም ስለዚህ ፈረንሳይኛ
እንዲናገሩ የሚያስገድድዎ ነገር የለም ” አለችው እንደ መሣቅ ብላ "
“እኔ ኮ አንዲት ፈረንሳዊት ልትመጣ ነው ሲባል ሰምቸ ነው " አንቺም ብትሆኚ በስምሽ ጭምር ፈረንሳዊት ትመስያለሽ" ሆኖም ባለመሆንሽ በጣም ደስ አለኝ ፈረንሳዊት መምህር ከቤት ማስገባት ደግ አይደለም " እነሱን በሩቁ ነው ” አለና ዱሮ ለልጆቹ መምህርነት የቀጠራት አንዲት አስተማሪ በምግብ ጊዜ እንቁራሪት እየተሠራ ካልቀረበ እያለች ስታስቸግር መኖሯንና በኋላም ከጦር ሜዳ ቆስሎ ከሱ ቤት ይቀመጥ ከነበረው አንድ ወንድሙ ጋር ፍቅር ገጥማ ስለ አገኛት ' ሁለቱንም
ማባረሩን ነገራቸ “ ኧረ እንኳን አልሆንሽ እኔ አሁን ፈረንሳይ አገር ብቀመጥና
መስዬ ሔር እየተባልኩ ብጠራ ለልጄ እንኳን የፈረንሳይ እንቁራሪት መስዬ ብታየው አልቀየመውም " አለቸው "
ሉሲ ባነጋገሩ እያጨበጨበች ከትከት ብላ ሣቀች "
"አንቺ ግድ የለም ሣቂ " ግን ለፈረንሳዊት አስተማሪ ቢሰጡሽ እስካሁን ወደ
አንቁራሪትነት ወይም ከዚያ ወደባሰ ነገር ትለወጭ ነበር " ያቺ ያልታደለች እናትሽ እንኳን በልጅነቷ ፈረንሳዊት አስተማሪ ባትኖራት ኖሮ በመጨረሻ እንዲያ ያለ ሥራ አትሠራም ነበር ። በሉ ይብቃን " ስሚ እስኪ ባርባራ ምን ነገር ነው ያሳሰብሻት ?”
“ ምን ማለትህ እንደሆነ አልገባኝም " እኔና አርኪባልድ አንተ ከለንደን እስክትመለስ ድረስ ከእኛ ጋር እንድትሰነብት እንፈልጋለን " ምናልባት የጠየቅኸው ይኸን ከሆነ ?
“ ጌትዮውም እመቤቲቱም በሌሉባት ቤቴ የሠራተኞች መጨፈሪያ እንዲሆን ነው " እናንተ ወጣቶችኮ ከጥጆች የተሻለ አታስቡም " እናንተ ዘንድ ከአንድ ቀን በላይ እንድትቆይ ከፈለጋችሁ ለምን እኔ እያለሁ እንድትመጣ አታደርጓትም?
“ እንደሱ እንዳይሆንማ እሷም ትታህ ለመምጣት እሺ እንደማትል አንተም
ታውቃለህ » እሷን የመሰለች ሚስት እኮ ታይታ አታውቅም " አሁን እኔ ለአርኪባልድ ከብዙ ዘመን በኋላ የሷን ግማሽ ያህል እንኳን ብሆንለት ዕድሌን ማመስገን ይኖርበታል አባባ
ሁልጊዜ አንተ ባልከው ነው የሚሆንልህ !እስኪ ዛሬ
ደግሞ የኛን ፈቃድ ፈጽምልን እማማ እኛ ዘንድ ለመምጣት ትፈልጋለችና እባክህ እሽ በል " ቤቱና የቤቱ ሠራተኞች ምንም አይሆኑም ፤ በኔ ይሁንብህ"
"ለውጥ እኮ ያስፈልጋቸዋል ጌታዬ አለ ሚስተር ካርላይል የባለቤቱዎን የጭንቀት ኑሮ ያውቁታል"
"ሁልጊዜ ስለዚያ ወሮበላ ስታስብ ነዋ !ለምን አትተወውም "
"እሳቸውኮ ለእርስዎ አዛኝና አፍቃሪ ሚስትም ናቸው "
አይደለችም አላልኩም "
“ እንግዳያውማ ጥቂት ቀን ከእኛ ጋር እንዲቆዩ ይንገሯቸው " ለውጡ ራሱ
በጣም ይበጃቸዋል " ከባርባራ ጋር ሲሆኑ ብዙ ይረዳቸዋል " እንዴት እንደሚወዷት እርስዎ ያውቃሉ ።
“ አዎን ከሚገባት በላይ ትወዳታለች » አሁንማ ይችም ከኔ ቁጥጥር ውጭ
የሆነች መሰላትና ያለመጠን ተዝናናችብኝ " አለ ጀስቲስ ሔር
"በኔ ቁጥጥር ውስጥ ስለሆነች ልክ አስገባታለሁ በዚህ አያስቡ ' አለ ሚስተር ካርሳይል ።
ዐውቃለሁ አለ አባትዮው ቆጣ ብሉ ። እሷን ልክ ከማስገባትህ በፊት
መረን ለቀሀ አቅብጠህ ትገድላታለህ ”
ለጀስቲስ ሔር መጠጥ ቀረበለት " በዚህ መኻል ሳቤላ ወደ ሚስዝ ካርላይል
ጠጋ ብላ ለመሔድ ይፈቀድላት እንደሆነ ጠየቀች ሚስዝ ካርላይል በጎ ፈቃዷ ሆኖ ጥያቄዋን ተቀብላ ለቀቀቻት "
ከግራጫዉ ሳሎን ገብታ ብቻዋን አመሸች " በጸጸት በኀዘን በንዴት በቁጭት የተመላ መራራ ምሽት በሦስትና በአራት ሰዓት መካከል ከመኝታ ቤቷ ገብታ ለማረፍ እየተሳበች ወደ ፎቅ ወጣች ከክፍሏ ልትግባ ስትል የዊልሰንን ረዳት ላራን ስታልፍ ብታገኛት ድንገተኛ ሐሳብ ድቅን አለባት -የዊልያምን መኝታ ቤት ጠይቃት አሳየቻትና ወርዳ ወደዚያው ሔደች ሳቤላ የሳራን መሔድ አረጋግጣ ከዊልያም ክፍል ቀስ ብላ ገባች ዊልያም አንድ ትንሽ ነጭ አልጋ ላይ ተኝቷል " ፊቱ ቦግ ብሎ ወዝቷል ። ትኩሳት
👍14😁1
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...ከዌስት ሊን ተመርጦ የሔደው የሕግ መምሪያ ምክርቤት አባል በጥፋት ከወንበሩ ተባረረ ከሱ በኋላ ደግሞ የዌስት ሊን ሕዝብ ጆን አትሊ የተባለ አንድ በአካባቢው የታወቀ ሰው መርጦ ላከ " እሱም ብዙ ሳይቆይ ሞተና በምትኩ ሌላ እንደ ራሴ መምረጥ አስፈለገ" ማን እንደሚሻል ተመከረበት በአካባቢው የነበሩ ይሆናሉ የተባሉ ሁሉ 'ዳኞችም ሳይቀሩ ተገመገሙ ።
ሚስተር ጀስቲስ ይሻል ይሆን ? እለ · እኔ ያልኩት ይሁን ከማለት በቀር
መተማመን አይሆንለትም ቢሔድም የራሱን ሐሳብ እንጂ የዌስትሊንን ሐሳብ መግለጽ አይችልም። ስኳየር ስፒነርሳ ? እሱ ደግሞ በሕይወቱ በአደባባይ ንግግር አድርጎ አያውቅም " ቀይ ሥር ከማብቀልና ከብት ከማርባት በቀር የሚያውቀው የለውም " ኮሎኔል ቤተል ? ለምርጫው ውድድር የሚያወጣው ገንዘብ አያገኝም » ሰርጆን ዶቢዴ?በጣም አርጅቷል እሱም ራሱ“ከምርጫው ገደብ ኻያ ዓመት አልፏል” ብሎ ሣቀና “ ሁላችንም ብቃት ያላቸውን እየዘለልን በማይሆኑትት ሰዎች ላይ ብቻ ነው ያተኮርነው " ስብሰባችንንኮ ያለዐዋቂዎች ስብሰባ አደረግነው አሁን ከመኻከላችን እንደራሴያችን መሆን የሚችል አንድ ሰው ብቻ ነው ያለን "
“ ማነው እሱ ? አለ ጉባኤው
“ አርኪባልድ ካርላይል ።
ለምን እንደ ረሱት ሁሉም ገረማቸው -ጥቂት ዝም ብለው ከቆዩ በኋላ የድጋፍ
ጉርምርምታ አሰሙ ።
“ እሺ ካለን ነው ” አለ ሰር ጆን ። “ ፈቃደኛ ላይሆን ይችላል ...”
ወዲያው ለጉዳዩ ጊዜ ባይስጡት አንደሚሻል ተስማሙና ተሰባስበው ወደ
ሚስተር ካርላይል ቢሮ አመሩ ። ወደ ቤቱ ሊሔድ ሲል ደረሱበትና በሰፊው እየተወያዩ ብዙ ከቆዩ በኋላ እንዴራሴያችሁ እንደሆን ነው የፈለጋቻችሁኝ ? ለጥቅሜ ሁላችሁንም እሸጣችሁ እንዶ ሆንሳ በምን ታውቃላችሁ ? አላቸው "
ግድ የለም ሚስተር ካርላይል ...እናምንሃለን።
እኔ በአሁኑ ጊዜ ፓርላማ ለመግባት ምንም ሐሳብ አልነበረኝም "
ይኸማ አይሆንም !ይልቁንስ ስምህን ለውድድር እንድናስተላልፍ ፍቀድልን ። ካንተ ሌላ ብቁ ነው የምንለው ሰው የለንም አሁን አንተ እያለህ ከኛ አንዳችንን መምረጥ የማይሆን ነው አውጥን አውርዶን ስናየው ' ከድፍን ዌስትሊን ለዚህ ቦታ አንተን ያህል የሚመጥን ሰው አላገኘንም " ስለዚህ አንተን ለውድድር ለማቅረብ ተስማምተናል ። ነገ ወደ ዌስት ሊን ስትመጣ ግድግዳዎቹ ሁሉ'
ምን ጊዜም ካርላይል በሚሉ መፊክሮች አሽብርቀው ታያቸዋለህ።
እንግዲያውስ ነገሩን ጥቂት እንዳስብበት እስከ ነገ ጊዜ ስጡኝ " ግድግዳዎቹን በመፈክሮች ማስጌጡንም ለአንድ ቀን አዘግዩት '' አላቸው "
“ የለም የለም አሁን ወስንና ንገረን የእሺታ ቃልህን ስጠን።
አሁን ከወሰንኩ በእምቢታዬ እጸናለሁ ይኸ እኮ ጥቂት ማሰብ የሚያስፈልገው ጉዳይ ነው እስከ ነገ ጊዜ ስጡኝ » ምናልባትም ጥያቄያችሁን ለመቀበል እችል ይሆናል
ሰዎቹ ከዚያ የተሻለ።
ሰዎቹ ከዚያ የተሻለ አማራጭ ስለ አልነበራቸው በቀጠሮዉ ተስማምተው
ሔዱ በውይይቱ ጊዜ አብሮ የነበረው ሚስተር ዲል እጆቹን በርካታ እያፋተገና ሚስተር ካርላይልን ዐይን ዐይኑን እያየ ወደ ኋላ ቀረት አለ "
“ዲል ምነው ? በጣም ደስ ያለሀና ስዎቹ የሚሉኝን እንድቀበል የፌለግህ ትመስላለህ …”
"መቀበል አለብህና" .... ሚስተር አርኪባልድ " ደስ ያለኝ ስለመሆኔ ግን እኔ ብቻ ሳልሆን በዌስት ሊን ውስጥ ደስ የማይለው ሴት ወንድ ልጅ አይገኝም
“ ተው ዲል . . . . በጣም እርግጠኛ አትሁን።
“ ስለምኑ ? እንደራሴያችን ስለ መሆንህ ነው ' ወይስ ስለ ሕዝቡ ደስታ ?
“ስለ ሁለቱም አለው ሚስተር ካርላይል ሣቅ ብሎ ።
ከቢሮው ወጥቶ ወደ ቤቱ ሲሔድ ጉዳዩን ያብላላው ጀመር " ከፊት ጀምሮ ፓርላማ ለመግባት ማሰቡ እርግጥ ነው ‥የሚወዳደርበትን ጊዜ ግን አልወሰነም " ዘመኑን በሙሉ ለግሉ ሙያ ብቻ የሚወስንበት ምክንያት አልታየውም ። ገንዘብ የማጣት ሥጋት የለበትም » በታወቀው የራሱ ሀብት ላይ ባርባራ ይዛው የገባችው
ሲጨመርበት ከአሁኑ ዐይነት አኗኗራቸው ከሚፈለገው በላይ ነው ሥራውን ለመተው ግን አሳብ የለውም ። ምክንያቱም ሥራው : በራሱም ጠንቃቃ አሠራር
ሳቢያ የሚያስከብረው ከመሆኑም በላይ ጠቀምቀም ያለ ገቢ የሚያገኝበትና ከልቡ
የሚወደው ሙያ ነው " ምንም ቢደረግ ሥራ ፈትቶ ለመኖር አይፈልግም " ነገር
ግን ሁልጊዜ ከሥራ ቦታው እንዳይለይ የሚያስገድደው ሁኔታ የለም ። ሚስተር ዲል
የሱን ያህል መምራት ይችላል እንዲያውም ያገልግሎት ዘመንና የሥራ ልምዱ ከተቆጠረ ይበልጠዋል " ስለዚህ ሚስተር ካርላይል ለፓርላማው ሥራ ወደ ለንደን ሲሔድ ኃላፊነቱን ያለምንም ሥጋት ለዲል ቢተውለት በሚገባ ሊያካሒድለት ይችላል " ፓርላማ መግባቱ ካልቀረ ደግሞ የበለጠ ጥቅምና መስሕብ ካለው ከማንኛውም ቦታ ይልቅ ዌስት ሊንን ወክሎ ቢገባ ይመርጣል አሁን ዌስትሊን አንድ አባል ስለሚያስፈልጋት ለሱ ይህ ጥሩ አጋጣሚ ሆኖ ታየው " ጥሩና ብቁ የሕዝብ
አገልጋይ እንደሚሆንም ያምናል " ተሰጥዎው ሰፊ ፡ ንግግሩ አርኪ ነው እውነተኛና ቀና መንፈስ አለው " ወገኖቹን በሙሉ ኃይሉና ችሎታው እንደሚያለግል ያውቃል " እነርሱም ያውቃሉ "
ቅጠላ ቅጠሎቹ ባበቡበት ' ዛፎችና ቁጥቋጦዎች አዲስ ያቆጠቆጠውን ለምለም ቅጠላቸውን በለበሱበት ' በዚያ ደስ በሚለው የጸደይ ምሽት ሁሉም ነገር በተስፋ የተመላ ይመስል ነበር ።
ሚስተር ካርላይልም በቀረበለት ፡ ተስፋ ያለው ዕድል ከልቡ ተደሰተ "
ባርባራ ከሳሎኑ መስኮት ቁማ ትጠብቀው ነበር ሲገባ ደንበክ ደንበክ እያለች ወደሱ ቀርባ በብሩህ ዐይኖቿ ውስጥ የፍቅር ብርሃን እየዋለለ ፊቷን ወደሱ ቀና አደረገች።
'' ምን ትፈልጊያለሽ?” አላት እንደዚያ ሆና እንደ ቆመች እጆቹን ከወደ ጀርባው
አድርጎ ።
" ምነው ? ደኅና እንዴት አመሸሽ ለማለት አቀበት ከሆነብህ እስከ ሳምንት ድረስ አትስመኝም ልል ሐሳብ አለኝ አርኪባልድ ”
ሚስተር ካርይል በአነጋገሯ ሳማቀና በዚህ የበለጠ የሚቀጣው ማነው ?”
አላት በሹክሹክታ
ባርባራ ለንቦጯን ጣለች እንባዋ ወዲያው በዐይኗ ሞላ “ ባንቺ ይብሳል '
ማለትህ ነው ! ለኔ ደንታ የለህምን አርኪባልድ ?”
በሁለት አጆቹ ጠምጥሞ ይዞ ከደረቱ እቅፍ አደረጋትና መልሶ መላልሶ ሳማት
ላንቺ ማሰብ አለማስቤንማ ታውቂው የለም ? አለት በጆሮዋ "
ይህ ሁሉ ሲሆን ያቺ የፈረደባት ሳቤላ ትመለከት ነበር በዘመኑ ለሷም ሲያደርገው የነበረው ሰላምታ ነው የገረጣው ፊቷ ደም እንደ ለበሰ ልክ እንዳመጣጧ ሹልክ ብላ ሳያዩዋት ወታ ወደ ክፍሏ ተመለሰች " ሚስተር ካርላይል ሚስቱን ወደ መስኮቱ ሳባትና ክንዱን በሽንጧ ሳይ አድርጎ እንደቆሙ “ስሚ እስቲ ባርባራ ካመት ውስጥ ለጥቂት ወሮች ለንደን ብንቀመጥ ምን ይመስልሻል ?
“ ለንደን ? እኔ እዚሁ በደስታ እኖራለሁ " የምን ለንደን አመጣህ ደግሞ ? ለንደን መቀመጥ አማረኝ እንዳትለኝ "
“ እርግጠኛ አይዶለሁም ግን አንድ ነገር ተጠይቄአለሁ ዌስትሊኖች እንደ ራሴያቸው እንድሆን ይፈልጉኛል " ከስሜ ላይ የፓርላማ አማካሪ የሚል ቅጽል ሲጨመርበት ማየቱ ደስ ይልሻል ?
“ጣም ጥሩ ነው ...አርኪባልድ " ሕዝቡ ወትሮም ቢሆን ይወድሃል አሁን ደግሞ የበለጠ ያከብርሃል " ዘለዓለም የገጠር ጠበቃ ሆኖ መኖር ላንተም ደግ አይደለም " ግን አሁን ለዕለት እንጀራህ ስትማስን አያለሁ " ተመርጠህ ብትሔድ ግን
ዌስት ሊን ላይ ለመሥራት አትችልም " ”
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...ከዌስት ሊን ተመርጦ የሔደው የሕግ መምሪያ ምክርቤት አባል በጥፋት ከወንበሩ ተባረረ ከሱ በኋላ ደግሞ የዌስት ሊን ሕዝብ ጆን አትሊ የተባለ አንድ በአካባቢው የታወቀ ሰው መርጦ ላከ " እሱም ብዙ ሳይቆይ ሞተና በምትኩ ሌላ እንደ ራሴ መምረጥ አስፈለገ" ማን እንደሚሻል ተመከረበት በአካባቢው የነበሩ ይሆናሉ የተባሉ ሁሉ 'ዳኞችም ሳይቀሩ ተገመገሙ ።
ሚስተር ጀስቲስ ይሻል ይሆን ? እለ · እኔ ያልኩት ይሁን ከማለት በቀር
መተማመን አይሆንለትም ቢሔድም የራሱን ሐሳብ እንጂ የዌስትሊንን ሐሳብ መግለጽ አይችልም። ስኳየር ስፒነርሳ ? እሱ ደግሞ በሕይወቱ በአደባባይ ንግግር አድርጎ አያውቅም " ቀይ ሥር ከማብቀልና ከብት ከማርባት በቀር የሚያውቀው የለውም " ኮሎኔል ቤተል ? ለምርጫው ውድድር የሚያወጣው ገንዘብ አያገኝም » ሰርጆን ዶቢዴ?በጣም አርጅቷል እሱም ራሱ“ከምርጫው ገደብ ኻያ ዓመት አልፏል” ብሎ ሣቀና “ ሁላችንም ብቃት ያላቸውን እየዘለልን በማይሆኑትት ሰዎች ላይ ብቻ ነው ያተኮርነው " ስብሰባችንንኮ ያለዐዋቂዎች ስብሰባ አደረግነው አሁን ከመኻከላችን እንደራሴያችን መሆን የሚችል አንድ ሰው ብቻ ነው ያለን "
“ ማነው እሱ ? አለ ጉባኤው
“ አርኪባልድ ካርላይል ።
ለምን እንደ ረሱት ሁሉም ገረማቸው -ጥቂት ዝም ብለው ከቆዩ በኋላ የድጋፍ
ጉርምርምታ አሰሙ ።
“ እሺ ካለን ነው ” አለ ሰር ጆን ። “ ፈቃደኛ ላይሆን ይችላል ...”
ወዲያው ለጉዳዩ ጊዜ ባይስጡት አንደሚሻል ተስማሙና ተሰባስበው ወደ
ሚስተር ካርላይል ቢሮ አመሩ ። ወደ ቤቱ ሊሔድ ሲል ደረሱበትና በሰፊው እየተወያዩ ብዙ ከቆዩ በኋላ እንዴራሴያችሁ እንደሆን ነው የፈለጋቻችሁኝ ? ለጥቅሜ ሁላችሁንም እሸጣችሁ እንዶ ሆንሳ በምን ታውቃላችሁ ? አላቸው "
ግድ የለም ሚስተር ካርላይል ...እናምንሃለን።
እኔ በአሁኑ ጊዜ ፓርላማ ለመግባት ምንም ሐሳብ አልነበረኝም "
ይኸማ አይሆንም !ይልቁንስ ስምህን ለውድድር እንድናስተላልፍ ፍቀድልን ። ካንተ ሌላ ብቁ ነው የምንለው ሰው የለንም አሁን አንተ እያለህ ከኛ አንዳችንን መምረጥ የማይሆን ነው አውጥን አውርዶን ስናየው ' ከድፍን ዌስትሊን ለዚህ ቦታ አንተን ያህል የሚመጥን ሰው አላገኘንም " ስለዚህ አንተን ለውድድር ለማቅረብ ተስማምተናል ። ነገ ወደ ዌስት ሊን ስትመጣ ግድግዳዎቹ ሁሉ'
ምን ጊዜም ካርላይል በሚሉ መፊክሮች አሽብርቀው ታያቸዋለህ።
እንግዲያውስ ነገሩን ጥቂት እንዳስብበት እስከ ነገ ጊዜ ስጡኝ " ግድግዳዎቹን በመፈክሮች ማስጌጡንም ለአንድ ቀን አዘግዩት '' አላቸው "
“ የለም የለም አሁን ወስንና ንገረን የእሺታ ቃልህን ስጠን።
አሁን ከወሰንኩ በእምቢታዬ እጸናለሁ ይኸ እኮ ጥቂት ማሰብ የሚያስፈልገው ጉዳይ ነው እስከ ነገ ጊዜ ስጡኝ » ምናልባትም ጥያቄያችሁን ለመቀበል እችል ይሆናል
ሰዎቹ ከዚያ የተሻለ።
ሰዎቹ ከዚያ የተሻለ አማራጭ ስለ አልነበራቸው በቀጠሮዉ ተስማምተው
ሔዱ በውይይቱ ጊዜ አብሮ የነበረው ሚስተር ዲል እጆቹን በርካታ እያፋተገና ሚስተር ካርላይልን ዐይን ዐይኑን እያየ ወደ ኋላ ቀረት አለ "
“ዲል ምነው ? በጣም ደስ ያለሀና ስዎቹ የሚሉኝን እንድቀበል የፌለግህ ትመስላለህ …”
"መቀበል አለብህና" .... ሚስተር አርኪባልድ " ደስ ያለኝ ስለመሆኔ ግን እኔ ብቻ ሳልሆን በዌስት ሊን ውስጥ ደስ የማይለው ሴት ወንድ ልጅ አይገኝም
“ ተው ዲል . . . . በጣም እርግጠኛ አትሁን።
“ ስለምኑ ? እንደራሴያችን ስለ መሆንህ ነው ' ወይስ ስለ ሕዝቡ ደስታ ?
“ስለ ሁለቱም አለው ሚስተር ካርላይል ሣቅ ብሎ ።
ከቢሮው ወጥቶ ወደ ቤቱ ሲሔድ ጉዳዩን ያብላላው ጀመር " ከፊት ጀምሮ ፓርላማ ለመግባት ማሰቡ እርግጥ ነው ‥የሚወዳደርበትን ጊዜ ግን አልወሰነም " ዘመኑን በሙሉ ለግሉ ሙያ ብቻ የሚወስንበት ምክንያት አልታየውም ። ገንዘብ የማጣት ሥጋት የለበትም » በታወቀው የራሱ ሀብት ላይ ባርባራ ይዛው የገባችው
ሲጨመርበት ከአሁኑ ዐይነት አኗኗራቸው ከሚፈለገው በላይ ነው ሥራውን ለመተው ግን አሳብ የለውም ። ምክንያቱም ሥራው : በራሱም ጠንቃቃ አሠራር
ሳቢያ የሚያስከብረው ከመሆኑም በላይ ጠቀምቀም ያለ ገቢ የሚያገኝበትና ከልቡ
የሚወደው ሙያ ነው " ምንም ቢደረግ ሥራ ፈትቶ ለመኖር አይፈልግም " ነገር
ግን ሁልጊዜ ከሥራ ቦታው እንዳይለይ የሚያስገድደው ሁኔታ የለም ። ሚስተር ዲል
የሱን ያህል መምራት ይችላል እንዲያውም ያገልግሎት ዘመንና የሥራ ልምዱ ከተቆጠረ ይበልጠዋል " ስለዚህ ሚስተር ካርላይል ለፓርላማው ሥራ ወደ ለንደን ሲሔድ ኃላፊነቱን ያለምንም ሥጋት ለዲል ቢተውለት በሚገባ ሊያካሒድለት ይችላል " ፓርላማ መግባቱ ካልቀረ ደግሞ የበለጠ ጥቅምና መስሕብ ካለው ከማንኛውም ቦታ ይልቅ ዌስት ሊንን ወክሎ ቢገባ ይመርጣል አሁን ዌስትሊን አንድ አባል ስለሚያስፈልጋት ለሱ ይህ ጥሩ አጋጣሚ ሆኖ ታየው " ጥሩና ብቁ የሕዝብ
አገልጋይ እንደሚሆንም ያምናል " ተሰጥዎው ሰፊ ፡ ንግግሩ አርኪ ነው እውነተኛና ቀና መንፈስ አለው " ወገኖቹን በሙሉ ኃይሉና ችሎታው እንደሚያለግል ያውቃል " እነርሱም ያውቃሉ "
ቅጠላ ቅጠሎቹ ባበቡበት ' ዛፎችና ቁጥቋጦዎች አዲስ ያቆጠቆጠውን ለምለም ቅጠላቸውን በለበሱበት ' በዚያ ደስ በሚለው የጸደይ ምሽት ሁሉም ነገር በተስፋ የተመላ ይመስል ነበር ።
ሚስተር ካርላይልም በቀረበለት ፡ ተስፋ ያለው ዕድል ከልቡ ተደሰተ "
ባርባራ ከሳሎኑ መስኮት ቁማ ትጠብቀው ነበር ሲገባ ደንበክ ደንበክ እያለች ወደሱ ቀርባ በብሩህ ዐይኖቿ ውስጥ የፍቅር ብርሃን እየዋለለ ፊቷን ወደሱ ቀና አደረገች።
'' ምን ትፈልጊያለሽ?” አላት እንደዚያ ሆና እንደ ቆመች እጆቹን ከወደ ጀርባው
አድርጎ ።
" ምነው ? ደኅና እንዴት አመሸሽ ለማለት አቀበት ከሆነብህ እስከ ሳምንት ድረስ አትስመኝም ልል ሐሳብ አለኝ አርኪባልድ ”
ሚስተር ካርይል በአነጋገሯ ሳማቀና በዚህ የበለጠ የሚቀጣው ማነው ?”
አላት በሹክሹክታ
ባርባራ ለንቦጯን ጣለች እንባዋ ወዲያው በዐይኗ ሞላ “ ባንቺ ይብሳል '
ማለትህ ነው ! ለኔ ደንታ የለህምን አርኪባልድ ?”
በሁለት አጆቹ ጠምጥሞ ይዞ ከደረቱ እቅፍ አደረጋትና መልሶ መላልሶ ሳማት
ላንቺ ማሰብ አለማስቤንማ ታውቂው የለም ? አለት በጆሮዋ "
ይህ ሁሉ ሲሆን ያቺ የፈረደባት ሳቤላ ትመለከት ነበር በዘመኑ ለሷም ሲያደርገው የነበረው ሰላምታ ነው የገረጣው ፊቷ ደም እንደ ለበሰ ልክ እንዳመጣጧ ሹልክ ብላ ሳያዩዋት ወታ ወደ ክፍሏ ተመለሰች " ሚስተር ካርላይል ሚስቱን ወደ መስኮቱ ሳባትና ክንዱን በሽንጧ ሳይ አድርጎ እንደቆሙ “ስሚ እስቲ ባርባራ ካመት ውስጥ ለጥቂት ወሮች ለንደን ብንቀመጥ ምን ይመስልሻል ?
“ ለንደን ? እኔ እዚሁ በደስታ እኖራለሁ " የምን ለንደን አመጣህ ደግሞ ? ለንደን መቀመጥ አማረኝ እንዳትለኝ "
“ እርግጠኛ አይዶለሁም ግን አንድ ነገር ተጠይቄአለሁ ዌስትሊኖች እንደ ራሴያቸው እንድሆን ይፈልጉኛል " ከስሜ ላይ የፓርላማ አማካሪ የሚል ቅጽል ሲጨመርበት ማየቱ ደስ ይልሻል ?
“ጣም ጥሩ ነው ...አርኪባልድ " ሕዝቡ ወትሮም ቢሆን ይወድሃል አሁን ደግሞ የበለጠ ያከብርሃል " ዘለዓለም የገጠር ጠበቃ ሆኖ መኖር ላንተም ደግ አይደለም " ግን አሁን ለዕለት እንጀራህ ስትማስን አያለሁ " ተመርጠህ ብትሔድ ግን
ዌስት ሊን ላይ ለመሥራት አትችልም " ”
👍15