አትሮኖስ
286K subscribers
117 photos
3 videos
41 files
566 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ምንትዋብ


#ክፍል_አስር


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

...እሷም አያቷም ታጥበው እንደተመለሱ፣ ራት በልተው በየክፍላቸው ገብተው ተኙ።
ወለተጊዮርጊስ፣ ጠዋት ከእንቅልፏ ስትነቃ የት እንዳለች ግራ ገባት።ቀስ በቀስ ጐንደር ቤተመንግሥት፣ እንግዳ ማረፊያ ክፍል ውስጥ መሆኗ ተገለጠላት። በመስኮቱ ቀዳዳዎች የገባውን ብርሃን አይታ ፀሐይ መውጣቷን አወቀች። አርፍዳ እንደነቃች ገባት፡፡ ምን ማድረግ እንዳለባት ግራ ገብቷት እዛው አረፍ ብላ ቆየች። ሲሰለቻት ተነስታ ስትወጣ፣ በር ላይ ቆመው የእሷን መውጣት የሚጠባበቁ ሁለት
ደንገጡሮች አያቷ ወዳሉበት ክፍል ወሰዷት።

አያቷ መስኮቱን ከፍተው አልጋው ላይ ጋደም ብለው የጸሎት
መጽሐፍ ያነባሉ። ስትገባ መጽሐፉን አስቀምጠው፣ “አድረሽ ነው? ሲሏት ደሕና ማደሯን ለመግለጽ እግራቸው ላይ ተጠመጠመች።በይ ተነሽ አሏት፣ ስሜታቸው ተነክቶ። ትንሽ እንደቆዩ ደንገጡሮቹ መጡላቸው። መፀዳጃ ቤት ወስደዋቸው ሲመለሱ ቁርስ አደረጉ።
ዮልያና ያረፉበት ክፍል ተመልሰው ስለ ምሳው ተወያዩ።

“ዛሬ እንግዲህ ኸጃንሆይ ጋር ማድ ምቀርቢበት ቀን ነው። እናም የነገርሁሽን ሁሉ ልብ እንድትይ። እንደገባሽ ኸደሽ በቅጡ አጎንብሰሽ እጅ ትነሽና እግር ትስሚያለሽ። ተቀመጭ እስቲለሽ ትጠብቂና ያመላከቱሽ ቦታ ኸደሽ ትቀመጫለሽ...”

የጀመሩትን ሳይጨርሱ ሁለት ደንገጡሮች በር ላይ ሆነው ለጥ ብለው እጅ ከነሱ በኋላ፣ አንደኛዋ፣ “እመቤቶቼ እንፋሎት እጥበት
እንኸዳ” አለቻቸው።

ወለተጊዮርጊስና አያቷ በደንገጡሮቹ ተከታይነት የአፄ ፋሲልንና የታላቁ ኢያሱን ቤተመንግሥታት ከኋላቸው ትተው ወደ ታች ወረዱ። የጻድቁ ዮሐንስን ቤተመዛግብት በግራ በኩል፣ ቤተመንግሥታቸውን
ወለተጊዮርጊስ በወሬ እንጂ በአካል አይታቸው የማታውቃቸውንና በስተቀኝ አልፈው፣ አንበሶቹ ቤትጋ ሲደርሱ አያቷ፣ “አንበሶች” ሲሉ ጠዋት ላይ ሲያገሱ የሰማቻቸውን አንበሶች ለማየት ቆም አለች። በአድናቆት ካስተዋለቻቸው በኋላ፣ከአንበሶቹ ቤት ጀርባ ያለውን የሣልሳዊ ዳዊትን የሙዚቃ አዳራሽ አሁንም በቀኝ በኩል ትተው ወደ ፊት አመሩ። ወለተጊዮርጊስ በየቤተመንግሥታቱ መተላለፊያ ላይ የተሰደሩት ወታደሮችና በየበሩ ላይ የቆሙት እልፍኝ አስከልካዮች
ቁጥር አስገረማት፣ ከእነሱ ጋር የመፋጠጥ ያህል ተሰማት። በመጨረሻም ቁመቱ አጠር ያለ ነገር ግን ሰፋ ያለ ግንብ ውስጥ ገቡ።

“እመቤቶቼ እኼ ንጉሦቹና እቴጌዎቹ እንፋሎት ሚገቡበት ነው” አለቻቸው፣ ከደንገጡሮቹ አንዷ ። ቀጥላም፣ “አጤ ፋሲል ናቸው ያሠሩት። እኼኛው የእቴጌዎቹ ነው። የንጉሦቹ በያኛው በኩል ነው።ልብሳችሁን ታወልቁና እነዝኸ መንጠቆዎች ላይ ትሰቅላላችሁ።ጌጦቻችሁን ደሞ እነዝኸ ውስጥ ታኖራላችሁ” አለቻቸው፣ ትንንሾቹን የድንጋይ ፉካዎች በሌባ ጣቷ እያመለከተቻቸው።

“በዝኸ በር ግቡና ኸነዛ ዳርና ዳር ያሉ መቀመጫዎች ላይ ተቀመጡ። ያ ሚጨሰው አረግ እሬሳና ጦስኝ ነው። እኛ ከውጭ ሁነን እንጠብቃለን” ብላቸው ከሌላዋ ደንገጡር ጋር ተያይዘው ወጡ።

ወለተጊዮርጊስና ዮልያና ጌጦቻቸውን አስቀምጠው፣ ልብሳቸውን አውልቀው የተባለው ክፍል ውስጥ አጎንብሰው ገብተው ተቀመጡ።ክፍሉ መሃል ላይ የተደረደሩት ድንጋዮች ሲግሉ፣ “አየሽ ያነን ምታይውን ወናፍ በዚያች በምታያት ቀዳዳ አሳልፈው፣ ኸውጭ ሁነው
ደንጊያዎቹን ያግላሉ” አሏት።

ድንጋዮቹ ሲግሉ፣ ከውጭ በቀርከሀ ዋሽንት ውሃ ድንጋዮቹ ላይ ፈሰሰ። ላብ አጠመቃቸው። እንደመታፈን ሲሉ ከጣሪያው ላይ ያሉት ትንንሽ ቀዳዳዎች ከውጭ ተከፈቱላቸው።

“አየር እንዲገባ ቀዳዳዎቹን ከፈቱልን። አለያማ ታፍነን እንሞት
ነበር” አሏት።

ቀዳዳዎቹ ተመልሰው ተዘጉ።

“እንፋሎት ተመልሶ እንዲመጣልን መልሰው ዘጉት” አለች፣ ነገሩ
የገባት ወለተጊዮርጊስ።

“እንዲህ አይሁን እንጂ እኛም እኮ በእንፋሎት መታጠብ እናውቃለን
አሉ፣ ዮልያና።

እሷ ይህን ዓይነቱን ነገር ከእሳቸው ቀርቶ ከማንም ጋር አድርጋው
ባለማወቋ እፍረቱ አላስቀምጥ አላት። ሰውነቷ እየተሟሟቀ ሲመጣ ግን ዘና አለች። ከፊቷና ከራሷ ላይ የሚፈልቀውን ላብ አስር ጊዜ ስትጠራርግ አዩና፣ “አይዞሽ አሁን ያነን ሁሉ የምንገድ ድካም ድራሹን ነው ሚያጠፋልሽ” አሏት።

ሲጨርሱ ወደ ገላ መታጠቢያው ክፍል ሄደው ዙርያውን የተከበበ
ገንዳ ውስጥ መጀመሪያ እሳቸው፣ ቀጥሎ እሷ ታጥበው የክት ልብሳቸውን ለብሰው ሲወጡ፣ ወለተጊዮርጊስ ከመቼውም ጊዜ በላይ አለምልማለች።

ዕረፍት እንዲያደርጉ ማረፊያ ክፍሎቻቸው ተወሰዱ።

ብዙም ሳይቆዩ ደንገጡሮቹ ለወለተጊዮርጊስ በእቅፋቸው ነጭ ረጅም የሐር ቀሚስ፣ በወርቅና በከበሩ ድንጋዮች ያጌጠ ጥቁር ካባ፣ የቆዳ ጫማ፣ ነጭ የሐር ሻሽና ከወርቅ የተሠሩ የአንገትና የጆሮ ጌጦች ይዘው መጡ። አንደኛዋ ታጥቦ የነበረውን ፀጉሯን ሾርባላት ሄዱ።ወለተጊዮርጊስ የመጣላትን ልብስ፣ ካባ፣ ሻሽ፣ ጫማና ጌጦች ግልጽ በሆነ አድናቆት አገላብጣ ስታይ፣ ጋደም ብለው የነበሩት አያቷ አይዋት።
በለጋ ዕድሜዋ እዚህ ደረጃ በመድረሷ ተደስተው እንባቸው ቀረር አለ። እንባቸው እንዳታይባቸው በነጠላቸው ተሸፍነው ፊታቸውን ወደ
ግድግዳው አዞሩ። ራሳቸውን አረጋግተው ነጠላቸውን ከፊታቸው ላይ ገለጥ አደረጉና ወደ እሷ ዞሩ። አሁንም የመጣላትን ዕቃ ታገላብጣለች።

“ጥሎሽ የመጣልሽም ኸዝኸ ይበልጥ እንጂ አይተናነስም። እሱን ልበሺ ስልሽ ለመንገድ አይሆንም ብለሽ የኔን ለበሽ። ለማንኛውም ጥሎሽ ይለቅ። አሁን እሱን አስቀምጭና ወደ ጃንሆይ ስትኸጂ እንዴት እንደሆነ አንዴ ተወጪልኝ” አሏት።
ልብሶቹን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አኑራ፣ ክብ ዐይኖቿን ሰበር አድርጋ
በተመጠነ፣ ንግሥታዊ በሚመስል እርምጃ ወደ እሳቸው ስትጠጋ፣ “እኼ ነው የኔ ልዥ ። ያሳየሁሽን ሁሉ አረሳሽም። እንዲያውም አክለሽበታል” አሉና ጠጋ እንድትላቸው በእጃቸው ጠቆሟት። ተጠግታቸው
ስታጎነብስ፣ “እንዲህ ያለች ምሽት ኸየትም አያገኙ” ብለው ጉንጫን
መታ አደረጓት።

ቀና አለችና የእፍረት ሳቅ ሳቀች። “ስንት መልከ መልካም ወይዛዝርት
አለ በሚባልበት... ስንት የንጉሥ ዘር ባለበት አገር?” አለቻቸው።

በስጨት እንደማለት ብለው፣ “አንቺ ደሞ እንግዲህ ሰው ሚልሽን ስሚ አሉና ከተጋደሙበት ተነሥተው ተቀመጡ። ወገባቸውን በሁለት እጃቸው ይዘው፣ “የንጉሥ ዘር የሆነ ሁሉ መልክ አለው መሰለሽ? አንቺ ሁሉን አሟልቶ ሰቶሻል። ደሞ ጃንሆይ የንጉሥ ዘር ቢፈልጉ አጥተው? አንቺስ ብትሆኚ የንጉሥ ዘር ማዶለሽ? አንድ መኰንን አልገዛም ብሎ
ሲያውክ በጋብቻ ለማሰር፣ ጥቅም ለማስጠበቅ አሊያም ደሞ አመጥ
ለማብረድ ሲሉ መሰለሽ አንቺን ማግባት የፈለጉ? ወደውሽ ነው።
ትምርትም ቢሆን ዳዊት ደግመሻል። ጥፈትም ቢሆን ሚደርስብሽ የለ። የጐንደር ወይዛዝርት እኩሌታዎቹ ስንኳ ዳዊት አልደገሙም...
ይቅር ኻንቺ ሊተካከሉ... ኧረ እንዲያው ምንሽም አይደርሱ።”

“አየ እሚታዬ ልዥሽ ስለ ሆንኩ ነው እንደሱ ምትይው። ግና ኣንድ
ጥያቄ ልጠይቅሽ... ጃንሆይ ኸዝኸ በፊት አላገቡም ነበር እንዴ?”

“አግብተው ነበር እንጂ።”

“እህስ?”

“በእንዴት ያለ ወግ ተጋብተው እሷ የሠርጉ ምሽት እንደ ወጉ ግብር
አብልታ፣ እህል ውሃ ስንኳ ሳትቀምስ በጥኑ ታማ በበነጋው ሞተች።እደብረብርሃን ሥላሤ ነው የተቀበረች፤ ኸዛው እናታቸው ኻሉበት። መርዝ ነው ይላሉ። እንዴት ያለች አለላና ብርቱ ሴት ነበረች አሉ። ደማምና ብርቱ ይሆናቸዋል።”

“እንዴ?” አለች ወለተጊዮርጊስ፣ ሰውነቷን ያልታወቀ ነገር ወረር
አድርጓት። ተነስታ ቆመች። “እኔስ ፈራሁ። እኔንስ በመርዝ ቢገሉኝ?"
👍171🔥1
#ትኩሳት


#ክፍል_አስር


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

ባህራም
ምጥ


ባህራም በሰኔ ወር የወደቀውን ፈተና እንደገና ለመፈተን
ማጥናት ጀመረ። የራሱ መኝታ ቤት ያረጀና የከረከሰ ሆኖ፣ ደምበኛ ጠረጴዛና ወምበር የለውም፡፡ እዚያ ማጥናት አልቻለም፡፡የዩኒቨርሲቲው ቤተመፃህፍት እየሄደ እንዳያጠና፣ ቆንጆ ቆንጆ ሴቶች ውር ውር እያሉ ሀሳቡን ይሰርቁታል። ከቀኙ፣ ከግራው፣ከፊቱ፣ ከኋላው ደሞ አስር፣ አስራ አምስት ፍራንክ ያበደሩት ሰዎች ያዩታል፣ ይከብዱታል። እነሉልሰገድ ቤት ሄዶ እንዳያጠና ወሬና
ጫጫታ ይበዛል። እኔ ቤት እየመጣ ያጠና ጀመር። ከሰአት በኋላ ሲኒማ እሄድለታለሁ፣ ሲያጠና ይውላል። ማታ እፅፋለሁ ወይም አነባለሁ፣ ሲያጠና ወይም የማኦ ትዜ ቱንግን መፃህፍት ሲያነብ ያመሻል፡፡ ጧት ግን ምንም ያህል አይሰራም፡፡ ወሬ እናበዛለን።

ጧት ገና ከእንቅልፌ ሳልነቃ መጥቶ፣ በቀስታ በሩን ከፍቶ
ገብቶ፣ ጠረጴዛው ዘንድ ተቀምጦ ሲሰራ ይቆያል። ስነቃ “Bon jour
እለዋለሁ። Bon jour ብሎኝ ቡና ይጥድና ስራውን ይቀጥላል።
አልጋዬ ውስጥ እንዳለሁ ትላንት የፃፍኩትን እመለካከታለሁ፤
አርማለሁ፣ እሰርዛለሁ፣ እቀዳለሁ። ሙሉ ሰአት ሲሆን ባህራም «አንድ ጊዜ ዜና ብንሰማ ይረብሽሀል?» ይለኛል፡፡ (የፈረንሳይ ራዲዮ በየሰአቱ አጫጭር ዜና ያሰራጫል) ራስጌዬ ያለችውን ራዲዮ እከፍታታለሁ። ባህራም ያፈላውን ቡና በዱቄት ወተት እየጠጣን ስለቪየትናም ወሬ እንሰማለን። ቪየትኮንግ የደፈጣ አሜሪካኖቹን አጥቅተዋቸው እንደሆን ባህራም ደስ ይለውና ደስታው
አላስጠና ይለዋል። መናገር ይጀምራል።ቬየትኮጎቹ ድል
ማድረጋቸው አይቀርም ይላል፡፡ ንግግሩ ቀስ ብሎ ወደ ኢራን
ይወሳስደዋል።ስለኢራን ሊነግረኝ ይጀምራል። ስለኢራን፣
ስለኮሙኒዝም፣ ስለማኦ ትዜ ቱንግ፣ ስለአሜሪካን ወራሪነትና
አጥቂነት፣ ስለካፒታሊዝም ስናወራ እንቆይና፡ ሙሉ ሰአት ሲደርስ
እንደገና ራዲዮ እንከፍታለን፡፡ ዜናው ያስደስተዋል ወይም
ያበሳጨዋል። ወሬያችንን እንቀጥላለን። የምሳ ሰአት እስኪደርስ እናወራለን፣ እናወራለን ማለት፣ በአብዛኛው እሱ ሲያወራ እኔ አዳምጠዋለሁ፤ እንዳንድ ጊዜ ጥያቄ እጠይቀዋለሁ፡፡ የነገረኝን
እያንዳንዱን ማታ ልተኛ ስል አንድ ትልቅዬ ደብተር ውስጥ አሰፍረው ነበር

አሁን ያንን ደብተር ሳነበው ባህራም ይታየኛል፡፡ እኔ አልጋ
ውስጥ ትራስ ተደግፌ ቁጭ ብዬ፡ እሱ በሽተኛ ሊጠይቅ የመጣ
ይመስል አጠገቤ ወምበር ላይ ተቀምጦ፣ በብልህ ቡናማ አይኖቹ
እያየኝ፣ ፀጉራም እጆቹን በብዙ እያንቀሳቀሰ፣ በወፍራም ልዝብ
ድምፁና በተሰባበረ ፈረንሳይኛው ሲያወራልኝ፣ ቁልጭ ብሎ
ይታየኛል

ወሬው አንድ መስመር ይዞ አይሄድም። ኢራን፣ ኒኮል፣
የባህራም ቤተሰብ፣ የባህራም ጓደኞች፣ ፈረንሳዮች፣ ጥቁሮች፣
ወጣት ኮሙኒስቶች የተባለ የኢራን አገር ማህበር፣ ትምህርት
ቤት፣ ሴቶች፣ ቡሽቲዎች፣ ጋዜጠኞች ብቻ ባህራም ያየውንና
የሰማውን ነገር፣ በህይወቱ የደረሰበትን ወይም በሌሎች ላይ
የደረሰባቸውን ነገር አሳዛኝ ነገር፣ አስደሳች ነገር፣ አስቂኝ ነገር፣
የሆነ ነገር ያወራልኝ ነበር፡፡ ስንቱን ብዬ ልናገረው እችላለሁ?
ጥቂቱን ብቻ ባጭሩ ላስፍረው፣ እንደ ባህራም ካንዱ ወደ ሌላው
እየዘለልኩ. እንደሚከተለው...

አሜሪካኖቹ ይወድቃሉ (ይላል ባህራም) ታያለህ፡፡ ስንቱን ህዝብ
ጨቁነው፣ ስንቱን አገር ፈትፍተው፣ ስንቱን መንግስት ገዝተው
ይችላሉ? አንድ ቀን ይወድቃሉ። እንኳን እንደነሱ ያለ ቂል ፈረስ
ይቅርና፣ እንደ እንግሊዝ ያለ ተንኮለኛ ቀበሮም ወድቋል። ተነስቶ ሌሎች ህዝቦችን
ጨቁኖ መውደቅ የሚቀርለት የለም፡፡ “አሜሪካኖችም ይወድቃሉ፡፡ ይወድቃሉ። ታይቶ የማይታወቅ አወዳደቅ ይወድቃሉ። ያን ጊዜ የአለም ህዝቦች እልል ይላሉ።
በአሜሪካ አግር ተረግጠው ደክመው እልል ለማለት ያህል አቅም ያነሳቸው ደሞ እፎይ ይላሉ

አሜሪካኖቹን መጀመሪያ
ሆ ቺ ሚን ከቪየትናም ያባርራቸዋል::ቀጥሎ እነ ማኦ ሴቱንግ ወይም ወራሾቹ ከሩቅ ምስራቅ ያስወጡዋቸዋል፡፡ ቀጥሎ እንግዲህ ማን ከየት እንደሚያስወጣቸው አላውቅም:: ብቻ እርግጠኛ ነኝ ያስወጡዋቸዋል። ይህን የሰው አገር ደም ጠጥቶ የወፈረ ቂጣቸውን በካልቾ እየመቱ “Yanked go home!
And stay honte!' (ያንኪ ወደ አገርህ ግባ እና እዚያው ቅር!»)
እያሉ ያስወጡዋቸዋል። ከሰው እድሜ በላይ በኖርኩ! አሜሪካ
ስትወድቅ ለማየት እንድችል ብቻ

ምን ማለትህ ነው? ለምን አልጠላቸውም? አሜሪካኖችን ያልጠላሁ ማንን ልጠላ ነው የነፃነትን ዋጋ እያወቅኩ፣ የተጨቆነ ህዝቤን እየወደድኩ፣ አሜሪካኖችን ካልጠላሁማ ሰው አይደለሁም ማለት ነው። ድንጋይ ነኝ ማለት ነው አሜሪካኖች አንድ የተቀደሰ ተግባር አላቸው:: ይኸውም፣ እባብ ያንዲትን ወፍ እንቁላል መጦ ጨርሶ ቅል ብቻ እንደሚያስቀርላት፣እነሱም ያንዲትን አገር ሀብት መጠው ጨርሰው፣ አፈርና ድንጋይ
ይተዉላታል። የኔን አገር ውሰድ። ዋና ሀብቷ ነዳጅ (ፔትሮል
ነው። ነዳጁን ከመሬት መጦ የሚወስደው አሜሪካ ነው

አንድ ቀን ሞሳዴግ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ። ተነሳና የኢራን
ሀብት ለኢራን ህዝብ ነው አለ፡፡ አሜሪካኖቹ ተሳስተሀል አሉት፡፡
በቃል ሳይሆን በተግባር፣ የኢራን ሀብት ለአሚሪካ ነው፣ የኢራን
ሀብት ለኢራን ነው ካልክ ኮሙኒስት ነህ ማለት ነው አሉት።
ሲ.አይ.ኤ ልከው ገለበጡት። ሞሳዴግ ተይዞ ሞት ተፈረደበት። ግን ሽማግሌ በመሆኑ፣ የሞት ፍርዱ ወደ እስራት ተሻሻለለት። አሁንም ታስሯል፡፡ የኢራን ሀብት ለአሜሪካኖቹና ለሻህ ነው ያለ ሰው ግን ይሾማል ያሸለማል። ሻህ ማለት በነሲሩስ፣ በነዳርዩሽና በነኻሻር ያዥ ስመ ጥሩ ዙፋን ላይ ተቀምጦ ኢራንን የሚጨቁን ጋንግስተር ማለት ነው:: አጋዦች አሉት። ህዝቡ ያረሰውን ለመንጠቅ የእርሻ ሚኒስትር ያግዘዋል። ህዝቡ ሲነግድ ከነጋዴው ለመቀማት የንግድ ሚኒስትር
ያግዘዋል። ለልዩ ልዩ አይነት ጭቆና ልዩ ልዩ ሚኒስትር አለው።
ህዝቡ በደስታ እንዲጨቆን፣ ማለትም ተጨቆንኩ ብሎ
እንዳያጉረምርም፣ ፀጥ የሚያሰኙ ያገር ግዛትና የፍርድ ሚኒስትሮች
አሉት

ያሻህን ሻህ ሚኒስትሮች፣ በተለይም የውጭ ጉዳይና ያገር ግዛት ሚኒስትሮቹ፣ ትእዛዛቸውን በቀጥታ ከዋሽንግተን ይቀበላሉ።
ምክንያቱም ኢራን የአሜሪካ የነዳጅ ማእድን ናት። ደሞ ኢራን
የሩሲያ ጎረቤት ስለሆነች፣ አሜሪካኖች በጣም ለኢራን
ይጠነቀቁላታል። አንድ ገበሬ ብዙ የምትታለብ ላም ብትኖረው
አይጠነቀቅላትም?

ሻህ ማለት ውሻ ነው፡፡ አሜሪካኖቹ ኢራንን አርደው ብልቷን ሲያወጡ እፉ ምራቅ እየሞላ በአይኑ ይከተላቸዋል፣ ሳምባ ወይም
ሌላ ቁራጭ ስጋ ጣል ያረጉለታል። እሱ ደሞ ህዝቡን ጨቁኖ
ይይዝላቸዋል። አየህ፣ ህዝቡ ተጨቁኖ ካልተያዘ፣ እንደ ሞሳዴግ
ተነስቶ የኢራን ሀብት ለኢራን ሰዎች ይላል። ስለዚህ አሜሪካኖቹ
ለህዝቡ የማይቆረቆር፣ ጥቂት ሚልዮን ብር ቢሰጡት የሚበቃው፣ ህዝቡን ጨቁኖ የሚይዝላቸው ገዥ ይፈልጋሉ፡፡ ለዚህ ነው ዙፋኑን
የሚጠብቁለት በሞሳዴግ ጊዜ ረብሻ ተነሳ፡፡ ሽህ ሽሽቶ ከአገር ወጣ።አሚሪካኖች መጥተወ «የኢራን ሀብት ለኢራን ሰዎች» የሚሉትን የሞሳዴግ ተከታዮች ፈጅተው፣ በዚያውም ያለ የሌለውን ኮሙኒስት አርደው ጨርሰው፣ አገሩን ጸት ካደረጉ በኋላ፣ ና ወደ ዙፋንህ
ተመለስ አሉት፡፡ ወደ ዙፋኑ ተመለሰ
👍22