#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...እንዲህ እንዳይመስሉሽ። ኸግር እስተራስሽ እያገላበጡ ነው ሚያዩሽ።ቄንጥ ሲያወጡ አይጣል ነው” ሲሉ መከሯት።
“እሚታዬ ልቤ ፈራ” አለቻቸው፣ እጆቿን እያፍተለተለች።
“ምን ሚያስፈራ ነገር አለ?” አሉ፣ ቆጣ ብለው። ለራሳቸው፣ እንደዛ
ቆፍጣና ምትመስለኝ ልዥ ምን ሆነች? ማታውቀው ቦታ ስለምትኸድ ነው? አሉና ለእሷ፣ “አብሬሽ ማዶል እንዴ ምመጣው? ንጉሥ የሆኑ እንደሁ ልዣችንን እንዳው ዝም ብለን ምንሰድ ይመስልሻል? ጐንደርንም ቢሆን አገላብጨ ነው ማውቃት። ጃንሆይ ሳይነግሡ በፊት... ነፍሳቸውን ይማርና ኸነእንኰዬ አባት ጋር ኑረናል። ጃንሆይ ኸነገሡ በኋላ አልኸድኹም እንጂ” አሏት።
“አብረሽኝ ምትመጪ ባትኾኚ ምን ይውጠኝ ኑሯል?” ብላ፣አንገታቸው ሥር ገብታ ሳይታሰብ ተንሰቀሰቀች። ውስጥ ውስጡን
ያስለቀሳት ግን ከጥላዬ መለያየቷ ነው።
“ደሞ ለክፉ ሆነ ለደግ ግዝየ ሚሆን ወልደልዑልን የመሰለ ወንድም አለሽ። ስንኳን ላንቺ ለእህቱ፣ አላየሽም እንዴ ላገር ሲተርፍ? አርከሌድስም አለ። ልዤ ነው ብዬ ማዶል ። አንቺም ብትሆኚ ታውቂያሽ እንዴት ብርቱና ታማኝ እንደሆነ። እንደ ኒቆላዎስስ ቢሆን... ጋሻና መከታ እንደሚሆንሽ አንቺም ታቂያለሽ” አሉ፡ ደረታቸውን መታ፣ አንገታቸውን ነቀነቅ አድርገው።
ምንጊዜም ቢሆን ስለሚወዱት ታናሽ ወንድማቸው ስለኒቆላዎስ
ሲያወሩ ደስ ይላቸዋል፤ ይኮሩበታል ። ቀጠለና፣ “አጎትሽ እሽቴም አለ። ደሞስ ያጎቶችሽ ልዦች ጌታ፣ አውሳቢዮስና፣ ነጮ አሉ ማዶል እንዴ? የወገን ጥላ አያሳጣኝ ማለት ነው” እያሉ እንባዋን በነጠላቸው ከፊቷ
ላይ ጠራረጉላት።
“ግና የቤተመንግሥት ወግ ኸየት አባቴ አውቄ?” አለች።
“አንቺ ደሞ ያልቸገረሽን። ወጉንስ እኼው እያስተማርሁ ማዶል
እንዴ? ሌላውን ደሞ ግዝየው ሲደርስ ትማሪያለሽ።”
“እሚታዬ፣ ቤተመንግሥት ልገባ?”
“ቤተመንግሥት ለመግባት ምን ያንስሻል? አጥንተ ጥሩ... ያውስ
የንጉሥ ዘር ማዶለሽ? አባትሽስ ቢሆኑ የደንብያው ባላባት የአቤቴ
ተክለሃይማኖት ልዥ ማዶለ? መልክስ ቢሆን ማን ደረሰብሽ? ቀይ ሰው መልክ አይፈጅም ይላሉ፤ አንቺ ፈጅተሻል። ቅላትሽ እኮ የኔና የናትሽ ነው። እንዳባትሽ ጠይም ብትሆኚ ኑሮኮ ምን የመሰለች ጠይም አሳ መሳይ ትሆኚ ነበር። ምግባርና ብሩህ አይምሮም አክሎልሻል።
ለዝህም እኮ ነው ጃንሆይ የመረጡሽ። እቴ ኸንግዲህ ማቄን ጨርቄን የለም፤ መኸድ ብቻ ነው።”
“ልጄ ዕድል ነው። ተሰጥቶሽ ነው። ደግ ሁኖልሻል፤ ሁሉን
አብዝቶልሻል” አሏት፣ እስከዛ ድረስ እናታቸው የሚሉትንና
የሚያደርጉትን በፀጥታ ሲታዘቡ የቆዩት እናቷ።
“የምን ዕድል ነው ምትይ? ዕድል ከሰማይ ይወድቃል? እንዲሁ
ነው እንዴ ንጉሡ ልዣችንን ሊያገቡ የፈለጉ? ልዣችን ሚገባትን ነው ያገኘችው። በደም ግባቷ፣ በብሩህ አይምሮዋ፣ በመልካም ምግባሯና
ጎንበስ ቀና ብላ ስላስታመመቻቸው ነው ንጉሡ ለንግሥትነት የመረጧት፣ ንግሥትነት እንደሚገባት አይተው መዝነው ነው እንጂ እንደ መደዴው ለውበቷ ወይም እንደገበሬ ለሙያዋ ብቻ ብለው
አይደለም።” ዮልያና ልጃቸውን ቆጣ አሉ።
“መቸም ደመ ግቡ ሁሉ... ያስታመመ ሁሉ ንጉሥ ባል አያገኝም። እንዳው የዕድል ነገር ይገርማል። እኼን ማን አሰበው?” አሉ፣ የእናታቸውን አፍ ብዙም የማይዳፈሩት ወይዘሮ እንኰዬ።
“የኔ ልዥ ገና ንግሥት እሌኒን አረግሻለሁ” አሉ፣ አያትየው።
“እሳቸውን መሆን እንዴት ይቻለኛል?”
“አንቺ ደሞ... እሌኒን ትሆኛለሽ ስልሽ እኮ ልክ እንደሳቸው ሁኚ
ማለቴም ማዶል። እንዴት እንደምኖሪ ማወቅ ያንቺ ፈንታ ነው። ሁሉ እየቅል ነው።”
ለጊዜው የአያቷ ምክር በመጠኑም ቢሆን አረጋጋት።
በነጋታው መንገደኛ ናትና ጥሩ እንቅልፍ እንድታገኝ እናትና አያት
ትኩስ ወተት በማር አጠጥተው አስተኟት። እሷ ግን እንደ ትናንቱ
ሁሉ ዛሬም እንቅልፍ በዐይኗ ሳያልፍ ፍርሐት፣ ጥላዬን ለመጨረሻ ጊዜ ሳታየው የመሄድ ጭንቀት፣ ብሎም ቀስ እያለ ውስጧ እየተጫረ የመጣው ቤተመንግሥት የመግባት ጉጉት መሳይ ነገር ሲፈራረቁባት
ሌሊቱ እንደመንጋት አለ።
ዶሮ ሲጮህ ቀሰቀሷትና ተጣጠበች። ቁርስ ብዪ ብለው ሲያቀርቡላት ግን ተናነቃት። እናቷ፣ “ትንሽ አፍሽ አርጊ፤ ምንገድ ባዶ አፍ አይከድም” እያሉ ሊያግባቧት ሞከሩ። እሷ ግን እንኳን እናቷን፣
አባቷን፣ ወንድሟን፣ ጥላዬንና የቤት አገልጋዮቹን ቋራን ራሱን ጥላ መሄዱ ዳገት ሆነባት።
ዐይኗ እንባ አቀረረ።
የእናቷን ፊት የተጫጫነውን ሐዘን ስታይ፣ ዐይኖቿ ጥግ ተጠልሎ
የነበረው እንባዋ ወደ ጉንጮቿ ኮለል አለ። እናቷ እስከዛ ሰዐት አምቀውት የነበረውን እንባ እንደ ድንገተኛ ዝናብ አወረዱት። ጉልበታቸው ላይ ተደፍታ፣ “እነየ መተሽ አታይኝም?” ስትላቸው፣ ትከሻዋ ላይ ተደፍተው
እዬዬ ሲሉ እሷም ስቅስቅ ብላ አለቀሰች።
አያትየው ልጃቸውን፣ “እንደማበርታት ጭራሽ ታባቢያታለሽ?” ብለው ቆጣ አሉና፣ ወለተጊዮርጊስን ትከሻዋን ነካ አድርገው፣ “ተይ እኮ የኔ ልዥ፣ በቅጡ እንዳልተኛሽ ስንኳ ያስታውቃል። ምንገደኛ ነሽ። ገና
ምንገዱ ሚያጠወልግሽ ይበቃል። ፊትሽን አታበላሺ። የቀባሁሽንም
ኩል እንባሽ አጠበው። በቃ እንድች ብለሽ እንዳታለቅሺ። በይ ነይ” አሉና ፊቷን በእጃቸው አባብሰው፣ እንደገና ሥር ኩል ዐይኗ ላይ አደረጉላት።
እንግዶቹ እህል አፋቸው ካደረጉ በኋላ፣ ለመሄድ ወደ ውጭ ሲወጡ በአቅራቢያ ያለ ቤተዘመድ፣ የወለተጊዮርጊስን ጐንደር መሄድ የሰማ
ጎረቤትና ጓደኞቿ ተሰብስበዋል። ወለተጊዮርጊስ የአያቷን ረጅም የሐር ቀሚስ ለብሳ፣ ከቀሚሱ ሥር በሐር ክር ጫፉ የተጠለፈና ተረከዟን ጠበቅ አድርጎ የያዘ ሱሪ ታጥቃ፣ በአያቷ ወርቅ አሸግና ብቅ ስትል፣እንግዶቹ ትንግርት እንጂ እውን ሰው የሚያዩ አልመስል አላቸው።
ዘመድና ጎረቤት ግቢውን በዕልልታ ሲያደምቀው፣ የወለተጊዮርጊስ ጓደኞች ዐይናቸው እያየ በጓደኛቸው ሕይወት ውስጥ ያልገመቱት
ዓይነት ለውጥ መምጣቱ፣ ካጠገባቸው ተነስታ ለንግሥትነት መታጨቷ አስደነቃቸው። በዓመት መለወጫ ቀን አደይ አበባ እያስቀጠፈች፣ከቤት ቤት በድፍረት ይዛቸው እየዞረች፣ የምታስተባብራቸውና እንደ
መሪያቸው የሚቆጥሯት ጓደኛቸው ከመሃከላቸው በመለየቷ አዘኑ፤
በታላቁ ዕድሏ ቀኑ፣ ተደሰቱ። በዚኹም ድብልቅልቅ ስሜት መሃል ግን በመለያየታቸው አለቀሱ።
ግራዝማች የልጃቸውን ውበት ገና ያን ቀን ያዩ ይመስል ዐይናቸው
ውሃ አቆረ። እሷን ለመሰናበት ማልደው የመጡት ታላቅ ወንድሟ
ወልደልዑል፣ አጎቷ አርከሌድስ፣ የዮልያና ወንድም ኒቆላዎስ፣ አጎቷ
እሽቴና የአጎቷ ልጆች አውሳቢዮስ፣ ጌታና ነጮ በኩራት ተመለከቷት።
ንጉሥ ቤት ነውና የምትገባው በልባቸው ዙርያ የተስፋ ድር አደራችበት።
እናትና ልጅ በሠሩት ጥበብ ተደንቀው ዐይን ለዐይን ተያዩ።
አያትየዋ ያ ሁሉ እንባ ምልክት ስንኳ አልተወም፡፡ ድንቅ እኒያ
ደርሰው ትከሻ ሚሰጡ የጐንደር ወይዛዝርት እንግዲኽ ዐይናቸው
ይደፍርስ አሉ።
ለሱ አይቅርበት አሉ እናትየው፣ እንባቸውን በነጠላቸው እየጠራረጉ።
ጎረቤትና ቤተዘመድ ምርቃት ሲያዘንብላት፣ ዕልል ሲልላት፣ ጓደኞቿ የደስታ እንባ ሲራጩላት፣ ምቀኛው ግን፣ “ታመው የተኙ ግዝየ መዳኒት አርጋባቸው እንደሁ እንጂ ውነት አሁን ንጉሡ…” እያለ ወሻከተ።
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...እንዲህ እንዳይመስሉሽ። ኸግር እስተራስሽ እያገላበጡ ነው ሚያዩሽ።ቄንጥ ሲያወጡ አይጣል ነው” ሲሉ መከሯት።
“እሚታዬ ልቤ ፈራ” አለቻቸው፣ እጆቿን እያፍተለተለች።
“ምን ሚያስፈራ ነገር አለ?” አሉ፣ ቆጣ ብለው። ለራሳቸው፣ እንደዛ
ቆፍጣና ምትመስለኝ ልዥ ምን ሆነች? ማታውቀው ቦታ ስለምትኸድ ነው? አሉና ለእሷ፣ “አብሬሽ ማዶል እንዴ ምመጣው? ንጉሥ የሆኑ እንደሁ ልዣችንን እንዳው ዝም ብለን ምንሰድ ይመስልሻል? ጐንደርንም ቢሆን አገላብጨ ነው ማውቃት። ጃንሆይ ሳይነግሡ በፊት... ነፍሳቸውን ይማርና ኸነእንኰዬ አባት ጋር ኑረናል። ጃንሆይ ኸነገሡ በኋላ አልኸድኹም እንጂ” አሏት።
“አብረሽኝ ምትመጪ ባትኾኚ ምን ይውጠኝ ኑሯል?” ብላ፣አንገታቸው ሥር ገብታ ሳይታሰብ ተንሰቀሰቀች። ውስጥ ውስጡን
ያስለቀሳት ግን ከጥላዬ መለያየቷ ነው።
“ደሞ ለክፉ ሆነ ለደግ ግዝየ ሚሆን ወልደልዑልን የመሰለ ወንድም አለሽ። ስንኳን ላንቺ ለእህቱ፣ አላየሽም እንዴ ላገር ሲተርፍ? አርከሌድስም አለ። ልዤ ነው ብዬ ማዶል ። አንቺም ብትሆኚ ታውቂያሽ እንዴት ብርቱና ታማኝ እንደሆነ። እንደ ኒቆላዎስስ ቢሆን... ጋሻና መከታ እንደሚሆንሽ አንቺም ታቂያለሽ” አሉ፡ ደረታቸውን መታ፣ አንገታቸውን ነቀነቅ አድርገው።
ምንጊዜም ቢሆን ስለሚወዱት ታናሽ ወንድማቸው ስለኒቆላዎስ
ሲያወሩ ደስ ይላቸዋል፤ ይኮሩበታል ። ቀጠለና፣ “አጎትሽ እሽቴም አለ። ደሞስ ያጎቶችሽ ልዦች ጌታ፣ አውሳቢዮስና፣ ነጮ አሉ ማዶል እንዴ? የወገን ጥላ አያሳጣኝ ማለት ነው” እያሉ እንባዋን በነጠላቸው ከፊቷ
ላይ ጠራረጉላት።
“ግና የቤተመንግሥት ወግ ኸየት አባቴ አውቄ?” አለች።
“አንቺ ደሞ ያልቸገረሽን። ወጉንስ እኼው እያስተማርሁ ማዶል
እንዴ? ሌላውን ደሞ ግዝየው ሲደርስ ትማሪያለሽ።”
“እሚታዬ፣ ቤተመንግሥት ልገባ?”
“ቤተመንግሥት ለመግባት ምን ያንስሻል? አጥንተ ጥሩ... ያውስ
የንጉሥ ዘር ማዶለሽ? አባትሽስ ቢሆኑ የደንብያው ባላባት የአቤቴ
ተክለሃይማኖት ልዥ ማዶለ? መልክስ ቢሆን ማን ደረሰብሽ? ቀይ ሰው መልክ አይፈጅም ይላሉ፤ አንቺ ፈጅተሻል። ቅላትሽ እኮ የኔና የናትሽ ነው። እንዳባትሽ ጠይም ብትሆኚ ኑሮኮ ምን የመሰለች ጠይም አሳ መሳይ ትሆኚ ነበር። ምግባርና ብሩህ አይምሮም አክሎልሻል።
ለዝህም እኮ ነው ጃንሆይ የመረጡሽ። እቴ ኸንግዲህ ማቄን ጨርቄን የለም፤ መኸድ ብቻ ነው።”
“ልጄ ዕድል ነው። ተሰጥቶሽ ነው። ደግ ሁኖልሻል፤ ሁሉን
አብዝቶልሻል” አሏት፣ እስከዛ ድረስ እናታቸው የሚሉትንና
የሚያደርጉትን በፀጥታ ሲታዘቡ የቆዩት እናቷ።
“የምን ዕድል ነው ምትይ? ዕድል ከሰማይ ይወድቃል? እንዲሁ
ነው እንዴ ንጉሡ ልዣችንን ሊያገቡ የፈለጉ? ልዣችን ሚገባትን ነው ያገኘችው። በደም ግባቷ፣ በብሩህ አይምሮዋ፣ በመልካም ምግባሯና
ጎንበስ ቀና ብላ ስላስታመመቻቸው ነው ንጉሡ ለንግሥትነት የመረጧት፣ ንግሥትነት እንደሚገባት አይተው መዝነው ነው እንጂ እንደ መደዴው ለውበቷ ወይም እንደገበሬ ለሙያዋ ብቻ ብለው
አይደለም።” ዮልያና ልጃቸውን ቆጣ አሉ።
“መቸም ደመ ግቡ ሁሉ... ያስታመመ ሁሉ ንጉሥ ባል አያገኝም። እንዳው የዕድል ነገር ይገርማል። እኼን ማን አሰበው?” አሉ፣ የእናታቸውን አፍ ብዙም የማይዳፈሩት ወይዘሮ እንኰዬ።
“የኔ ልዥ ገና ንግሥት እሌኒን አረግሻለሁ” አሉ፣ አያትየው።
“እሳቸውን መሆን እንዴት ይቻለኛል?”
“አንቺ ደሞ... እሌኒን ትሆኛለሽ ስልሽ እኮ ልክ እንደሳቸው ሁኚ
ማለቴም ማዶል። እንዴት እንደምኖሪ ማወቅ ያንቺ ፈንታ ነው። ሁሉ እየቅል ነው።”
ለጊዜው የአያቷ ምክር በመጠኑም ቢሆን አረጋጋት።
በነጋታው መንገደኛ ናትና ጥሩ እንቅልፍ እንድታገኝ እናትና አያት
ትኩስ ወተት በማር አጠጥተው አስተኟት። እሷ ግን እንደ ትናንቱ
ሁሉ ዛሬም እንቅልፍ በዐይኗ ሳያልፍ ፍርሐት፣ ጥላዬን ለመጨረሻ ጊዜ ሳታየው የመሄድ ጭንቀት፣ ብሎም ቀስ እያለ ውስጧ እየተጫረ የመጣው ቤተመንግሥት የመግባት ጉጉት መሳይ ነገር ሲፈራረቁባት
ሌሊቱ እንደመንጋት አለ።
ዶሮ ሲጮህ ቀሰቀሷትና ተጣጠበች። ቁርስ ብዪ ብለው ሲያቀርቡላት ግን ተናነቃት። እናቷ፣ “ትንሽ አፍሽ አርጊ፤ ምንገድ ባዶ አፍ አይከድም” እያሉ ሊያግባቧት ሞከሩ። እሷ ግን እንኳን እናቷን፣
አባቷን፣ ወንድሟን፣ ጥላዬንና የቤት አገልጋዮቹን ቋራን ራሱን ጥላ መሄዱ ዳገት ሆነባት።
ዐይኗ እንባ አቀረረ።
የእናቷን ፊት የተጫጫነውን ሐዘን ስታይ፣ ዐይኖቿ ጥግ ተጠልሎ
የነበረው እንባዋ ወደ ጉንጮቿ ኮለል አለ። እናቷ እስከዛ ሰዐት አምቀውት የነበረውን እንባ እንደ ድንገተኛ ዝናብ አወረዱት። ጉልበታቸው ላይ ተደፍታ፣ “እነየ መተሽ አታይኝም?” ስትላቸው፣ ትከሻዋ ላይ ተደፍተው
እዬዬ ሲሉ እሷም ስቅስቅ ብላ አለቀሰች።
አያትየው ልጃቸውን፣ “እንደማበርታት ጭራሽ ታባቢያታለሽ?” ብለው ቆጣ አሉና፣ ወለተጊዮርጊስን ትከሻዋን ነካ አድርገው፣ “ተይ እኮ የኔ ልዥ፣ በቅጡ እንዳልተኛሽ ስንኳ ያስታውቃል። ምንገደኛ ነሽ። ገና
ምንገዱ ሚያጠወልግሽ ይበቃል። ፊትሽን አታበላሺ። የቀባሁሽንም
ኩል እንባሽ አጠበው። በቃ እንድች ብለሽ እንዳታለቅሺ። በይ ነይ” አሉና ፊቷን በእጃቸው አባብሰው፣ እንደገና ሥር ኩል ዐይኗ ላይ አደረጉላት።
እንግዶቹ እህል አፋቸው ካደረጉ በኋላ፣ ለመሄድ ወደ ውጭ ሲወጡ በአቅራቢያ ያለ ቤተዘመድ፣ የወለተጊዮርጊስን ጐንደር መሄድ የሰማ
ጎረቤትና ጓደኞቿ ተሰብስበዋል። ወለተጊዮርጊስ የአያቷን ረጅም የሐር ቀሚስ ለብሳ፣ ከቀሚሱ ሥር በሐር ክር ጫፉ የተጠለፈና ተረከዟን ጠበቅ አድርጎ የያዘ ሱሪ ታጥቃ፣ በአያቷ ወርቅ አሸግና ብቅ ስትል፣እንግዶቹ ትንግርት እንጂ እውን ሰው የሚያዩ አልመስል አላቸው።
ዘመድና ጎረቤት ግቢውን በዕልልታ ሲያደምቀው፣ የወለተጊዮርጊስ ጓደኞች ዐይናቸው እያየ በጓደኛቸው ሕይወት ውስጥ ያልገመቱት
ዓይነት ለውጥ መምጣቱ፣ ካጠገባቸው ተነስታ ለንግሥትነት መታጨቷ አስደነቃቸው። በዓመት መለወጫ ቀን አደይ አበባ እያስቀጠፈች፣ከቤት ቤት በድፍረት ይዛቸው እየዞረች፣ የምታስተባብራቸውና እንደ
መሪያቸው የሚቆጥሯት ጓደኛቸው ከመሃከላቸው በመለየቷ አዘኑ፤
በታላቁ ዕድሏ ቀኑ፣ ተደሰቱ። በዚኹም ድብልቅልቅ ስሜት መሃል ግን በመለያየታቸው አለቀሱ።
ግራዝማች የልጃቸውን ውበት ገና ያን ቀን ያዩ ይመስል ዐይናቸው
ውሃ አቆረ። እሷን ለመሰናበት ማልደው የመጡት ታላቅ ወንድሟ
ወልደልዑል፣ አጎቷ አርከሌድስ፣ የዮልያና ወንድም ኒቆላዎስ፣ አጎቷ
እሽቴና የአጎቷ ልጆች አውሳቢዮስ፣ ጌታና ነጮ በኩራት ተመለከቷት።
ንጉሥ ቤት ነውና የምትገባው በልባቸው ዙርያ የተስፋ ድር አደራችበት።
እናትና ልጅ በሠሩት ጥበብ ተደንቀው ዐይን ለዐይን ተያዩ።
አያትየዋ ያ ሁሉ እንባ ምልክት ስንኳ አልተወም፡፡ ድንቅ እኒያ
ደርሰው ትከሻ ሚሰጡ የጐንደር ወይዛዝርት እንግዲኽ ዐይናቸው
ይደፍርስ አሉ።
ለሱ አይቅርበት አሉ እናትየው፣ እንባቸውን በነጠላቸው እየጠራረጉ።
ጎረቤትና ቤተዘመድ ምርቃት ሲያዘንብላት፣ ዕልል ሲልላት፣ ጓደኞቿ የደስታ እንባ ሲራጩላት፣ ምቀኛው ግን፣ “ታመው የተኙ ግዝየ መዳኒት አርጋባቸው እንደሁ እንጂ ውነት አሁን ንጉሡ…” እያለ ወሻከተ።
👍11❤1
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ባህራም
ከቅርብ
ማክሰኞ ነበር አስታውሳለሁ፡፡ ከምሳ በኋላ Le Monde ጋዜጣዬን ገዝቼ ካፌ ዶርቢቴል ገብቼ እንደ ልማዴ petit creme አዝዤ ካርታ የሚጫወቱት ሀበሾች አጠገብ ቁጭ አልኩ። ትንሽ ቆይቶ ባህራም መጣ፡፡ ሳየው የተለወጠ መሰለኝ፡፡ ልማዱ በፍጥነት እርምጃው ከተፍ ብሎ ሲያበቃ፣ ሀበሾቹን «እናትክን! ሀለላሴ ሙት! Je veux jouer
aux cartes.» («ካርታ አጫውቱኝ») ብሎ ቁጭ ማለት ነበር፡፡ ዛሬ ግን በቀስታ እርምጃ መጣ። እንደ ድሮው አልቀለደም፡፡ እንደ አጋጣሚ ለካርታ ጨዋታው አንድ ሰው ጎድሏቸው ስለነበረ «ባህራም! ና ካርታ እንጫወት አሉት
«ካርታ ጨዋታ አላሰኘኝም» አለና ዝም ብሎ ቁጭ አለ።
የተበሳጨ ይመስላል
«ምን ሆነሀል?» አለው ሉልሰገድ
«በፈተና ወደቅኩ» አለ
ሁሉም የሚሉትን አጡ
እንግዲህ በፈረንሳይ ዩኒቨርሲቲዎች ደምብ፣ አንድ ተማሪ የሰኔ ወር ፈተናውን የወደቀ እንደሆነ በእረፍት ጊዜው ሲያጠና
ይከርምና፣ በጥቅምት (ትምህርት ቤት ሲከፈት) እንደገና
ይፈተናል። ስለዚህ ተመስገን
«አይዞህ በጥቅምት ፈተና ታልፋለህ» አለው ባህራም አልተፅናናም፡፡ ሁሉም ዝም አሉ። ካርታ ጨዋታቸውን ቀጠሉ።
ባህራም «ዘላለም ካርታ ጨዋታ ምን ያረጋል? እንውጣ ትንሽ
እንንሽርሽር» አለ። ማንም መልስ አልሰጠውም፡፡አብረውት
መውጣት ፈርተዋል። ካርታ ጨዋታቸውን ቀጠሉ ለጨዋታው
ብቻ ሳይሆን ከባህራም ብስጭት ለማምለጥም ጭምር። ገባው::
ተነስቶ ብቻውን ወጣ፡፡ ተከትዬው ወጣሁ። ወደ መናፈሻው በኩል
እያመለከትኩ
«ወደዚያ እንሂድ?» አልኩት፡፡ መልስ ሳይሰጠኝ ወደዚያው
አመራ። ትንሽ እንደተራመድን
«ያውና ተካ። ወደኛ በኩል ይመጣል» አለኝ «አደራህን አብሮን እንዳይመጣ። ዛሬ እሱ ሁለት ቃላት ቢያናግረኝ አብዳለሁ»
«አትስጋ» አልኩት
ተካ አቆመንና በፈረንሳይኛ
«ከየት ነው የምትመጡት?» አለን
«አሁን ከየትም ብንመጣ ደንታ የለህ። ለምንድነው የምትጠ
ይቀን?» አልኩት በአማርኛ
«ከዶርቢቴል ነው የምትመጡት?» አለኝ ባማርኛ
«አዎን» አልኩት ባህራም እጁን ኪሱ ከቶ ወደዚያ ይመለከታል
«ወዴት ነው የምትሄዱት?» አለኝ ተካ
«ወዴትም፡፡ ምን ያረግልሀል?»
«ወደ ሲቴ ነው የምትሄዱት?»
«ምነው? ከኛ ጋር ሲቴ መሄድ አማረህ?»
«አይ! እኔ ለራሴ ከዛ መምጣቴ ነው። ቡና አምሮኛል»
«እንግዲያው ሂድና ቡናህን ጠጣ»
«ጋዜጣህን አሁን አታነበው እንደሆነ ስጠኝ»
ጋዜጣዬን ሰጠሁትና መንገዳችንን ልንቀጥል ስንል
«ይሄ አቃጣሪ ገንዘብ እንዳያጭበረብርህ ተጠንቀቅ» አለኝ
«ሂድ ቡናህን ጠጣ» እልኩት። ሄደ
እኔና ባህራም አንድ ቃል ሳንነጋገር መናፈሻው ደረስን፡፡ ዛፎች
ጥላ ስር አንድ አግድም ወምበር ላይ ቁጭ አልን ፈተና መውደቅ የተለመደ ነገር ነው:: በጥቅምት ታልፋለህ» አልኩት
በተገማመደ ፈረንሳይኛው፣ በወፍራም ልዝብ ድምፁ መናገር
ጀመረ መውደቄ አይደለም የሚያበሳጨኝ፣ አወዳደቄ ነው።
ትምህርቱን በደምብ ይዤዋለሁ። በምን እንደጣሉኝ ታውቃለህ?
በፈረንሳይኛዬ ጉድለት: አያስቅህም? ፈተናውን የወደቅኩት እኔ ራሴ ባልሆን ያስቀኝ ነበር
«እኔንና ፈረንሳዮቹን የክፍሌን ልጆች አስተያየን እስቲ፡፡
ትምህርቱን እኩል እናጠናቀው። ፈተና እንግባና ጥያቄው ይሰጠን።
መልሱን እኔም እነሱም እኩል እንወቀው። እነሱ ምን ያረጋሉ?
መልሱን በፍጥነት ይፅፋሉ፡ አሰካኩንና አገባቡን ያማርጣሉ፡፡
ጥቃቅኗን ነገር ጭምር ያስገቧታል፡፡ ሀያ ሀያ አንድ ገፅ ፅፈው ይወጣሉ፡፡ ያልፋሉ፡፡ እኔም መልሱን ከነሱ እኩል አውቀዋለሁ፡፡
ታድያ ፈረንሳይኛው ከየት ይምጣ? ከሱ ጋር ስታገል የጊዜዬን
ግማሽ አጠፋለሁ:: ለዚያውም አምጩ የማመጣው ፈረንሳይኛ አንካሳ ሽባ ስለሆነ፣ በደምብ የማውቀውን መልስ ልክ እንደማላውቀውና
በግምት ወይም በነሲብ እንዳገኘሁት ያስመስልብኛል። ዘጠኝ አስር ገፅ ፅፌ እወጣለሁ፣ በመጥፎ ፈረንሳይኛ፡፡ ትምህርቱን እያወቅኩት ፈተናውን እወድቃለሁ
«ፈረንሳዮች ደሞ ታውቃቸዋለህ። በቋንቋቸው የመጣ በጣም
አንጎለ ጠባብ ናቸው። ለምሳሌ አስተውለህ እንደሆነ በፍጥነትና ያለ ስህተት ያነጋገርካቸው እንደሆነ ያከብሩሀል፣ «Intelligentይሉሀል።
እየተንተባተብክ ያነጋገርካቸው እንደሆነ ግን ምንም ቁም ነገር
ብትናገር መሃይም ነህ ማለት ነው። በቋንቋህ ብታናግራቸው እንደ ቂል አፋቸውን ከፍተው እንደሚቀሩና፣ የነሱም ቋንቋ ላንተ ያንን ያህል እንግዳ እንደነበረ፣ የሚሉት ሁሉ «ዠቨሹቪ» ይመስልህ እንደነበረ፣ በስንት ልፋት በመጠኑ ልታውቀው እንደቻልክ፣ በቋንቋቸው መንተባተብ ስለቻልክም ሊያመሰግኑህ እንጂ ሊንቁህ
እንደማይገባቸው፣ ይህን ለመገመት ያህል ሰፊ አንጎል የላቸውም።ተራውስ ሰው እንዲህ ቢሆን አልፈርድበትም፡፡ የዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰሮቹ እንዲህ ሲሆኑ ግን በጭራሽ አይገባኝም፡፡ እንግዲያውኑ የነሱ ትምህርት የታል? እቺን ያህል ቀላል ነገር ማመዛዘን ካልቻሉ አንጎላቸውስ ትምህርታቸውስ ምን ትርጉም ይኖረዋል?
«እማናውቀው አገር መጥተን፣ በማናውቀው ቋንቋ
የማናውቀውን ህዝብ ባህልና ታሪክ ለመማር ስንታገል፣ ለምን
አስተያየት አያደርጉልንም?»
“ምን አይነት አስተያየት ሊያደርጉልን ይችላሉ?» አልኩት
«ፈረንሳይኛችን ትንሽ የተጣመመ እንደሆነ፣ የቋንቋውን መጣመም ችላ ብለው የፍሬ ነገሩን እዚያ መገኘት ለምን አያስቡልንም? አገራችን ስንመለስ በራሳችን ቋንቋ ነው የምንmቅመው፣ ስለዚህ ፈረንሳይኛውን አንደነሱ ቻልነው በመጠኑ ተንተባተብንበትስ ምን ያህል ልዩነት ያመጣል? እንግዳ ስንሆን፣ ፈረንሳይኛውን በሀያ ሶስት፣ በሀያ አራት፣ በሀያ አምስት
አመታችን ስንጀምረው፣ እንዴት ከናታቸው ጡት ጋር ሲጠቡት
ካደጉ ሰዎች እኩል ካልሆነ ተብለን እንቀጣበታለን? ቅጣት መሆኑ
ይታይሀል? ፍሬ ነገሩን እንደማውቀው ግልፅ ሳለ፣ የተጠቀምኩበት ፈረንሳይኛ የተቀመመ ፈረንሳይኛ ባለመሆኑ ፈተናዬን ስወድቅ፣አንድ አመት ሙሉ የለፋሁበትን ስከለከል፣ ይሄ ቅጣት ነው እንጂ ምንድነው? ፍትህ የሌለው ቅጣት
«አንድ አመት ምን ያህል እንደሆነ ይገባሀል? አስበው፡፡ የዘጠኝ
የአስር አመት ልጆች ሳለን ክፍል በመድገም አንድ አመት ብናጠፉ
ምንም አይደለም፡፡ በህያ ስድስት፣ በሀያ ሰባት አመታችን አንድ
አመት ማጥፋት ግን ሌላ ነገር ነው:: ምክንያቱም እነዚህ አመታት
ከሀያ አምስት እስከ ሰላሳ አምስት ሰፈር ያሉት አመታት የሌሎቹን አመታት ሶስት አራት እጥፍ ዋጋ አላቸው። አሁን ነው ህይወታችንን ለመጨረሻ የምንቀርፀው:: አሁን ነው ያለ የሌለንን ለሀገራችን ልናበረክትላት የሚገባን። አሁን ነው የኑሮ ስራችንን የምንመርጥበት የምንጀምርበት ጊዜ። አሁን ነው የኑሮ ጓደኛችንን
የምንመርጥበት፣ ትዳራችንን የምንቆረቁርበት ጊዜ፡፡ አሁን ነው።
አሁን! አሁን! አሁን ነው ልጅነትም የማያታልለን፣ እርጅናም የማይ
ጫጫነን፡፡ አሁን ነው ፍሬ ለመስጠት ዋጋ ለማስገኘት የምንችለው» ረጋ ባለ ድምፅ
«አሁን ነው ፈረንሳዮች "ለምን ቋንቋችንን ከኛ እኩል
አልቻላችሁም?' ብለው ወርቅማ አመታችንን የሚያጠፉብን
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ባህራም
ከቅርብ
ማክሰኞ ነበር አስታውሳለሁ፡፡ ከምሳ በኋላ Le Monde ጋዜጣዬን ገዝቼ ካፌ ዶርቢቴል ገብቼ እንደ ልማዴ petit creme አዝዤ ካርታ የሚጫወቱት ሀበሾች አጠገብ ቁጭ አልኩ። ትንሽ ቆይቶ ባህራም መጣ፡፡ ሳየው የተለወጠ መሰለኝ፡፡ ልማዱ በፍጥነት እርምጃው ከተፍ ብሎ ሲያበቃ፣ ሀበሾቹን «እናትክን! ሀለላሴ ሙት! Je veux jouer
aux cartes.» («ካርታ አጫውቱኝ») ብሎ ቁጭ ማለት ነበር፡፡ ዛሬ ግን በቀስታ እርምጃ መጣ። እንደ ድሮው አልቀለደም፡፡ እንደ አጋጣሚ ለካርታ ጨዋታው አንድ ሰው ጎድሏቸው ስለነበረ «ባህራም! ና ካርታ እንጫወት አሉት
«ካርታ ጨዋታ አላሰኘኝም» አለና ዝም ብሎ ቁጭ አለ።
የተበሳጨ ይመስላል
«ምን ሆነሀል?» አለው ሉልሰገድ
«በፈተና ወደቅኩ» አለ
ሁሉም የሚሉትን አጡ
እንግዲህ በፈረንሳይ ዩኒቨርሲቲዎች ደምብ፣ አንድ ተማሪ የሰኔ ወር ፈተናውን የወደቀ እንደሆነ በእረፍት ጊዜው ሲያጠና
ይከርምና፣ በጥቅምት (ትምህርት ቤት ሲከፈት) እንደገና
ይፈተናል። ስለዚህ ተመስገን
«አይዞህ በጥቅምት ፈተና ታልፋለህ» አለው ባህራም አልተፅናናም፡፡ ሁሉም ዝም አሉ። ካርታ ጨዋታቸውን ቀጠሉ።
ባህራም «ዘላለም ካርታ ጨዋታ ምን ያረጋል? እንውጣ ትንሽ
እንንሽርሽር» አለ። ማንም መልስ አልሰጠውም፡፡አብረውት
መውጣት ፈርተዋል። ካርታ ጨዋታቸውን ቀጠሉ ለጨዋታው
ብቻ ሳይሆን ከባህራም ብስጭት ለማምለጥም ጭምር። ገባው::
ተነስቶ ብቻውን ወጣ፡፡ ተከትዬው ወጣሁ። ወደ መናፈሻው በኩል
እያመለከትኩ
«ወደዚያ እንሂድ?» አልኩት፡፡ መልስ ሳይሰጠኝ ወደዚያው
አመራ። ትንሽ እንደተራመድን
«ያውና ተካ። ወደኛ በኩል ይመጣል» አለኝ «አደራህን አብሮን እንዳይመጣ። ዛሬ እሱ ሁለት ቃላት ቢያናግረኝ አብዳለሁ»
«አትስጋ» አልኩት
ተካ አቆመንና በፈረንሳይኛ
«ከየት ነው የምትመጡት?» አለን
«አሁን ከየትም ብንመጣ ደንታ የለህ። ለምንድነው የምትጠ
ይቀን?» አልኩት በአማርኛ
«ከዶርቢቴል ነው የምትመጡት?» አለኝ ባማርኛ
«አዎን» አልኩት ባህራም እጁን ኪሱ ከቶ ወደዚያ ይመለከታል
«ወዴት ነው የምትሄዱት?» አለኝ ተካ
«ወዴትም፡፡ ምን ያረግልሀል?»
«ወደ ሲቴ ነው የምትሄዱት?»
«ምነው? ከኛ ጋር ሲቴ መሄድ አማረህ?»
«አይ! እኔ ለራሴ ከዛ መምጣቴ ነው። ቡና አምሮኛል»
«እንግዲያው ሂድና ቡናህን ጠጣ»
«ጋዜጣህን አሁን አታነበው እንደሆነ ስጠኝ»
ጋዜጣዬን ሰጠሁትና መንገዳችንን ልንቀጥል ስንል
«ይሄ አቃጣሪ ገንዘብ እንዳያጭበረብርህ ተጠንቀቅ» አለኝ
«ሂድ ቡናህን ጠጣ» እልኩት። ሄደ
እኔና ባህራም አንድ ቃል ሳንነጋገር መናፈሻው ደረስን፡፡ ዛፎች
ጥላ ስር አንድ አግድም ወምበር ላይ ቁጭ አልን ፈተና መውደቅ የተለመደ ነገር ነው:: በጥቅምት ታልፋለህ» አልኩት
በተገማመደ ፈረንሳይኛው፣ በወፍራም ልዝብ ድምፁ መናገር
ጀመረ መውደቄ አይደለም የሚያበሳጨኝ፣ አወዳደቄ ነው።
ትምህርቱን በደምብ ይዤዋለሁ። በምን እንደጣሉኝ ታውቃለህ?
በፈረንሳይኛዬ ጉድለት: አያስቅህም? ፈተናውን የወደቅኩት እኔ ራሴ ባልሆን ያስቀኝ ነበር
«እኔንና ፈረንሳዮቹን የክፍሌን ልጆች አስተያየን እስቲ፡፡
ትምህርቱን እኩል እናጠናቀው። ፈተና እንግባና ጥያቄው ይሰጠን።
መልሱን እኔም እነሱም እኩል እንወቀው። እነሱ ምን ያረጋሉ?
መልሱን በፍጥነት ይፅፋሉ፡ አሰካኩንና አገባቡን ያማርጣሉ፡፡
ጥቃቅኗን ነገር ጭምር ያስገቧታል፡፡ ሀያ ሀያ አንድ ገፅ ፅፈው ይወጣሉ፡፡ ያልፋሉ፡፡ እኔም መልሱን ከነሱ እኩል አውቀዋለሁ፡፡
ታድያ ፈረንሳይኛው ከየት ይምጣ? ከሱ ጋር ስታገል የጊዜዬን
ግማሽ አጠፋለሁ:: ለዚያውም አምጩ የማመጣው ፈረንሳይኛ አንካሳ ሽባ ስለሆነ፣ በደምብ የማውቀውን መልስ ልክ እንደማላውቀውና
በግምት ወይም በነሲብ እንዳገኘሁት ያስመስልብኛል። ዘጠኝ አስር ገፅ ፅፌ እወጣለሁ፣ በመጥፎ ፈረንሳይኛ፡፡ ትምህርቱን እያወቅኩት ፈተናውን እወድቃለሁ
«ፈረንሳዮች ደሞ ታውቃቸዋለህ። በቋንቋቸው የመጣ በጣም
አንጎለ ጠባብ ናቸው። ለምሳሌ አስተውለህ እንደሆነ በፍጥነትና ያለ ስህተት ያነጋገርካቸው እንደሆነ ያከብሩሀል፣ «Intelligentይሉሀል።
እየተንተባተብክ ያነጋገርካቸው እንደሆነ ግን ምንም ቁም ነገር
ብትናገር መሃይም ነህ ማለት ነው። በቋንቋህ ብታናግራቸው እንደ ቂል አፋቸውን ከፍተው እንደሚቀሩና፣ የነሱም ቋንቋ ላንተ ያንን ያህል እንግዳ እንደነበረ፣ የሚሉት ሁሉ «ዠቨሹቪ» ይመስልህ እንደነበረ፣ በስንት ልፋት በመጠኑ ልታውቀው እንደቻልክ፣ በቋንቋቸው መንተባተብ ስለቻልክም ሊያመሰግኑህ እንጂ ሊንቁህ
እንደማይገባቸው፣ ይህን ለመገመት ያህል ሰፊ አንጎል የላቸውም።ተራውስ ሰው እንዲህ ቢሆን አልፈርድበትም፡፡ የዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰሮቹ እንዲህ ሲሆኑ ግን በጭራሽ አይገባኝም፡፡ እንግዲያውኑ የነሱ ትምህርት የታል? እቺን ያህል ቀላል ነገር ማመዛዘን ካልቻሉ አንጎላቸውስ ትምህርታቸውስ ምን ትርጉም ይኖረዋል?
«እማናውቀው አገር መጥተን፣ በማናውቀው ቋንቋ
የማናውቀውን ህዝብ ባህልና ታሪክ ለመማር ስንታገል፣ ለምን
አስተያየት አያደርጉልንም?»
“ምን አይነት አስተያየት ሊያደርጉልን ይችላሉ?» አልኩት
«ፈረንሳይኛችን ትንሽ የተጣመመ እንደሆነ፣ የቋንቋውን መጣመም ችላ ብለው የፍሬ ነገሩን እዚያ መገኘት ለምን አያስቡልንም? አገራችን ስንመለስ በራሳችን ቋንቋ ነው የምንmቅመው፣ ስለዚህ ፈረንሳይኛውን አንደነሱ ቻልነው በመጠኑ ተንተባተብንበትስ ምን ያህል ልዩነት ያመጣል? እንግዳ ስንሆን፣ ፈረንሳይኛውን በሀያ ሶስት፣ በሀያ አራት፣ በሀያ አምስት
አመታችን ስንጀምረው፣ እንዴት ከናታቸው ጡት ጋር ሲጠቡት
ካደጉ ሰዎች እኩል ካልሆነ ተብለን እንቀጣበታለን? ቅጣት መሆኑ
ይታይሀል? ፍሬ ነገሩን እንደማውቀው ግልፅ ሳለ፣ የተጠቀምኩበት ፈረንሳይኛ የተቀመመ ፈረንሳይኛ ባለመሆኑ ፈተናዬን ስወድቅ፣አንድ አመት ሙሉ የለፋሁበትን ስከለከል፣ ይሄ ቅጣት ነው እንጂ ምንድነው? ፍትህ የሌለው ቅጣት
«አንድ አመት ምን ያህል እንደሆነ ይገባሀል? አስበው፡፡ የዘጠኝ
የአስር አመት ልጆች ሳለን ክፍል በመድገም አንድ አመት ብናጠፉ
ምንም አይደለም፡፡ በህያ ስድስት፣ በሀያ ሰባት አመታችን አንድ
አመት ማጥፋት ግን ሌላ ነገር ነው:: ምክንያቱም እነዚህ አመታት
ከሀያ አምስት እስከ ሰላሳ አምስት ሰፈር ያሉት አመታት የሌሎቹን አመታት ሶስት አራት እጥፍ ዋጋ አላቸው። አሁን ነው ህይወታችንን ለመጨረሻ የምንቀርፀው:: አሁን ነው ያለ የሌለንን ለሀገራችን ልናበረክትላት የሚገባን። አሁን ነው የኑሮ ስራችንን የምንመርጥበት የምንጀምርበት ጊዜ። አሁን ነው የኑሮ ጓደኛችንን
የምንመርጥበት፣ ትዳራችንን የምንቆረቁርበት ጊዜ፡፡ አሁን ነው።
አሁን! አሁን! አሁን ነው ልጅነትም የማያታልለን፣ እርጅናም የማይ
ጫጫነን፡፡ አሁን ነው ፍሬ ለመስጠት ዋጋ ለማስገኘት የምንችለው» ረጋ ባለ ድምፅ
«አሁን ነው ፈረንሳዮች "ለምን ቋንቋችንን ከኛ እኩል
አልቻላችሁም?' ብለው ወርቅማ አመታችንን የሚያጠፉብን
👍17❤5😁1