አትሮኖስ
286K subscribers
117 photos
3 videos
41 files
565 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ትኩሳት


#ክፍል_ሁለት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

#እንደወረደ_ነውና_ለአንባቢ
#የማይመቹ_እኛ_ፀያፍ_የምንላቸው
#ቃላቶች_አሉትና_አሁንም
#በድጋሚ_እንደምናገረው
#የማይመቸው_እንዳታነቡት
#እመክራለሁ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አማንዳ
ለጥቂት ጊዜ


ያን ሰሞን አንዲት ቆንጆ አሜሪካዊት ነበረችኝ፣ አይኗ
ሰማያዊ፣ ፀጉሯ በጣም ንፁህ ቡና አይነት፡፡ እጅግ ደስ ትላለች፣
አልጋ ውስጥ ልብ ታጠፋለች ግን በማልፈልጋት ሰአት ሆቴሌ
እየመጣች አላሰራ ስላለችኝ፤ ቤተ መፃህፍት እየሄድኩ መስራት ግድ
ሆነብኝ፡፡ ሆቴሌ ስታጣኝ ወደ ቤተ መፃህፍቱ መምጣት ጀመረች።

እሷን ለመሸሽና በዚያውም ባህራምን ለማወቅ ስል ሀበሾቹን
እጠጋቸው ጀመር ምግብ ቤት አብሬያቸው እገባለሁ፣ ካፌ
ዶርቢቴል አብሬያቸው ካርታ እጫወታለሁ ከባህራም ጋር ግን ላይ ላዩን እየቀለዱ ለመሳቅ እንጂ፣ የልብ ለመጫወት አጋጣሚ ለጊዜው አላገኘሁም። ይልቅስ ከሀበሾቹ ጋር ግንኙነት በማድረጌ «ሚስቶቻቸውን» በመጠኑ እያወቅኳቸው ሄድኩ፡፡

የነበርንበት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሴቶች ከወንዶቹ በጣም ይበዛሉ፡፡
ስለዚህ ለሁሉ ሴት 'ሚዳረስ ወንድ የለም....አሉ ሶስት፣ አራት፣
አምስት 'የሆኑ ወንድ 'ሚያድኑ ልጃገረዶች። ታድያ ወንዱን ቆንጆ
ቆንጆዎቹ ይዘውታል፣ ተጠምጥመውበታል። ነፃ የሆነ ወንድ አይገኝም፣ ቢገኝም ወይ የደስ ደስ የለውም፣ ወይ ጥቁር ነው። ጥቁር ደሞ ምን ቢወዱት አገሩ መመለሱ አይቀርም፡፡ ብልጥ ወይም ውብ ወይም እድለኛ ካልሆኑ፣ ፈረንሳይ ወንድ ማግኘት አይቻልም። ሳያገቡ የማርጀት ፍርሀት በወራቱ ዋሻ ሰአመታቱ ጫካ አድፍጦ
ይጠብቃል.

ጥቁሮቹ ወንዶች ገና እንደመጡ፣ በንግድነት ምክንያት ቆንጆ
ሴት ማጥመዱን ለጊዜው ስለማያውቁበት፣ የተገኘችውን እሺ ብለው ይቀበላሉ። የምትገኘው ደሞ ቆንጆ ያልሆነች ናት፣ ስለዚህ ማቆያ
ናት...

«የሀበሾቹ ሚስቶች» ጎደሎ ብጤዎች ነበሩ፡- እዚህ ቅርፅ
ይጎድሳል፣ እዚያ ድምፅ ይጎድላል፣ እዚያ ጠባይ ይጎድሳል። ብቻ፣ሉልሰገድ እንዳለኝ ሁሉም ያ ነገር ኣላቸው ለጊዜው ሀበሾቹ የፈለጉት እሱን ነው:: መልኩ፣ የደስደሱ፣ ደማምነቱ፣ ጠባዩ፣ በኋላ
ዝግ ተብሉ ይፈለጋል ከሁሉም አስቀያሚ አማንዳ ሳትሆን አትቀርም፡፡ ድብልብል
አሜሪካዊት ናት፡፡ ወፍራም አንገቷ ዙርያ ስጋው ተጣጥፏል፣ ሽንጥ
ሚሉት የላትም፣ ስትራመድ የሚንቀጠቀጠው ባቷ ረዥም ቂጥ ይመስላል። በጭራሽ ስሜት አትቀሰቅስም። ሉልሰገድ ለምን
እንደያዛት ለጊዜው ሊገባኝ አልቻለም፡፡ የቸገረው እርጉዝ ያገባል ይባላል፣ እሱ ግን አቅፏት ይዞራል። ወገቧ ዙርያ እጁ ስለማይደርስ ትከሻዋን አቅፎ እሷ ወገቡን አቅፋ ሲሄዱ አያቸዋለሁ። የአማንዳ ፈገግታ ደግና ንፁህ ነው፣ ትንንሽ አይኖቿ ንፁሀ ሰማያዊ ናቸው፣ ረዥም ፀጉሯ በጣም ንፁህ ነጭ ሆኖ፣ ጨረቃ ውስጥ ተነክሮ የወጣ ይመስላል። ግን ይህን ሁሉ ውበት ጮማዋ አፍኖ ይዞ እንደሌለ አድርጎታል። ስታያት ውፋሬዋ ነው 'ሚታይህ፣ ስታስታውሳት ጮማዋ ነው ትዝ ሚልህ

ሲልቪ ግን በጣም ቆንጆ ናት። «እጥር ምጥን» ያለች ፈረንሳዊት ሆና፣ ቡናማ ጉልህ አይኖቿ ውስጥና ውብ ሰፊ አፏ
ዙርያ እንደ ነበልባል የሚውለበለበው ፈገግታዋ ልብ ያሞቃል። ወደ ኋላ የተለቀቀው ንፁህ ጥቁር ፀጉሯ ያብለጨልጫል፣ ስትራመድ
ረዥም አንገቷን እያወዛወዘች ስለሆነ፣ ይሄ ጥቁር ሀር ፀጉሯ ዥው ዥው ይጫወታል። ከታች ደሞ አበጥ ያለው ዳሌዋ ያንኑ ያህል ይወዛወዛል። እግሯ በብዙ ጥንቃቄ የተቀረፀ ውብ ፍጥረት ነው::ፍቅርም ምኞትም የምትቀሰቅስ ወጣት ትመስላለች። ተመስገንን በጣም ትወደዋለች ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ ይሄ ተመስገን ፈረንሳይ አገር የተስማማው ይመስላል።

ዩኒቨርሲቲውን «ሲቴ» ይሉታል። ሲቴ ውስጥ መኝታ ቤት
ያላቸው ሀበሾች ተመስገን፣ ሉልሰገድ፣ ተካ፣ ሀይለየሱስ ናቸው፡፡
ሌሉቹ እንደኔው የሆቴል ክፍል ወይም የከተማ ቤት ተከራይተው
ይኖራሉ ቆንጆዋን አሜሪካዊት እንዳላገኝ ስፈልግ ከሉልሰገድ ወይም ከተመስገን ቁልፍ ለምኜ መኝታ ቤታቸው ቁጭ ብዬ ሰራለሁ::ሀይለየሱስ ቤት እንዳልሰራ ሰውየውን አልወደውም። ተካ ቤት
እንዳልሰራ ደሞ የተካ ቤት ይገማል። አይ ተካ! እግዜር ይይለት አንዳንዴ እንኳ እግሩን ቢታጠብና እግር ሹራቡን ቢያጥብ ምን ቸገረው ነበር? ዝም ብሎ ብቻ ጥፍሩን እየነከሰ መነጫነጭ ምን ያረግለታል?

ሉልሰገድ ወይም ተመስገን ቤት ቁጭ ብዬ ስስራ አንዳንዴ
ባህራም ይመጣል፡፡ ትንሽ እናወራና ፂሙን ተላጭቶ መልካም ስራ ብሉኝ ይወጣል። ፀጉራም ነው። እጆቹን፣ ደረቱን፣ አንገቱን፣ ፊቱን ፀጉር ወሮታል። ፂሙን ሲላጭ አይኑ፣ አፍንጫውና ጆሮው ብቻ ናቸው መላጨት የሌለባቸው:: ቢሆንም ፀጉሩ አያስቀይምም፡፡ በጣም
ንፁህ ሰው ነው።

አንዳንዴ ደሞ ቁጭ ብዬ ስሰራ ድቡልቡሏ አማንዳ ወይም
ውቢቷ ሲልቪ ይመጣሉ ወዳጃቸውን ፍለጋ፡፡ ቀስ በቀስ እነዚህን ሁለት ልጃገረዶች» እያወቅኳቸው፣ እየወደድኳቸው ሄድኩ፡፡ እነሱም ሊወዱኝ እንደጀመሩ ታወቀኝ። ስለራሳቸው ኑሮ በመጠኑ ይነግሩኝ ጀመር ..

አንዳንድ ቅዳሜ ማታ ሀበሾቹና ጓደኞቻቸው «ሱርፕሪዝ ፓርቲ»
ያደርጋሉ። «ሰርፕሪዝ ፓርቲ» ድንገተኛ ብጤ ነው። ታስቦ የታቀደ
ፓርቲ ሳይሆን፣ ጓደኛሞች ሲገናኙ «ዛሬ ምን እናርግ? ሲኒማ
እንግባ ወይስ ምን ይሻላል?» ይባባሉና ለምን ሰርፕሪዝ ፓርቲ
አናረግም?» ይላሉ፡፡ ያን እለት ማታ ፓርቲው ይደረጋል። የተገኙ
ሰዎች ይጠራሉ፣ የራሳቸውን መጠጥ ይዘው እንደሚመጡ የታወቀ ነው:: አንዱ ቤት ፓርቲው ይደረጋል። ለዚህ ጉዳይ ሀበሾቹን
ባህራም ያገለግላቸዋል
ይጀምራል፤ ወንዶቹን ይጠራል፣ ሴቶቹን ይጋብዛል፣ እዚህ ትእዛዝ
እንደ አውሎ ነፋስ በፍጥነት መዘዋወር ይጀምራል ወንዶቹን ይጠራል ሴቶቹን ይጋብዛል እዚህ ትእዛዝ እዚያ ምክር ይሰጣል፣ ከዚህ ዲስክ ከዚያ ሴት ይዋሳል፣ ፓርቲው ይጀመራል። ተሳታፊዎቹ ወንዶች ኣብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያንና ኢራናውያን ናቸው፣ የሁለቱ አገሮች ማህበር ይመስላል።

እንዲህ አይነት ፓርቲ ውስጥ ነበር ሉልሰገድ አማንዳን ያገኛት። ፓርቲው ውስጥ ጥቂት ሴቶች ብቻ ነበሩ፣ እነሱም ተይዘዋል፡፡ ያልተያዙ አንዲት በጣም ደቃቃ የሆነች የሩቅ ምስራቅ
ልጅና እንዲት አስቀያሚ ድቡልቡል ኣሜሪካዊት ብቻ ናቸው::ምስራቃዊቷ በጣም ደስ ትላለች፣ ግን ሉልሰገድ እሷን ይዞ አልጋ ውስጥ ሲገባ ሊታየው አልቻለም። «ዎ! ብትሞትብኝስ?» ብሎ አሰበ፡፡ ተዋት። ድቡልቡሏ አሜሪካዊት ፈፅማ ደስ አትልም፣ ግን ሙዚቃውና መጠጡ እየገፋፉ ወደሷ ወሰዱት። ተዋወቃት። ስሜ
አማንዳ ነው አለችው፣ አብረው ይደንሱ ጀመር፡፡ በእንግሊዝኛ
እያወሩ ሁለቱም በብሉይ ጠጡ፣ ሞቅ አላቸው:: ስታቅፈው
ስታናግረው በጣም ደስ እያለችው ሄደች ይስማት ጀመር

«ተው እዚህ አትሳመኝ» አለችው

«ምናለበት?» አላት ጆሮዋን እየሳመ አልችልም፡፡ ስሜቴ በጣም ይቀሰቀሳል» አለችው:: ድምፅዋ
በጣም አቆመበት።

ታድያ ምናለበት?» አለ እየተሻሻት

"ያኔ መሳም ብቻ አይበቃኝም» ብላ በሀይል ተጠጋችው::

ሉልሰገድ ቀስ ብሎ ወደ አንዱ መኝታ ክፍል ገብቶ እዚያ
ይሳሳሙ የነበሩትን ሁለት ፈረንሳዮች አስወጣቸው። (መኝታው የማን እንደሆነ እንጃ መብራቱን አጠፋ። ተመልሶ መጥቶ አማንዳን ወደዚህ ጭለማ መኝታ ቤት ወሰዳት፡፡ በሩን ቆለፈ። አልጋው ላይ አጋድሞ ይስማት ጀመር። እየሳመ፣ እያሻሽ ሙታንታዋን አስወለቃት። ጭለማ በመሆኑ አስቀያሚ መልኳ ስለማይታየውና፣አሳሳም ከማወቁም በላይ ወፍራም ገላዋ ምቹ ስለሆነ፣ እጅግ በጣም ተደሰተባት ጠግቦ ከላይዋ ሊነሳ ሲል፣ እቅፍ አደረገችውና እንዳይነሳ ከለከለችው
👍231
#ምንዱባን


#ክፍል_ሁለት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

....አልፎ አልፎ መስመሩን
የሚዘረጋው ጨረቃና ደፋ ቀና የሚሉት ከዋክብተ አካባቢው ጨርሶ ጨለማ እንዳይሆን ረድተዋል :: ስለዚህ የመሬቱን የሰማዩን ያህል አልጨለመም:: ሆኖም አካባቢው በጣም ያስፈራል፡፡.

ከጉብታውና ከተንጣለለው ሜዳ ላይ ከአንድ ቅርጸ ቢስ ዛፍ ሌላ
ምንም አልነበረም፡፡ ዛፉ መንገደኛው ከደረሰበት ሩቅ አልነበረም:: ሁናቴው ስላላማረው መንገደኛው ወደመጣበት ተመለሰ፡፡

ከምሽቱ ወደ ሁለት ሰዓት ገደማ ሆኖአል፡፡ አካባቢውን ስለማያውቅ
መንገድ እንደመራው ብቻ ዝም ብሎ ተጓዘ፡፡ የከንቲባውን ቤት እንዳለፈ ከትምህርት ቤት አካባቢ ደረሰ፡፡ ትምህርት ቤቱን አልፎ እንደ ሄደ ቤተክርስቲያን አጋጠመው:: ገና ቤተክርስቲያኑን ሲያይ እጁን ጨብጦ ዓይኑን ወደላይ አንጋጠጠ፡፡

ከቤተክርስቲያን ፊት ለፊት አንድ ማተሚያ ቤት አለ፡፡ ሰውዬው
ድካም አወራጭቶት ስለነበር ከዚህ የተሻለ ሥፍራ ሳይፈልግ ከማተሚያ ቤቱ አጠገብ ከነበረው የድንጋይ አግዳሚ መቀመጫ ላይ ተጋደመ::

ወዲያው እንደተጋደመ አንዲት አሮጊት ከቤተክርስቲያኑ ወጡ፡፡
«ወዳጄ ከዚህ ምን ታደርጋለህ?» ሲሉ ጠየቁት፡፡

«አየሽ የእኔ አዛኝ፤ መተኛቴ ነዋ!» አሊ በቁጣና በድፍረት የማይሆን
መልስ መስጠቱ ሳይታወቀው:: ክብር የሚገባቸው አዛኝዋና ደግዋ ሴት ማዳም ላ ማርኩዚ ይባላሉ::

«እንዴ! ከድንጋይ ላይ!» አሉ፤ «ሌሊቱን በሙሉ ከድንጋይ ላይ
ተኝተህ ሊነጋልህ አይችልም:: ረሃብ እንዳንገላታህና ብርድ እንዳጠቃህ ሰውነትህ ይመስክራል፡፡ የሚያስጠጋ አላገኘህም?»

«ብዙ ቤት ሞከርኩ፤ የየቤቱን ደጃፍ አንኳኳሁ::»

«እና!»

‹‹ሁሉም ሰው ከበራፌ ሂድ አለኝ::
ደግዋ ሴት የሰውዬውን ጀርባ እየመቱ፡ ከአደባባዩ ባሻገር የሚታየውንና ከጳጳሱ ቤት አጠገብ የነበረውን ቤት ጠቆሙት፡፡
«ያንን ቤት ሞክረሃል?» ሲሉ ጠየቁት::

«አዎን::»

«ከዚያ ማዶ ከሚታየው ቤት አንኳኩተሃል?»

«የለም::»

«እዚያ ሞክር እስቲ፡፡»

እናያ ደገ ጳጳስ ከተማ ወስጥ ሲዘዋወሩ በመቆየታቸው ስለደከማቸው ያን እለት ማታ ከክፍላቸው ሳይወጡ ብዙ ቆዩ:: በተጨማሪም ብዙ ስራ
ስለነበራቸው «ሥራዩን ሳልጨርስ አልነሳም» በማለት አእዚያው አመሹ::

ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ሲሆን እዚያው ሥራቸው ላይ ነበሩ:: በብጣሽ ወረቀትና በማስታወሻ ደብተር ላይ ጉልበታቸውን እያስደገፉ ሲፅፉ
እንደተለመደው አልጋቸው አጠገብ ከነበረው ቡፌ ከብር የተሠራ ሣህን ለማውጣት መዳም ማግልዋር ይገባሉ:: ሴትዬዋ ከተመለሱ በኋላ ጥቂት
ቆይቶ ገበታ እንደቀረበና እህታቸው እንደሚጠብቋቸው በመገመት ጳጳሱ ወደ ምግብ ቤት ሄዱ:: ምግብ ቤቱ፡ የአራት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ዓይነት ሆኖ የእሳት ማንደጃ አለው:: ቢፈለግ ወደ አውራ ጎዳናው የሚያስወጣ በርም አለው:: በአትክልቱ በኩል መስኮት አለ፡፡

ማዳም ማግልዋር ገበታውን ሠርተው ከጨረሱ በኋላ ጠረጴዛውን እያስተካከሉ ከመድምዋዚል ባፕቲስታን ጋር ይጫወታሉ:: ገበታው አጠገብ
ሻማ ከትንሽ ጠረጴዛ ላይ ተቀምጦ እየተቀጣጠለ ነው:: ከማንደጃው ውስጥ
የተቀጣጠለው እሳት ፍም ብዛት ስለነበረው ክፍሉ ይሞቃል፡፡ የቤታቸው በር እንዴት መቆለፍ እንዳለበት መዳም ማግልዋር ሲያወሩ ጳጳሰ ይገባሉ፡፡

ማዳም ማግልዋር ለእራት የሚሆን ሸቀጣሸቀጥ ለመግዛት ወደ ገበያ ሄደው ሳለ አንድ መግቢያ ያጣ ማጅራት መቺ ከተማ መግባቱንና ይህ ሰው
በጊዜ ከቤታቸው በማይገቡ ሰዎች ላይ አደጋ ሊያደርስ እንደሚችል ሲወራ ይሰማሉ፡፡ ሁለቱ ሴቶች ስለዚሁ ጉዳይ ሲያወሩ ጳጳስ ስለገቡ «አባታችን
መዳም ማግልግር የሚናገሩትን ይሰማሉ?» በማለት ጠየቅዋቸው::

«የምትሉት ነገር ግልጽ ባይሆንልኝም ሰምቼአለሁ» አሉ ጳጳሱ፡፡ከዚያም ፊታቸውን ወደሚነድደው እሳት በማዞርና እጆቻቸውን ከጉልበታቸው
ላይ በማሳረፍ ሠራተኛቸውን እያዩ

«ታዲያስ ፤ ምንድነው ጉዳዩ? የሚያስፈራ ነገር አለ እንዴ?» ሲሉ ጠየቁ፡፡

ይህን ጊዜ መዳም ማግልዌር ሳያስቡት ታሪኩን በማጋነን አዋሯቸው::
«ያለመጫሚያ ባዶ እግሩን የሚጓዝ ማጅራት መቺ፧ ሌባ፤ ቀማኛ ከተማ ገብቷል» አሉ፡፡ «ክዊን ላባር ሄዶ ማረፊያ ቢጠይቅ ባለቤቱ አልፈቀደለትም::
ከመሸ በኋላ ከተማ ውስጥ ሲዘዋወር ታይታል:: ስልቻውን በገመድ አስርና ተሸክሞ ይዞራል:: መልኩ ደግሞ በጣም የሚያስፈራ ነው::

«እውነትሽን ነው?» ሲሉ ጳጳሱ ጠየቁ፡፡

ጳጳሱ በታሪኩ የተመሰጡና ፍርሃትም ያደረባቸው ስለመሰላቸው

መዳም ማግልዋር ታሪካቸውን በኩራት ይቀጥላሉ:: «አዎን አባታችን፤ እውነት ነው:: ዛሬ ማታ ከተማ ውስጥ አንድ ነገር ይሆናል፡፡ ከተማው ሁሉ ይህንኑ ነው የሚያወራው:: መድምዋዜል ባፕቲስታን ደግሞ እንደምትለው...» በማለት ሴትዬዋ ንግግርዋን ስትቀጥል «እኔ» በማለት የጳጳሱ እህት ጣልቃ ገብተው «ያልኩት ነገር የለም» ይላሉ፡፡

ተቃውሞውን እንዳልሰሙ መስለው መዳም ማግልዋር ልፍለፋቸውን ቀጠሉ፡፡

«የዚህ ቤት ደህንነት ይህን ያህል አስተማማኝ አይደለም:: አባታችን
ቢፈቅዱልኝ ሄጄ ቁልፍ ለሚሠሩት ሰወዬ የድሮዎቹን መቀርቀሪያዎች
መልሰው እንዲገጥሟቸው ልንገራቸው:: መቀርቀሪያዎቹ ስላሉ በደቂቃ ይሰርዋቸዋል፡፡ ለዛሬ ማታ ብቻ እንኳን ባይሆን ለወደፊቱም ጥሩ ነው፤
በራችን ጠንካራ መቀርቀሪያ ይግባለት:: በቀላሉ የሚከፈት በር እጅግ አደገኛና አስፈሪ ነው:: አባታችን እንደሆነ ይቅርታ ቢደረግልኝ እኩለ ሌሊት
እንኳን ቢሆን ቤት ለእንግዳ፤ ይግቡ የማለት ልምድ አለብዎት:: ግን መቼም ለዚህ ፈቃድ መጠየቅ እንኳን አስፈላጊ» ሴትዮዋ አሳባቸውን ሳያጠቃልሉ በር በኃይል ይንኳኳል፡፡ «ይግቡ» አሉ ጳጳሱ፡፡

በሩ ተከፈተ:: ኣንድ ሰው ሰዎቹ ከነበሩበት ክፍል ውስጥ ገባ፡፡
ያ የምናውቀው ማደሪያ ፍለጋ ከቤት ቤት ፤ ከሥፍራ ሥፍራ
ይንከራተት የነበረው መንገደኛ ነበር፡፡ ሰውዬው በሩን መልሶ ሳይዘጋ አንድ እርምጃ ወደፊት ተራምዶ ቆም አለ፡፡ ስልቻውን በጀርባው ተሽክሞ ዱላውን
በእጁ እንደያዘ ነው:: የእሳቱ ውጋጋን ከፊቱ ላይ ሲያርፍ ሻካራውና ድካም ያጎሳቆለው ፊቱ የጭካኔ ምልክት እንዳለበት አጉልቶታል፡፡ ሆኖም ያ ስሜት ወደ ውስጥ የተቀበረ እንጂ በግልጽ የወጣ ኣልነበረም:: የመናፍስት
በአካል መታየት ነበር የሚመስለው::

ማዳም ማግልዋር ለመጮህ እንኳን አቅም አልነበራቸውም፡፡ እንደቆሙ እየተንቀጠቀጡ አፋቸውን ከፍተው ቀሩ፡፡
መድምዋዜል ባፕቲስታን ዞር ሲሉ ሰውዬው ወደ ውስጥ ሲገባ አዩ፡፡
በፍርሃት ተውጠው ከመቀመጫቸው ብድግ አሉ፡፡ ከዚያም ዝግ ብለው ወደሚነድደው እሳት ዞረው ወንድማቸውን ተመለከቱ፡፡ ፊታቸውን ሲያዞሩ ትንሽ መንፈሳቸው ተረጋጋ፡፡

ጳጳሱ ሰውዬውን በጥሞና ተመለከቱት:: ምን እንደሚፈልግ ሊጠይቁት አፋቸውን እንደከፈቱ ለመናገር እድል ሳይሰጣቸው የያዘውን ዱላ በሁለት
እጁ በመመርኮዝ ከዚያ የነበሩትን ሰዎች አንድ በአንድ ከቃኘ በኋላ ድምፁን ከፍ አድርጎ መናገር ጀመረ::

«ተመልከቱኝ! ስሜ ዣን ቫልዣ ይባላል፡፡ የተፈረደብኝ ወንጀለኛ
👍27