አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
566 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


«በፍፁም» አለ ዶክተር ደጀኔ እርግጠኛ ስለመሆኑ ለመግለፅ ጭንቅላቱንም እየወዘወዘ"ቀድሞ ነገር ውድድር አልተካሄደም ነገሩ ከላይ ተወስኖ ነው የመጣው አለው»
«ከላይ ማለት?» ሲል ጠየቀ አስቻለው በእርግጥ የቃሉ ትርጉም ጠፍቶአልና አልነበረም።
ነገር ግን ከዚያው ከአውራጃው ወይስ ከክፍለ ሀገር አለያም ከማዕከል ለማለት ፈልጎ እንጂ።
«ብቻ ከላይ ሌላው ምን ያደርጋል።»ካለ በኋላ ዶክተር ደጀኔ ድንገት ወደ ሌላ ሐሳብ ውስጥ ገባና መሬት መሬት እያየ
ይተክዝ ጀመር አስቻለው በበኩሉ በንዴት አንጀቱ ተቃጥሎ በእግሩ መሬቱን መታ መታ ያደርግ ጀምር።
«ግን አስቻለው» ሲል ዶክተር ደጀኔ ለራሱ አለና አስቻለውንም አነቃው።
«አቤት ዶክተር»
«ለመሆኑ እዚህ ሆስፒታል ውስጥ ለምን ያህል ጊዜ ሰራህ ?»
«ሰባት አመት አለፈኝ!»
«ዝውውር ሞክረክ አታውቅም?»
«አልሞከርኩም»
«አሁንስ ለመሞከር አታስብም?»
«ይሳካል ብለህ ነው ዶክተር?»
«እርግጠኛ ነኝ በዚህ ከተማ ውስጥ የምትጦራቸው አሮጊትና ሽማግሌ የለህም።»
«ምንም » አለ አስቻለው፡፡ ግን ደግሞ ወድያው ሔዋንን ጨምሮ ታፈሡ በልሁና መርዕድ ትዝ አሉት፡፡ ከእናትና አባቱ ባልተናነሰ ሊለያቸው የማይፈልጋቸው የፍቅር ቤተሰቦች ናቸውና።
እንደኔ እንደኔ ከዚህ ሆስፒታል ወደሌላ ብትዛወር የተሻለ ርምጃ መስሎ ይታየኛል፡፡ ለምን መስለህ አስቻለው!»
«እሺ ዶክተር »
አስቻለው በጽሞና እያዳመጠው "መሆኑን የተረዳሁ ዶክተር ደጀኔ ሀሳቡን ቀየር አደረገና በቅድሚያ አንድ ነገር ልጠይቅህና አንተም ትክክለኛውን ንገረኝ::ሲል ፈገግ እያለ በማየት አሳሰበው::
«ምንም አልደብቅም ዶክተር፣»
«ለመሆን እዚህ ከተማ ውስጥ 'የሴት ጓደኛ አለች» ሲል አሁንም ፈገግ ብሎ እያተ ጠየቀ። አስቻለው ድንግጥ ብሎ ድንገት ስሜቱ ሲለዋወጥ አይቶ
ዶክተር ደጀኔ አሁንም ፈገግ እያለ “ምነው ደነገጥክ?» ሲል ደግሞ ጠየቀው፡፡
አስቻለው የምንተነፍረቱን «አይ …ማለት» አለና እንደ መርበትበት
ከአደረገው በኋላ «መኖር አለችኝ ግን ምነው?» ሲል ዶክተር ደጀኔን መልሶ ጠየቀው።
«እስከገባኝ ድረስ አልጅቷ ጋር አብራችሁ አይደላችሁም፡፡ ልጅቷ
ምትኖረው ከእህቷ ጋር ነው። ልክ ነኝ?»
«እንዴት ልታውቅ ቻልክ ዶክተር»
ዶክተር ደጀኔ በያዘው እስርቢቶ ጠረጴዛጠን መታ መታ አደረገና እንደገና ወደ አስቻለው ቀና በማለት «ቅድም በቤታችንና በግቢያችን ወስጥ የሚከናወነውን እንኳ አናውቅም ብዬህ ተማምነንስ እልነበረም!» እለው፡፡
«ልጅቷ ገና በልቤ ወስጥ ነው ያለችው»
ዶክተር ደጀኔ ድንገት ሃ..ሃ..ሃ...ሃ ብሎ ሳቀና አየህ! ግማሽ አካሏ ከውጭ ቀርቶ ኗሯል አለና አሁንም ሃ ሃ ሃ ሃሃ
«የ'ሷን ነገር ለምን አነሳኸው አለው አስቻለው ዶክተሩ ሳቁን ሲጨርስ፡፡
«ግን እንደው አርግዛብህ ታዉቃለችን።?»
«በፍጹም ዶክተር እንዲያውም አታምነኝ እንደሆነ እንጂ ልጅቷ ገና ድንግል ናት።»
ዶክተር ደጀኔ እንደ መደነቅ ብሎ «ድንግል! ድንግል!»
«ከልቤ ነው የምነግርህ ዶክተር»
ዶክተር ደጀኔ በመገረም ዓይነት ፍዝዝ ብሎ አስቻለውን ሲመለከት ቆየና ራሱንም ወዘወዘ «ገና ብር አምባር ሰበረልዎ እንላለና»
«እዚያ ካደረሰን! አለና አስቻለው ግን የእሷን ነገር ለምን እንዳነሳህ
አለገባኝም ዶክተር አለ አሁንም ዓይኑን በዶክተር ደጀኔ ላይ እያንከራተተ፡፡
«ምክንያት አለኝ!»
«ምን?»
«ያልተወለደ ገዳይ የሆንከው ከእሷ ጋር በተገናኘ ሁኔታ ነው፡፡
እኔ ግን ነገሩ አሉባልታ ስለመሆኑ በትክክል ገብቶኛል፡፡» አለው፡፡
«ምኑ ከምን ጋር ተገናኝቶ?»
አሁን አሁን እየተበሳሽ ነው::
«ምኑም ከምንም!» አለና ዶክተር ደጀኔ በአጭር ቃል መለሰለትና ራሱ ቀጠለ፡፡ «እንደሚመስለኝ የአንተና የልጅቷ እህት ግንኙነታችሁ ጥሩ አይደለም፡፡
የልጅቷ እህትና ባርናባስ እንደሚግባቡስ ታውቃለህን?»
«ሰሞኑን ሲደንቀኝ የሰነበተው ይህ ነው ብትነግረኝ ይከብድህ ይሆን?"
«ብዙ የማውቀው ነገር የለም፡፡ አንድ ቀን ግን እኔና ባርናባስ ከተማ ውስጥ አብረን ስንዘዋወር መንገድ ላይ ከአንዲት ሴት ጋር ተነጋግሮ ወደኔ እንደመጣ
«ህቺ ሴት መምህርት ናት፡ ያቤሎ በነበርኩበት ወቅት እሷም እዚያ ስለነበረች እንተዋወቃለን፡፡ ብቻ ነው ያለኝ አለው ዶክተር ደጀኔ፡፡ አስቻለው የሁለቱን የትውውቅ መሠረት በማውቁ ሳይሆን አይቀርም አንገቱን ደጋግሞ ነቀነቀና «አሁን ብዙ ነገር ገባኝ ዶክተር፡፡» አለው::
«አዎ እስቻለው! የጓደኛህ እህትና ባርናባስ ከፈጠሩት ግንኙነት በመነጨ ነው ያልወሊደ ገዳይነትህ የተወራብህ፡፡ ይህን ደግሞ የነገረኝ ራሱ ባርናባስ ነው!
መምህርቷ ነገረችኝ ብሎ። ግን ደግሞ ይህን ሁሉ የምነግርህ ብዙ ጊዜ አካሄድ ፊትለፊት ስለሆነ ድንገት ሳታውቀው እንዳትጠለፍ ለጥንቃቄ ይረዳሃል ብዬ ነውና
አስብበትት፡፡ የዝውውሩንም ጉዳይ ችላ ባትለው መልካም
ይመስለኛል።» አለው፡፡
እስቻለው በረጅሙ ተንፍሶ ጥቂት ካሰላሰለ በኋላ
«የሰሞኑ እንቆቅልሽ ገና ዛሬውኑ ተፈታልኝ ዶክተር» ብሎ ከንፈሩን ነክሶ ጣሪያ ጣሪያ እያየ በሀሳብ ጭልጥ ብሎ ሄደ፡፡ የዶክተር ደጀኔን የዝውውር ሃሳብ በቀላሉ አልተመለከተውም፤ እንዲያውም በርካታ ነገሮች በተዘዋዋሪ መንገድ ይህንኑ ጉዳይ ሲያሳስቡት ሰንብተዋል። በልሁና መርዕድ ታፈሡና ሽዋዬን ለማስታረቅ ከሞከሩ በኋላ
ተመልሰው የገለፁለት ነገር ሔዋን በሃሳብ ምን ጊዜም ከአንተ ጋር ናት። ሸዋዩ ባለችበት አካባቢ ግን እንጃ….” የሚል ፍሬ ሃሳብ የነበረው ነው። ከዚያም በላይ
የእርቅ ሙከራ በተደረገ ሶስተኛ ቀን ረፋዱ ላይ ሔዋን ሳያስባት ለዚያውም ፊቷ በእንባ ረስርሶ ወደ ቤቱ መጥታ ነበር።
«ምነው ሔዩ» ነበር የአስቻለው ጥያቄ።
«እንካ ይኸን ወረቀት አንብብ ብላ አንዲት ወረቀት ሰጠችው።
አስቻለው ወረቀቷን ገለጥ አድርጎ ሲያነብ የሚከተለውን መልዕክት
አገኘባት።

«ለተከበራችሁ አባትና እናቴ ለአቶ ተስፋዩ ይርጋ እና ለወይዘር ስንዱ በላቸው፣ለጤናችሁ እንደምን አላችሁ። እኔ ግን በጣም ተቸግሬያለሁ። እናንተንም እሷንም
ለመርዳት ስል ሔዋን የተባለች ልጃችሁን ወደ ዲላ ይዣት መጥቼ ነበር። እሷ ግን ትምህርቷን እርግፍ አድርጋ ትታ ሥራዋ ወንድ ማባረር ብቻ ሆኗል። እንዲያውም
መዘዟ ለኔ ተርፎ ችግር ላይ ወድቄአለሁ።ከመቸገሬ የተነሳ በጥቂት ቀናት ውስጥ ከቤቴ ላባርራት ነው ።ምናልባት ልጃችን ባክና መቅረት የለባትም የምትሉ ከሆነ ከሁለት አንዳቹ መጥታችሁ ውሰዷት። መጥተን እንወስድም ካላችሁ ውርድ ከራሴ።

ልጃችሁ ሽዋዬ ተስፋዬ

አስቻለው ደብዳቤውን አንብቦ ከጨረሰ በኋላ በንዴት እሳት ለብሶ እሳት ጉርሶ ፈጠን ባለ አነጋገር ሴትዮዋ ምን እያለች ነው?» ሲል ሔዋንን ጠየቃት፡፡
«እኔ እንጃ አስቹ፣ ግራ ገባኝ» ሔዋን እያለቀሰች፡፡
«የት አገኘሽው?»
«ዛሬ ጠዋት ሥራ ስትሄድ ረስታው መሰለኝ አልጋዋ ላይ ተቀምጦ አገኘሁት።»
«ቀዳድጄ ልጣለው?»
«ተው አስቹ፣ ነገር ይባባስብኛል። ግን አንድ ነገር ላማክርህ?
👍3
#ምንትዋብ


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ


....በመጨረሻም ምንትዋብ ብያታለሁ” ብለው በቀኛቸው ያለው ድንክ አልጋ ላይ
እንድትቀመጥ አደረጓት። እሷን ተከትለው የገቡት አያቷ፣ በካፋን
ለጥ ብለው እጅ ነስተው በእልፍኝ አስከልካዩ መሪነት ከንጉሣውያን
ቤተሰቦች ጋር የተዘጋጀላቸው ቦታ ሄደው ተቀመጡ።
ወዲያው ሙሉ ቤት አዛዥ እንጀራ አሳላፊውንና እንጀራ የያዙ
ተከታዮቹን፣ በወጥ ቤቱ መሪነት ሰታቴ ተሸክመው ወገባቸው
እየተንቀጠቀጠ የሚራመዱትን ሴቶችና ወንዶች፣ ወጥ ቤቶቹንና ወጥ ጨላፊዎቹን፣ የጠጅ መልከኛው የጠጅ ገንቦ፣ ብርሌዎችና ዋንጫዎች የያዙ ጠጅ ቀጅዎቹን፣ ጠላና አረቄ ቤቶቹ ጠላና አረቄ ቀጂዎቹን፣
ግምጃ ቀሚስ ያጠለቀው ሥጋ ቤት ሥጋ ተሸክሞ የተሳለ ቢላዋዎች ያቀፉትንና ዐዋዜና ድቁስ የያዙትን ተከታዮቹን እየመራ ሲገቡ እንግዶቹ ተነሥተው ቆሙ።

እልፍኝ አስከልካዩ ገበታ እንዲወርድ ትዕዛዝ አስተላለፈ።

ያደገደጉ የእልፍኝ አስከልካዩ ጭፍሮች ንጉሠነገሥቱ የተቀመጡበትን አካባቢ በነጩ መጋረጃ ጋረዱት። ባለ ሦስት ጭፍራው የአስታጣቢ
ሹም አሸርጦ፣ ንጉሠ ነገሥቱ ላይ ውሃ እንዳይፈናጠቅ ክንዱ ላይ
አንጠልጥሎት የነበረውን ያማረ የእጅ መጥረጊያ ጨርቅ ጭናቸው ላይ አስቀመጠላቸው። ለብ ያለ ውሃ በወርቅ ቅብ ማንቆርቆሪያ አድርጎ፣ የወርቅ ቅብ ሳህን ላይ ሊያስታጥባቸው በርከክ ሲል መሣፍንቱ፣ መኳንንቱና ሌሎቹ እንግዶች እንደቆሙ ፊታቸውን ወደ ውጭ አዙረው በኩታቸው ሸፈኑት። አፄ በካፋ እጃቸውን ከታጠቡ በኋላ፣ አስታጣቢው
ትከሻው ላይ ጣል ያደረገውን እጅ መጥረጊያ ሰጣቸው። እጃቸውን
አድርቀው መልሰው ሲሰጡት ተቀብሎ ከቀኛቸው የተቀመጠችውን
ወለተጊዮርጊስን በርከክ ብሎ አስታጠባት።

ያደገደገ አጋፋሪ በግርዶሽ ተከልሎ፣ በቀኝ እጁ የተከበረውን የንጉሠ ነገሥቱን የወርቅ ዋንጫ፣ በግራ እጁ ፍንጃል ይዞ በሕዝቡ መሃልዐሰንጥቆ ንጉሠ ነገሥቱ ዘንድ ሲደርስ፣ ግራ መዳፉ ላይ ወይን ጠጅ ጠብ አድርጎ ቀመሰና ዋንጫቸውን ሞላላቸው። ዋንጫውን ከእጁ ላይ
ወሰዱ።

ሙሉ ቤት አዛዥ የነጠላውን ጫፍ ከትከሻው ላይ አጠፍ አድርጎ፣
ቀደም ሲል በቀማሽ በኩል ያለፈውን፣ ወርቀ ዘቦ ቀሚስ ባጠለቀ መሶብ የተሰናዳውን እንጀራ ይዞ በቆሙት ታዳሚዎች መሃል፣ “እንጀራ ይስጣችሁ” እያለ አልፏቸው ሄዶ፣ በቀኝና በግራ ረድፎቹ መሃልና ንጉሡ ፊት ለፊት በወርቀ ዘቦ ተሸፍኖ የተቀመጠው የንጉሠ ነገሥቱ መመገቢያ ጠረጴዛ ላይ አኖረው። ዓይነታቸው ለቁጥር የሚያታክት፣ ዶሮ፣ ቀይ ስጋ፣ ምንቸታብሽ፣ አይብ፣ አልጫና ሌሎችም የወጥ
ዓይነቶች የያዙት አነስተኛ ሸክላ ድስቶች ጠረጴዛው ላይ ቀረቡ። አቡነ ክርስቶዶሉ ተነሥተው መስቀላቸውን ጨብጠው ቡራኬ ከሰጡ በኋላ፣ቆመው የነበሩት እንግዶች ተቀመጡ።

ያን ጊዜ ያሸረጠ አሳላፊ የንጉሠ ነገሥቱን መሶብ ልብስና ክዳን
አንስቶ ከኋላው ለቆመ አስተናጋጅ ሰጠው። ከመሶቡ ጥግ እንጀራ
ቆረስ አድርጎ ግራ እጁ ጀርባ ላይ አስቀመጠ። ወጥ አውጭው ከየድስቱ ውስጥ በትንሹ ጨለፍ እያደረገ እንጀራው ላይ ሲያፈስለት፣ አሳላፊው
እጁ ከንፈሩን እንዳይነካ ተጠንቅቆ ፊቱን ዞሮ ምግቡን ቀመሰ። ወጥ
አውጭው ከየዓይነቱ ወጥ መሶቡ ላይ ሲያደርግ፣ አሳላፊው ንጉሠ
ነገሥቱን ማጉረስ ጀመረ።
ወለተጊዮርጊስም ለመጀመሪያ ጊዜ ከንጉሠ ነገሥት ጋር ማዕድ ተቋደሰች።

ንጉሠ ነገሥቱ፣ ወለተጊዮርጊስና መጋረጃ ውስጥ የተፈቀደላቸው እንግዶች በልተው ካበቁ በኋላ፣ መጋረጃው ሲከፈት
አስተናጋጆች ከመጋረጃ ውጭ ደረጃቸው ተጠብቆ የተቀመጡትን
እንግዶች እንደየክብራቸው እጃቸውን በብር፣ በነሐስ ወይንም በብረት ማስታጠቢያ አስታጠቡ።

በእንጀራ ቤቱ ሥር ያሉት አስተናጋጆች በቀረበው ገበታ ላይ
እንጀራ ሲያደርጉ፣ ወጥ ቤቶቹ የተለያየ ወጥ የያዙ ሰታቴዎችን ይዘው እየተንገዳገዱ ሲቀርቡ፣ ወጥ ጨላፊዎች እየጨለፉ የተዘረጋው እንጀራ ላይ አወጡ፤ እንግዶቹም በፀጥታ መብላት ጀመሩ።

ወጥ ቤቶች እንደ ሸማኔ መወርወሪያ ወዲህ ወዲያ እየተዘዋወሩ ባዶዎቹን ሰታቴዎች ይዘው በፍጥነት ሲወጡ፣ ሌሎች ወጥ የያዙ ሰታቴዎችን ይዘው ከመቅጽበት ይመጣሉ። ለንጉሠ ነገሥቱ የመጣ ገፀ በረከትና ደጅ መጥኚያ ሙክት፣ ሰንጋ፣ ቅቤና እህል በሙሉ ቤት አዛዥ የበላይ ተቆጣጣሪነት ለድግሱ በመዋሉ፣ የምግቡ ዓይነት ልክ
አልነበረውም።

በትልልቅ ድስቶች ጥብስ እየተንቸሰቸሰ፣ ሽታው እያወደ ሲመጣ፣እንግዶቹ ቀዩን ከጮማው እያማረጡ፣ ዐዋዜ ወይንም ድቁስ ላይ እየተመተሙ፣ በጠጅ አለበለዚያም በአረቄ አወራረዱት።

ቀጥሎም የሥጋ ቤት ሹሙ ተሸክሞት ከመጣው ሥጋ ሻኛው፣
ብርንዶው፣ ጎድን ተዳቢቱ፣ ሽንጡና ሌሎችም ዋና ዋና የሥጋ ብልቶች በየገበታው ሲቀርቡ፣ ቢላዋ ለእያንዳንዱ ሰው ታደለ። ዐዋዜና ድቁስ የያዙት አስተናጋጆች ደግሞ በእያንዳንዱ ገበታ አንፃር ሲያስቀምጡ፣
እንግዶቹ እንደየምርጫቸው እያነሱ ሥጋውን አጣጣሙ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ግርዶሹ እንደ ተከፈተ ነው። ወለተጊዮርጊስ፣ ውስጣዊና ውጫዊ ብርሃን እየረጨች በተመስጦ ዕድምተኛውን ትመለከታለች። ዐይኗን
ከአስተናጋጆቹ ላይ ማንሳት አቅቷታል። በሥራቸው የተካኑት ሙሉ ቤት አዛዥ፣ የእልፍኝ አስከልካዩና ጭፍሮቹ፣ ሰታቴ ተሸካሚዎቹና ወጥ ጨላፊዎቹ፣ የሥጋ ከብቱን ተረክቦ ያሳረደው ሥጋ ቤቱና ጭፍሮቹ
ነጠላቸውን ትከሻቸው ላይ አጣፍተው ወይንም ቡሉኮ ደርበው በየቦታው ተሰማርተው እንደየኃላፊነታቸው በቅልጥፍና ማስተናገዳቸው አስደንቋታል።

ጠጅ አሳላፊው አስተናጋጆቹ የት ሄደው የጎደሉትን ብርሌዎች
መሙላት እንዳለባቸው በዐይኑ ሲጠቁም፣ እንጀራ ቤቱ እንጀራ አለቀ አላለቀ እያለ ከሩቅ መሶብ ሲያማትርና ገበታ ደንገጥ ያለበትን በጥቅሻ ለእንጀራ አሳላፊዎች ሲያመለክት፣ ወጥ ጨላፊዎች እየዞሩ ከየዓይነቱ ወጥ ሲጨልፉ፣ ሥጋ ቤቱ አንጓ አንጓ ሥጋ ተሸክሞ በየገበታው ሲያዞር፣ሥርዓታቸው፣ ትጋታቸው፣ ፍጥነታቸው፣ ቅልጥፍናቸውና ለሥራቸው
ያላቸው ፍቅርና አክብሮት አስደምሟታል።

በልቶ የጨረሰውም እንግዳ ሲወጣ ሌሎች እንደየተራቸው እየገቡ፣ያለግርግርና ያለትርምስ ሁሉም ደንብና ሥርዐት ተከትሎ መደረጉ አስገርሟታል።

ያለ የሌላትን መረጋጋት አጠረቃቅማ ሙሉ ጨረቃ መስላ
ተቀመጠች። ድፍረት እንዳይሆንባት ተጠንቅቃ ንጉሠ ነገሥቱን ሰረቅ አድርጋ አየቻቸው። እንደዚያ በወርቅ ተንቆጥቁጠው፣ ግርማ ሞገስ ተጎናጽፈው፣ ያ ሁሉ ሰው ቁጭ ብድግ የሚልላቸውን ሰውዬ፣ ቋራ እነሱ ቤት መደብ ላይ ተኝተው በወባ ትኩሳት ከተንደፋደፉትና ቤት ያፈራውን እየተመገቡ ካገገሙት ሰውዬ ጋር ማዛመድ አልሆንልሽ
አላት። ለማመንም አቃታት።

ዕጣ ፈንታ ይሁን ሌላ እዚህ ሕይወት ውስጥ የጨመራትን አሰላስላ ተገረመች። እሷ፡ አባቷና የጥላዬ አባት ታርቀው ከጥላዬ ጋር ጎጆ ቀልሰው ለመኖር አልማ ነበር እንጂ እንደዚህ የተንጣለለ ሕይወት ውስጥ እገባለሁ ብላም አልገመተች። ከጥላዬ ውጭ ከሌላ ጋር የመኖር ፍላጎትም ሐሳብም አልነበራት። ጥላዬ ራሱ በዚያን ሰዐት ቢያያት ምን
ሊል እንደሚችል መገመት አቃታት። የንጉሠ ነገሥቱ ታመው ወላጆቿ ቤት መምጣት፣ የእሷ ማስታመምና የእሳቸው አገግሞ መመለስ፣ ለእሷ ቤተመንግሥት መግባት መነሻ ምክንያት መሆኑ ታምር ሆነባት።
👍16